feta daily - ፈታ ዴይሊ- ዜና እና ሌሎች ጉዳዮች

feta daily - ፈታ ዴይሊ- ዜና እና ሌሎች ጉዳዮች Ethiopia - FETA - DAILY | ፈታ ዴይሊ_ዜና እና ሌሎች የመዝናኛ ጉዳዮችንም ጭምር ያካተተ...
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር

ሙሉ  የመግለጫ ቃል!!➢ ረቡዕ ጥቅምት 06/02/2017 ዓ.ም ከማለዳው 12፡00 ጀምሮ እስከ ቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ በመንፈስ ልጆቻቸው መኖሪያ ቤት ይቆያሉ፤➢ ከቀኑ 10፡00 እስከ 11...
17/10/2024

ሙሉ የመግለጫ ቃል!!
➢ ረቡዕ ጥቅምት 06/02/2017 ዓ.ም ከማለዳው 12፡00 ጀምሮ እስከ ቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ በመንፈስ ልጆቻቸው መኖሪያ ቤት ይቆያሉ፤

➢ ከቀኑ 10፡00 እስከ 11፡00 ከመኖሪያ ቤታቸው ወደ ርዕሰ አድባራት ደብረ መድኃኒት መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ወደተዘጋጀው የደብሩ ስብከተ ወንጌል የወልድ ዋሕድ ሰንበት ት/ቤት አዳራሽ ማረፊያ ቦታ ይወሰዳል (ይጓዛሉ) ሌሊቱን በሰዓታት ጸሎት ሲታሰቡ ያድራል፤ ➢ ጥቅምት 7 እና ጥቅምት 8/2017 ዓ.ም ከማለዳው 12፡00 እስ ምሽት 1፡00 ሰዓት ድረስ በደሴ ከተማ ባሉ አብያተ ክርስቲያናት በሰዓታት እና በጸሎት ሲታሰቡ አድረው ይውላሉ!

➢ ጥቅምት 8/2017 ዓ.ም ለጥቅምት 9/2017 ዓ.ም ከምሽቱ 2፡00 ሰዓት እስከ ሌሊቱ 10፡00 ድረስ የማህሌት ስነስርዓት በርዕሰ አድባራት ደብረ መድኃኒት መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ስብከተ ወንጌል ወልድ ዋሕድ ሰንበት ት/ቤት አዳራሽ የደሴ ከተማና ከተለያዩ ገዳማት በመጡ ሊቃውንት ቤተ ክርስቲያን የማህሌት ሥነ ስርአት ይፈጸማል !

➢ የሀዘን መግለጫ እና የአበባ ጉንጉን በማቆያ ቦታ የማስቀመጥ መርህ ግብር ይክናወናል ➢ በተዘጋጀው የባህር መዝገብ ላይ የሀዘን መግለጫ በጽሑፍ እንዲቀመጥ ይደረጋል

> ከሌሊቱ 10፡00 አስከ 10፡30 አስከሬኑ በክብር ወደ ርዕሰ አድባራት ደብረ መድኃኒት መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ይገባና ጸሎተ ኪዳን ተደርሶ የቅዳሴ ስነስርዓት እስክ ማዳው 12፡00 ድረስ ይከናወናል፤

ጥቅምት 9/2017 ዓ.ም ክርዕስ አድባራት ደብረ መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን ከማለዳው 12:00 ጀምሮ እስከ ጧቱ 2፡00 ሰዓት ድረስ በሊቃነ ጳጳላት፤ በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፤ በአባቶች ካህናትና መዘምራን በሰንበት ት/ቤት ወጣቶች እና በደሴ ከተማ አካባቢ ከተለያዩ ልዩ ቦታ በመጡ ህዝበ ክርስቲያንና ወዳጆቻቸው አማካይነት ታጅበው ወደ ደሴ ደብረ ቤቴል ቅ/ሥላሴና ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል በሰልፍ ይደርሳሉ

> ከጧቱ 2:00 ሰዓት እስከ ቀኑ 6፡00 ሰዓት የጸሎተ ፍትሐት በተመረጡ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ካህናትና መዘምራን ይካሄዳል!

➢ የህይወት ታሪክ፤ቅኔ፤ ትምህርተ ወንጌል የተለያዩ ባስልጣናትና የኃይማት መሪዎች ተወካይ የሐዘን መግለጫ እና የአበባ ጉንጉን ማስቀመጥ መርሀ ግብር ይከናወናል፣

➢ ከቀኑ 7፡00 እስከ ቀኑ 8፡30 ድረስ ጉዞ ወደ ሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳም ተደርጎ ከቀነ- 8:30- 9:00 ስርዓተ ቀብሩ ይፈፀማል፡፡

ስለአባታችን   አንዳንድ መረጃዎች ስለመስጠት ይመለከታል ✍️ስርአተ ቀብራቸው ቅዳሜ   ገዳም ከቀኑ በ9 ሰአት ይከናወናል ❗️     ✍️ወደ ሀይቅ ጉዞ ከመደረጉ በፊት   ወደ   ምዕመኑ ሽኝ...
16/10/2024

ስለአባታችን አንዳንድ መረጃዎች ስለመስጠት ይመለከታል ✍️ስርአተ ቀብራቸው ቅዳሜ ገዳም ከቀኑ በ9 ሰአት ይከናወናል ❗️

✍️ወደ ሀይቅ ጉዞ ከመደረጉ በፊት ወደ ምዕመኑ ሽኝት ያደርግላቸዋል ❗️
👉❗️ማንኛውም ምዕመን በሽኝት ፕሮግራሙ ላይ የተከለከለ ነው #ነጭበነጭ ተለብሶ በዝማሬ ስርአታቸው ይከናወናል ክብራችንን ለመግለፅ 🤲 አዲስ መረጃ እንደደረሰኝ አሳውቃችሗለው 😭

16/10/2024

አባ መፍቀሬ ሰብ

አባ መፍቀሬ ሰብ … ረዥም ቁመታቸው ለክህነት ቀሚሳቸው በልክ የተሳራ የሚመስል ዠርጋዳ ናቸው ….ሲራመዱ በረዥም መቋሚያቸው መሬቱን በቀስታ ወጋ እያደረጉ አላፊ አግዳሚውን በፍቅር የሚመለከቱ ….ቀይ አዛውንት ናቸው !!ልክ እንደሴት ቦርሳ የድምፅ ማጉሊያ በትከሻቸው የሚያነግቱ ….የትም ይሂዱ የት ከአባ መፍቀሬ ትከሻ የድምፅ ማጉሊቸው ወርዳ አታውቅም ….እንግዲህ እኔ ሳልወለድ ደሴ ነበሩ… ዛሬም አሉ …የድምፅ ማጉያቸውም ትከሻቸው ላይ አለች !የድምፅ ማጉያቸው እንደአንድ የአካል ክፍላቸው ስልተዋሃደቻቸው መንገድ ላይ ሰው ሰላም ሲሉም ሲመክሩም ሲገስፁም በድምፅ ማጉያው ነው …

‹‹ሸህ ሰይድ ደህና አደሩ ›› ይላሉ መንገድ ላይ ሲያልፉ ያገኟቸውን ሸኪ
‹‹አልሃምዱሊላሂ …እንደምን አሩ አባ መፍቀሬ ››
‹‹እግዚሃር ይመስገን … እማማ ነፊሳ ተሸላቸው ወይ …አላደርሰኝ ብሎ ሳልጠይቃቸው ››
‹‹በጎ ናት አሁንማ ሽራለች…አልሃምዱሊላሂ ›› ይላሉ …አባ ማፍቀሬ …ይሄን የሚሉት አባ ማፍቀሬ የድምፅ ማጉያቸውን በእጃቸው ከፍተው እንደያዙ ነው ….አባ መፍቀሬ ጋር ሚስጥር የለም !! አለፍ እንዳሉ አንዱን ጎረምሳ መንገድ ላይ ሊያዩት ይችላሉ

‹‹አንተ የሰናይት ልጅ …አተውም …ምን አድርጊ ብለህ ነው የመትጎትታት …እንደው ልጃገረድ ተልካ ማለፊያ ትጣ ….ቆይ ለናትህ ባልነግራት ›› ብለው ይገስፁታል …ድምፅ ማጉሊያቸው በእጃቸው ተከፍቶ ስለሚይዙት የልጁ እናት እቤቷ ሁና ሰምታይሆናል ! አይ አባ ማፍቀሬ !ደሴ ውስጥ አባ መፍቀሬን በፍቅር የማያከብራቸው ማን አለ … ሰብአዊ ቅርስኮ ናቸው ! አባ መፍቀሬ የሌሉባት ደሴ ኦና ናት ! እዚህ ድረስ ተፅእኖ ማሳደር የቻሉ ድንቅ አባት ናቸው !
‹‹አንች ሳራ …አሁን በዚህ በብርድ እንዲህ ይለበሳል …ኧረ እግዚሃርን ፍሪ …እንደው እግዜሩንም የሰውንም አይንም ባትፈሪ እንኳን ብርዱን አትፈሪም …›› መንገደኛው ይስቃል …

አባ መፍቀሬ እስካሁን በአደባባይ ከማውቃቸው የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን አገልጋዮች ስለፍቅር …ስለአንድነት ስለመሃበራዊ ህይዎት ስለአካባቢ ጥበቃ ሳይቀር ዘብ በመቆም የሚስተካከላቸው ያለ አይመስለኝም !! አባ መፍቀሬ በሙስሊሙ በፕሮቴስታንቱ በአዋቂው በወጣቱ በህፃናቱ ሁሉ የሚወደዱ ሰው ናቸው !! ከተጠሩበት የወንጌል አገልግሎት ጎን ለጎን የአገርን ባህል ቅርስና ታሪክ በማስተዋወቅ አቻ የሌላቸው ድንቅ አባት ! (አባ መፍቀሬ መፅሃፍ ላይ ያሉ ገፀ ባህሪ እንጅ የእውነት ምድር ላይ ያሉ ሰው አይመስሉም ! ይሄንን ሁሉም የደሴ ከተማ ነዋሪ ይነግራችኋል ) በህፃንነታችን ኳስ ስንጫዎት …አንዱ ጎረቤ ይወጣና ‹‹እዚህ አትንጫጩ ..አቧራ ቤቴ ላይ ቦነነ ›› ምናምን ሲለን አባ መፍቀሬ ደረሱ እንበል የሚቆጣንን ጎረቤት በድምፅ ማጉያቸው ያስታጠቁልናላ

‹‹አሃ ….እነዚህ ልጆች የት ሂደው ይጫወቱ …ምንድነው ልጅ መነተፍ …እነዚህኮ የግዜር ፀጋዎች ናቸው …ወዴት ይሂዱ እኛ ያበረርናቸውን ማን ሊቀበላቸው ነው ›› ብለው ሞቅ ያደርጉናል እኛም ቀበጥ ብለን ኳሱን ስንጠልዘው የሰው ጓሮ ይገባ የለ... አባ ማፍቀሬ ወደኛ ዞረው
‹‹አይ በወጉ በጉ ነው እንጅ ...ኮባውን ገነጠላችሁትኮ …የማሪያም ዝክር የቡሄ ሙልሙል የምትገምጡት ይሄን ኮባ ስትንከባከቡ ነው ›› ይሉና የውሻሸት ይቆጡናል ….ስንወዳቸውኮ !

በነገራችን ላይ አባ መፍቀሬ ከሃይማኖታዊ ታላቅ አገልግሎታቸው ጎን ለጎን እኔ ነኝ ያለ የማስታወቂያ ባለሙያም አጠገባቸው የማይደርስ ድንቅ የፕሮሞሽን ሰው ናቸው …. ለምሳሌ ኢየሱስ የተሰቀለበት መስቀል አንድ ክፍል (ግማደ መስቀሉ) እንደሚገኝባት የሚታመነው የግሸን ማሪም አምባ ከደሴ ወደ ሰማኒያ ኪሎ ሜትር ርቆ ይገኛል ….በየአመቱ በመቶ ሽዎች የሚቆጠሩ ምእመናነን እለተ ቀኑን ለማክበር (መስከረም 21 ) ይጎርፋሉ ደሴ በአንድ እግሯ ትቆማለች …አባ ማፍቀሬ ታዲያ ከዛ በፊት ስለጊሸን መንገድ በተለይ የደሴ ነዋሪ በእለተ ቀኑ እንዳይቀር እንዲሁም የሚመጣውን እንግዳ በስርዓት እንዲያስተናግድ ልብ ሰቃይ ቅስቀሳቸውን በማትለያቸው ድምፅ ማጉሊያ ያሰማሉ

‹‹ አወ….የጊሸን መንገድ እንደድሮው እንዳይመስላችሁ ….አሳርሰን አስለስልሰን የተናደውን ክበን የፈረሰውን ጠግነን ጤፍ ቢፈስበት የሚያስለቅም እንዴት ያለ መኪና መንገድ አሰርተናል … አውራጎዳና መንገዱን ጠርጎ አስተካክሎልናል ምእመናን ለአውራ ጎዳና ሃላፊዎችና ሰራተኞች አንዴ ጭብጨባ ……›› ህዝቡ ከሳቅ ጋር ጭብጨባውን ያስነካዋል ……‹‹ አሮፓ ነው ሚመስል..ብታዩት …አሮፓ …..አዎ ›› ሰው ይስቃል አባ መፍቀሬን በፍቅር እየተመለከተ …ሲናገሩ ከልባቸው ስለሆነ ከጉልበታቸው ሸብረክ… አንዳንዴም እንጣጥ ይላሉ …..‹‹ ….. እንደድሮው አደጋ የለ ምን የለ ....መንገዱ አልጋ ባልጋ ….‹ደረስን እንዴ ከምኔው › ነው የምትሉት …..ማየት ማመን ነው ….አደጋ የለም !! መለዓኩ ቅዱስ ገብርኤል የት ሂዶ … እቅፍ ድግፍ አድርጎ በክንፉ ጋርዶ አምባው ላይ ቁጭ ነው!! …ዘንድሮ ይለያል ብያለሁ … ታ……ዲያ ተቀላቅሎ የሚመጣ ሌባም ስለሚኖር እንግዶቻችንን እንዳያስቀይምብን በአይነቁራኛመጠበቅ ነው ….ለነገሩ ልጃችን ሳጅን ምትኩ ቦሊሱንና ሰራዊቱን በተጠንቀቅ አዘጋጅቷል …ወዮሉሽ ሌባ …ያሰብሽ ካለሽ ካሁኑ ንስሃ ግቢ ….ነግሪያለሁ …እስቲ ላሳጅን ምትኩ ሞቅ ያለ ጭብጨባ ምእመናን ›› ህዝቡ ይስቃል ያጨበጭባል ይቀጥላሉ አባ መፍቀሬ ሰብ …የከተማዋ ድምቀት ድንቅ የግዜር ሰው …..

‹‹ እንግዶቻችን ታዲያ ሲመጡ እንዳይታዘቡን መንገን ጠዳ ጠዳ ….ምግብ ቤቶችም ቤርጎዎችም በደንብ ንጥህና ….እ ….አዎ! ለእንግዶቻችንን ቦታ ስለማይበቃ ….ያው በየአመቱ እንደሚደረገው በየቤታችሁ አምስትም ስድስትም እንግዶች ተቀብላችሁ ማስተናገዱን እንዳትረሱ … ሸህ መሃመድ እንዳምናው አምሳ ሰው እቀበላለሁ ብለዋል ….ለሸህ መሃመድ እስቲ አንዴ ጭብጨባ ….›› በነገራችን ላይ ወደጊሸን ማሪያም ለመሳለም የሚጎርፈው ህዝብ ከብዛቱ የተነሳ ደሴ ውስጥ ያሉ ሆቴሎች ግማሹን እንኳን ማስተናገድ አይችሉም ነበር …ታዲያ በደብሩ ህዝቡ ምግብ ከየቤቱ እያወጣ …አዋጥቶ እያረደ እና እንጀራም እየጋገረ ያስተናግዳል …ያለምንም ግነት እነዚህን ምእመናን ለማስተናገድ የደሴ ክርስቲያን ሙስሊም ሁሉም ቤቱን አዘጋጅቶ ነበር የሚጠብቀው ያለምንም ክፍያ …ሃብታም ሙስሊሞች ግቢያቸውን ቤታቸውን አስነጥፈው አንዳንዶቹ የክርስቲያን አሳርደው በደመቀ ድግስ መንገደኞቹን ይቀበሉ ነበር !!

አባ ማፍቀሬ ቤተክርስቲያን ሲፈርስ እያለቀሱ ጭምር ቤት ለቤት ብር ለምነው የሚያስጠግኑ ምርጥ አባት ናቸው ‹‹ ….ተው እንጅ ተው እንጅ እግዜሩስ ምን ይላል ….እናተ ይሄን የመሰለ ፎቴ ላይ ተመቻችታችሁ ብስል ከጥሬ ስታማርጡ የግዜር ቤት ፈርሶ ቅዱሳን መፅሃፍቱ ዝናብና ጠሃይ ሲያበላሻቸው ዝም ይባላል ….? ነውር አይደለም …. እምነቱ ቢቀር ከግዜር ፊታችሁ ቢሸሽ ቅርስ አይደለም የአገር ሃብት አይደለም …. የመንግስት ባለስልጣናትስ …. ቱሪስት ነገ ሲመጣ ምን ልታሳዩ በምን ልትኮሩ ….›› እያሉ ህዝቡን አስተባብረው የተበላሸውን በማስጠገን የፈረሰውን በማሰራት ተቆጥሮ የማያልቅ ሚና ለቤተክርስቲያንም ለአገርም ያበረከቱ ታላቅ አባት ናቸው ….

አንድ ቀን ከደሴ ወደመቅደላ እየሄድን ነው … ወቅቱ ተንታ ሚካኤል የሚከበርበት ወቅት ይመስለኛል … አባ ማፍቀሬም አውቶብሱ ውስጥ አሉ …እናም መንገድ ላይ ድንገት ‹‹ ሹፌር ያዝልኝ ይሄን መኪና ›› ብለው ተናገሩ አውቶብስም ውስጥ ሁነው በድምፅ ማጉሊያው ነው የሚናገሩት ….ሹፌሩ ግራና ቀኝ በደን የተሸፈነው መንገድ ላይ ጥጉን ይዞ ቆመ አባ መፍቀሬ ከመኪናው ወረዱ ….ተራራውን የሸፈነው እድሜ ጠገብ የአበሻ ፅድ በወቅቱ ገብቶ በነበረው የፅድ በሽታ ክሽልል ብሎ ደርቆ ተራራው በሙሉ ድርቆሽ የተሰጣበት መስሏል ….አባ ማፍቀሬ እጃቸውን ወደሰማይ ዘርግተው እግዚኦ እያሉ ጮኹ አለቀሱ … ምን አደረግን ማረን ….አሉ … ሁላችንም ከዛ በፊት ምንም ያልመሰለንን የደን መድረቅ ያኔ ክብደቱ ገባን … አባ ማፍቀሬ ለደን እና ለአካባቢ ጥበቃ ያላቸው ቅንዓት የሚገርም ነው ….

አባ ማፍቀሬ የደሴ ሰው ሁሉ እንደአባት ስለሚያያቸው ታክሲ ውስጥ ገብተው ብዙ ጊዜ አያስከፍሏቸውም... የግል መኪናዎችም አባ ማፍቀሬን አይተው አያልፏቸውም... አንድ ቀን ታዲያ አንዲት የድርጅት መኪና ቆመችላቸው አሉ ….ገቡ አባ ማፍቀሬ ሳቂታው ሹፌር ….አባ ማፍቀሬን መተንኮስና ማናገር ፈልጓል ….ያው አባ ማፍቀሬ በል ሲላቸው ጥርስ አያስከድኑም ተጨዋችም ናቸዋ … ታዲያ አባ ማፍቀሬን ለመተንኮስ አንዷ መንገድ ስለፕሮቴስታንት እምነት ማውራት ነው … ከመካነ ኢየሱስ ከሙሉ ወንጌል እና ከሌሎችም አብያተ ክርስቲያናት መሪዎች ጋር ወዳጅ ቢሆኑም በተለይ ስለቅድስት ድንግል ማሪያም አንስተው ሊከራከሯቸው ከሞከሩ መኪናም ላይ ከሆኑ ‹‹ወራጅ ›› ነው የሚሉት … ክፉ ደግ ሳይናገሩ …በቃ መስመራቸው ናት …..

እና ይሄ ያሳፈራቸው ሰው ‹‹አባ መፍቀሬ ግን እንደው ማሪያም ታማልዳለች ? ››ይላቸዋል…አባ መፍቀሬ መኪናዋ የፕሮቴስታንቶቹ መሆኗን ከጥያቄው አወቁ እና ዝም !….ጥያቄውን ደገመው ሳቂታው ወጣት ….አባ ማፍቀሬ ተበሳጩ …‹‹ አይ …እንግዲያው የበሪሁን እናት ናታ የምታማልደን ›› ብለውት ከመኪናው ውልቅ ብለው ሄዱ …. ሹፌሩ ባለበት በሳቅ ወደቀ …በሪሁን ማለት እንግዲህ በወቅቱ ደሴ ውስጥ ስሙ የገነነ የደሴ መካነ ኢየሱስ ሰባኪ ነበር ! ታዲያ አባ መፍቀሬ ‹‹የበሪሁን እናታ የምታማልደን ›› ያሉት በሪሁን ራሱ ሹፌሩ ነበር !! አባ መፍቀሬ ግን አላወቁትም ! ይህ አስቂኝ አጋጣሚ ደሴ ውስጥ ለረዥም ጊዜ ይወራ ነበር ! በሪሁን በወቅቱ በክፉ በደጉ በተለይም የልማትና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ከአባ ማፍቀሬ ጋር አብረው ይሰሩ እንደነበር ትዝ ይለኛል !

እንግዲህ አባ መፍቀሬ ማናቸው ከየት መጡ በቤተ ክህነት አገልግሎታቸውና ማእረጋቸው ምን ነበር ..የሰሯቸው ስራዎችስ የሚለውን አንድ ቀን በሰፊው እናወራለን ….እስከዛው ግን አባ መፍቀሬ አንዴ ሰውን አስተባብረው ኡራኤል የሚባል አካባቢ ባሰሩት የልማት ስራ አንድ ትልቅ ሸህ በመረቋቸው ምርቃት ፅሁፌን ልቋጭ ‹‹አላህ የአባ መፍቀሬን እድሜ ያርዝምልን!! ከ(አሌክስ አብርሃም)

ነፍስ ይማር

13/10/2024

ሰው ከህግ በላይ ትራፊክን ሲፈራ ህዝብ ላይ አደጋ የሚጥልን ነገር እንደ ጀግንነት ቆጥሮ አደባባይ መውጣቱ ትልቅ ክስረት ነው

       #ፈታይበሉ
03/10/2024

#ፈታይበሉ

03/10/2024

የጠ_ሩ_ቅጥር_ነፍሰ_ገዳዮች!__የሳምንቱ_አሳዛኝ_እና_አስደናቂ_ክስተቶች!___Ethiopia

03/10/2024

እንተዋወቃለን_ወይ____“_የወገቤ_ቁጥር_አንድ_ሜትር_ከ_ዘጠና_ነው__😂”__በእሁድን_በኢቢኤስ ebs@tv

03/10/2024

Ethiopia_-_የባህርዳሩ_ከፍተኛ_አመራሮች_እስር፣_14_ሺ_መምህራን_ጠፉ፣_አነጋጋሪው_እርቅ፣_የኦርቶዶክስ_አዲሱ_ኮሚቴ፣_ተፈናቃዮች_ለቀው_እየወጡ daily

♦️   1905 ዓ.ም ቤተአምሐራወሎ!⛪🙏
01/10/2024

♦️ 1905 ዓ.ም ቤተአምሐራወሎ!⛪🙏

30/09/2024

አለም_ያፈነችው_ታላቅ_ታሪካዊ_ሚስጥር፣_እንግሊዝን_አንበርክኮ_እስራኤልን_የመሰረተው_ሃያል_ቤተሰብ ፈታ ዴይሊ - feta daily

30/09/2024

HR6600ን_ሽባ_የምናደርግበት_የኢራን_ባለ_400_ቢሊዮን_ዶላር_ጸረ_ማእቀብ_ስትራቴጂ

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when feta daily - ፈታ ዴይሊ- ዜና እና ሌሎች ጉዳዮች posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share