DAF news

DAF news business

11/01/2025

ለነጋዴዎች እና ሱቅ ፈላጊዎች ፒያሳ ታክሲ ተርሚናል ፊትለፊት❗️

ፒያሳ ሀገር ፍቅር ቲያትር እና ሚኒሊክ አደባባይ መሀል የንግድ ሱቆች

* የግል የሚያደርጉት የንግድ ሱቆች ፒያሳ ላይ ብቸኛው እየሸጠ ያለው ቴምር ሪልስቴት ነው

* ሚኒሊክ አደባባይ ጋር በመንግስት የሚሰራው የ አውቶብስ እና የታክሲ ተርሚናል አጠገብ

* በከተማው ከፍተኛ እንቅስቃሴ የሚደረግበት ቦታ ከተማው ላይ ሱቅ የፈረሰባቸው ነጋዴዎች የከተሙበት

* 4700 ካሬ ላይ ያረፈ ዘመናዊ እስኬሌተር የሚገጠምለት G+5 የሆነ የገበያ ማዕከል

* በ 1 ዓመት ከ 6 ወር የሚያልቅ ከፍለው እስኪጨርሱ በዶላርም ሆነ በግንባታ እቃዎች ግሽበት ምንም ዓይነት የዋጋ ጭማሪ አይደረግም

* በወር ከ80,000 ብር በላይ የኪራይ ገቢ የሚኖራቸው

* ከ 900,000 ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ

ቴምር ሪልስቴት.......

ከሀገር ውጪ ለምትኖሩ ወገኖቻችን በሙሉ ካላችሁበት ሀገር ሆናችሁ ፕሮሰስ ማድረግ የምትችሉበትን እና መግዛት መዋዋል የምትችሉበትን መንገዶች አመቻችተናል!

ለበለጠ መረጃ በቀጥታ ወይም በዋትሳፕ ዋናው ቢሮ ይደውሉ

☎️ 0908770077
0967770077

ዋትሳፕ ሊንክ -

18/12/2024

የባንክ ስራ አዋጅ ቁጥር 1360/2017 ጸደቀ

- የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መግለጫ

ባንኮች ከአገር ዉስጥና ከዉጭ አገር ገንዘብ በማሰባሰብና ለኢንቨስትመንትና ለልማት በማዋል እንዲሁም የክፍያ ሥርዓትንና የገንዘብ ፖሊሲን በማሳለጥ ለአንድ አገር ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ዓይነተኛ ሚና ይጫወታሉ፡፡ ከዚህም አኳያ የባንክ ዘርፍ ከሌሎች ዘርፎች በተለየ መልኩ በዓለም አቀፍ ደረጃ ጥብቅ ቁጥጥርና ክትትል የሚደረግበት ሲሆን ይህንንም ውጤታማ በሆነ መንገድ ተግባራዊ ለማድረግ ጊዜዉን የዋጀ፣ ከዓለም ዓቀፍ ደረጃ እና አሰራር ጋር የተጣጣመ እንዲሁም የተሟላ የሕግ ማዕቀፍ በማዉጣት ተግባራዊ ማድረግ እጅግ ወሳኝ ነዉ፡፡

ከዚህ አኳያ የባንክ ዘርፍን በዘመናዊ ዕዉቀት እና ቴከኖሎጂ ለመደገፍ፤ ከዓለም አቀፍ ገበያ ጋር ያለዉን ትስስር ለማጠናከር፤ የዘርፉን ተወዳዳሪነት፣ ዉጤታማነትና ቀልጣፋነት ለማሳደግ፣ በቂ የፋይናንስ አቅርቦት እንዲኖር እና የዉጭ ምንዛሪ አቅርቦት እንዲያድግ እንዲሁም ቀጣይነት ያለዉ የኢኮኖሚ ዕድገት ለማረጋገጥ እንዲያስችል ተዘጋጅቶ የቀረበውን የባንክ ሥራ ረቂቅ አዋጅ ቁጥር 1360/2017 በኢፌድሪ የሕዝብ ተወካዮች ም/ቤት ጸድቋል።

ይህ ህግ ጸድቆ ትግበራ ላይ ሲውል በመሰረታዊነት ከዚህ የሚከተሉትን ዓላማዎች እንደሚያሰካ ይጠበቃል፡

አዳዲስ ባንኮች ወደ ባንክ ዘርፍ ሲቀላቀሉ ሊያሟሉ ስለሚገባዉ መስፈርት እና የፈቃድ አሰጣጥ ሂደት ለመወሰን

አደጋን መሠረት ያደረገ የተጠናከረ የቁጥጥር ሥርዓት ዘርግቶ ተከታታይነት ባለዉ አግባብ ተግባራዊ ለማድረግ፤

የሀገራችን የባንክ ዘርፍ ለዉጭ ኢንቨስትመንት ክፍት ማድረግ እና የዉጭ ባንኮች እና ኢንቨስተሮች በዘርፉ ተሰማርተዉ ለኢኮኖሚዉ ቀጣይ ዕድገት የበኩላቸዉን አበርክቶ እንዲሰጡ የሚያስችል የህገ ማዕቀፍ ለመዘርጋት፣እና

በአንድ ባንክ ላይ የፋይናንስ ቀዉስ በሚከሰትበት ጊዜ ባንኩ ከቀዉሱ እንዲወጣ እና እንዲያገግም ይህም ካልተቻለ በባንክ ዘርፍ እና በአጠቃላይ ኢኮኖሚዉ ላይ አለመረጋጋት ሳይፈጠር አንዲሁም የገንዘብ አስቀማጮች እና ሌሎች አበዳሪዎች ጥቅም ለከፍተኛ አደጋ ሳይጋለጥ የተለያዩ አማራጮች እና ስልቶችን በመጠቀም ባንኩ ከገበያ እንዲወጣ የሚደረግበትን ማዕቀፍ መዘርጋት ይገኙበታል፡፡

በመጨረሻም፣ ይህ አዋጅ የባንክ ዘርፍን የቀጣይ ዓመታት አሠራር የበለጠ ጤናማ እና የተረጋጋ እንዲሆን በማስቻል ዘርፉ ለኢኮኖሚ ዕድገት ቀጣይነት መረጋገጥ የበኩሉን ጉልህ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ይታመናል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ
ታህሳስ 8 ቀን 2017 ዓ.ም አዲስ አበባ፤ ኢትዮጵያ

Congratulations 🎆🎉The 47 president of USA 🇺🇸 Congratulated Donald J. Trump
06/11/2024

Congratulations 🎆🎉
The 47 president of USA 🇺🇸
Congratulated Donald J. Trump

14/09/2024

ዶ/ር አሸብር እና የሿሿ ድራማው...

ዛሬ ዶ/ር አሸብር "እነ ሀይሌ በመሰረቱብን ክስ ላይ መግለጫ ስለምሰጥ ጋዜጠኞች እንድትገኙ ይሁን" አሉንና ሄድን። መግለጫው የተጠራው ለረፋድ 4:00 ሰዓት ቢሆንም አብዛኛው ጋዜጠኛ ስፍራው የደረሰው ቀደም ብሎ ነው (እኔ ራሴ ያልለመደብኝን ቀደም ብዬ 3:20 ደርሻለሁ። እንደዛም ሆኖ የቀደሙኝ ጋዜጠኞች አሉ)።

መጀመሪያ መግለጫው የተጠራው ወሎ ሰፈር በሚገኘው የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ፅ/ቤት አዳራሽ ነበር። እዛ ከደረስን በኋላ ደግሞ መግለጫው እዛው አካባቢ በሚገኘው Best Western Premium ሆቴል መሆኑ ተነገረንና ወደዛው ሄድን።

ለመግለጫው የተያዘልን 1ኛ ፎቅ ላይ የሚገኘው ጣና አዳራሽ ጠበብ ያለች ናት። እንደዛም ሆኖ ግን በአንዴ በጋዜጠኞች ተሞላች። ወንበር ያላገኙ በርካታ ባልደረቦቻችን ሂደቱን ቆመው ለመከታተል ተገደዋል።

ሐሙስ ዕለት ጠዋት እነ ሀይሌ ገ/ስላሴ የመሰረቱትን ክስ አስመልክቶ የሰጡትን መግለጫ ተከታትለናል። የዛኑ ዕለት ኦሎምፒክ ኮሚቴው አቋሙን ያንፀባረቀበትን መግለጫ አግኝተን በየሚዲያዎቻችን አስተጋብተነዋል።

ስለዚህ "ሰውዬው ዛሬ ደግሞ ምን ሊለን ይሆን?" የሚለው የበርካቶቻችን ጥያቄ ነበር። ሁሉም በየራሱ ስለሚያነሳው ጥያቄ እያሰላሰለ ነው። እኔ እንኳን በግሌ ወደ 10 የሚጠጉ ጥያቄዎችን አዘጋጅቼ ነበር የሄድኩት። "እዛ ደግሞ ከእነሱ መግለጫ ተነስቼ የምጨምረው ጥያቄ ይኖረኛል" እያልኩ አሰላስላለሁ።

እንደማይደርስ የለም ሰዓቱ ደረሰና 4:05 ላይ ዶ/ር አሸብር ማይኩን ጨበጡ።

"ዛሬ ስንጠራችሁ ስለተመሰረተብን ክስ እና ታግደውብን ስለነበሩትና ስላስለቀቅናቸው የባንክ አካውንቶቻችን መግለጫ ለመስጠት እንደሆነ እንደምትገምቱ ይገባኛል። ነገር ግን የጠራናችሁ ስለቀጣዩ የ8 ዓመት የስትራቴጂክ ዕቅዳችን ልናስረዳችሁና እንደዚሁም በቀጣይ ከእናንተ ከጋዜጠኞች ጋር በምን ዓይነት መንገድ ነው አብረን የምንሰራው? በሚለው ጉዳይ ላይ ለመነጋገር ነው" ብለውን አረፉት።

ይሄን ተናግረው ብዙም ሳይቆዩ ማይኩን ለአቶ ቢልልኝ መቆያ ሰጡ። አቶ ቢልልኝ ትንሽ ማብራሪያ ከሰጡ በኋላ ለኦሎምፒክ ኮሚቴ ባለሙያ አሻገሩን። ሰውዬው ምንም ያልገባንን የ8 ዓመት ስትራቴጂካዊ ዕቅድ አውርተው ጨረሱ።

ዶ/ር አሸብር "በዚህ ጉዳይ ላይ ጥያቄ መጠየቅ ትችላላችሁ" አሉን። አንደኛ እጄን አወጣሁ። የተቀመጥኩት ከፊት ለፊት የመጀመሪያው ረድፍ ላይ ስለሆነ ዶክተሩ እንደከዚህ ቀደሙ ባላየ ሊዘሉኝ አልቻሉምና ቅር እያላቸውም ቢሆን የቅድሚያ ዕድሉን ሰጡኝ።

እኔ ከማውራቴ በፊት ግን አንድ ባልደረባችን "አካሄድ" ብሎ ጣልቃ ገባና የተጠራንበት ጉዳይና አሁን የተብራራልን ጉዳይ እንደማይገናኝ ጠቆመ። ወደ እኔ ሲመጡ እኔም ተመሳሳይ ስሜት ነው ያለኝ። በተጨማሪም የዕቅዱ ገለፃ ምንም እንዳልገባኝ ተናገርኩ። ሶስት ወይም አራት ያህል የሙያ አጋሮቼም ተቀራራቢ ሀሳብ ሰነዘሩ።

ዶ/ር አሸብር ማይኩን ተቀብለው "ስለክሱ ጉዳይ ብናወራም ባናወራም ምን ይሰራላችኋል? እናንተ እንደሆነ የምታወሩት አታጡም። ከዛ ይልቅ እንደሚዲያ ሰው የሚጠቅማችሁ ይሄን ማወቅ ነው" ካሉ በኋላ እንደልማዳቸው በሻለቃ ሀይሌ ገ/ስላሴ ጀምረው ገዛኸኝ አበራ፣ አቶ እያሱ (ቦክስ ፌዴሬሽን) እና አቶ ታምራት (ቴኒስ ፌዴሬሽንን) ወረፍ አድርገው ሲያበቁ "ሌላ ጊዜ በሌላ ፕሮግራም እንገናኛለን፤ ለዛሬው ግን እዚህ ላይ ይበቃናል" ብለው መግለጫው ማብቃቱን ገለፁ።
* * *
ከመግለጫው በኋላ...

አዳራሹን ለቅቄ በመውጣት ላይ ሳለሁ ከኦሎምፒክ ኮሚቴው

29/08/2024

📌አንዳንድ ነጥቦች…‼️

የፋኖ መሪዎች ጫካ የገቡት ስርዓት ለመትከል ነውና አንበጥብጧቸው!!!

ጥቂት የፌስቡክ አውደልዳዮች የሕዝብን ትግል ለመከፋፈል ብቅ ብቅ እያሉ ነው። እየተካሄደ ያለው የሰፈር ጨዋታ አይደለም፤ የህልውና ትግል እንጅ። አንዳንዱ በግሉ ሲተች እኔ ጎንደሬ ስለሆንኩ ነው፤ እኔ ጎጃሜ ስለሆንኩ ነው እያለ ሲጃጃል እያየን ነው። ይህ ጨዋታ አልፎበታል።

የጎጃም፣ የሸዋ፣ የወሎና የጎንደር የትግል መሪዎች የጋራ ቤታቸውን ለማቆም ዝናብን፣ ብርድንና አገዛዙን ገጥመዋል።

አንተ አንድ ሰው ነህ በቃ! በዛ ላይ ሕዝብ አልወከለህም። እናም ድክመትህም ሆነ ጥንካሬህ የግልህ እንጅ የትውልድ አካባቢህ አይደለም። ጎንደሬ ተተቸ፤ ጎጃሜ ተሰደበ፣ ሸዋ ተገላመጠ፣ ወሎዬ ተንኳሰሰ የምትለው አንተ ማን ሆነህ ነው?

የፋኖ መሪዎች ነፍጥ ይዘው ጫካ የገቡት ሰፈራቸውን ነጻ በማድረግ የጎበዝ አለቃ ለመሆን አይደለም፣ ሀገር ለመረከብ እንጅ!

በመሆኑም በጋራ እየታገሉ ያሉ መሪዎችን አትከፋፍሉ፤ እረፉ‼️

#መውጫ:- ይህ ከአማራነት አንፃር የሚቆረቆሩትንና የሚሞግቱትን አይጨምርም❗️

‼️ በአስቸኳይ የሚሸጥ 0903060610▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬🔰 የመኪናው አይነት:- Yaris compact 🔰 ሞዴል :-2005🔰 Code 2 AA **🔰 Automatic Transmissio...
14/08/2024

‼️ በአስቸኳይ የሚሸጥ
0903060610
▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬
🔰 የመኪናው አይነት:- Yaris compact
🔰 ሞዴል :-2005
🔰 Code 2 AA **
🔰 Automatic Transmission
🔰 የሚታየው -around 24

👀ዋጋ👀

💥 1,250,000 ብር fixed 💥

‼️ኮሚሽን 2% የሚከፍል እና ትክክለኛ ገዢ ከሆኑ ብቻ ከታች ባሉት ስልክ ይደውሉልን ‼️

☎️ 0903060610

📛የሚሸጡት ወይም የሚያከራዩት መኪና ካሎት እዝች👇👇 ላይ ሙሉ መረጃውንይላኩልን📛

www.utopiacar.com
ይጎብኙ✅

✅ፍተሻ ሪፓርት እንደደረሰኝ እለጥፋለሁ✅

14/08/2024

ሰሞንኛ
(በእውቀቱ ስዩም)

የማራቶን አሰልጣኝነት ቀላል የሚመስላችሁ ሰዎች ግን ክፉኛ ተሳስታችሁዋል!
የማራቶን አሰልጣኝ ከሆንክ ሲነጋጋ ትነሳለህ፤ አትሌቶች እንጦጦ መግቢያው ላይ ተከማችተው ይጠብቁሀል፤ ከዛ ታጣፊ ክላሽ ታወጣና ወደ ላይ ተኩሰህ ታስጀምራቸዋለህ ፤ እነሱ መሮጥ ሲጀምሩ ቀለል ባለች ፎርድ ትራክ መኪና ቀስ እያልህ ትከተላቸዋለህ፤ እንደመዘግየት ሲሉ በ”ክላክስ” እያስደነበርህ ታሯሩጣቸዋለህ፤ ዳገቱ ላይ ስትደርስ፥ የፌሮ ከዘራህን መዘዝ አድርገህ በጋቢና መስኮት በኩል ታሾልክና ከሁዋላ የቀረውን አትሌት ትዠልጠዋለህ ፥ የተኮማተረ ትከሻውን እያሻሸ ዞር ሲል “ ገና መሮጥ ከጀመርክ እኮ አንድ ሰአት አልሞላም፤ ምናባህ እግርህን እንደ ተሳቢ መኪና ትጎትታለህ፤ ከዚህ በላይ ከዘገየህ የጫንኩትን ጀርመን ሼፓርድ ውሻ ነው ፈትቼ የምለቅብህ፤ ” ብለህ ታስቦካዋለህ፤ እና በዚህ መንገድ የሰለጠነ አትሌት እንኳን ሪከርድ የጎረቤት አገር ድንበር አይሰብርም?

ለማንኛውም ሽልማት አይናቅም፤ ባይሆን ወደ ዶላር ተርጉሙና አስቀምጡልኝ ማለት ይቻላል፤ አበበ ቢቂላ በቸርኬ ነድቶ( በባዶ እግሩ ሮጦ) የግልገል ፈረስ ጉልበት ያላት ቮልስዋገን፥ ካጼ ሀይለስላሴ ሲሸለም እንኳ አልደበረውም ፤ “ ጃንሆይ ለኔ ቮልስ እንደሸለሙኝ የእርስዎም መጨረሻዎ በቮልስ ይሁን “ ብሎ አልተራገመም🙂

እደግመዋለሁ ሽልማት አይናቅም! እኔ ይሄን ዘመን ያህል በስነጽሁፍ ለናት አገሬ ተሩዋሩጫለሁ፤ በየመድረኩ እየተጋበዝኩ፤ የቀበሌ የባህር መዝገብ የሚያክል ሰርተፍኬት ከመሰብሰብ ውጭ ምን አገኘሁ? ኮለኔል መንግስቱ እንዳሉት “Nothing”ይልቅ ታምራት ቶላ ሰባት ሚሊዮን ብር በመሸለሙ ደስ ብሎኛል! ታሜ በቅርቡ የራስህን የኮሪደር መሮጫ እንደምትገነባ

14/08/2024

“የጠበቅነው ሽልማት መኪና እንጂ ብር አልነበረም” አሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ

በፓሪስ ኦሊምፒክ ለተሳተፉ የኢትዮጵያ ቡድን አባላት በተዘጋጀ የሽልማት ሥነ ሥርዓት ላይ የተበረከተላቸውን የ2 ሚሊዮን ብር ሽልማት አልቀበልም በማለት መወዛገቢያ የሆኑት አሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ መኪና እንዲሰጣቸው ጠብቀው እንደነበር ለቢቢሲ ተናገሩ።

በፓሪስ ኦሊምፒክ ለኢትዮጵያ በማራቶን የሩጫ ውድድር የወርቅ እና የብር ሜዳሊያ ያስገኙትን ሁለት አትሌቶች አሠልጣኝ የሆኑት ገመዶ ደደፎ መኪና መሸለም እንደነበረባቸው ለቢቢሲ ገልጸዋል።

አሠልጣኙ ከዚህ ንግግራቸው በኋላ በአገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን እና በማኅበራዊ ሚዲያ ላይ መነጋገሪያ በመሆን የተለያዩ አስተያየቶች እየተሰነዘሩባቸው ይገኛል።

ቢቢሲ አሰልጣኝ ገመዶ ለምን ሽልማቱን መመለስ እንደፈለጉ ላቀረበላቸው ጥያቄ ከዚህ ቀደም ለአሠልጣኞች የሚሰጠው ሽልማት መቀየሩ እንዲሁም የተሰጠው ዋጋ አነስተኛ በመሆኑ ተበሳጭተው መሆኑን ለቢቢሲ አስረድተዋል።

“ከዚህ ቀደም በቤተ መንግሥት በነበሩ ስነ ስርዓቶች አትሌቶች እና አሠልጣኞች መኪና ነበር የሚሸለሙት፤ ዘንድሮ ለምን እንደተቀየረ አላውቅም” በማለት ቀደም ሲል የተበረከቱ የመኪና ሽልማቶችን አንስተዋል።

በለንደን ኦሊምፒክ ተሳትፈው ውጤት ላመጡ አትሌቶች እና አሠልጣኞች የመኪና ሽልማት እንደተበረከተላቸው የሚጠቅሱት አሠልጣኝ ገመዶ “በለንደን ኦሊምፒክ ወቅት ሦስት መኪና ነው የተሸለሙት። ሁሴን ሺቦ [የረዥም ርቀት አሰልጣኝ] እና መላኩ መኪና ተሸልመዋል” ሲሉ ምክንያታቸውን ምሳሌ በመጥቀስ አስረድተዋል።

በተጨማሪም የረዥም ርቀት ሩጫ አሰልጣኝ የነበሩት ዶ/ር ይልማ ብርታ እና ዶ/ር ወልደመስቀል ኮስትሬ የመኪና ሽልማት እንደዚሁ ከዚህ ቀደም እንደተሰጣቸው አሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ ገልጸዋል።

አሰልጣኙ ከዚህ በፊት በነበረው የቶኪዮ ኦሊምፒክ በ10 ሺህ ሜትር የሩጫ ውድድር የወርቅ ሜዳሊያ ላሸነፈው ሰለሞን ባረጋ የስድስት ሚሊዮን ብር መኪና መሸለሙን በማስታወስ አሁን በማራቶን ወርቅ ላገኘው ታምራት የተሰጠውን ሽልማት ዋጋ አነጻጽረውታል።

“ለታምራት7 ሚሊዮን ብር ተሰጥቶታል። የዚያን ጊዜ ዶላር 50 ብር አካባቢ ነበር። ይህ ማለት አሁን ላይ ለታምራት የተሰጠው ሦስት ሚሊዮን ብር ብቻ ነው ማለት ነው። ሌላ ምንም ሽልማት የለም” በማለት ለቢቢሲ ሁኔታውን አስረድተዋል።

ፕሬዝዳንት ሳህለ ወርቅ ዘውዴ በተገኙበት በተካሄደው የሽልማት ሥነ ሥርዓት ላይ በወንዶች ማራቶን በፓሪስ ኦሊምፒክ ለኢትዮጵያ ብቸኛውን የወርቅ ሜዳሊያ ያስገኘው ታምራት ቶላ የ7 ሚሊዮን ብር እና የወርቅ ኒሻን ሽልማት ተበርክቶለታል።

በሽልማቱ ወቅት ከመንግሥት በተሰጣቸው የሁለት ሚሊዮን ብር ደስተኛ አለመሆናቸውን በጠንካራ ቃላት የተናገሩት አሠልጣኝ ገመዶ ደደፎ “መኪና እንጂ የብር ሽልማትን አልጠበቅንም። ሽልማቱ መኪና መሆን ነበረበት” ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

በፓሪስ ኦሊምፒክ የወርቅ ሜዳሊያ ካገኘው ታምራት ቶላ በተጨማሪ የብር ሜዳሊያ ላስገኙ አትሌቶች ትዕግስት አሰፋ ፣ ጽጌ ዱጉማ እና በሪሁ አረጋዊ አራት ሚሊዮን ብር በነብስ ወከፍ ሲሸለሙ፣ ለተቀሩት የቡድኑ አባላት እንደየተሳትፏቸው ከ50ሺ ብር ጀምሮ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።

ዘገበው የቢቢሲ አማርኛ ነው።

14/08/2024

ሰውየው

አሁንም ቢሆን ነገሮች ካልተስተካከሉ ሁለት ሚልዮን ብሩን አልቀበልም

😎😎😎

"የኢትዮጵያ ህዝብ እና ክብርት ፕሬዝዳንትን ይቅርታ እጠይቃለሁ!"

- አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ

አሰልጣኝ ገመዱ ደደፎ የተሰጠውን የሁለት ሚልዮን ብር ሽልማት ያልተቀበልኩት “ ለሙያው የተሰጠው ክብር አነስተኛ በመሆኑ ነው “ ሲል ተናግሯል።

"ለአሰልጣኝ የሚሰጠው ክብር አነሰተኛ ነው" ያለው አሰልጣኙ

"እኛ የብር ችግር የለብንም ፤ ለእኔ ከገንዘቡ ስሙ ይሻለኛል።

እንደ ታምራት ኒሻኑን ቢሰጡኝ በቂ ነበር" ብሏል።

"የሰው ልጅ ይሳሳታል" ያለው አሰልጣኝ ገመዶ ደደፎ " በብዙ ችግሮች የመጣው ነገር ስሜታዊ አድርጎኝ ነው” ብሏል።

“ የኢትዮጵያን ህዝብ እና ክብርት ፕሬዝዳንትን ይቅርታ እጠይቃለሁ" ብሏል።

አሰልጣኙ በመጨረሻም አሁንም ቢሆን ነገሮች ካልተስተካከሉ ሁለት ሚልዮን ብሩን እንደማይቀበል ሲገልጽ ነገሮች ከተስተካከሉ ሽልማቱን እንደሚቀበል ተናግሯል።

ከEBC ጋር ካደረገው ቃለመጠይቅ የተወሰደ

😎😎😎

🌴🌴🌴

ሳባ ዳንኤል ትባላለች ደብረ ማርቆስ ኢትዮጵያ ተወላጅ ስትሆን 11 አመት ልጅ ናት ፤አባቷ እንግሊዛዊው ሲሆን እናቷ ኢትዮጵያዊት ናት በልጅ አገረዶች የእግር ኳስ ክለብ ውስጥ ተሳታፊ ስትሆን ...
14/08/2024

ሳባ ዳንኤል ትባላለች ደብረ ማርቆስ ኢትዮጵያ ተወላጅ ስትሆን 11 አመት ልጅ ናት ፤አባቷ እንግሊዛዊው ሲሆን እናቷ ኢትዮጵያዊት ናት በልጅ አገረዶች የእግር ኳስ ክለብ ውስጥ ተሳታፊ ስትሆን ብዙ ጎሎችን በማስቆጠር ትታወቃለች ወደፊት እንደ ሳካ መሆን ምኞቷ እንደሆነ አስታውቃለች። በርቺ ይቅናሽ Mahilet Girma Abebe

12/08/2024

🙏🙏🙏❤️❤️❤️

"With immediate effect."

ኢንስትራክትር መሰረት መንግስቱ

ዶ/ር አሸብርን በመተካት የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ፕሬዚዳንት ሆነው ቢሾሙ

ምን ይመስላችዋል⁉️

?????

🙏🙏🙏

🌴🌴🌴

07/07/2023

Address

Kasanchis
Addis Ababa

Telephone

+251972183031

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when DAF news posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to DAF news:

Share