Niftalem promotion Worke

Niftalem promotion Worke I am promoter

ሀላባ : በጎርፍ  የ5 ሰዎች ሕይወት አለፈ  | በሀላባ ዞን በትላንትናዉ እለት  ነፋስና በረዶ ቀላቅሎ በጣለዉ ከባድ ዝናብ ባስከተለዉ ጎርፍ  የ5 ሰዎች ህይወት መጥፋቱ ፖሊስ ገለፀሆሳዕና ...
05/05/2024

ሀላባ : በጎርፍ የ5 ሰዎች ሕይወት አለፈ

| በሀላባ ዞን በትላንትናዉ እለት ነፋስና በረዶ ቀላቅሎ በጣለዉ ከባድ ዝናብ ባስከተለዉ ጎርፍ የ5 ሰዎች ህይወት መጥፋቱ ፖሊስ ገለፀ

ሆሳዕና ሚያዚያ 27 ቀን 2016 (ማ.ኢ.ፖ.ኮ) በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሀላባ ዞን ነፋስና በረዶ ቀላቅሎ በጣለዉ ከባድ ዝናብ ባስከተለዉ ጎርፍ 5 ሰዎች ተወስደዉ ህይወታቸዉ ማለፉ የዞኑ ፖሊስ ገለፀ።

የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ በጠፋዉ የሰዉ ህይወት ማዘናቸዉን ገልፀዉ ለሟች ቤተሰቦች መፅናናትን ተመኝተዋል።
በዞኑ በዌራ ዲጆ ወረዳ በሁሉም ቀበሌያት ከባድ ዝናብ በመጣሉ አካባቢዉ በጎርፍ መጥለቅለቁ ነዉ የተገለፀዉ።

በወረዳዉ በበንዶ ጮሎክሳ ቀበሌ (3)ሰዎች በኡደና ጮሎክስ (1) ሰው በሀለባ ቁሊቶ በገለቶና በገደባ መሀል (1) ሰው በአጠቃለይ ( 5)ሰዎች በጎርፍ የተወሰዱ ሲሆን ሲሆን የሶስት ሰዎች አስክሬን በፍለጋ ሲገኝ የሁለት ሰዎች አስክሬን ያልተገኘ በመሆኑ ፖሊስ ከአካባቢዉ መሀበረሰብ ጋር በመሆን የሟቾችን አስክሬን በማፈላለግ ላይ እንደሚገኝ ተገልጿል።

ሀይለኛ ወጀብና በረዶ የተቀላቀለበት ዝናብ በመጣሉ ምክንያት 5 ሰዎች ህይወታቸዉን በጎርፍ አደጋ ምክንያት በማጣታቸዉ በእጅጉ ማዘናቸዉ የገለፁት የሀላባ ዞን ዋና አስተዳደሪ አቶ ሙህድን ሁሴን ለሟች ቤተሰቦች መፅናናትን ተመኝተዋል።

ዋና አስተዳዳሪዉ አክለዉም ሀገራዊና ክልላዊ የዝናብ ትንበያ መረጃዎችን ከመከታተል ባለፈ በዞናችን የተለያዩ መዋቅሮች ሊኖር የሚችለውን የዝናብ/አየር ሁኔታዎች በመገናዘብ ተጨማሪ አደጋ እንዳይከሰት ህብረተሰቡ ጥንቃቄ ሊያደርግ እንደሚገባ መልዕክታቸዉን አስተላልፈዋል።

በታጁ ነጋሽ(ምክትል ኮማንደር)

በአገረ ጀርመን በኮሮና ምክንያት ህይወቱ ያለፈን ኢትዮጵያዊ መንግስት በህጋቸው መሰረት እሬሳውን ሊያቃጥለው ሲል ሊቀ ካህናት ዶ/ር መርዓዊ በአካል የማያውቁትን ሰው እኔ አለሁት በማለት  ብቻ...
04/03/2021

በአገረ ጀርመን በኮሮና ምክንያት ህይወቱ ያለፈን ኢትዮጵያዊ መንግስት በህጋቸው መሰረት እሬሳውን ሊያቃጥለው ሲል ሊቀ ካህናት ዶ/ር መርዓዊ በአካል የማያውቁትን ሰው እኔ አለሁት በማለት ብቻቸውን አልቅሰው፣ ብቻቸውን ቀድሰው፣ ብቻቸውን አፈር አልብሰውታል••• ኢትዮጵያዊነት መገለጫ ቀለሙ ብዙ ነው!

አንድ ካህን ቆሞ አልቅሶ የቀበረህ
ውዱ ኢትዮጵያዊ አፈሩ ይቅለልህ።❤❤❤

Zelalem Tsegaye

28/02/2021

ታማኝነት ልክ እንደመስታወት ነዉ..አንዴ ከተሰበረ እንደ ድሮ ማየት አይቻልም

Waw እንኳን ደስ አላችሁ ብዙዎቻቹ ስጠይቁኝ የነበረው የአድዋ ፈሪጥ የነበረው የካዎ ጦና photo የምገኝበት ትሸሪት ታትሞ እያለቀ ይገኛል Pulalliya የህትመት ስራየት እናገኛለን ለምት...
27/02/2021

Waw እንኳን ደስ አላችሁ ብዙዎቻቹ ስጠይቁኝ የነበረው የአድዋ ፈሪጥ የነበረው የካዎ ጦና photo የምገኝበት ትሸሪት ታትሞ እያለቀ ይገኛል

Pulalliya የህትመት ስራ
የት እናገኛለን ለምትሉን
አድራሻችን ቦዲቲ አዋሽ ባንክ ጎን እንገኛለን
አድዋን ከካዎ ጦና ጋር
ዋጋው ስንት ነዉ ለምትሉ በተናጠል 200
በጉሩፕ ስሆን ቅናሽ እናደርጋለን
ለበለጠ መረጃ ። 0923800426

ሀ
26/02/2021

Tona vs Minilik1896 ታርካዊ ቀን።።።።ንቃቃት የክነ ጥበብ ቡድን
26/02/2021

Tona vs Minilik

1896 ታርካዊ ቀን

።።።።ንቃቃት የክነ ጥበብ ቡድን

እንኳን ለ125 ዓመት ለአድዋ በዓል አደረሳችሁ ንቃቃት የክነ ጥበብ ቡድን።።።።። Niftalem promotion Worke
26/02/2021

እንኳን ለ125 ዓመት ለአድዋ በዓል አደረሳችሁ

ንቃቃት የክነ ጥበብ ቡድን
።።።።። Niftalem promotion Worke

Shar&like
24/02/2021

Shar&like

አስካለ ተስፋዬን እንታደግ..በጠና ታማለች!! # እውነተኛ  # ጋዜጠኝነት  # የቢሮ ስራ አይደለም። ወሬውን ከፈረሱ አፍ ይዞለመምጣት  # ውጭ  # ውሎ ውጭ የማደር ግድ እንጂ። በተለይ ጋዜ...
15/02/2021

አስካለ ተስፋዬን እንታደግ..በጠና ታማለች!!
# እውነተኛ # ጋዜጠኝነት # የቢሮ ስራ አይደለም። ወሬውን ከፈረሱ አፍ ይዞ
ለመምጣት # ውጭ # ውሎ ውጭ የማደር ግድ እንጂ። በተለይ ጋዜጠኝነት
ባህል እና ህዝብን የማቀራረብ፣ ታሪክና ማንነትን የማሳወቅ ሃላፊነትን ሲሸከም
ያኔ ለአንድ ዜናና ፕሮግራም ቀናትን ውጭ ውሎ ውጭ የማደሩ ግድነት ይፀናል።
እንግዲህ ይህንን ከበድ ያለ ስራ ብዙው ጋዜጠኛ መርጦት አላይም። ምቾት
ይነሳል። እልም ያለ ሩቅ ስፍራ መጓዝን፣ ከስልጣኔ ተራርቆ መቆየትን፣ አቀበት
ወጥቶ ቁልቁለት ወርዶ አንድ ቁምነገር ይዞ ወደየሰዉ ቤት መምጣትን፣
የህዝብን ኑሮ መኖርን፣ የበሉትን በልቶ የጠጡትን ጠጥቶ ያደሩበት ማደርን
ይፈልጋል። ሆቴል አማርጦ ማደርና በሜኑ አዝዞ መብላት በዚህ ጋዜጠኝነት ዘርፍ
ላይ ቢፈልጉትም አይገኝም። ታዲያ በግሌ ይህን አድካሚ ስራ ሴት ጋዜጠኞች
ሲወጡት ሳይ ደግሞ አድናቆቴን ለመግለፅ አፌን አያነቅፈኝም።
በል ጀምር በሉኝና በቱሪዝም ጋዜጠኝነት አንድ ሰው ጥራ ካላችሁኝ የ Atsede
Wudineh ን ስም ከአፌ የሚነጥቀኝ የለም።በፅናቷ እንዳስደመመችኝ ድንገት
ጠፋች። ኢቢኤስ የእውነት ጋዜጠኛ ዘውዱን ያወለቀው እሷ ያንን የመሰለ
ፕሮግራም ጥላ የሄደች ቀን ነው። እመጣለሁ ብላለች ለነገሩ።
በባህልና ህብረተሰብ ጋዜጠኝነት ዘርፍ ሌላ ሴት ጨምር ካላችሁኝ ደግሞ
ፎቶዋን የምታዩዋት Askale Tesfaye አስካለ ተስፋዬን ካልጠራሁ ቀሽም ነኝ
ማለት ነው።
ጋዜጠኛ ሸልም ብባል ግን ቀድሜ ዋንጫ የማቀብላት ጠንካራ ጋዜጠኛ እሷ
ናት። "ውሎ አዳር" የተሰኘ የባህልና ህብረተሰብ ዘውግ የቴሌቪዥን ፕሮግራሟን
ስከታተል ዝንብ እንድትከልለኝ እንኳን አልፈቅድም። ትችላለች። ከልብ፣
በፍላጎትና በፍቅር ሙያውን አክብሮ ላቡን ጠብ የሚያደርግ እንደሷ ያለ ሰው
የልቤ ሰው ነው። ኢቢሲ በርሷ እድለኛ ነው። ፈጣሪ ይማርሽ..melaku
Share,ሼር እናድርገው

Romiyo and Julete ❤❤❤❤❤❤❤Happy Valentine day   በንቃቃት የክነ ጥበብ ብዱን ተዘጋጅቶ የቀረበ ሮምዮ ና ጁለት❤❤❤❤❤❤❤የተሰኘ በይዘቱ ለየት ያለ የመድረክ ላይ ትያ...
10/02/2021

Romiyo and Julete ❤❤❤❤❤❤❤

Happy Valentine day

በንቃቃት የክነ ጥበብ ብዱን ተዘጋጅቶ የቀረበ

ሮምዮ ና ጁለት❤❤❤❤❤❤❤

የተሰኘ በይዘቱ ለየት ያለ የመድረክ ላይ ትያትር በ ሁለገብ አዳራሽ ስለሚቀርብ በቀነ ቅዳሜ ማለትም በቀን 6/6/2013 ሁላችሁም በ አክብሮት ተጋብዘዋል❤❤❤❤❤❤

30/01/2021

ለመንግስት የተፃፈ ደብዳቤ
ተፃፈ በ (በላይ በቀለ ወያ)
እንደምነህ መንግስት? ፣ እኔ አለሁ በደህና
ባመቻቸህልኝ የልማት ጎዳና
ታክሲ ለመጠበቅ ፣ ሰልፍ ተሰልፌ
ለወንበር ስጋፋ ፣ ኪሴን ተዘርፌ
አለሁልኝ በተድላ
በቀን ሶስት ጊዜ...
ቁርስ ምሳ ራቴን ፣ መከራ ስበላ
ያንተ ደህንነት ነው ፣ እኔን ሚያስጨንቀኝ
ኑረህ እንደሌለህ ፣ የምትናፍቀኝ
ቀልድ ቁምነገርህ ፣ አመት የሚያስቀኝ
እንደምነህ አንተ?
አንተ ደና ከሆንክ ፣ እኔንኳ ደና ነኝ፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እንደምነህ መንግስት ፣ እኔ አለሁ በደና
ባመቻቸህልኝ የልማት ጎዳና
እየተጠቀምኩኝ
ለማይበራ መብራት ፣ ቀብድ እየከፈልኩኝ
ለማይሰራ ኔትወርክ ፣ ካርድ እየገበርኩኝ
በሰጠኸኝ እድል ፣ ቆንጆ ሴት አፍቅሬ
የማይመጣ ውሃ
የማይመጣ መብራት
የማትመጣን ሴት ፣ አንድ ላይ ቀጥሬ
ትመጣለች እያልኩ እጠብቃታለሁ
አንተ ግን እንዴት ነህ? እኔ እንዳለሁ አለሁ፡፡
፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡፡
እንደምነህ መንግስት ? እኔ አለሁ በደህና
ባመቻቸህልኝ የልማት ጎዳና
አንድ ላምስት ሆኜ ፣ እየተደራጀው
ማይተገበር ህግ ፣ ፅፌ እያዘጋጀው
አለሁኝ በተድላ
እንደምነህልኝ
እንደምነህልኝ ፣ ካልኩህስ በኅላ?
እኔ አለው በድሎት....
ኖረህ እንደሌለህ አለሁ ስትናፍቀኝ
ቀልድ ቁምነገርህ ፣ አመት እያሳቀኝ
በጠና ታምሜ...
ያንተ ደና መሆን ፣ አለሁ ሲያስጨንቀኝ
አንተ ግን እንዴት ነህ?
አንተ ሰላም ከሆንክ ፣ እኔም ሰላም አለኝ፡፡

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Niftalem promotion Worke posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share