አል ቀለም

አል ቀለም The role of this association is to contribute professional insights for Ethiopian Muslim community.

በUstaz Abubeker Ahmed/ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ. አማካኝነት ግምቱ ከ 60 ሚሊየን ብር በላይ የሆነ የህክምና መገልገያ ቁሳቁስ ለትግራይ ጤና ቢሮ ተበረከተ።♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦...
05/03/2025

በUstaz Abubeker Ahmed/ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ. አማካኝነት ግምቱ ከ 60 ሚሊየን ብር በላይ የሆነ የህክምና መገልገያ ቁሳቁስ ለትግራይ ጤና ቢሮ ተበረከተ።
♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️

በኡስታዝ አቡበክር አህመድ አማካኝነት ከ Orphans in Need usa የተገኙትንና ግምታቸው ከ 60 ሚሊየን የኢትዮጵያ ብር በላይ የሆኑ የህክምና መገልገያ ቁሳቁስ በዛሬዉ እለት ለትግራይ ጤና ቢሮ በኡስታዝ አቡበክር ወኪል በኩል እንዲደርስ ተደርጓል።

የትግራይ ጤና ቢሮ የህክምና ቁሳቁሶች እርዳታ በመደረጉ አመስግነው የጤና መድህንን ለማሳካት እገዛ እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

ኡስታዝ አቡበክር አህመድ በግል ከሚደግፉት አልፈዉ መንግስታዊና መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች በማስተባበር በሀገሪቱ የተለያዩ አከባቢዎች በችግር ዉስጥ ለሚገኙ ወገኖቻችን ከፍተኛ እርዳታ እያደረጉ በመሆኑ በእጅጉ ያስመሰግናቸዋል:: እ ና መ ሰ ግ ና ለ ን::

15/12/2023
የኢትዮጵያ ባንኮችና ለሐጅ ዶላር የማግኘት ፈተናዎች🔵🔴🔵🔴🔵🔴🔵🔴🔵🔴🔵🔴🔵🔴🔵ክፍል ሦስት🌼🌼🌼«የኢትዮጵያ ባንኮችና ለሐጅ ዶላር የማግኘት ፈተናዎች» በሚል ርዕስ ላለፉት ሁለት ክፍሎች ብዙ ነጥቦ...
27/06/2022

የኢትዮጵያ ባንኮችና ለሐጅ ዶላር የማግኘት ፈተናዎች
🔵🔴🔵🔴🔵🔴🔵🔴🔵🔴🔵🔴🔵🔴🔵
ክፍል ሦስት
🌼🌼🌼

«የኢትዮጵያ ባንኮችና ለሐጅ ዶላር የማግኘት ፈተናዎች» በሚል ርዕስ ላለፉት ሁለት ክፍሎች ብዙ ነጥቦችን ተመልክተናል። ከጽሑፉ ጋር በተያየዘ በርካታ አስተያየቶችም ደርሰውኛል።በእርማት መልክ ከደረሱኝ መካከል የኦሮሚያ ሕብረት ሥራ ባንክ ለዘንድሮ ሐጅ ሁለት ሚሊዮን ዶላር መሸጡን መጠቀሱ ጋር የተያያዘ አንዱ ነበር። የባንኩ የወለድ ነጻ ዘርፉ ሃለፊ የተንቀሳቃሽ ስልክ መልዕክት ልከው የኦሮሚያ ሕብረት ባንክ የወለድ ነጻ ክፍል የሆነው «አልሁዳ» ለዘንድሮ የሐጅ ተግባር የሰጠው ዶላር ሁለት ሚሊዮን ብቻ ሳይሆን በተጨማሪነት ከሰጠው 250ሺህ ዶላር ጋር በጠቅላላው 2,250,000(ሁለት ሚሊዮን ሁለት መቶ ሀምሳ ሺህ) መሆኑን ገልጸውልኛል። ክፍል ሦስት እነሆ፤

ለምን ያክል ሰዎች ብድር ሰጡ?
🔷🔷🔷🔷🔷🔷🔷🔷🔷

ቀደም ባለው ክፍል እያንዳንዱ ባንክ በወለድ አልባ ባንክ ዘርፍ ምን ያክል ገንዘብ ለደንበኞች ፋይናንስ እንደሰጠና ምን ያክል እንዳልሰጠ ተመልከተናል።አሁን ደግሞ ብድር መውሰድ የቻሉትን የደንበኞች ብዛት በዝርዝር እንመለከታለን፤ የተሰጠውን የገንዘብ መጠን ብቻ ማየት ትክክለኛ ምስል ላይ ሰጠን ስለሚችል ለምን ያክል ተጠቃሚዎች ተሰጠ የሚለውን ማየት ጠቃሚ ነው። ምክንያቱም አንድ ባንክ አንድ ቢሊዮን ብር ብድር ሰጠ ብቻ ብለን ካለፍን ያን አንድ ቢሊየን ብሩን ለስንት ሰው ሰጠ የሚለውን አይገልጽምና።

ለምሳሌ ባንኩ ያንን አንድ ቢሊዮን ብር ለአንድ ነጋዴ ለብቻው እንደለ አበድሮት፥ለአምስት፥አስር ወይም መቶ ነጋዴዎች አከፋፍሏቸው ሊሆን ይችላልና።ስለዚህ ከወለድ ነጻ የባንክ ዘርፍ ምን ያክል ደንበኞች ፋይናንስ በማግኘት ተጠቃሚ እንደሆኑ ማየትም እጅግ ጠቃሚ ነው።

የወለድ አልባ ባንክ ዘርፍ በሀገራችን ከተጀመረ ጊዜ አንስቶ እስከ መጋቢት 22 ቀን 2013(ማርች 31 ቀን 2021) ድረስ በሁሉም ባንኮች በወለድ አልባ ዘርፍ አማካኝነት ብድር መውሰድ የቻሉ ሰዎች ብዛት በጠቅላላ 3,319(ሦስት ሺህ ሦስት መቶ አስራ ዘጠኝ) ብቻ ናቸው።

የወለድ ነጻ የባንክ ዘርፍን የጀመሩት ባንኮች መካከል እያንዳንዳቸው ለምን ያክል ደንበኞች ፋይናንስ እንደሰጡ በማርች 31 ቀን 2021 የተሰበሰበ መረጃን መሠረት በማድረግ እንደሚከተለው እንመለከታለን፦

1. ቡና ባንክ-0(በጊዜው ምንም ብድር አልሰጠም)።በደረጃ 11ኛ።

2. ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ፡-ብድር የወሰዱት ደንበኞች ብዛት 28(ሃያ ስምንት) ሲሆን ከአጠቃላዩ ላይ 0.844% ድርሻ ኖሮት በደረጃ 10ኛ፤

3. ወጋገን ባንክ፡- ብድር የወሰዱት ደንበኞች ብዛት 59(ሀምሳ ዘጠኝ) ሲሆን ከአጠቃላዩ ላይ 1.78% ድርሻ ኖሮት በደረጃ 9ኛ።

4. አቢሲኒያ ባንክ-ብድር የወሰዱት ደንበኞች ብዛት 71(ሰባ አንድ) ሲሆን ከሀገር ዐቀፉ 2.14% ድርሻ ሲኖረው በደረጃ 8ኛ።

5. አባይ ባንክ-120(አንድ መቶ ሃያ) ሲሆን ከሀገር ዐቀፉ 2.62% ድርሻ ኖሮት በደረጃ 7ኛ።

6. ሕብረት ባንክ፡- ብድር የወሰዱት ደንበኞች ብዛት 241(ሁለት መቶ አርባ አንድ) ሲሆን ከሀገር ዐቀፉ 7.26% ድርሻ ሲኖረው በደረጃ 6ኛ።

7. የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፦ ብድር የወሰዱት ደንበኞች ብዛት 387(ሦስት መቶ ሰማንያ ሰባት) ሲሆን ከጠቅላላው 11.66% ድርሻ በደረጃ 5ኛ።

8. ዳሸን ባንክ፦ ብድር የወሰዱት ደንበኞች ብዛት 391(ሦስት መቶ ዘጠና አንድ) ሲሆን ከሀገር ዐቀፉ 11.78% ድርሻ ሲኖረው በደረጃ 4ኛ።

9. አዋሽ ባንክ፦ ብድር የወሰዱት ደንበኞች ብዛት 406(አራት መቶ ስድስት) ሲሆን ከሀገር ዐቀፉ 12.23% ድርሻ ሲኖረው በደረጃ 3ኛ።

10. ኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ፦ ብድር የወሰዱት ደንበኞች ብዛት 752(ሰባት መቶ ሀምሳ ሁለት) ሲሆን ከሀገር ዐቀፉ 22.66% ድርሻ ሲኖረው በደረጃ 2ኛ።

11. ኦሮሚያ ሕብረት ሥራ ባንክ፦ ብድር የወሰዱት ደንበኞች ብዛት 864(ስምንት መቶ ስልሳ አራት) ሲሆን ከሀገር ዐቀፉ ዉስጥ 26.03% ድርሻ ኖሮት በደረጃ 1ኛ ነው።

ለምንድነው የማያበድሩት? ብሩስ የት ሄደ?
🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁🍁

በወለድ ነጻ የባንክ ኢንደስትሪ ዘርፍ አምና ከ97 ቢሊዮን ብር በላይ የነበረው ተቀማጭ በአሁኑ ጊዜ እንደምንሰማው ከመቶ ሀያ ቢሊዮን ብር አልፏል።የዘርፉ የፋይናንስ መጠን ማደጉ ለሀገር ኢኮኖሚ እጅግ ጠቃሚ ነው። ሆኖም ጠቃሚ የሚሆነው የሰዎችን ገንዘብ ሰብስቦ በማስቀመጥ ግሽበት እንዲበላው በማድረግ ሳይሆን ገንዘቡን ለሚፈልጉት ፋይናንስ በማድረግ አስቀማጩን፥ ተበዳሪውንና በአጠቃላይ የሀገር ኢኮኖሚውን ማገዝ ሲቻል ነው።

ወደ ባንኮች በመሄድ በወለድ አልባ ዘርፍ ፋይናንስ ለማግኘት የሚሄዱ አንዳንድ ሙስሊሞች እንደሚሉት የተወሰኑ ባንኮች «በሸሪዓው መሠረት» እያሉ የሚያስተዋዉቁት ሙስሊሞች ያለወለድ ገንዘባቸውን እነርሱ ጋር እንዲያስቀምጡ እንጂ እንዲበደሩ የሚፈልጉ አይመስሉም እያሉ ቅሬታ ያቀርባሉ።ሌሎች ደግሞ የዶ/ር አብይ መንግስት ዉሳኔ ሆኖባቸው እንጂ ዛሬም ድረስ የወለድ አልባ የባንክ ዘርፍ ራሱ በኢትዮጵያ እንዲኖር የማይፈልጉ አካላት እንዳሉ ይጠቁማሉ።

እንዲያውም አንድ የባንክ ባለሞያ እንደሚሉት በሆነ መንገድ የመንግስት ለውጥ ቢመጣ የወለድ ነጻ ባንኮችን ብቻ ሳይሆን ዘርፉንም ጭምር በሀገሪቱ እንዳይኖሩ ለማገድ የሚፈልጉ የሚመስሉ በፋይናንስ ዘርፍ ያሉ ጥቂት የመንግስት አካላት ጭምር እንዳሉ በማሳያነት አብነቶችን አንስተው የግለሰቦቹን ስም ጭምር እየጠቀሱ አብራርተውልኛል። ሆኖም ስለግለሰቦቹ እዚህ ላይ ለማቅረብ ይቸግረኛል።

በወለድ ነጻ ዘርፍ የተሰማሩ የሀገራችን ባንኮች የሚጠበቅባቸውን ያክል ብድር ለምን እንዳልሰጡ በርካታ ምክንያቶች ይጠቀሳሉ። በጉዳዩ ላይ ካናገርኳቸው የተለያዩ ወገኖች ያገኘኋቸው ምክንያቶች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል።

1. ባንኮቹ ከፍተኛ ብር ሰብስበው የሚጠበቅባቸውን ያክል ብድር ካልሰጡ ያ የተሰበሰበው ብር የት ሄደ? ብለው የሚጠይቁም አልጠፉም።አንዳንዶች በወለድ አልባ በኩል የሰበሰቡትን ገንዘብ እንደሚገባው ካላበደሩ መቼስ ገንዘቡ ተቀምጦ ግሽበት(Inflation) እንዲበላው ያደርጋሉ ብሎ ማሰብ አይቻልም።ይህ ካልሆነ አንድ የግል ባንክ ሠራተኛ እንጠቀሰው አንድም በወለድ አልባ በኩል የሰበሰቡትን በወለድ አልባ በኩል ካላበደሩ ያን ያላበደሩትን ገንዘብ በመደበኛ ባንካቸው በኩል ማለትም በወለዱ በኩል እያበደሩት ነው ማለት ነው።

አልያም ባንኮቹ ከሰበሰቡት ገንዘብ ዉስጥ እስከ 80% ያክል አበድረው ቀሪውን 20% ደግሞ ለብሄራዊ ባንክ (ለሊኪዩዲቲ ሬሾ/ደንበኞች ሲፈልጉት እንዲሰጣቸው በባንኮቹ ዉስጥ የሚቀመጥ/ እና ሪዘርቭ ሬሾ/ብሩ በተጠባባቂነት ብሄራዊ ባንከ ጋር የሚቀመጥ) ማሳየት ስለሚጠበቅባቸው በወለድ በሚሰራው ቅርንጫፋቸው በኩል አብዛኛዎቹ ባንኮች ያበደሩት ከ80 % በላይ እያለፈ ስለሆነ የወለድ አልባውን ተቀማጭ ገንዘብ ለወለድ ዘርፉ ባንክ 20% ለብሄራዊ ለማሳየት እየተጠቀሙበት ነው ማለት ነው ይላል።

2. በአንድ ባንክ ብድር ክፍል ዉስጥ ይሠራ የነበረ አንድ ሠራተኛ እንደገለጸልኝ እኔ የነበርኩበት ባንክ የባንኩ ቦርዶች ብዙ ገንዘብ በተቀማጭነት ሲሰባሰብ እጅግ ደስ ይላቸዋል። ሆኖም ከተሰበሰበው ላይ ብድር ሲሰጥ ግን እጅግ ይከፋቸዋል።በአንድ ወቅት በተቀማጭነት ከሰበሰብነው ገንዘብ ጋር ሲነጻጻር እጅግ ጥቂት የሆነ መጠነኛ ገንዘብ በብድር ስንሰጥ የባንኩ አመራሮች «ብዙ ብሮችን ብድር ሰጣችሁ» ብለው ገመገሙን» በማለት «ማበደር ያን ያክል አይፈልጉም» ለሚለው ሀሳቡ ማሳያነት ያቀርባል።

3. በጉዳዩ ላይ ያናገርኳቸው ጥቂት ነጋዴዎች ደግሞ በወለድ አልባ ዘርፍ የባንኮቹ አሠራር ሆነ ተብሎ ሰዉ ብድር እንዳይጠይቅ በሚመስል መልኩ ለመበደር ፕሮሰስ የሚበዛውና ዉስብስብ አድርገውታል ይላሉ።

4. በመደበኛው ባንክ በወለድ መበደር በኢስላም እጅግ የተኮነነ በመሆኑ የፋይናንስ አማራጭ በማጣት በወለድ የተበደሩ ሙስሊሞች ብዙውን ጊዜ ሲከስሩና ያስያዙት ንብረት በሀራጅ ሲሸጥ ታይቷል።ተሰምቷል። ይህም በርካታ ሙስሊሞች ዘንድ ከባንክ መበደር የሚለው ሀሳብ ላይ ራሱ አሉታዊ እይታ ፈጥሯል። ብዙ ሙስሊሞች ወደ ባንክ ለመበደር እንዳይመጡ የሚያደርጋቸው ይህ ነው የሚሉ አሉ።

5. በተለያዩ ከተሞች ላይ በወለድ ነጻ ባንክ ዘርፍ የተሰበሰበው ገንዘብ በዚያ በተሰበሰበበት ከተማ ቢሮክራሲውን ታግሶና ጫና ፈጥሮ ገፍቶ መጥቶ ብደር የሚጠይቅ ብዙ ሰው ባለመኖሩ ያ የተቀመጠው ገንዘብ የሚበደሩ አካላት በብዛት ወደ አሉበት ሌሎች አከባቢዎች ይሄዳል። ከዚህ የተነሳ ሙስሊሞች አስቀማጭ እንጂ ተበዳሪ አልሆኑም የሚሉም አሉ።

6. አብዛኛው የባንክ ገንዘብ አስቀማጭ በዝቅተኛና በመካከለኛ ገቢ ደረጃ ያለው ሲሆን እነኚህ የህብረተሰብ ክፍሎች ደግሞ ከባንክ በሸሪዓው መሠረት ተበድረው ሥራ ለመሥራት ግንዛቤውም ሆነ ተነሳሽነት የሌላቸው ናቸው። ተነሳሽነት ቢኖራቸው እንኳ የሚያስይዙት ኮላትራል(ንብረት) ስለሌላቸው ብድር ቢጠይቁም አይሰጣቸውም።ከፍ ያለ ገንዘብ የሚያንቀሳቅሱ ነጋዴዎች ደግሞ ከባንክ ይበደራሉ እንጂ ገንዘባቸውን በካሽ በባንክ ዉስጥ አያስቀምጡም። ይህ በመሆኑ ያስቀመጡት አካላት ስለመበደር ግንዛቤ የሌላቸውና መበደር የማይችሉ ሲሆኑ ሀብታሞቹ ደግሞ ያላስቀመጡትን የሚጠይቁ ናቸው።ከዚህና የነጋዴው ግንዛቤ ማነስ የተነሳ ባንኮቹ ዘና ብለው በፈለጉበት መንገድ ያበድራሉ። የሚሉ አሉ።

7. ሌላኛው የሚጠቀሰው በወለድ አልባ ዘርፍ ያለው የሕዝቡ ግንዛቤ ማነስ ነው።አንዳንድ ሙስሊሞች ከወለድ ነጻ ባንክ ሲባል ያለምንም ትርፍ ወይም ከትርፍ ነጻ ሆኖ ብድር የሚሰጥ ይመስላቸዋል።ስለሆነም ባንኮች ዘንድ መጥተው ፋይናንስ ሲጠይቁና ባንኩ በሙራበሃ ፋይናንሲንግ ከነርሱ የሚፈልገውን የትርፍ መጠን ሲሰሙ «ከወለድ ነጻ ብላችሁ» በሚል ዓይነት ሁኔታ ትርፉንና ወለዱን አምታተው በመረዳት ቅር የሚላቸው እንዳሉ ይናገራሉ።

8. በአሁኑ ሰዓት በሀገራችን በወለድ አልባ ባንኮች በኩል በአብዛኛው እየተሰጠ ያለው ብድር(ፋይናንስ) ለሙራበሃ ፋይናንሲንግ ዘርፍ (ባንኩ ደንበኛው የሚፈልገውን ነገር ገዝቶለት ደንበኛው ብደሩን የሚከፍልበትን የጊዜ ገደብ ግምት ዉስጥ በማስገባት የራሱን/ሪብህ/ ትርፍ ጨምሮበት እቃውን መልሶ ለደንበኛው የሚሸጥበት አሰራር) እና ለኤክስፖርት በቀጥታ ገንዘብ የሚሰጥበት(ደንበኛው በብሩ እቃዎችን ገዝቶ ወይም አምርቶ ኤክስፖርት ካደረገ በኋላ ገንዘቡን ትርፍ ሳይጨምርበት በብር ሳይሆን በዶላር በወሰደበት ጊዜ በነበረው የምንዛሬ ስሌት የወሰደውን ገንዘብ የሚመጥን ዶላር ለባንኩ የሚመልስበት) የፋይናንስ አሰራር ብቻ ነው።በመሆኑም ከዚህ አማራጭ ዉጭ ያሉ የወለድ አልባ ፕሮዳክቶች በብዛት እየተሰራባቸው ባለመሆኑ ይህም የተበዳሪዎችን ቁጥር እንደቀነሰ የሚጠቅሱ አሉ።

9. ሌላኛው በምክንያትነት የሚነሳው ነጥብ የብድር ጠያቂዎች የፕሮጀክት ዝግጅት፥ብድር የሚጠይቁበት ዘርፍ አዋጭነትና ትርፋማነት ማሳያ ዳሰሳ እና ሌሎች ተያያ ሰነዶችን በትክክል አለመረዳትና ማዘጋጀት አለመቻል ነው።ከዚህ አንጻር ይህንን ችግር ለመቅረፍ ስለወለድ ነጻ ዘርፍ የምክር፥የስልጠና፥ አስፈላጊ ጥናትና ሰነዶችን የማዘጋጀት አገልግሎት የሚሰጡ ባለሞያዎችና ተቋማት በየከተማው በስፋት መኖር እንዳለባቸው የሚጠቁሙ አሉ።

10. አንድ የባንክ ሠራተኛ እንደሚሉት ባንኮች በወለድ አልባ ዘርፍ እንደፈለጉት እንዳያበድሩ አንዱ እንቅፋት የሆነባቸው ባንኮች በኢንቨስትመንት ላይ ለመሳተፍ ያላቸውን መብት የሚገድበው መመሪያ እንደሆነም ይጠቅሳሉ።

የብሄራዊ ባንክ መመሪያ ቁጥር SBB/65/2017 መሠረት ማንኛውም ባንክ በቀጥታ ከባንክ ጋር ባልተያያዙ ዘርፎች ከአስር በመቶ በላይ ኢንቨስት እንዲያደርግ ከልክሏል።ይህ የወለድ ነጻ ባንኮችን አሠራር ግምት ዉስጥ ያልከተተ መመሪያ በመሆኑ በወለድ አልባ ባንክ ላይ የተሰማሩ ባንኮች እንደሌሎች ሀገራት በተለያዩ የቢዝነስ ዘርፎች ዉስጥ ከደንበኞቻቸው ጋር ጭምር በጋራ ኢንቨስት እንዳያደርጉ አቅቧቸዋል።

ምክንያቶቹ ከሞላ ጎደል ይህን ይመስላሉ።ባንኮቹ የሚሉት የተለየ ሀሳብ ካላቸውም አብረን እንመለከታለን።

ይቀጥላል...

Ahmedin Jebel-አሕመዲን ጀበል

የኢትዮጵያ ባንኮችና የሐጅ ዶላር ጥያቄ ነገርክፍል ሁለት❗❗❗❗❗❗❗❗❗❗❗❗❗❗❗❗በዚህ ጽሑፍ ክፍል 1 ቀደም ብለን እንደጠቀስነውም በአምናው ሪፖርት መሠረት ከዘጠና ሰባት ቢሊዮን በላይ ብር ...
26/06/2022

የኢትዮጵያ ባንኮችና የሐጅ ዶላር ጥያቄ ነገር
ክፍል ሁለት
❗❗❗❗❗❗❗❗❗❗❗❗❗❗❗❗

በዚህ ጽሑፍ ክፍል 1 ቀደም ብለን እንደጠቀስነውም በአምናው ሪፖርት መሠረት ከዘጠና ሰባት ቢሊዮን በላይ ብር በወለድ አልባ ባንኮቹ ጋር አስቀምጠዋል። ጥያቄው ማስቀመጡ በራሱ ችግር ሆኖ አይደለም። በባንኮቹ ዘንድ ገንዘባቸውን ያስቀመጡት ምን ጥቅም እያገኙበት ነው? የሚለው ነው። ባንኮቹ በሀላል መንገድ ከሚያተርፉት ብዙም ድርሻ እንደሌላቸው ቀደም ባለው ክፍል ተመልክተናል፤

ለሐጅ ተግባርም በርካታ ባንኮች ዶላር ለመሸጥም እንደሚያግደረድሩም አይተናል፤ቀጥሎ የምንመለከተው ደግሞ በባንኮቹ ዘንድ በወለድ ነጻ አማካኝነት ከተቀመጠው ገንዘብስ ሙስሊም ነጋዴዎች በሃላል መንገድ እየተበደሩ (ፋይናንስ እያገኙ) ሥራቸውን ማስፋፋትና ማሳደግ ችለዋል ወይ? የሚለውን ነው።ምክንያቱም ይህም ነጠብ ባንኮቹ ለሙስሊሞች ያበረከቱት አስተዋጽኦ ሊመዘንበት የሚገባው ሌላኛው ወሳኝ ነጥብ ነውና።

ከተቀማጭ ገንዘቡስ ምን ያክል ተጠቃሚ አደረጉ?
💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢💢

የሙስሊም ነጋዴዎች ዋና ችግር ቢዝነሳቸውን ለማሳደግ ያለባቸው ማነቆ ወለድ ነጻ ሥርዓት የሚቀርብ የገንዘብ አቅርቦት ችግር ነው። አብዛኛዎቹ ባንኮች «በሸሪዓው መሠረት» እያሉ ሙስሊሞች ገንዘባቸውን እነርሱ ጋር እንዲያስቀምጡ ማስታወቂያ እየሠሩ ይወተውታሉ። እስካሁን ከአስራ አንድ ሚሊዮን በላይ ሰዎች በወለድ ነጻ ዘርፍ ገንዘባቸውን ባንኮቹ ዘንድ ማስቀመጥ ጀምረዋል።

በኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ መመሪያ መሠረት ባንኮች ደንበኞቻቸው እነርሱ ጋር ተቀማጭ ካደረጓቸው ገንዘቦች መካከል 80% (ሰማንያ በመቶ ማለትም ከእያንዳንዱ መቶ ብር ላይ እስከ ሰማንያ ብር) ድረስ ለተበዳሪዎች ማበደር ይፈቅድላቸዋል።

በሀገራችን መደበኛ ባንኮች ዘንድ ከተቀመጠው አንድ ትሪሊዮን አራት መቶ ቢሊዮን(1,400,000,000,000) ተቀማጭ ገንዘብ ዉስጥ ወለድን የሚጠነቀቁ ሙስሊሞች ወለድ ስለማይወስዱና ስለማይከፍሉ ከዚህ ገንዘብ መበደር አይችሉም።

በወለድ ነጻ ባንክ ዘርፍ የተቀመጠው ገንዘብ በሀገሪቱ በባንኮች አጠቃላይ ከተቀማጭ ገንዘብ ዉስጥ ሰባት በመቶ(7%) ድርሻ ሲኖረው ይህም በብሄራዊ ባንክ ይፋዊ ሪፖርት እስከ አምና ድረስ አጠቃላይ መጠኑ ዘጠና ሰባት ቢሊዮን ብር ደርሷል።ከዚህ ተቀማጭ ገንዘብ ዉስጥ እያንዳንዱ ባንክ እርሱ ዘንድ ካለው ምን ያክሉን በሸሪዓው መሠረት ፋይናንስ አደረጉ የሚለውን እጅግ ወሳኝ በመሆኑ ምን ያክል ባንኮቹ ሙስሊም ነጋዴዎችንና ግለሰቦችን ለሥራቸው ማስፋፊያ፥ለቤት ግዢ፥ወዘተ እንዳበደሩ እንመለከታለን።

በብሄራዊ ባንክ መመሪያ መሠረት በአጠቃላይ ባንኮች ካለው 97 ቢሊዮን በላይ ብር ዉስጥ ሰባ ስምንት ቢሊዮን(78) ድረስ ማበደር ይችላሉ። ሆኖም እስከ ጁን 30 ቀን 2021 ድረስ ሰባ ስምንት ቢሊዮን ዉስጥ በአጠቃላይ ያበደሩት መጠን ግን 25,876,177,940 (ሀያ አምስት ቢሊዮን ስምንት መቶ ሰባ ስድስት ሚሊዮን አንድ መቶ ሰባ ሰባት ሺህ ዘጠኝ መቶ አርባ) ብር ያክል ብቻ ነው። ይህ ማለት እንዲያበድሩ ከተፈቀደላቸው ገንዘብ ዉስጥ ያበደሩት 33%(ሠላሳ ሦስት በመቶ) ብቻ ነው።ወይም ደግሞ ማበደር ከተፈቀደላቸው የተቀማጩ ገንዘብ 80%(ሰማንያ ከመቶ) ዉስጥ ያበደሩት የተቀማጩን ገንዘብ 26%(ሀያ ስድስት በመቶ) ብቻን ነው ማለት ነው። ቀጥሎ እያንዳንዱ ባንክ ካለው ተቀማጭ ላይ በብድር የሰጠውን ድርሻ በቅደም ተከተል እንመለከታለን።

1) እንደሀገር ከተቀማጭ ገንዘቡ ዉስጥ ለበርካታ ደንበኞች በማበደር የቀዳሚነቱን ሥፍራ የሚይዘው የኦሮሚያ ሕብረት ሥራ ባንክ ነው።የኦሮሚያ ሕብረት ሥራ ባንክ በሀገር ደረጃ በወለድ ነጻ ዘርፍ ከተሰጠው አጠቃላይ ፋይናንስ(ብድር) ዉስጥ 35.91%(ሠላሳ አምስት ነጥብ ዘጠኝ አንድ በመቶ) የሚሆነውን የርሱ ድርሻ ነው።

የኦሮሚያ ሕብረት ሥራ ባንክ በአጠቃላይ ካለው 11,978,627,691(አሥራ አንድ ቢሊዮን ዘጠኝ መቶ ሰባ ስምንት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሀያ ሰባት ሺህ ስድስት መቶ ዘጠና አንድ) ብር ዉስጥ እንዲያበድር በሕግ የሚፈቀድለት 9,582,902,152.8(ዘጠኝ ቢሊዮን አምስት መቶ ሰማኒያ ሁለት ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ሁለት ሺህ አንድ መቶ ሀምሳ ሁለት ብር ከሰማኒያ ሳንቲም) ያክል ብቻ ነው።ከዚህ ዉስጥ የኦሮሚያ ሕብረት ሥራ ባንክ በብድር የሰጠው 9,291,625,584.46(ዘጠኝ ቢሊዮን ሁለት መቶ ዘጠና አንድ ሚሊዮን ስድስት መቶ ሀያ አምስት ሺህ አምስት መቶ ሰማኒያ አራት ብር ከአርባ ስምንት ሳንቲም) ያክሉን ነው፤ይህ ማለት ፋይናንስ ማድረግ ከሚፈቀድለት ገንዘብ ዉስጥ 96.96%(ዘጠና ስድስት ነጥብ ዘጠና ስድስት በመቶ) ያክሉን አበድሯል።

በሌላ አነጋገር ከአጠቃላይ ተቀማጭ ገንዘብ ዉስጥ 80% ማበደር ሲፈቀድለት እርሱ ግን ያበደረው 78%(ሰባ ስምንት በመቶ) ያክሉን አበድሮ የቀረው 2%(ሁለት በመቶ) መጠን ነው ማለት ነው፤በዚህ ረገድም የኦሮሚያ ሕብረት ሥራ ባንክ ለበርካታ ቢዝነሶች በሸሪዓው መሠረት በሰጠው ፋይናንስ(ብድር) በእጅጉ ሊመሰገን ይገባል።

2) በቀጣይነት የሚገኘው ደግሞ በሀገሪቱ ደረጃ ካለው አጠቃላይ የወለድ አልባ ባንክ ዘርፍ ተቀማጭ ገንዘብ ዉስጥ ከግማሽ በላይ ማለትም 53.28 % (ሀምሳ ሦስት ነጥብ ሁለት ስምንት) ያክሉን ድርሻ የሚይዘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሲሆን ያበደረው ግን በተቀማጭ ገንዘብ መጠኑ ከአራት እጥፍ ከሚያንሰው ከኦሮሚያ ሕብረት ባንክ መጠን በ11.71% (አስራ አንድ ነጥብ ሰባት አንድ በመቶ) ያነሰ ማለትም በሀገር ደረጃ ከተሰጠው አጠቃላይ ፋይናንስ ዉስጥ 24̀.2%(ሀያ አራት ነጥብ ሁለት) ያክል ብቻ ነው።
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአጠቃላይ ካለው 52,039,110,704 (ሀምሳ ሁለት ቢሊዮን ሰላሳ ዘጠኝ ሚሊዮን አንድ መቶ አስር ሺህ ሰባት መቶ አራት)ብር ዉስጥ እንዲያበድር በሕግ የሚፈቀድለት 41,631,288,563.2 (አርባ አንድ ቢሊዮን ስድስት መቶ ሠላሳ አንድ ሚሊዮን ሁለት መቶ ሰማንያ ስምነት ሺህ አምስት መቶ ስልሳ ሦስት ብር ከሃያ ሳንቲም) ያክል ብቻ ነው።

ከዚህ ዉስጥ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በብድር የሰጠው 6,261,216,099.20 (ስድስት ቢሊዮን ሁለት መቶ ስልሳ አንድ ሚሊዮን ሁለት መቶ አስራ ስድስት ሺህ ዘጠና ዘጠኝ ብር ከሃያ ሳንቲም) ያክሉን ነው፤

ይህ ማለት ፋይናንስ ማድረግ ከሚፈቀድለት ገንዘብ ዉስጥ 15.04%(አስራ አምስት ነጥብ ዜሮ አራት በመቶ) ያክሉን አበድሯል።በሌላ አነጋገር ከአጠቃላይ ተቀማጭ ገንዘብ ዉስጥ 80% ማበደር ሲፈቀድለት እርሱ ግን ያበደረው 12%% ያክሉን አበድሮ ሳያበድር የቀረው 68% መጠን ነው ማለት ነው፤

3) በ3ኛ ደረጃ ላይ የሀገሪቱን አጠቃላይ 13.69%(አስራ ሦስት ነጥብ ስድስት ዘጠኝ በመቶ) በመያዝ ኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ(አሁን ኦሮሚያ ባንክ በሚል ስያሜውን ቀይሯል) ይገኛል።ኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ በአጠቃላይ ካለው 4,879,909,490 (አራት ቢሊዮን ስምንት መቶ ሰባ ዘጠኝ ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ዘጠኝ ሺህ አራት መቶ ዘጠና) ብር ዉስጥ እንዲያበድር በሕግ የሚፈቀድለት 3,903,927,592(ሦስት ቢሊዮን ዘጠኝ መቶ ሦስት ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ሃያ ሰባት ሺህ አምስት መቶ ዘጠና ሁለት) ብር ያክል ብቻ ነው።

ከዚህ ዉስጥ ኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ በብድር የሰጠው 3,542,349,948.43(ሦስት ቢሊዮን አምስት መቶ አርባ ሁለት ሚሊዮን ሦስት መቶ አርባ ዘጠኝ ሺህ ዘጠኝ መቶ አርባ ስምንት ብር ከአርባ ሦስት ሳንቲም) ያክሉን ነው፤ይህ ማለት ፋይናንስ ማድረግ ከሚፈቀድለት ገንዘብ ዉስጥ 90.74%(ዘጠና ነጥብ ሰባት አራት በመቶ) ያክሉን አበድሯል።በሌላ አነጋገር ከአጠቃላይ ተቀማጭ ገንዘብ ዉስጥ 80% ማበደር ሲፈቀድለት እርሱ ግን ያበደረው 73%%% ያክሉን አበድሮ ሳያበድር የቀረው 7%(ሰባት በመቶ) መጠን ብቻ ነው ማለት ነው።

4) ከሀገሪቱ በወለድ ነጻ ዘርፍ ከተሰጠው ፋይናንስ ዉስጥ 8.46% ድርሻ በመያዝ በ4ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ዳሸን ባንክ ነው። ዳሸን ባንክ በአጠቃላይ ካለው 4,608,841,903 (አራት ቢሊዮን ስድስት መቶ ስምንት ሚሊዮን ስምንት መቶ አርባ አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ሦስት) ብር ዉስጥ እንዲያበድር በሕግ የሚፈቀድለት 3,687,073,522.4 (ሦስት ቢሊዮን ስድስት ሰማኒያ ሰባት መቶ ሦስት ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ሃያ ሰባት ሺህ አምስት መቶ ዘጠና ሁለት) ብር ያክል ብቻ ነው።

ከዚህ ዉስጥ ዳሸን ባንክ በብድር የሰጠው 2,190,291,997.47 (ሁለት ቢሊዮን አንድ መቶ ዘጠና ሚሊዮን ሁለት መቶ ዘጠና አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ዘጠና ሰባት ብር ከአርባ ሳንቲም) ያክሉን ነው፤ይህ ማለት ፋይናንስ ማድረግ ከሚፈቀድለት ገንዘብ ዉስጥ 59.4%(ሀምሳ ዘጠኝ ነጥብ አራት አራት በመቶ) ያክሉን አበድሯል።በሌላ አነጋገር ከአጠቃላይ ተቀማጭ ገንዘብ ዉስጥ 80% ማበደር ሲፈቀድለት እርሱ ግን ያበደረው 48% ያክሉን አበድሮ ሳያበድር የቀረው 32%(ሰላሳ ሁለት በመቶ) መጠን ነው ማለት ነው።

5) በሀገር ደረጃ 8.21% ድርሻ በመያዝ 5ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው አዋሽ ባንክ ነው።አዋሽ ባንክ በአጠቃላይ ካለው 7,510,232,463 (ሰባት ቢሊዮን አምስት መቶ አስር ሚሊዮን ሁለት መቶ ሰላሳ ሁለት ሺህ አራት መቶ ስልሳ ሦስት) ብር ዉስጥ እንዲያበድር በሕግ የሚፈቀድለት 6,008,185,970.4(ስድስት ቢሊዮን ስምንት ሚሊዮን አንድ መቶ ሰማንያ አምስት ሺህ ዘጠኝ መቶ ሰባቶ ብር ከአርባ ሳንቲም) ብር ያክል ብቻ ነው።

ከዚህ ዉስጥ አዋሽ ባንክ በብድር የሰጠው 2,123,779,822.54 (ሁለት ቢሊዮን አንድ መቶ ሃያ ሦስት ሚሊዮን ሰባት መቶ ሰባ ዘጠኝ ሺህ ሰምንት መቶ ሃያ ሁለት ብር ከሀምሳ አራት ሳንቲም) ያክሉን ነው፤ይህ ማለት ፋይናንስ ማድረግ ከሚፈቀድለት ገንዘብ ዉስጥ 35.35%(ሰላሳ አምስት ነጥብ ሰላሳ አምስት በመቶ) ያክሉን አበድሯል።በሌላ አነጋገር ከአጠቃላይ ተቀማጭ ገንዘብ ዉስጥ 80% ማበደር ሲፈቀድለት እርሱ ግን ያበደረው 28% ያክሉን ሲሆን ሳያበድር የቀረው 52%(ሀምሳ ሁለት በመቶ) መጠን ያክል ነው ማለት ነው።

6) በ3.66% ሀገራዊ ድርሻ በ6ኛ ደረጃ ላይ አቢሲኒያ ባንክ ይገኛል።አቢሲኒያ ባንክ በአጠቃላይ ካለው 8,306,077,368 (ሰምንት ቢሊዮን ሦስት መቶ ስድስት ሚሊዮን ሰባ ሰባት ሺህ ሦስት መቶ ስልሳ ስምንት) ብር ዉስጥ እንዲያበድር በሕግ የሚፈቀድለት 6,644,861,894.4 (ስድስት ቢሊዮን ስድስት መቶ አርባ አራት ሚሊዮን ስምንት መቶ ስልሳ አንድ ሺህ ስምንት መቶ ዘጠና አራት ብር ከአርባ ሳንቲ፥እ) ብር ያክል ብቻ ነው።

ከዚህ ዉስጥ አቢሲኒያ ባንክ በብድር የሰጠው 945,995,707.74 (ዘጠኝ መቶ አርባ አምስት ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ዘጠኛ አምስት ሺህ ሰባት መቶ ሰባት ብር ከሰባ አራት ሳንቲም) ያክሉን ነው፤ይህ ማለት ፋይናንስ ማድረግ ከሚፈቀድለት ገንዘብ ዉስጥ 14.24%(አስራ አራት ነጥብ ሁለት አራት በመቶ) ያክሉን ብቻ አበድሯል።

ይህ ማለት ሳያበድር የያዘው 5,698,866,186.66(አምስት ቢሊዮን ስድስት መቶ ዘጠና ስምንት ሚሊዮን ስምንት መቶ ሰልሳ ስድስት ሺህ አንድ መቶ ሰማንያ ስድስት ብር ከስልሳ ሳንቲም) አለው ማለት ነው።በሌላ አነጋገር ከአጠቃላይ ተቀማጭ ገንዘብ ዉስጥ 80% ማበደር ሲፈቀድለት እርሱ ግን ያበደረው 11% ያክሉን ሲሆን ሳያበድር የቀረው 69%(ስልሳ ዘጠኝ በመቶ) መጠን ያክል ነው ማለት ነው።

7) በሀገር ዓቀፍ ወለድ አልባ ፋይናንስ በመስጠት ደረጃ በ3.18% ድርሻ ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ 7ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ በአጠቃላይ ካለው 3,056,420,485 (ሦስት ቢሊዮን ሀምሳ ስድስት ሚሊዮን አራት መቶ ሃያ ሺህ አራት መቶ ሰማንያ አምስት) ብር ዉስጥ እንዲያበድር በሕግ የሚፈቀድለት 2,445,136,388 (ሁለት ቢሊዮን አራት መቶ አርባ አምስት ሚሊዮን አንድ መቶ ሰላሳ ስድስት ሺህ) ብር ያክል ብቻ ነው።ከዚህ ዉስጥ ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ በብድር የሰጠው 823,806,749.29 (ስምንት መቶ ሃያ ሦስት ሚሊዮን ስምንት መቶ ስድስት ሺህ ሰባት መቶ አርባ ዘጠኝ ብር ከሃያ ዘጠኝ ሳንቲም) ያክሉን ነው፤ይህ ማለት ፋይናንስ ማድረግ ከሚፈቀድለት ገንዘብ ዉስጥ 33.69%(ሰላሳ ሦስት ነጥብ ስድስት ሰባት በመቶ) ያክሉን ብቻ አበድሯል።

በሌላ አነጋገር ከአጠቃላይ ተቀማጭ ገንዘብ ዉስጥ 80% ማበደር ሲፈቀድለት እርሱ ግን ያበደረው 27% ያክሉን ሲሆን ሳያበድር የቀረው 53%(ሀምሳ ሦስት በመቶ) መጠን ያክል ነው ማለት ነው።

8) በ8ኛ ደረጃ ላይ በ3.10% ሀገራዊ የወለድ አልባ ፋይናንሲንግ ድርሻ ሕብረት ባንክ
ይገኛል።ሕብረት ባንክ በአጠቃላይ ካለው 1,847,561,771 (አንድ ቢሊዮን ስምንት መቶ አርባ ሰባት አምስት መቶ ስልሳ አንድ ሺህ ሰባት መቶ ሰባ አንድ) ብር ዉስጥ እንዲያበድር በሕግ የሚፈቀድለት 1,478,049,416.8 (አንድ ቢሊዮን አራት መቶ ሰባ ስምንት ሚሊዮን አርባ ዘጠኝ ሺህ አራት መቶ አስራ ስድስት ብር ከሰማንያ ሳንቲም) ብር ያክል ብቻ ነው።

ከዚህ ዉስጥ ሕብረት ባንክ በብድር የሰጠው 803,191,681.33(ስምንት መቶ ሦስት ሚሊዮን አንድ መቶ ዘጠና አንድ ሺህ ስድስት መቶ ሰማንያ አንድ ብር ከሳላሳ ሦስት ሳንቲም) ያክሉን ነው፤ይህ ማለት ፋይናንስ ማድረግ ከሚፈቀድለት ገንዘብ ዉስጥ 54.34%(ሀምሳ አራት ነጥብ ሦስት አራት በመቶ) ያክሉን አበድሯል። በሌላ አነጋገር ከአጠቃላይ ተቀማጭ ገንዘብ ዉስጥ 80% ማበደር ሲፈቀድለት እርሱ ግን ያበደረው 43% ያክሉን ሲሆን ሳያበድር የቀረው 37%(ሰላሳ ሰባት በመቶ) መጠን ያክል ነው ማለት ነው።

9) 9ኛ ደረጃ ላይ በ2.08% መጠን ሀገራዊ ድርሻ አባይ ባንክ ይገኛል።አባይ ባንክ በአጠቃላይ ካለው 1,277,435,441 (አንድ ቢሊዮን ሁለት መቶ ሰባ ሰባት ሚሊዮን አራት መቶ ሰላሣ አምስት ሺህ አራት መቶ አርባ አንድ) ብር ዉስጥ እንዲያበድር በሕግ የሚፈቀድለት 1,021,948,352.8 (አንድ ቢሊዮን ሃያ አንድ ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ አርባ ስምንት ሺህ ሦስት መቶ ሀምሳ ሁለት ብር ከሰማንያ ሳንቲም) ብር ያክል ብቻ ነው።

ከዚህ ዉስጥ አባይ ባንክ በብድር የሰጠው 537,573,724.00(አምስት መቶ ሰላሳ ሰባት ሚሊዮን አምስት መቶ ሰባ ሦስት ሺህ ሰባት መቶ ሃያ አራት በመቶ) ያክሉን ነው፤ይህ ማለት ፋይናንስ ማድረግ ከሚፈቀድለት ገንዘብ ዉስጥ 52.60%(ሀምሳ ሁለት ነጥብ ስድስት በመቶ) ያክሉን አበድሯል። በሌላ አነጋገር ከአጠቃላይ ተቀማጭ ገንዘብ ዉስጥ 80% ማበደር ሲፈቀድለት እርሱ ግን ያበደረው 42% ያክሉን ሲሆን ሳያበድር የቀረው 38%(ሰላሳ ስምንት በመቶ) መጠን ያክል ነው ማለት ነው።

10) 1.38% ሐገራዊ የወለድ አልባ ብድር መስጠት ድርሻ በመያዝ ወጋገን ባንክ በ10ኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።ወጋገን ባንክ በአጠቃላይ ካለው 1,536,191,534 (አንድ ቢሊዮን አምስት መቶ ሰላሳ ስድስት ሚሊዮን አንድ መቶ ዘጠና አንድ ሺህ አምስት መቶ ሰላሳ አራት) ብር ዉስጥ እንዲያበድር በሕግ የሚፈቀድለት 1,228,953,227.2(አንድ ቢሊዮን ሁለት መቶ ሃያ ስምንት ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ሀምሳ ሦስት ሺህ ሁለት መቶ ሃያ ሰባት ብር ከሃያ ሳንቲም)ብር ያክል ብቻ ነው።ከዚህ ዉስጥ ወጋገን ባንክ በብድር የሰጠው 356,346,626.03 (ሦስት መቶ ሀምሳ ስድስት ሚሊዮን ሦስት መቶ አርባ ስድስት ሺህ ስድስት መቶ ሃያ ስድስት ብር ከሦስት ሳንቲም) ያክሉን ነው፤ይህ ማለት ፋይናንስ ማድረግ ከሚፈቀድለት ገንዘብ ዉስጥ 29%(ሃያ ዘጠኝ በመቶ) ያክሉን አበድሯል። በሌላ አነጋገር ከአጠቃላይ ተቀማጭ ገንዘብ ዉስጥ 80% ማበደር ሲፈቀድለት እርሱ ግን ያበደረው የተቀማጩን 23% ያክሉን ሲሆን ሳያበድር የቀረው 57%(ሰላሳ ስምንት በመቶ) መጠን ያክል ነው ማለት ነው።

11) ብድር ባለመጀመር ወይም በ0% መጠን ቡና ባንክ በመጨረሻ ደረጃ ላይ ይገኛል።ቡና ባንክ በአጠቃላይ ካለው 624,000,000 (ስድስት መቶ ሃያ አራት ሚሊዮን ብር) ብር ዉስጥ እንዲያበድር በሕግ የሚፈቀድለት 499,200,000 (አራት መቶ ዘጠና ዘጠኝ ሚሊዮን ሁለት መቶ ሺህ) ብር ያክል ብቻ ነው።ከዚህ ዉስጥ ቡና ባንክ እስከ ጁን 30 ቀን 2021 ድረስ የሰጠው ብድር የለም ወይም ዜሮ ነው ማለት ነው።ስለዚህ ሳይሰጥ የያዘው ሙሉውን 499,200,000 (አራት መቶ ዘጠና ዘጠኝ ሚሊዮን ሁለት መቶ ሺህ) ብር ያክሉን ነው፤ይህ ማለት ፋይናንስ ማድረግ ከሚፈቀድለት ገንዘብ ዉስጥ ምንም አላበደረም ማለት ነው።

በአምናው የብሄራዊ ባንክ ሪፖርት መሠረት ከሀገራችን ባንኮች መካከል ወለድ አልባ ዘርፍን ከተቀላቀሉት መካከል ከሰበሰቡት የተቀማጭ ገንዘብ ዉስጥ የተቀማጫቸውን ስንት በመቶ በወለድ አልባ ዘርፍ ገንዘቡን መልሰው ለደንበኞች አበደሩ የሚለው ደረጃቸው ከላይ ያየነውን ይመስላል፤ ካላቸው ተቀማጭ ገንዘብ ዉስጥ በማበደር ደንበኞች ቢዝነሳቸውን እንዲያሳድጉ የፋይናንስ በማድረግ ባንኮቹ ያላቸው ደረጃ ቅደም ተከተል ሲጠቃለል የሚከተለው ነው።

1ኛ-የኦሮሚያ ሕብረት ሥራ ባንክ፥
2ኛ፡-ኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ፥
3ኛ-ዳሸን ባንክ፥
4ኛ-ሕብረት ባንክ
፥5ኛ-አባይ ባንክ፥
6ኛ-አዋሽ ባንክ፥
7ኛ-ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ
፥8ኛ-ወጋገን ባንክ፥
9ኛ-የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
፥10ኛ-አቢሲኒያ ባንክ፥
11ኛ-ቡና ባንክ ላይ ይገኛሉ።

ይቀጥላል…

የኢትዮጵያ ባንኮችና የሐጅ ዶላር ፍለጋ ፈተናክፍል አንድ💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥የኢትዮጵያ መገበያያ የሆነው «ብር» ከኢትዮጵያ ዉጭ ለመገበያያነት ተቀባይነት ስለሌለው በዉጭ ሀገር ለሚደረግ ...
25/06/2022

የኢትዮጵያ ባንኮችና የሐጅ ዶላር ፍለጋ ፈተና
ክፍል አንድ
💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥💥

የኢትዮጵያ መገበያያ የሆነው «ብር» ከኢትዮጵያ ዉጭ ለመገበያያነት ተቀባይነት ስለሌለው በዉጭ ሀገር ለሚደረግ ግብይት እንደ ዶላር(ዩሮ፥ፓውንድ፥ወዘተ) ያሉ በዓለም ሀገራት ዘንድ ለመገበያያነት ተቀባይነት ያላቸውን ገንዘቦች ማግኘት ግድ የሚል የዓለም አሰራር ሆኗል።በመሆኑም ለሐጅ ተግባር ለሚያስፈልጉ ክፍያዎችም (መኖሪያ፥ትራንስፖርት፥ ሂደቶች፥ ወዘተ) እንደ መጅሊስ በዓመቱ አስፈላጊውን ዶላር ማግኘት ግዴታው ሆኗል፡፡ ከዚህ የተነሳ በየዓመቱ የሐጅ ኮሚቴ ዶላር ፍለጋ የሀገራችንን ባንኮችን ደጃፍ ይጠናል። ይማጸናል።

እንደየሀገራቱ የህዝበ ሙስሊሙ ቁጥር ብዛት የሐጅ ተሳታፊዎች ኮታ ለየሀገራቱ የሚሰጥ ሲሆን መደበኛው የኢትዮጵያ ኮታ 43ሺህ ነው።ሆኖም ዘንድሮ በኮቪድ ችግር ምክንያት አጠቃላይ የሐጅ ተሳታፊዎች ብዛት እንዲቀንስ በመደረጉ የኢትዮጵያ ኮታም ከ43ሺህ ወደ 19ሺህ ዝቅ ተደርጓል። ሆኖም ባለው የመጅሊስ የማስፈጸም አቅም ዉስንነትና የዶላር ችግር ምክንያት እስከ ዛሬ በዓመት ለሐጅ የሚጓዙ ኢትዮጵያውያን ቁጥር ከ15ሺህ አልፎ አያውቅም። ብዙ ጊዜም የተጓዦች ብዛት ከ11-13ሺህ መካከል ይሆናል።

ዘንድሮ የተሰጠው ኮታ 19ሺህ ቢሆንም ካለው ችግር አንጻር መጅሊስ 12ሺህ ያክል ተጓዦችን መዝግቦ ከዚህ በላይ አልችልም በማለት አቁሟል። ዋናው የሐጅ ተግባር ሊጀመርም ከሁለት ሳምንት ያነሰ ጊዜ ብቻ በመቅረቱ በርካታ ሀገራት ተጓዦቻቸውን ወደ ሳውዲ ዐረቢያ አጓጉዘው እያጠናቀቁ ይገኛሉ።የኛ ሀገር ደግሞ በመጅሊስ ችግሮችና ባለው ሀገራዊ የሰላም እጦት ችግሮች ተገቢውን ትኩረት ሳያገኝ ዜጎች እየተንገላቱ ይገኛሉ። ይህን ምክንያት በማድረግ ስለጉዳዩ ከባንክ ጋር በተለይም ከወለድ አልባ ባንክ ዘርፍ ጋር በማያያዝ ለመዳሰስ እሞክራለሁ።

ኢትዮጵያውያን ሐጅ አድራጊዎች ለዘንድሮ ሐጅ በነፍስ ለየክልሎቹ የከፈሉትን ገንዘብ(6,500 ብር) ትተን ለፌደራል መጅሊስ የሐጅ አካውንት ብቻ እያንዳንዱ ሰው 242,000 (ሁለት መቶ አርባ ሁለት ሺህ) ብር በባንኮች ገቢ አድርገዋል። በጠቅላላው ክፍያውን ከፍሎ ፕሮሰስ ያጠናቀቀው ተመዝጋቢ 12,000(አሥራ ሁለት ሺህ) በመሆኑ ባንኮቹ በድምሩ ከሁሉም ሑጃጆች በድምሩ 2 ነጥብ ዘጠኝ ቢሊዮን (2,904,0000,000) ብር ተቀብለዋል።

ባለኝ መረጃ መሠረት ለሐጅ ማስፈጸሚያ ከተጠየቀው 36 ሚሊዮን ዶላር ዉስጥ እስካሁን ለሦስት ሺህ ሰው ብቻ የሚሆን ዘጠኝ ሚሊዮን ዶላር ብቻ ነው ከባንኮች የተገኘው። ከተመዝጋቢዎቹ 75%(ሰባ አምስት በመቶ) የሚሆኑት ጉዳያቸውን ቢጨርሱም በዶላር እጥረት ምክንያት እንደማይሄዱ እየተነገራቸው ነው።አብዛኞቹ የሐጅ ተጓዦች ሐጅን በሕይወት ዘመናቸው አንድ ጊዜ ለማድረግ ዓመታት ገንዘብ አጠራቅመውና ያላቸውን ንብረት ሽጠው ጭምር የሐጅ ጉዳያቸውን ለማስጨረስ ከየክልሉ መጥተው ከአንድ ወር በላይ በአዲስ አበባ ከቆዩ በኋላ የሚበሩበትን ቀን እየተጠባበቁ ሳለ ይህን በመስማታቸው በሐዘንና በንዴት ተቃውሞዋቸውን እያሰሙ ይገኛሉ።

ባለው ነባራዊ ሁኔታ እንደ ሀገር የዶላር እጥረት መፈጠሩ እርግጥ ነው።ሆኖም አብዛኞቹ ባንኮች በሌላም ጊዜ ቢሆን ካላቸው የዶላር ክምችት በዓመት አንዴ ለሚጠየቁት የሐጅ ሂደት ተገቢውን ዶላር ያለጫናና ደጅ መጥናት የሚጠበቅባቸወን ያክል ዶላር እየሰጡ ነበር ወይ? የሚለው ጉዳይ እጅግ አጠያያቂ ነው። በተለይም ደግሞ በኮሮና ምክንያት ለሁለት ዓመታት ተቋርጦ ዘንድሮ የተጀመረ በመሆኑ ላለፉት ሁለት ዓመታት ዶላር አልተጠየቁም።አልሰጡምም።

ይህን የምለው ባንኮቹ ወለድ ሳይከፍሉበት ደንበኞች ገንዘባቸውን በባንካቸው እንዲያስቀምጡ ለማድረግ «በሸሪዓው መሠረት» በሚል ማስታወቂያዎች በትኩረት የሚሰሩት ባንኮች ሐጅ ለማድረግ ሲሉ ገንዘባቸውን ለዓመታት በባንኮቹ ላጠራቀሙት የባንኮቹ ደንበኞች በሕይወት ዘመን አንዴ ለሚያደርጉት ሐጅ በዓመት አንዴ ለሑጃጆች የሚሆን ዶላር በመጅሊስ አማካኝነት ሲጠየቁ ጥያቄው ለባንካቹ ተጠቃሚ ደንበኞቻቸው መሆኑ እየታወቀ ወገቤን የሚሉትና የሚያንገራግሩት ነገር የጤንነት አይመስለኝም።ይህን እያልኩ ያለሁት ያለምክንያት አይደለም።ምክንያቶቼን ደግሞ ቀጥሎ እንደሚከተለው በዝርዝር አብራራለሁ።

የትኞቹ ባንኮች በወለድ አልባው ዘርፍ ስንት ብር ሰበሰቡ?
💰💰💰💰💰💰💰💰💰💰💰💰💰💰💰💰

የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ በየዓመቱ በጁን 30 የባንኮችን አጠቃላይ እንቅስቃሴን አስመልክቶ ሪፖርት ያወጣል። የወለድ ነጻ ባንክ ዘርፍ ከሀገራችን የባንክ ኢንደስትሪ ዘርፍ ዉስጥ አዲስ በመሆኑ እስከ አምና ሰኔ ወር ድረስ የነበረውን ድርሻ ካየን ገና ሰባት በመቶ(7%) ብቻ ነው።ማለትም ከአንድ ነጥብ አራት ትሪሊዮን የሀገሪቱ አጠቃላይ ተቀማጭ ገንዘብ ዉስጥ 97 ቢሊዮን ብቻ ነው።ይህ ማለት በመደበኛ የባንክ ዘርፍ ገንዘባቸውን ካስቀመጡት መካከል ሙስሊሞች እንደዚሁም በወለድ አልባ ካስቀመጡት መካከል ሙስሊም ያልሆኑ ወገኖች የሉበትም ማለት ባይሆንም በወለድ ነጻ ባንክ ከዘርፉ አዲስነት አንጻር ሙስሊም ያልሆኑት እጅግ ጥቂት ወይም ከነአካቴው የሉበትም ብሎ መውሰድ ይቻላል።የዘንድሮ ዓመታዊ ሪፖርት ከጥቂት ቀናት በኋላ ይወጣል ተብሎ ይጠበቃል።

በጁን 30 ቀን 2021 የወጣው ሪፖርት እንደሚገልጸው እስከዚያን ጊዜ ድረስ ከወለድ ነጻ በሆነ መንገድ ማለትም በሸሪዓው መሠረት በሁሉም የወለድ ነጻ ባንክን በጀመሩ የሀገራችን ባንኮች ዉስጥ ተቀምጦ የነበረው አጠቃላይ ተቀማጭ ገንዘብ ድምር ዘጠና ሰባት ቢሊዮን ስድስት መቶ ስልሳ አራት ሚሊዮን አራት መቶ ስምንት ሺህ ስምንት መቶ ሀምሳ ብር(97,664,408,850) ያክል ነበር። ከዚህ ዉስጥ ማበደር የሚፈቀድላቸው መጠን ማለትም የተቀማጩን ገንዘብ 80%(ሰማንያ በመቶ) ማለትም 78,131,527,080 ያክል ብቻ ነው።

ሙስሊሞች ወለድ ቢቀበሉ ኖሮ በዚህ ገንዘብ ላይ ባንኮቹ በዓመት ይከፍሉት የነበረውን ዝቅተኛውን የ7%(ሰባት በመቶ) ወለድን መጠንን ስናሰላው መጠኑ 5,469,206,895.6 (አምስት ቢሊዮን አራት መቶ ስልሳ ዘጠኝ ሚሊዮን ሁለት መቶ ስድስት ሺህ ስምንት መቶ ዘጠና አምስት ብር ከስልሳ ሳንቲም) ብር ያክል ይሆናል። ይህን ገንዘብ ደግሞ ወደ ዶላር ለመለወጥ በጊዜው ማለትም በጁን 30 ቀን 2021 በነበረው የባንኮች የዶላር ምንዛሬ ዋጋ የአንድ ዶላር 43.8753 ብር ያክል ስናካፍለው 124,653,435 (አንድ መቶ ሀያ አራት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሀምሳ ሦስት ሺህ አራት መቶ ሠላሳ አምስት) ዶላር ያክል ይሆናል ማለት ነው። ነገር ግን ወለድ በኢስላም ክልክል ስለሆነ ሙስሊሞች ባንኮችን ወለድን አይጠይቁም።ይህ ማለት ባንኮቹ ወለድ የማይከፍሉባቸውና በነጻ ያገኙት ገንዘብ ሆነላቸው ማለት ነው።ባንኮቹ በተቀማጭነት እነርሱ ጋር ያሉትን የሙስሊሞችን ገንዘብ ለሌሎች ደንበኞቻቸው አበድረው በየዓመቱ ከፍተኛ ቢሊዮን ብሮችን ትርፍ እያገኙ ነው።

ዓምና የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ ባወጣው ሪፖርት ላይ ከሀገራችን ባንኮች መካከል የወለድ ነጻ ባንክ ዘርፍን በመስኮትና ሙሉ ለሙሉ ወለድ ነጻ ባንክ የሆኑ 14 ባንኮችን በሰም ጠቅሶ ሪፖርቱ ላይ አካቷቸዋል።እያንዳንዱ ባንክ በወለድ ነጻ ባንክ ዘርፍ የሰበሰቡትን የተቀማጭ ገንዘብን መጠንም እንደሚከተለው ነው።

⑴ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ:-(ሀምሳ ሁለት ቢለዮን ሰላሳ ዘጠኝ ሚሊዮን አንድ መቶ አስር ሺህ ሰባት መቶ አራት ብር (52,039,110,704) ፥

⑵ የኦሮሚያ ሕብረት ሥራ ባንክ፦አስራ አንድ ቢሊዮን ዘጠኝ መቶ ሰባ ስምንት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሀያ ሰባት ሺህ ስድስት መቶ ዘጠና አንድ ብር (11,978,627,691) ፥

⑶ አቢሲኒያ ባንክ፦ ሰምንት ቢሊዮን ሦስት መቶ ስድስት ሚሊዮን ሰባ ሰባት ሺህ ሦስት መቶ ስልሳ ስምንት ብር(8,306,077,368)፥

⑷ አዋሽ ባንክ፦ሰባት ቢሊዮን አምስት መቶ አስር ሚሊዮን ሁለት መቶ ሰላሳ ሁለት ሺህ አራት መቶ ስልሳ ሦስት(7,510,232,463)፥

⑸ ኦሮሚያ ኢንተርናሽናል ባንክ(አሁን ኦሮሚያ ባንክ ተብሏል)፦ አራት ቢሊዮን ስምንት መቶ ሰባ ዘጠኝ ሚሊዮን ዘጠኝ መቶ ዘጠኝ ሺህ አራት መቶ ዘጠና ብር (4,879,909,490)፥

⑹ ዳሸን ባንክ፦ አራት ቢሊዮን ስድስት መቶ ስምንት ሚሊዮን ስምንት መቶ አርባ አንድ ሺህ ዘጠኝ መቶ ሦስት ብር (4,608,841,903) ፥

⑺ ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ፦ ሦስት ቢሊዮን ሀምሳ ስድስት ሚሊዮን አራት መቶ ሀያ ሺህ አራት መቶ ሰማንያ አምስት ብር(3,056,420,485)፥

⑻ ሕብረት ባንክ፦ አንድ ቢሊዮን ስምንት መቶ አርባ ሰባት ሚሊዮን አምስት መቶ ስልሳ አንድ ሺህ ሰባት መቶ ሰባ ሰባት ብር (1,847,561,771) ፥

⑼ ወጋገን ባንክ፦ አንድ ቢሊዮን አምስት መቶ ሠላሳ ስድስት ሚሊዮን አንድ መቶ ዘጠና አንድ ሺህ አምስት መቶ ሠላሳ አራት ብር (1,536,191,534)፥

⑽ አባይ ባንክ፦አንድ ቢሊዮን ሁለት መቶ ሰባ ሰባት ሚሊዮን አራት መቶ ሠላሳ አምስት ሺህ አራት መቶ አርባ አንድ ብር(1,277,435,441) ፥

⑾ ቡና ባንክ፦ ስድስት መቶ ሀያ አራት ሚሊዮን ብር(624,000,000)፥

ሒጅራና ዘምዘም ባንክ ሪፖርቱ በወጣበት ጊዜ ሥራ ያልጀመሩ ስለነበር የነርሱ አልተካተተም።ለተጨማሪ ዝርዘር ከዚህ ጽሑፍ ጋር የተያያዘውን ሰንጠረዥ አንድን ይመልከቱ።

"ብር ለማስቀመጥ ወደኛ ኑ
ለሐጅ ዶላር ከሆነ ግን አትምጡብን!"
💵 💵💵💵💵💵💵💵💵💵💵

የአምናው ሪፖርት እንደሚጠቅሰው በሀገራችን በወለድ ነጻ የባንክ ዘርፍ የባንክ ሒሳብ በመክፈት ተጠቃሚ የሆኑ የባንክ ደንበኞች ቁጥር ከዘጠኝ ሚሊዮን አልፏል።በደንበኞች ብዛት ረገድ ከአራት ሚሊዮን በላይ ደንበኞች በመያዝ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሲመራ የኦሮሚያ ሕብረት ሥራ ባንክ ደግሞ አንድ ነጥብ ስምንት ሚሊዮን ደንበኞችን በመያዝ በሁለተኛነት ይከተላል።አምና ሪፖርቱ በወጣበት ጊዜ ሥራ ስላልጀመሩ ሙሉ የወለድ ነጻ አገልግሎት ለመስጠት የተቋቋሙት ሒጅራና ዘምዘም በሪፖርቱ ላይ አልተካተቱም። ሆኖም እኔ በግል ባለኝ መረጃ መሠረት እስከዚህ ሰኔ 14 ቀን 2014(ጁን 21 ቀን 2022) እለት ድረስ በመላ ሀገሪቱ የባንክ አካውንት እነርሱ ጋር የከፈቱ ደንበኛች ቁጥር እጅግ በጣም ዝቅተኛ ነው።

በማርች 2022 በተሰበሰበ ይፋዊ ባልሆነ ሪፖርት ላይ እንደተጠቀሰው የወለድ አልባ ባንክ ደንበኞች ብዛት ከአምናው በሁለት ሚሊዮን በላይ ጨምሮ አስራ አንድ ሚሊዮን ተኩል ደርሷል።የተቀማጭ ገንዘቡ መጠንም 121 ቢሊዮን ደርሷል፤

ከ11.5 ሚሊዮን ተኩል ካለፈው የወለድ አልባ ባንክ ዘርፍ ደንበኞች መካከል በመላ ሀገሪቱ ወደ ሒጅራ ባንክ በመሄድ ባንኩ ከተከፈተበት አንስቶ እስከ ሰኔ 14 ቀን 2014(ጁን 21 ቀን 2022) ድረስ የባንክ ሒሳብ ያወጡት ደንበኞች ቁጥር በጠቅላላ 133,000 (አንድ መቶ ሠላሳ ሦስት ሺህ) ብቻ ሲሆን የዘምዘም ባንክ ደግሞ ሺህ 74,000 (ሰባ አራት) ብቻ ነው።ይህ ማለት ከአጠቃላይ የወለድ አልባ ባንክ ተጠቃሚዎች መካከል ሒጅራ አንድ በመቶ ገደማ ድርሻ ሲወስድ ዘምዘም ደግሞ ዜሮ ነጥብ ሰባት የተጠጋ ነው።

በተቀማጭ ገንዘብ ደግሞ ሁለቱም ባንኮች በመጋቢት 2014 ላይ 121,000,000,000(አንድ መቶ ሃያ አንድ ቢሊዮን) ካለፈው ጠቅላላ የሀገሪቱ ወለድ አልባ ባንክ ተቀማጭ ዉስጥ ዘምዘም ባንክ ከሒጅራ በጥቂቱ ቢበልጥም ሁለቱም ግን ያላቸው ተቀማጭ ገንዘብ ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ አልፏል።ዘምዘምም ሆነ ሒጅራ ባንክ ከሀገሪቱ የወለድ ነጻ ተቀማጭ ገንዘብም ዉስጥ እያንዳንዳቸው ያላቸው ድርሻ አንድ በመቶ ገደማ ብቻ ነው።ይህ ማለት 98% የወለድ አልባ ባንክ ተቀማጭ ገንዘብ ከዘምዘምና ሒጅራ ባንክ ዉጭ ባሉ መደበኛ ባንኮች ዘንድ ነው ማለት ነው።ከዚህ የተነሳ ሌሎች ባንኮች በሐጅ ዶላር ጉዳይ ያላቸውን አፈጻጸም መመልከትና መጠየቅ ተገቢ ይሆናል።

ሕዝበ ሙስሊሙን የሚመጥንና ተደማጭ ጠንካራ መጅሊስ ቢኖር ኖሮ የባንኮቹ ደንበኞች ለሆኑ ሑጃጆች (መጀሊስ) አንኳንስ ለሐጅ አገልግሎት ዶላር ሊቸገር ቀርቶ የማስተባበር ሚናውን በመውሰድ ይህ ዘርፍ በትክክል የሕዝበ ሙስሊሙን ጥቅሞች በሚያስከብር መልኩ እንዲንቀሳቀስ በማድረግ ከዚህ ዘርፍ ለሕዝቡም ሆነ ለሀገር የሚጠቅሙ የልማት ሥራዎች ማከናወኛ በጀት ከወለድ ነጻ ባንክ ዘርፍ ማግኘት ይችል ነበር።

ቀደም ብለን ከላይ እንደጠቀስነው ሙስሊሞች ወለድም ሳይቀበሉ፥ ትርፍም ሳይጠይቁ ዝም ብለው «በሸሪዓው መሠረት» ብለው አምና ካስቀመጡት 97 ቢሊዮን ብር በላይ ገንዘብ ብቻ ቢያንስ ባንኮቹ ይከፍሉት የነበረው ወለድ ብቻ ከአምስት ነጥብ አራት ቢሊዮን በላይ ነበር። ይህን ስል ሙስሊሞች ከባንክ ወለድ ይውሰዱ እያልኩኝ አይደለም! ፈጽሞ! ነገር ግን ባንኮቹ ይህን ተቀማጭ ገንዘብ በሸሪዓው መሠረት ለሌሎች ደንበኞች አበድረው ትርፍ ያገኛሉ። በሀላል መንገድም ከተሰጠው በዚህ ብድር ባንኮቹ ከፍተኛ ገቢ ያገኛሉ። ብዙ ሰው ጉዳዩ ገብቶት ስለማይጠይቅ እነርሱ ላስቀመጠው ሰው ከትርፋቸው አያጋሩም። ትርፉን እነርሱ ብቻ ይወስዳሉ ማለት ነው።

ለሐጅ ተግባር የሚያስፈልገውን ዶላር በጋራ አዋጥተው እንዲሸጡ እየተጠየቁ ያሉት እነዚሁ ባንኮች ሙስሊሞች ወለድ ባለመቀበላቸው ምክንያት በአንድ ዓመት አምና ብቻ 5,469,206,895.6(አምስት ቢሊዮን አራት መቶ ስልሳ ዘጠኝ ሚሊዮን ሁለት መቶ ስድስት ሺህ ስምንት መቶ ዘጠና አምስት ብር ከስልሳ ሳንቲም) ብር ያክል አግኝተዋል። ይህን ገንዘብ በዶላር ለማስላት በጊዜው ማለትም በጁን 30 ቀን 2021 በነበረው የባንኮች የአንድ ዶላር ምንዛሬ ዋጋ 43.8753(አርባ ሦስት ብር ከሰማኒያ ሰባት አምስት ሦስት) ብር ያክል ስናካፍለው 124,653,435 (አንድ መቶ ሀያ አራት ሚሊዮን ስድስት መቶ ሀምሳ ሦስት ሺህ አራት መቶ ሠላሳ አምስት) ዶላር ያክል ይሆናል ማለት ነው።

አንድ መቶ ሀያ አራት ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር(124 million USD) ማለትም ለሐጅ በነጻ እንዲሰጡ ሳይሆን አትርፈው እንዲሸጡ ከተጠየቁት 36 ሚሊዮን ዶላር 3.46(ሦስት ነጥብ አራት ስድስት) እጥፍ የሚሆን ዶላር በነጻ አግኝተዋል ማለት ነው። በየዓመቱም ይህንኑ ትርፍ እያገኙ ነው። ሆኖም አምና በነጻ ካገኙት 124 ሚሊዮን ዶላር የሚሆን ገንዘብ ዉስጥ ለሐጅ ተግባር ማስኬጃ 36 ሚሊዮን ዶላር ወይንም 29 %(ሀያ ዘጠኝ በመቶ) ያክሉን እንኳ በነጻ ሳይሆን አትርፋችሁ ሽጡልን ተብለው ሲጠየቁ ከጥቂቶች በቀር አብዛኛዎቹ ባንኮቹ ወገቤን እያሉ ደጅ ያስጠናሉ።

እኔ ባለኝ መረጃ መሠረት ለ2014 ሐጅ ከሁሉም ባንኮች እስካሁን የተገኘው በድምር ዘጠኝ ሚሊዮን ዶላር ብቻ ነው።ከዚህ ዉስጥ የኦሮሚያ ሕብረት ሥራ ባንክ ብቻውን ሁለት ሚሊዮን ዶላር ሲሰጥ ሌሎች የግል ባንኮች ደግሞ በጋራ አዋጥተው ኦሮሚያ ሕብረት ሥራ ባንክ ብቻውን የሰጠውን ያክል ሁለት ሚሊዮን ዶላር ያክል ብቻ ሰጥተዋል። በዚህ ረገድ የኦሮሚያ ሕብረት ሥራ ባንክ ሊመሰገን ይገባል። በአጠቃላይ ወለድ አልባ ባንክ ኢንደስትሪ የሀገሪቱ ተቀማጭ ገንዘብ ዉስጥ 53% (ሀምሳ ሦስት በመቶውን) ድርሻ ያለው እንዲሁም በአሁኑ ሰዓት አምስት ሚሊዮን ገደማ የወለድ ነጻ ባንክ ደንበኞች ያሉት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ደግሞ አምስት ሚሊዮን ዶላር ሰጥቷል።

ከባንኮቹ ትርፍስ ለሙስሊሙ ምን ያክል ይደርሳል?
❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄

የወለድ ነጻ ባንክ ዘርፍ መኖር ለሙስሊሞች ከሚያስገኛቸው ጥቅሞች መካከል ለሰማንያ ዓመታት ተከልክለው በነበሩበት እና አትራፊ በሆነው የሀገራችን የባንክ ኢንደስትሪ ዘርፍ የባንክ ባለቤትበመሆን ከትርፉ መቋደስ እና በወለድ ምክንያት ማግኘት ያልቻሉትን የፋይናንስ አገልግሎት በማግኘት ሥራቸውን ማስፋፋት በዋናነት ሊጠቀሱ የሚችሉ የባንክ ዘርፍ ጥቅሞች መካከል ናቸው።

በባንክ ባለቤትነት ረገድ ካየን በአቅምም ሆነ በትርፍ ከፍተኛውን ድርሻ የያዘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባለቤትነቱ የመንግስት በመሆኑ ባለአክሲዮን የሆኑ ባለቤቶች የሉትም።በቅርቡ ሙሉ ለሙሉ የወለድ ነጻ ባንክ በመሆን ወደ ኢንደስትሪው የተቀላቀሉት ሒጅራና ዘምዘም ባንክን ሳይጨምር ሌሎች የግል ባንኮች ደግሞ ከጅምሩ ሲቋቋሙ ወለድን መሠረት አድርገው በመሆኑ ወለድን የሚጠነቀቁ ሙስሊሞች ያን ያክል በባለቤትነት/በባለ አክሲዮንነት/ አብረው ተሳትፈዋል ማለት አይቻልም። ይህ ማለት ባንኮች በየዓመቱ ከሚያተርፉት በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ዉስጥ ሙስሊሞች አያገኙም ማለት ይቻላል።

በዚህ ረገድ ከወለድ ነጻ ባንክ በመሆን የተቋቋሙት ሒጅራና ዘምዘም ባንክ(እየመጣ ያለው ራሚስ ባንክንም ጨምሮ) በባንክ ኢንደስትሪ በስፋት ተሳትፈው የየድርሻቸውን ትርፍ ሲያገኙ ያኔ የባንኮቹ ባለአክሲዮኖች ከባንክ ኢንደስትሪ ዘርፍ ትርፍን ማግኘት ይጀምራሉ ማለት ነው። እስከዚያው ግን ባንኮች አተረፍን ከሚሉት ከፍተኛ ቢሊዮን ብሮች መካከል (አምና የሁሉም ባንኮች ድምር የተጣራ ትርፋቸው 30 ቢሊዮን ብር ነበር።) ወለድን የሚጠነቀቁ ሙስሊሞች እስከ ዛሬ በየዓመቱ ከሚገኘው የባንክ ዘርፍ ትርፍ የሉበትም ማለት ይቻላል።በኢትዮጵያ በወለድ አልባ ባንክ አማራጭ ተከልክሎ መቆየቱ ሙስሊሞች ከዚህ አትራፊ ዘርፍ ተጠቃሚ እንዳይሆኑ አግዷቸው ነበር።

ይቀጥላል…

Ahmedin Jebel-አሕመዲን ጀበል

ክርስቲያናዊ ብሔርተኝነት ኢትዮጵያን ጉዳት ላይ እየጣለ ነው ሲል ፎሬይን ፖሊሲ ላይ የቀረበ ሰፊ ትንታኔ ገለጸ። ሙሉውን ጹሁፍ ሀሩን ሚዲያ በአማርኛ ቋንቋ ተርጉሞታል።.ሀሩን ሚዲያ፥ ሰኔ 11...
19/06/2022

ክርስቲያናዊ ብሔርተኝነት ኢትዮጵያን ጉዳት ላይ እየጣለ ነው ሲል ፎሬይን ፖሊሲ ላይ የቀረበ ሰፊ ትንታኔ ገለጸ። ሙሉውን ጹሁፍ ሀሩን ሚዲያ በአማርኛ ቋንቋ ተርጉሞታል።.
ሀሩን ሚዲያ፥ ሰኔ 11/2014.
ክርስቲያናዊ ብሔርተኝነት ኢትዮጵያን ጉዳት ላይ እየጣለ ነው ሲል ፎሬይን ፖሊሲ ላይ የቀረበ ሰፊ ትንታኔ ገልጿል። በአንድሪው ዲኮርት የቀረበው ይህ ትንታኔ የኢትዮጵያን ሀገረ መንግስት ስሪት ከታሪካዊው መነሻው በመዳሰስ የጀመረ ሲሆን ጹሁፉ ወቅታዊ ጉዳዮችን በተመለከተ ሰፊ ዳሰሳ አድርጓል።
ሰለሞናዊው ስርአትን በመናፈቅ በግላጭ ከሚታገሉ አካላት ጀምሮ በመንግስታዊ ስርአቱ ውስጥ የሚገኙ ጽንፈኛ አላማ ያላቸው ሀይማኖተኞችን በመግለጽ የወደፊት እቅዳቸውን ለማብራራት ሞክሯል።.
◾️ የሀሩን ሚዲያ ዶክመንቴሽን ክፍል አርቲክሉን ወደ አማርኛ ቋንቋ የተረጎመው ሲሆን በዛሬው ምሽት የወቅታዊ ዳሰሳ መሰናዷችን የሚቀርብ ይሆናል። ምሽት 3:00 ላይ ይጠብቁን...
© ሀሩን ሚዲያ
___________
በቴሌግራም
https://t.me/harunmedia

በዩቲዩብ
http://bit.ly/3MXs17j

በሃገራችን የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ የቁርዓን እና የአዛን ውድድር የፊታችን እሁድ ይካሄዳል!በመጪው እሁድ ሰኔ 5/2014 በአዲስ አበባ ስቲዲዮም ለሚካሄደው ዓለም አቀፍ የቁርዓን እና የአዛን...
08/06/2022

በሃገራችን የመጀመሪያው ዓለም አቀፍ የቁርዓን እና የአዛን ውድድር የፊታችን እሁድ ይካሄዳል!

በመጪው እሁድ ሰኔ 5/2014 በአዲስ አበባ ስቲዲዮም ለሚካሄደው ዓለም አቀፍ የቁርዓን እና የአዛን ውድድር በርካታ እንግዶች እየገቡ ይገኛሉ ።

ሀገራችን በዓለም አቀፍ ደረጃ የሚያስጠራው ይህ ውድድር ከ56 በላይ ሀገራት የሚወዳደሩበት ሲሆን ለውድድሩ ከፍተኛ ዝግጅት ሲካሄድ ቆይቷል ።

ውድድሩን በዘይድ እብን ሳቢት የቁርአን ማህበር አዘጋጅነትና በአገሪቱ ከሚገኙ የተለያዩ የመንግስት ተቋማት እንዲሁም ታላላቅ ድርጅቶች ጋር በመተባበር የሚካሄድ ነው:

ውድድሩ በሦሥት ዘርፎች የሚካሄድ ሲሆን በአዛን በቁርአን ሒፍዝና በ30ጁዝዕ የድምጽ ውድድር ይካሔዳል።

እስካሁን ድረስ ባለው መረጃም ከፍተኛ ቁጥር ያለው ተወዳዳሪዎች ዳኞች እንዲሁም ታዳሚዎች እንደገቡና እየገቡ መሆኑን ተገልጿል።

በዚህ ታላቅ ፕሮግራም ላይ ሁላችንም ከጠዋቱ 12 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ አበባ ስታድየም በመገኘት የሃገራችንን ስም ከፍ አድርገን ለአለም ልናስተዋውቅ ይገባል::

ለበለጠ መረጃ
በዚህ ይደውሉ
0911755245
0911723051

እንኳንስ ተጋብዘው ድሮም እንዲያ ናቸው‼ ❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄(ዐብዱልጀሊል ሸኽ ዐሊ ካሣ)ጠንካራ ተቋንም እንዲኖርህ ሊፈልጉ አይችሉም። ከፈለጉም አንተን ለመቆጣጠር የሚያስችላቸውን ተቋም...
03/06/2022

እንኳንስ ተጋብዘው ድሮም እንዲያ ናቸው‼ ❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄❄
(ዐብዱልጀሊል ሸኽ ዐሊ ካሣ)

ጠንካራ ተቋንም እንዲኖርህ ሊፈልጉ አይችሉም። ከፈለጉም አንተን ለመቆጣጠር የሚያስችላቸውን ተቋም እንጅ ሌላ አይሰጡህም። አንተን ለመቆጣጠር የሚያሰችል ተቋም ሲፈጥሩ ሁነኛ ሰዎችን መሰንቀራቸው የተለመደ ነው። ለዓላማቸው የሚያድር አሊያም የሚመች አሊያም ቢያንስ እንቅፋት የሚሆን ሰው መስቀመጣቸው የተለመደ ነው።

ዓላማቸው የበታችነቱን አምኖ ትኙ የሆነ ሙስሊም ማህበረሰብ መፍጠር ነው። ይህንን የሚያሟላ ህዝብ ለነሱ ጨዋ ነው። ለዚህ ግባቸው ተባባሪ ሰዎችን አፍርተው ተንቀሳቅሰዋል።

ማህበረ ቅዱሳን በ1995/2002 አውጥቶት በነበረው ጥናቴ ባለው ዶክመንት ላይ እንዲህ ይላል፡፡

"የኢትዮጵያ እስልምና አመሰራረቱ በሰላም ስለነበር እንደሌሎቹ የእስልምና ወይም የአፍሪካ አገሮች ኢትዮጵያ ውስጥ የነበረው ሁናቴ ጠንካራ አልነበረም፤ Coexistence ያልነውም ለዚህ ነው፡፡ ከክርስቲያ መንግስት በታች ሆኖ አቅምን አውቆ የመኖር ምልክት ይታይ ነበር፡፡ (ማ/ቅዱሳን/2002 በኢ/ኦ/ተ/ቤ/መምሪያ ማህበረ ቅዱሳን የአዲስ አበባ ንኡስ ማዕከል ስልጠና ክፍል፣ እስልምናና የእስልምናን እንቅስቃሴ)

በማህበሩ ትርጓሜ መሰረት እስልምናና ሙስሊሞች አቅማቸውን አውቀው በክርስቲያኑ መንግሥት ስር ሲኖሩ መቻቻል ወይም ኮኤግዚስታንስ ይባላል፡፡

ሙስሊሙ የበታችነቱን አምኖ አቅሙን አውቆ እንዲኖር ደግሞ እያንዳንዷን እንቅስቃሴውን መቆጣጠር አለባቸው፤ ሁሉንም ለመቆጣጠር ደግሞ ተጠሪነቱ ለነሱ የሆነ ተቋም እንጅ ነጻ የሆነ ተቋም እንዲረን ፈጽሞ አይፈልጉም፤ ከታሪክ የምንማረውም ይህንኑ ነው።

ዛሬ ላይ በቀጥታ ይህን ማድረግ ስለማይችሉ ቢያንስ ለነሱ የሚያድር፣ ከነሱ ጋር እስልምናንና ሙስሊሞችን በማዳከም የሚተባበር ተቋም ወይም አመራር ይፈልጋሉና እያደረጉት ያለው ይህንኑ ነው፡፡ እስኪ ትናንትን እንፈትሽ።

1⃣ በአጼ ኃ/ሥላሴ ዘመን ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ሀጅ ለማድረግ ቪዛ የሚያገኙትና ቪዛው በአገር ግዛት ሚኒስቴር ሹመኞች እጅ ላይ ይሆን ነበር

2⃣ አቶ መኮነን ሀብተወልድ የሙስሊሙን እንቅስቃሴ ለመቆጣጠር የሀጅና ኡምራ ጉዞ በእሳቸው ስር እንዲሆኑ አድርገው ነበር፤ ይሄ ይሂድ ያኛው እንዳይሄድ እያሉ የመወሰን ስልጣንን ተቆጣጥረው ነበር።

3⃣ ተፈቅዶላቸው የሚሄዱትንም ከኢትዮጵያ እስከ ሳዑዲ አረቢያ ደርሰው እስኪመለሱ የሚቆጣጠሩ፣ የሚሰልሉ ሰዎችን አብረው የሚሄዱ የአገር ሽማግሌዎች እያሉ ይመድቡባቸው ነበር፡፡

በዘመኑ ጥብቅ ምስጢር በሚል ለተለያዩ የንጉሱ የጸጥታ መዋቅር ይላኩ ከነበሩ የስለላ ውጤቶች መካከል ትቂቶቹን እንቀንጭብ:–

ሸህ አብደላ መድሃኔ (መድኔ) (ለ8 ዓመታት በወቅቱ የሐጅ ኮሚቴ አባል የነበሩ) ሰኔ 28/1964 ማስታዎሻ በሚል ርዕስ ለክቡር አቶ ጌታሁን ተሰማ የአገር ግዛት ሚኒስትር የጻፉትና ምስጢር የሚል ኮድ ተሰጥቶት የተቀመጠ ሰነድ እንዲህ ይላል:–

«ዓላማቸውን ከግብ ለማድረስ ሲያቅታቸው ከሀገር ወጥተው በዓረብ ክፍለ ዓለም ተበታትነው ጥቅም ለሚሰጧቸው መሰሪ በመሆን የኢትዮጵያን ስም ለማጥፋት የሚሰሩ ጥቂቶች አይደሉም፤

…በልዩ ልዩ ስልትና ሥራ ከሀገራቸው ወጥተው የትም የሚኖሩ ወንበዴዎችና ከቤተ ዘመዶቻቸው ጋር የሚገናኙት በዚህ የጸሎት (የሀጅና ኡምራ) ሥፍራ ነው፤ ለዚህም አንድ ጥሩ አቋም ያለው የሐጅ ጉዳይ አስፈጻሚ ድርጅት መቋቋም አለበት፤

….የአሁኑም አምባሳደራችን የኢትዮጵያ መንግሥት እስላም ዜጎቹን ይበድላል፡፡ ተብሎ ከአረቦች ለሚቀርበው ወቀሳ ጥሩ ማስረጃ ሆነው ተገኝተዋል፡፡» ይላል።

🅱 ደጃች ከተባሉ ሰው ነሀሴ 1/1964 ማስታዎሻ በሚል ርዕስ ለክቡር አቶ ጌታሁን ተሰማ የአገር ግዛት ሚኒስትር የጻፉትና ምስጢር የሚል ኮድ ተሰጥቶት የተቀመጠ ሰነድ ደግሞ ይህን ይላል:–

«በመሰረቱ እስካሁን የተደረገው መጻጻፍ ሁሉ ወደ መካ ከሚሄዱት ተሳላሚዎች ውስጥ በብዛት ከዚያው አገር እየቀሩ የኤርትራ ወንበዴዎች አባል ስለመሆናቸው ሌሎችም በአሽከርነት በገረድነት እየተቀጠሩ የሀገሪቱን ስምና ክብር በዝቅተኛ ግምት ማስጠራታቸው፣ በዚህም ሥራቸው ላይ ሆነው ለወንበዴዎቹ ድርጅትም ሆነ ለሌሎች ተቃራኒዎች የፖለቲካ መሳሪያ መሆናቸው

….ነገር ግን (ከዚህም በላይ) ወደ አገር የሚመለሱት ተሳላሚዎች ከዚያ ከወንበዴዎችና ከሀገሪቱ ጠላቶች የሰበሰቡትን ክፉ መንፈስ ለሰላማዊውና ለዘላኑ ነዋሪ በማስተላለፍ ያላሰበውን እንዲያስብ በማድረግ የባሰ ጉዳት ሊያደርሱ ከመቻላቸውም በላይ ከጊዜ ብዛት በ15ኛው መቶ ዓመት ላይ በኢትዮጵያ (ግራኝ ሙሀመድ) ያደርስ የነበረውን በማስታወስ ወደፊትም በረጅም ጊዜ ውሥጥ ይህ ሁኔታ ሊደርስ ይችል ይሆናል ብሎበማሰብ ሰፊና የዘለቄታ ጥናት ሊደረግ የሚገባ መሆኑን በቅድሚያ ማስታወስ ይበጀናል።

….ይልቁንም ወደ መካ የሚሄዱትን ምዕምናን ቁጥር መቀነስ እንደ እውነት ከሆነ ከማናቸውም ሃይማኖት እስልምና በኢትዮጵያ ሙሉ ነጸነት አለው ሊባል ይችላል፡፡ ስለዚህ በሃገሪቱ ውስጥ ጊዜና ምክንያት ጠብቆ የሃይማኖት ልዩነትና መከፋፈል እንዲነሳሳና እንዲስፋፋ ምክንያትና መግቢያ ከሚሆኑት ነገሮች ዋናው የኢትዮጵያውያን ወደ መካ መዲና በየዓመቱ መጓዝ ሊሆን እንደሚችል አያጠራጥርም፡፡

ይህንንም የሚያሰኘው አንዱ ምክንያት ኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን እምነቷን ባላደረሰችበትና ባላጠናከረችበት ክፍለ ግዛት ሁሉ እስልምና እንዴት ባለ ፍጥነት እየተስፋፋ እንደሄደ ማየት የሚያስተማምን ማስረጃ ሊሆን ይችላል፡፡

ይህንንም ስል በሲዳማና በሽዋ እኔ ራሴ የማውቃቸው አረመኔዎች (አዋሚዎች፣ ሃይማኖት የሌላቸው ሰዎች) የነበሩና ይልቁንም ፍጹም ክርስቲያኖች የነበሩ ብዙዎቹ መስለማቸውን የዓይን ምስክር ነኝ፡፡ ስለዚህ የተለመደውን መካና መዲና መሄዱ በግልጽና በአንድ ጊዜ ማስቀረት አስፈላጊ ይሆናል።˝ይላል።

እናም ወዳጄ ጉዳዩ ከጥንት ነው፤ ከቻሉ ተቋምህን ከላይ ሆነው ተቆጣጥረው ይጫወቱብሃል ካልቻሉ ደግሞ ያንተን ሃይማኖታዊ እንቅስቃሴ ሁሉ በስጋት፣ ለአገር አደጋ እንደሆነ በመተንተን፣ እነሱ ብቻ ለአገር አሳቢ አንተ ደግሞ የጠላት በር እንደሆንክ በመተንተን ሽፋን እስልምናህ እንዳያድግ፣ ፕራክቲካል ሙስሊም እንዳትሆን ቀይደው ይይዙሃል፡፡

ስለዚህ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ተቋምህንና አመራሮችህን የሚቆጣጠሩበትን መንገድ ይዘይዳሉ፤ ከመካከልም አድርባይ፣ ሆዳም፣ ለስልጣኑና ለስሙ የሚያድር፣ ሙናፊቅ ሸህም ሆነ ቃዲ አሊያም ዓሊም ፈልገው የውስጥ ትስስር ይፈጥሩብሃል፡፡

ሰላዮቻቸው፣ ተባባሪዎቻቸውን በተቋም ላይ ዘለዓለማዊ ሆነው ሰለልለውም፣ ቀይደውም ይይዙላቸው ዘንድ በማንኛውም መንገድ ከጎናቸው ይቆማሉ፡፡ ዛሬ ከነባሩ አስልምና ጎን ነን ሲሉህ የበታችነቱን አቅሙን አውቆ ከሚኖረው እስልምና ዘብ ነን እያሉህ ነው፤ ዛሬ ከዑለማዎቹ ጎን ነን ሲሉህ ከነ ሸህ አብደላ መድኔና ከነ ሀጂ ከማል ሐጂ መሰሎች ጎን ነን እያሉህ ነው፡፡

ለዛሬው አላብዛብህ፤ በቀጣይ ለሙስሊሙ ተቆርቋሪ፣ መሪ፣ ዓሊም፣ አዋቂ በመምሰል የሀጅ ኮሚቴ የሚባል ለስለላና ለቁጥጥር የሚመች ተቋም ስለመሰረቱልህ አንድ ጉደኛ ሸሕ በአላህ ፈቃድ እነግርሃለሁ።

🔴 ጆይን ያድርጉ https://t.me/ahmedin99

Address

Addis Ababa

Telephone

+447908114597

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አል ቀለም posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to አል ቀለም:

Share