ሐበሻ ጣዕም/Habesha Taem

ሐበሻ ጣዕም/Habesha Taem ሐበሻ ጣዕም ስለ ሁሉም የሚያወራ ስለ ሁሉም የሚያነሳሳ #የመዝናኛ , #የመረጃ ,እና, #የቁምነገር ሬዲዮ ፕሮግራም ነው

የሎንኪንግ የከባድ ማሽነሪዎች በኢትዮጽያ ዩኒክ ትሬዲንግ ኃ.የተ.የግ.ማ. ከቻይናው የሎንኪንግ የግንባታ ማሽኖች አምራች ጋር ብቸኛ ወኪል ሆኖ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ፈረመ። በትናን...
14/09/2025

የሎንኪንግ የከባድ ማሽነሪዎች በኢትዮጽያ

ዩኒክ ትሬዲንግ ኃ.የተ.የግ.ማ. ከቻይናው የሎንኪንግ የግንባታ ማሽኖች አምራች ጋር ብቸኛ ወኪል ሆኖ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ፈረመ።

በትናንት እለት በተደረገው ስምምነት መሠረት እንደ ሎደር እና ኤክስካቫተር ያሉ የግንባታ ማሽኖችን በኢትዮጵያ ገበያ የማስተዋወቅና የማቅረብ እድልን እንደሚፈጥር በመርሐግብሩ ላይ ተገልጸዋል።

የዩኒክ ትሬዲንግ መስራች እና ስራ አስኪያጅ አቶ መሀመድ ኢንድሪስ እንደገለፁት የንግድ ስራውን የጀመሩት ከአባታቸው በመነጨ የንግድ ልምድ ሲሆን፣ ስራውንም የጀመሩት ከ12 አመታት በፊት ቄራ አካባቢ በሚገኘው ሶፍያ ሞል ውስጥ በሚገኝ አንድ ትንሽዬ ሱቅ ውስጥ እንደነበር ገልጸዋል።

ዩኒክ ትሬዲንግ ሁለተኛ ቅርንጫፉን ሃና ማርያም አካባቢ መክፈት እንደቻለ እና የተለያዩ ተጎድተው የነበሩ ማሽነሪዎችን በመግዛት እና በመጠገን ወደ ገበያ በማቅረብ ስራውን ማስፋት እንደቻለ ተናግረዋል።

ይህ የስራ መስፋፋት ተጨማሪ ቦታን ስለሚያስፈልግ፣ ድርጅቱ ቦሌ ቡልቡላ አካባቢ 3000 ካሬ ሜትር ላይ የጥገና አገልግሎት የሚሰጥበት ማዕከል እና መጋዘን በመክፈት ስራውን ይበልጥ ማሳደግ ችሏል። ድርጅቱ የመለዋወጫ እቃዎችንም ከቻይና፣ ከኮሪያ እና ከዱባይ በማስመጣት ስራውን ይበልጥ እንዳጠናከረ አቶ መሀመድ አብራርተዋል።

አቶ መሀመድ ለውጭ ምንዛሪ እጥረት መፍትሄ ለመስጠት ድርጅቱ ከሁለት አመት በፊት ወደ ቡና ኤክስፖርት ስራ መግባቱን ገልጸዋል።

አሁን ደግሞ በቡልቡላ አግሮ ኢንዱስትሪ ፓርክ ውስጥ 13,000 ካሬ ሜትር ቦታ በመውሰድ የቡና ፕሮሰሲንግ እና የኩኪስ ብስኩት ፋብሪካ ግንባታ ማጠናቀቁን ገልጸው በመጪው ጥቅምት ወር ምርት ለመጀመር ዝግጅት ላይ መሆናቸውን አስታውቀዋል። በአሁኑ ጊዜ ዩኒክ ትሬዲንግ 53 ቋሚ እና 25 ጊዜያዊ ሰራተኞች አሉት።

ዩቱብ
https://youtube.com/?si=c6Wc8RignrUhSQp_

ቴሌግራም https://t.me/Habsha_Taem

ፌስቡክ https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL

ሊንክ ዲን https://www.linkedin.com/in/dj-fortin-k-ሐበሻ-ጣዕም-555600202

ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የቤተሠብ ቀንን በሚሊኒየም አዳራሽ አከበረ ‎በሚሊኒየም አዳራሽ ያከበረ ሲሆን፤ ዓመታዊ የሠራተኞች የእውቅናና ሽልማት መርሃግብርንም አካሂዷል። በመርሃ ግብሩ ላይ ...
13/09/2025

ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የቤተሠብ ቀንን በሚሊኒየም አዳራሽ አከበረ

‎በሚሊኒየም አዳራሽ ያከበረ ሲሆን፤ ዓመታዊ የሠራተኞች የእውቅናና ሽልማት መርሃግብርንም አካሂዷል።

በመርሃ ግብሩ ላይ በሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የእቅድና አፈፃፀም ሪፖርት ኮርፖሬት ዳይሬክተር አክሊሉ ሙሉጌታ፤ ባለፈው በጀት ዓመት የተከናወኑ ዓመታዊ የእቅድ አፈፃፀም ሪፖርተር አቅርበዋል።

በቀረበው ሪፖርት መሠረት በ2017 በጀት ዓመት በምርት ዋጋ 89 ነጥብ 7 በመቶ አፈጻጸም የተመዘገበ ሲሆን፤ ይህም ካለፈው ዓመት የ55 በመቶ ጭማሪ ማሳየቱዐተገልጿል።

በሽያጭ ዕቅድ በ112 ነጥብ 8 በመቶ መመዝገቡን በመግለጽም፤ ይህም ካለፈው ዓመት የ86 በመቶ ብልጫ አሳይቷል ተብሏል።

ከታክስ በፊት የተገኘው ትርፍ ከዕቅዱ በላይ 167 ነጥብ 5 በመቶ ሲሆን፤ ይህም ካለፈው ዓመት የ134 ነጥብ 1 በመቶ ጭማሪ እንዳለው ተመላክቷል።

በበጀት ዓመቱ 263 ሚሊዮን ዶላር የውጭ ምንዛሪ ገቢ ማግኘቱን የገለጸው ሚድሮክ፤ በዚህም የዕቅዱን 136 በመቶ ማሳካቱን አስታውቋል።

አብዛኛው የውጭ ምንዛሪ ወይም 75 በመቶ የተገኘው ከማዕድን ዘርፍ መሆኑንም ገልጿል።

ማህበራዊ ኃላፊነትን በመወጣት በኩል በ2017 በጀት ዓመት ከአንድ ነጥብ አንድ ቢሊዮን ብር በላይ ወጪ ማድረጉ የተገለጸ ሲሆን፤ በዚህም አራት የዳቦ እና ዱቄት ፋብሪካዎች ግንባታ ጨምሮ የተለያዩ ሥራዎች ማከናወን እንደቻለ ተገልጿል።

ሞሃ ለስላሳ መጠጦች ኢንደስትሪ በ2016 ዓ.ም ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕን መቀላቀሉ ይታወሳል።

በወቅቱ ኪሳራ ውስጥ የነበረው ድርጅቱ ግሩፑን ከተቀላቀለ በኋላ ትርፋማ መሆን መቻሉ የተገለጸ ሲሆን፤ በበጀት ዓመቱ የፀጥታ ችግር እና የብድር አቅርቦት ያጋጠሙ ችግሮች እንደነበሩ ተጠቁሟል።

የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ምክንያት ዋና ሥራ አስፈፃሚዎች ባስተላለፉት መልክት፤ ባለፈው በጀት ዓመት ያልተሳኩ እቅዶችን በ2018 በጀት ዓመት ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ ተናግረዋል።

ከምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚዎች መካከል የንግድ ዘርፍ ምክትል ሥራ አስፈፃሚ የሆኑት ሁሴን አህመድ፤ በተያዘው በጀት ዓመት ዘጠኝ ግዙፍ ሱፐር ማርኬቶች እንደሚከፈቱ ገልጸዋል።

በዕለቱ የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ ጀማል አህመድ ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት የላቀ አፈፃፀም ላስመዝገቡ ሠራተኞች እና አመራሮች ከ100 ሺሕ እስከ 500 ሺሕ ብር ሽልማት ተበርክቷል።

ሚድሮክ የዉጪ ምንዛሬን በማዳን፣ ገቢ ምርቶችን በመተካት፣ ገበያን በማረጋጋት፣ ማህበራዊ ኃላፊነትን በመወጣት እና ከ79 ሺሕ በላይ ለሆኑ ዜጎች የሥራ እድል በመፍጠር ለሀገር እድገት ከፍተኛ አሰተዋጽኦ እያበረከተ እንደሚገኝ በመድረኩ ተገልጿል።

ሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ በማኑፋክቸሪንግ፣ በግብርና፣ በማዕድን፣ በንግድና አገልግሎት፣ በሆስፒታሊቲ እንዲሁም በኮንስትራክሽንና ሪል እስቴት ዘርፎች መዋቀሩ ይታወቃል።

ዩቱብ
https://youtube.com/?si=c6Wc8RignrUhSQp_

ቴሌግራም https://t.me/Habsha_Taem

ፌስቡክ https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL

ሊንክ ዲን https://www.linkedin.com/in/dj-fortin-k-ሐበሻ-ጣዕም-555600202

እንኳን ለአዲሱ ዓመት 2018 ዓ/ም በሰላም በጤና አደረሳቹ🌼አዲሱን ዓመት የሰላም፣ የፍቅር፣ የጤና፣ የጸጋና የበረከት ያድርግልን🌼! #የሐበሻጣዕምአዘጋጆች  #ዲጄፎርቲንኬ  #ሜሮን  #ሀያት🌼...
11/09/2025

እንኳን ለአዲሱ ዓመት 2018 ዓ/ም በሰላም በጤና አደረሳቹ🌼አዲሱን ዓመት የሰላም፣ የፍቅር፣ የጤና፣ የጸጋና የበረከት ያድርግልን🌼!

#የሐበሻጣዕምአዘጋጆች #ዲጄፎርቲንኬ #ሜሮን #ሀያት
🌼 መልካም አዲስ ዓመት🌼

አዲሱን አመት በምስጋና ልዩ የአዲስ አመት ፕሮግራም በደማቁ ተካሄደ።በሞላልን ብቻ ሳይሆን በጎደለንም እናመስግን በሚል የስነልቦና ባለሙያዎች እና አማካሪዎች፣የትውልዱ ምልክት  አትጊ የሆኑ ወ...
08/09/2025

አዲሱን አመት በምስጋና ልዩ የአዲስ አመት ፕሮግራም በደማቁ ተካሄደ።

በሞላልን ብቻ ሳይሆን በጎደለንም እናመስግን በሚል የስነልቦና ባለሙያዎች እና አማካሪዎች፣የትውልዱ ምልክት አትጊ የሆኑ ወጣቶች፣ስኬታማ የቢዝነስ ልምዶች፣የህይወት ጉዟቸውን በጣፋጭ ታሪክ እያዋዙ ከመድረክ፣የግጥም ስራዎች፣ሙዚቃ፣ምስጋና ቀርበዋል።
የ2017 አመቱን በምስጋና ሸኝተን 2018ን በምስጋና እንቀበል ያሉት አዘጋጆቹ የምስጋና ባህል እንዲያድግ በየአመቱ ግንቦት 30 ላይ ጣፋጭ ህይወት ምስጋና እያዘጋጁ እንደቆዩም ተገልፃል።

ዩቱብ
https://youtube.com/?si=c6Wc8RignrUhSQp_

ቴሌግራም https://t.me/Habsha_Taem

ፌስቡክ https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL

ሊንክ ዲን https://www.linkedin.com/in/dj-fortin-k-ሐበሻ-ጣዕም-555600202

ሰላም አዲስ አበባ ኢትዮጵያ   የመዝናኛ የመረጃ የቁምነገር ፕሮግራም  .1 ላይ እሁድ ከ8_9 ሰዓት እንደመጣለን ።ከተለያዩ መረጃዎች እና ጣፋጭ ዜማዎች ጋር አብረናቹ እንቆያለን። መጋበዝ ም...
06/09/2025

ሰላም አዲስ አበባ ኢትዮጵያ የመዝናኛ የመረጃ የቁምነገር ፕሮግራም .1 ላይ እሁድ ከ8_9 ሰዓት እንደመጣለን ።
ከተለያዩ መረጃዎች እና ጣፋጭ ዜማዎች ጋር አብረናቹ እንቆያለን።

መጋበዝ ምትፈልጉት ሙዚቃ inbox አርጉልኝ ማህበራዊ ሚዲያዎቻችንን ሼር ያረጋቹ ቤተሰቦች

#ስፖንሰሮቻችን
#ኢትዮቴሌኮም
#ኬናስፔሻሊቲየጥር ክሊኒክ
#አቶባባ

ሀሳብ አስታየት ለመስጠት እና በቀጥታ ለማድመጥ
አድራሻችን 👇👇

ዩቱብ https://youtube.com/?si=c6Wc8RignrUhSQp_

ቴሌግራም https://t.me/Habsha_Taem

ፌስቡክ https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL

ሊንክ ዲን https://www.linkedin.com/in/dj-fortin-k-ሐበሻ-ጣዕም-555600202

ኢትዮ ቴሌኮም አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ የተለያዩ ድጋፎችን አደረገበመርሀገብሩ የተገኙት የኢትዮ - ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ፍሬህይወት ታምሩ እንደገለጹት ኩባንያው የኢትዮጵያ...
05/09/2025

ኢትዮ ቴሌኮም አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ የተለያዩ ድጋፎችን አደረገ

በመርሀገብሩ የተገኙት የኢትዮ - ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ የሆኑት ፍሬህይወት ታምሩ እንደገለጹት ኩባንያው የኢትዮጵያን ዲጂታል መፃዒ ዕድል በመቅረፅና በአፍሪካ ዘላቂና አካታች ዕድገትን ለማስፋፋት ያለውን ሚና አዲስ መልክ እንዲይዝ ለማድረግ የሚያስችል “ቀጣዩ አድማስ” ስትራቴጂን በስራ ላይ በማዋል በቁርጠኝነት እየተንቀሳቀሰ የሚገኝ ሲሆን፣ ከዚህም ጎን ለጎን ማህበራዊ ፋይዳ ባላቸው ዘርፈ ብዙ የበጎ አድራጎት ስራዎች ላይ የበኩሉን መልካም አሻራ እያሳረፈ ይገኛል ብለዋል፡፡

በዛሬው ዕለትም ኩባንያው “ለነገ ተስፋዎች” የሚል መርሃ ግብር በመቅረጽ እና በየዓመቱ ተግባራዊ በማድረግ ተቋማዊ ማህበራዊ ኃላፊነቱን በዘላቂነት እየተወጣ እንደሚገኝ ዋና ስራ አስፈጻሚዋ የገለፁ ሲሆን፣ በዘንድሮው ለነገ ተስፋዎች መርሃ ግብሩም በመላው የሀገራችን ክፍሎች ለሚገኙ እና አነስተኛ ገቢ ያላቸውን የማህበረሰብ ክፍሎችን መደገፍን ታሳቢ ያደረገ የመማሪያ ደብተር ድጋፎችን አድርጓል፡፡

በዚህም መሰረት ለ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን “ለነገ ተስፋዎች” በሚል መርህ ባዘጋጀው የመማሪያ ደብተር መርሃ ግብር በአዲስ አበባ እና በሁሉም የኢትዮ ቴሌኮም ሪጅኖች ለሚገኙ የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለሚማሩ 80ሺ ተማሪዎች ከ98.8 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ለእያንዳንዳቸው አንድ ደርዘን ደብተር ድጋፍ መርሃ ግብር አስጀምሯል፡፡

ኩባንያው የዘንድሮን ጨምሮ ባለፉት ስድስት ተከታታይ ዓመታት “ለነገ ተስፋዎች” በሚል መርሃ ግብር በመላው የሀገራችን ክፍሎች ለሚገኙ እና አነስተኛ ገቢ ያላቸውን የማህበረሰብ ክፍሎችን ለመደገፍ ታሳቢ ያደረገ የመማሪያ ደብተር ድጋፍ ሲያደርግ የቆየ ሲሆን፣ በአጠቃላይ እስከ አሁን በአንደኛ ደረጃ ት/ቤቶች ውስጥ ለሚማሩ 373 ሺህ ተማሪዎች ከ320.8 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ በማድረግ ድጋፍ ማድረጉ ተገልጿል፡፡

በዚህም መሰረት በእነዚህ የበጎ አድራጎት ተቋማት ለሚገኙ 13,674 አረጋዊያን፣ ህጻናት፣ እናቶች፣ አቅመደካሞች እና አካል ጉዳተኞች ከ47.8 ሚሊዮን ብር በላይ የገንዘብ ድጋፍ ያደረገ ሲሆን፣ የዘንድሮውን ጨምሮ ባለፉት አራት ተከታታይ ዓመታት በተመሳሳይ የበጎ አድራጎት መርሃ ግብሮች በመላው የሀገራችን ክፍሎች በሚገኙ 117 የበጎ አድራጎት ተቋማት ለሚገኙ 32,700አረጋዊያን፣ ህጻናት፣ እናቶች፣ አቅመደካሞች እና አካል ጉዳተኞች ከ78.8 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ አድርጓል፡፡

በተመሳሳይ ቀንም የኩባንያው የማኅበራዊ ኃላፊነት አካል የሆነው የደም ልገሳ መርሃግብር በማዘጋጀትና “በጎነት ለሰብዓዊነት!” በሚል መርህ ከብሔራዊ የደም ባንክ ጋር በመተባበር በተቋሙ ዋና መ/ቤት፣ በዞን እና በሪጅን ጽ/ቤቶች በአጠቃላይ በ19 ቦታዎች የኩባንያው በጎ ፈቃደኛ ሠራተኞች እና የሥራ ኃላፊዎች ደም የመለገስ መርሃግብር አዘጋጅቷል

ዩቱብ
https://youtube.com/?si=c6Wc8RignrUhSQp_

ቴሌግራም https://t.me/Habsha_Taem

ፌስቡክ https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL

ሊንክ ዲን https://www.linkedin.com/in/dj-fortin-k-ሐበሻ-ጣዕም-555600202

 !ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1 ሺሕ 500ኛው የመውሊድ በዓል አደረሳችሁ! #ሐበሻጣዕም በዓሉ የሰላም፣ የጤና፣ የፍቅር እና የመተሳሰብ በዓል እንዲሆን ከልብ ይመኛል።የሐበ...
04/09/2025

!

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1 ሺሕ 500ኛው የመውሊድ በዓል አደረሳችሁ!

#ሐበሻጣዕም በዓሉ የሰላም፣ የጤና፣ የፍቅር እና የመተሳሰብ በዓል እንዲሆን ከልብ ይመኛል።

የሐበሻ ጣዕም አዘጋጆች ዲጄ ፎርቲን ኬ ሀያት ሜሪ

ማሞ ምህረቱ ከብሔራዊ ባንክ ገዥነት እና ከመንግስት ስራ ለቀቁየኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥና የቀድሞ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ማሞ ምህረቱ ለሰባት ዓመታት ...
03/09/2025

ማሞ ምህረቱ ከብሔራዊ ባንክ ገዥነት እና ከመንግስት ስራ ለቀቁ

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ገዥና የቀድሞ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ማሞ ምህረቱ ለሰባት ዓመታት ያገለገሉበትን የመንግስት የስራ ሃላፊነት መልቀቃቸውን አስታወቁ።

አቶ ማሞ ከስልጣን መልቀቃቸውን ባሳወቁበት መልዕክታቸው፣ በመንግስት ውስጥ በተለያዩ የስራ ሃላፊነቶች ማገልገላቸው ትልቅ ክብር እንደሆነ ገልጸዋል።

በተለይም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ በመሩት የቤት-አስተዳደር ኢኮኖሚ ማሻሻያ ፕሮግራም ውስጥ በመስራታቸው እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክን በገዥነት መምራታቸው ከፍተኛ እርካታ እንዳስገኘላቸው ገልጸዋል።

በብሔራዊ ባንክ ቆይታቸው፣ ባንኩን ከ50 ዓመታት በኋላ ከፍተኛ የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች እንዲያከናውን መምራታቸውን አብራርተዋል።

ከቡድን አጋሮቻቸው ጋር በመሆን ዘመናዊ የገንዘብ ፖሊሲ ማዕቀፍን ተግባራዊ ማድረጋቸውን፣ ወደ ገበያ-ተኮር የውጭ ምንዛሪ ስርዓት መሸጋገራቸውን እና የባንኩን ነጻነት የሚያረጋግጥ አዲስ ህግ መውጣቱን አስታውሰዋል።

በተጨማሪም የፋይናንስ ዘርፉን ለውጭ ባንኮች ክፍት ማድረጋቸውን፣ ዲጂታል ክፍያን ማስፋፋታቸውን እና 10.58 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ፋይናንስ ማስገኘታቸውን በዝርዝር አስቀምጠዋል።

አቶ ማሞ ይህንን የስራ እድል የሰጣቸው እና የመራቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ መሆናቸውን በመግለጽ ምስጋና አቅርበዋል ከማቅረብ ወጪ በምን ምክንያት ከስራቸዉ እንደለቀቁ አላሳወቁም እንደ ካፒታል ዘገባ።
ዩቱብ
https://youtube.com/?si=c6Wc8RignrUhSQp_

ቴሌግራም https://t.me/Habsha_Taem

ፌስቡክ https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL

ሊንክ ዲን https://www.linkedin.com/in/dj-fortin-k-ሐበሻ-ጣዕም-555600202

ሰላም የሐበሻ ጣዕም ቤተሰቦች በተቻላቹ አቅም ያሉንን ማህበራዊ ፔጆች ሼር በማድረግ ለጓደኞቻቹ በማጋራት ዩቱባችንን ሰብስክራይብ በማድረግ አጋርነታቹን አሳዩን ለድጋፋቹ እናመሰግናለንዩቱብhtt...
02/09/2025

ሰላም የሐበሻ ጣዕም ቤተሰቦች በተቻላቹ አቅም ያሉንን ማህበራዊ ፔጆች ሼር በማድረግ ለጓደኞቻቹ በማጋራት ዩቱባችንን ሰብስክራይብ በማድረግ አጋርነታቹን አሳዩን ለድጋፋቹ እናመሰግናለን

ዩቱብ
https://youtube.com/?si=c6Wc8RignrUhSQp_

ቴሌግራም https://t.me/Habsha_Taem

ፌስቡክ https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL

ሊንክ ዲን https://www.linkedin.com/in/dj-fortin-k-ሐበሻ-ጣዕም-555600202

ሐበሻ ጣዕም ስለ ሁሉም የሚያወራ ስለ ሁሉም የሚያነሳሳ የመዝናኛ ,የመረጃ ,እና, የቁምነገር ሬዲዮ ፕሮግራም ነው። የማህበራዊ ሚዲያ አድራሻችን ሰብስክራይብ በማድረግ አበረታቱን የተለያ...

ኪዳን ትምህርት ቤት ላለፉት አመታት ተማሪዎችን በስነምግባር እንዲያድጉ እንዲሁም የግዕዝ ትምህርት እንደ አንድ የትምህርት ክፍል እየሰጠ እንደሚገኝ ገለፀ።በትላንትናው እለት በነበራቸው ፕሮግራ...
01/09/2025

ኪዳን ትምህርት ቤት ላለፉት አመታት ተማሪዎችን በስነምግባር እንዲያድጉ እንዲሁም የግዕዝ ትምህርት እንደ አንድ የትምህርት ክፍል እየሰጠ እንደሚገኝ ገለፀ።

በትላንትናው እለት በነበራቸው ፕሮግራም ታላላቅ የእምነት አባቶች እንዲሁም ረዳት ፕሮፌሰር ነብዩ ባዬን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው የክብር እንግዶች የሚዲያ አካላት በተገኙበት የተለያዩ ዝግጅቶችን አከናውነዋል።

ልጆች የሰሩትን የኮፒውተር ስራዎች መንፈሳዊ መዝሙሮች የተለያዩ የፈጠራ ስራዎች አቅርበዋል።

የእምነት አባቶች እና የክብር እንግዶች ባዩት ነገር መደሰታቸውን እና ኪዳን ትምህርት ቤት የጀመረውን ስራ አጠናክሮ እንዲቀጥል አሳስበዋል።

ኪዳን ትምህርት እና ስልጠና አክሲዮን ማህበር አክሲዮን ለመግዛት ከ10,000 ብር ጀምሮ እንደሆነ ተናግረዋል።

በሚቀጥለው በ2018 ዓ/ም ትምህርት ቤቱ በበለጠ ሁኔታ በአዳዲስ ስራዎች እንደሚመጣ ኪዳን ትምህርት ቤት የስራ ሀላፊዎች ገልፀዋል።

ዩቱብ
https://youtube.com/?si=c6Wc8RignrUhSQp_

ቴሌግራም https://t.me/Habsha_Taem

ፌስቡክ https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL

ሊንክ ዲን https://www.linkedin.com/in/dj-fortin-k-ሐበሻ-ጣዕም-555600202

“እንቁ ለጣጣሽ ኦቪድ ለቤትሽ” ታላቅ የቤት ሽያጭ ገበያ ተጀመረ  ኦቪድ ሪል ስቴት አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ ከዛሬ ነሐሴ 24 ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 7 ቀናት የሚቆይ ኤክስፖ በገርጂ ...
30/08/2025

“እንቁ ለጣጣሽ ኦቪድ ለቤትሽ” ታላቅ የቤት ሽያጭ ገበያ ተጀመረ

ኦቪድ ሪል ስቴት አዲስ ዓመትን ምክንያት በማድረግ ከዛሬ ነሐሴ 24 ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 7 ቀናት የሚቆይ ኤክስፖ በገርጂ የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ሳይት ቅጥር ግቢ ውስጥ አስጀምሯል፡፡

ብዙዎችን የቤት ባለቤት ለማድረግ በተዘጋጀው ኤክስፖ በልዩ ቅናሽ የመኖሪያ ቤትና የንግድ ሱቆች ለሽያጭ ቀርበዋል።

ኦቪድ ሪል ስቴት በሚያዝያ ወር በርካቶችን የቤት ባለቤት ያደረገ የቤት ገበያ በልዩ ቅናሽ አዘጋጅቶ እንደነበር ይታወሳል፡፡

ኤክስፖው በድጋሚ የተከፈተው በበርካታ ቤት ፈላጊዎች ጥያቄ መሰረት መሆኑን የኦቪድ ግሩፕ ማርኬቲንግ ማኔጀር መቅደስ ቀደመ ገልፀዋል።

ቤት ፈላጊዎች ከተዘጋጀው የአዲስ ዓመት ልዩ ቅናሽና ምቹ የአከፋፈል ዘዴም ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

ዩቱብ
https://youtube.com/?si=c6Wc8RignrUhSQp_

ቴሌግራም https://t.me/Habsha_Taem

ፌስቡክ https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL

ሊንክ ዲን https://www.linkedin.com/in/dj-fortin-k-ሐበሻ-ጣዕም-555600202

Address

Addis Ababa

Telephone

+251923484891

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሐበሻ ጣዕም/Habesha Taem posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ሐበሻ ጣዕም/Habesha Taem:

Share