ሐበሻ ጣዕም/Habesha Taem

ሐበሻ ጣዕም/Habesha Taem ሐበሻ ጣዕም ስለ ሁሉም የሚያወራ ስለ ሁሉም የሚያነሳሳ #የመዝናኛ , #የመረጃ ,እና, #የቁምነገር ሬዲዮ ፕሮግራም ነው

በዓለም አቀፍ ደረጃ በፊልም ሥራዎቹ የሚታወቀው እና ኦስካር ተሸላሚው ተዋናይ ሊዮናርዶ ዲካፕሪዮ፣ በታዋቂው ታይም (TIME) መጽሔት የ2025 "የዓመቱ ምርጥ አርቲስት" (Entertainer ...
09/12/2025

በዓለም አቀፍ ደረጃ በፊልም ሥራዎቹ የሚታወቀው እና ኦስካር ተሸላሚው ተዋናይ ሊዮናርዶ ዲካፕሪዮ፣ በታዋቂው ታይም (TIME) መጽሔት የ2025 "የዓመቱ ምርጥ አርቲስት" (Entertainer of the Year) ክብርን ተቀዳጀ።

አሁን በ51 ዓመቱ ላይ የሚገኘው ዲካፕሪዮ፣ ይህን ክብር ያገኘው በፊልም ኢንደስትሪው ውስጥ ላሳየው ተከታታይ እና አስደናቂ ብቃት እንዲሁም በቅርቡ One Battle After Another በተሰኘው ፊልም ላይ ላሳየው ልዩ ተሳትፎ ነው።

በ15 ዓመቱ የፊልም ዓለምን የተቀላቀለው ዲካፕሪዮ፣ የመጀመሪያውን ትልቅ እድል ያገኘው ከሮበርት ደኒሮ ጋር በሰራበት This Boy’s Life (1993) ፊልም ነበር።

በወቅቱ ጄምስ ዲንን እንደ አርአያ በመውሰድ ራሱን ያዘጋጀው ዲካፕሪዮ፣ በተለይም በ What’s Eating Gilbert Grape ፊልም ላይ የአዕምሮ እድገት ውስንነት ያለበትን ታዳጊ ገጸ-ባህሪ ወክሎ በመተወን የሆሊዉድን ትኩረት መሳብ ችሎ ነበር።

ከዚያን ጊዜ ጀምሮ Titanic፣ The Aviator፣ The Wolf of Wall Street እና The Revenant (ለኦስካር ያበቃው) በመሳሰሉ ፊልሞች ላይ የማይረሱ ገጸ-ባህሪያትን ወክሎ ተጫውቷል።

የ2025 ድንቅ ሥራ፡ One Battle After Another

ዲካፕሪዮ በ2025 ይህን ክብር እንዲያገኝ ትልቅ አስተዋጽኦ ያደረገው፣ በፖል ቶማስ አንደርሰን በተመራው One Battle After Another ፊልም ላይ "ቦብ ፈርጉሰን" የተባለውን ገጸ-ባህሪ ወክሎ በመተወኑ ነው። በዚህ ፊልም ላይ፡-

አንዲት ሴት ልጁን (በቼዝ ኢንፊኒቲ የተወከለች) ብቻውን የሚያሳድግ፣
ዘመኑ ያለፈበት እና ራሱን ከዓለም ያገለለ፣
ነገር ግን ለልጁ ደህንነት ሲል ማንኛውንም መስዋዕትነት የሚከፍል አባት ሆኖ ተጫውቷል።

ፊልሙ ምንም እንኳን ለንግድ አዋጭ አይሆንም ተብሎ ተሰግቶ የነበረ ቢሆንም፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ200 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ በማስገኘት ስኬታማ ሆኗል።

ከፊልም ሥራው በተጨማሪ ዲካፕሪዮ በአካባቢ ጥበቃ ላይ ባለው ጽኑ አቋም ይታወቃል።

ሪ ዋይልድ የተሰኘ ድርጅት በማቋቋም ከአካባቢው ማህበረሰብ ጋር በመሆን የተፈጥሮ ስነ-ምህዳርን ለመጠበቅ እየሰራ ይገኛል።

በቅርቡ በታዋቂዋ የአካባቢ ጥበቃ ተመራማሪ ጄን ጉዶል የቀብር ሥነ-ሥርዓት ላይ ተገኝቶ ባደረገው ንግግር፣ "ተስፋ መቁረጥ ሳይሆን በተግባር መለወጥ" እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥቷል።

ዲካፕሪዮ ስለ ዝና እና ስለ ግል ሕይወቱ ሲናገር፣ "የእኔ ፍልስፍና ቀላል ነው፤ የምትናገረው ቁምነገር ወይም የምታሳየው ስራ ከሌለህ፣ ከሰዎች እይታ መሰወር እና በፀጥታ መስራት የተሻለ ነው" ብሏል።

በአጠቃላይ፣ ዲካፕሪዮ ከልጅነት ጀምሮ በፊልም ኢንደስትሪው ውስጥ የዘለቀ፣ ስታርነቱ ያልደበዘዘ እና አሁንም ድረስ በተመልካቾች ዘንድ ተወዳጅነቱን ጠብቆ የቆየ "የመጨረሻው እውነተኛ የፊልም ኮከብ" ተብሎ በብዙዎች ይገለጻል።

ዩቱብ
https://youtube.com/?si=c6Wc8RignrUhSQp_

ቴሌግራም https://t.me/Habsha_Taem

ፌስቡክ https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL

ሊንክ ዲን https://www.linkedin.com/in/dj-fortin-k-ሐበሻ-ጣዕም-555600202

ሰላም አዲስ አበባ ኢትዮጵያ   የመዝናኛ የመረጃ የቁምነገር ፕሮግራም  .1 ላይ እሁድ ከ8_9 ሰዓት እንደመጣለን ።ከተለያዩ መረጃዎች እና ጣፋጭ ዜማዎች ጋር አብረናቹ እንቆያለን።  #ስፖንሰ...
07/12/2025

ሰላም አዲስ አበባ ኢትዮጵያ የመዝናኛ የመረጃ የቁምነገር ፕሮግራም .1 ላይ እሁድ ከ8_9 ሰዓት እንደመጣለን ።
ከተለያዩ መረጃዎች እና ጣፋጭ ዜማዎች ጋር አብረናቹ እንቆያለን።

#ስፖንሰሮቻችን
#ኢትዮቴሌኮም
#ዳሽንባንክ
#አሪፍፔይ
#ፍሌበርኮፊ
#ኬናስፔሻሊቲየጥር ክሊኒክ
#አቶባባ

ሀሳብ አስታየት ለመስጠት እና በቀጥታ ለማድመጥ
አድራሻችን 👇👇

ዩቱብ https://youtube.com/?si=c6Wc8RignrUhSQp_

ቴሌግራም https://t.me/Habsha_Taem

ፌስቡክ https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL

ሊንክ ዲን https://www.linkedin.com/in/dj-fortin-k-ሐበሻ-ጣዕም-555600202

ሰብስክራይብ ያረጋቹ ቤተሰቦች
05/12/2025

ሰብስክራይብ ያረጋቹ ቤተሰቦች

Enjoy the videos and music you love, upload original content, and share it all with friends, family, and the world on YouTube.

ኢትዮ ቴሌኮም እና ካምቴል በካሜሩን የዲጂታል ሽግግርን ለማፋጠን የሚያስችል ታሪካዊ ስምምነት ተፈራረሙ!ኢትዮ ቴሌኮም ከካምቴል (CAMTEL) ጋር የካሜሩንን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ለማፋጠን...
05/12/2025

ኢትዮ ቴሌኮም እና ካምቴል በካሜሩን የዲጂታል ሽግግርን ለማፋጠን የሚያስችል ታሪካዊ ስምምነት ተፈራረሙ!

ኢትዮ ቴሌኮም ከካምቴል (CAMTEL) ጋር የካሜሩንን የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ለማፋጠን የሚያስችል ታሪካዊ የማስተር ሰርቪስ የኮንትራት ስምምነት በካሜሩን ያውንዴ ከተማ ተፈራርሟል!

ይህ ስምምነት፤ የካምቴል የስራ ሃላፊዎች ወደ ሀገራችን በመምጣት ኩባንያችን በ"ዲጂታል ኢትዮጵያ" ግንባታ ውስጥ ያሳየውን የላቀ የቴክኖሎጂ አመራር ከተመለከቱ በኋላ፣ ተሞክሮውን ወደ ካሜሩን ለመውሰድ ከነበራቸው ፍላጎት የመነጨ ነው።

በዚህም መሰረት ሁለቱ ኦፕሬተሮች በካሜሩን የፋይናንስ ተደራሽነትን የሚያረጋግጥ የዲጂታል ክፍያ ስርዓት ለማስፋፋት፣ ብሄራዊ ክላውድ በመገንባት የመንግስት አገልግሎቶችን ዲጂታላይዝ ለማድረግ፣ የሞባይል ኔትወርክ ጥራትን ለማረጋገጥ እንዲሁም የካምቴልን አሰራር በይበልጥ በማዘመን ደንበኛ ተኮር ባህል ለመገንባት በጋራ ይሰራሉ።

በተጨማሪም ስምምነቱ፤ ለካሜሩን የዲጂታል ኢኮኖሚ ቁልፍ የሆኑ ተቋማትና ቢዝነሶች የሚያቀላጥፉ ዲጂታል መፍትሄዎችን፣ የተጨማሪ እሴት እና የኢንተርኮኔክት አገልግሎቶችን በጋራ ለመተግበር ያስችላል፡፡

ይህ ስምምነት በኩባንያችን የ‘ቀጣዩ አድማስ፡ ዲጂታልና ከዚያም ባሻገር 2028 ስትራቴጂ’ መሰረት፣ ድንበር ተሻጋሪ አገልግሎት በማቅረብና አህጉራዊ ትብብርን በማጎልበት የዲጂታል አፍሪካን ጉዞ ለማፋጠን የሚያስችል ታሪካዊ ምዕራፍ ነው።

ዩቱብ
https://youtube.com/?si=c6Wc8RignrUhSQp_

ቴሌግራም https://t.me/Habsha_Taem

ፌስቡክ https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL

ሊንክ ዲን https://www.linkedin.com/in/dj-fortin-k-ሐበሻ-ጣዕም-555600202

ታዬ ደንደአ በእስራት ተቀጡየቀድሞው የሠላም ሚኒስትር ዴኤታ እና የኦሮሚያ ምክር ቤት አባል አቶ ታዬ ደንደአ ጥፋተኛ በተባሉበት ክስ የ7 ዓመት ከ2 ወር እስር ተፈረደባቸው።አቶ ታዬ ዛሬ አር...
05/12/2025

ታዬ ደንደአ በእስራት ተቀጡ

የቀድሞው የሠላም ሚኒስትር ዴኤታ እና የኦሮሚያ ምክር ቤት አባል አቶ ታዬ ደንደአ ጥፋተኛ በተባሉበት ክስ የ7 ዓመት ከ2 ወር እስር ተፈረደባቸው።

አቶ ታዬ ዛሬ አርብ ኅዳር 26/2018 ዓ.ም. የቅጣት ውሳኔ የተላለፈባቸው በፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 1ኛ የሕገ መንግሥት እና በሕገ መንግሥት ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች ችሎት ጥፋተኛ በተባሉበት ሕገወጥ የጦር መሣሪያ ይዞ በመገኘት ነው።

የመንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣን እና የክልል ምክር ቤት አባል የነበሩት አቶ ታዬ ሕገ ሕገ ወጥ የጦር መሣሪያ ይዞ በመገኘት እንዲሁም ፍቃድ ሳይኖራቸው በቤታቸው ውስጥ አንድ ታጣፊ ክላሽንኮቭ ጠመንጃ ከ60 ጥይቶች ጋር ተገኝቷል በሚል ክስ ቀርቦባቸው ነበር።

ዩቱብ
https://youtube.com/?si=c6Wc8RignrUhSQp_

ቴሌግራም https://t.me/Habsha_Taem

ፌስቡክ https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL

ሊንክ ዲን https://www.linkedin.com/in/dj-fortin-k-ሐበሻ-ጣዕም-555600202

የአፍሪካ የኢነርጂ  ኮንፍረንስ በኢትዮጵያ ሊካሄድ ነዉ!የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው  የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ (Energy Efficiency conference) ታህሳስ 2 እ...
03/12/2025

የአፍሪካ የኢነርጂ ኮንፍረንስ በኢትዮጵያ ሊካሄድ ነዉ!

የአፍሪካ ህብረት ያዘጋጀው የመጀመሪያው የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ (Energy Efficiency conference) ታህሳስ 2 እና 3 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይካሄዳል።

ኮንፍረንሱ የኢነርጂ ውጤታማነትን በማረጋገጥ የአፍሪካ ኢኮኖሚ እድገት፣ ዘላቂ ልማትና ለአየር ንብረት ለውጥ የተግባር ምላሽ አቀጣጣይ ሞተር የማድረግ አላማ ያለው መሆኑ ተገልጿል።

የኮንፍረንሱ መሪ ሀሳብ “የአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት አጀንዳን በስትራቴጂካዊ አጋርነት ውጤታማ ማድረግ” መሆኑን የአፍሪካ ኢነርጂ ኮሚሽን ዋና ዳይሬክተር አቶ ራሺድ አሊ ገልፀዋል።

የኢነርጂ ውጤታማነት የኃይል ብክነት፣ የካርቦን ልቀት እና ወጪ ለመቀነስ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ የኢኮኖሚ እድገት ማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል።

ከአፍሪካ የኢነርጂ ውጤታማነት ኮንፍረንስ ጎን ለጎን ሌሎች ሁነቶች ይኖራልም ተብሏል።

ዩቱብ
https://youtube.com/?si=c6Wc8RignrUhSQp_

ቴሌግራም https://t.me/Habsha_Taem

ፌስቡክ https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL

ሊንክ ዲን https://www.linkedin.com/in/dj-fortin-k-ሐበሻ-ጣዕም-555600202

"ልቤን" እያለ አረፈኮሜድያን ወንደወሰን አውራሪስ በድንገተኛ የልብ ህመም በዳግማዊ ምንልክ ሆስፒታል በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ ዛሬ ሕይወቱ አልፏል።ትናንት "ልቤን" ብሎ ወደ ህክምና አምርቶ ነበ...
30/11/2025

"ልቤን" እያለ አረፈ

ኮሜድያን ወንደወሰን አውራሪስ በድንገተኛ የልብ ህመም በዳግማዊ ምንልክ ሆስፒታል በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ ዛሬ ሕይወቱ አልፏል።

ትናንት "ልቤን" ብሎ ወደ ህክምና አምርቶ ነበር።

ለሊቱን ሁሉ ሕክምና እየወሰደ ከአንድም ሁለት ጊዜ አሰቸጋሪ ደረጃ እየደረሰ በሕክምና ህይወቱ ተመልሷል።

ይሁንና የአንዲት ሴት ልጅ አባት የሆነው ኮሜድያን ወንደወሰን አውራሪስ ዛሬ ማለዳ ላይ አርፏል።

ሐበሻ ጣዕም ለቤተሰቦቹ ለአድናቂዎቹ መፅናናትን ይመኛል

ዩቱብ
https://youtube.com/?si=c6Wc8RignrUhSQp_

ቴሌግራም https://t.me/Habsha_Taem

ፌስቡክ https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL

ሊንክ ዲን https://www.linkedin.com/in/dj-fortin-k-ሐበሻ-ጣዕም-555600202

3ተኛውን መኪና ቻርጅ መሙያ ጣቢያ ተመረቀ ኢትዮ ቴሌኮም ፍየል ቤት ተብሎ በሚታወቀው አካባቢ ያስገነባውን 3ኛውን ዘመናዊ እና ፈጣን የኤሌክትሪክ መኪና መሙያ ጣቢያ በዛሬው እለት አስመርቋልይ...
27/11/2025

3ተኛውን መኪና ቻርጅ መሙያ ጣቢያ ተመረቀ

ኢትዮ ቴሌኮም ፍየል ቤት ተብሎ በሚታወቀው አካባቢ ያስገነባውን 3ኛውን ዘመናዊ እና ፈጣን የኤሌክትሪክ መኪና መሙያ ጣቢያ በዛሬው እለት አስመርቋል

ይህ ዘመናዊ የመኪና ኤሌክትሪክ ኃይል መሙያ በ1 ሰከንድ 1 ኪሎ ሜትር ለመጓዝ የሚያስችል የኤሌክትሪክ ቻርጅ ለማድረግ ሲሆን፣ እንደ ተሸከርካሪው አቅም በ15 ደቂቃ ውስጥ ሙሉ (100%) የኤሌክትሪክ ኃይል መሙላት ያስችላል፡፡ ሲስተሙ በሰው ሰራሽ አስተውሎት (AI) ቴክኖሎጂ የባትሪ መስፈርቶች እና የደንበኛን ትዕዝዝ ተቀብሎ በመመርመር በተፈለገው መጠን ቻርጅ ያደርጋል ተብሏል፡፡

ይህ የኤሌክትሪክ መኪና ኃይል መሙያ ጣቢያ በአንድ ጊዜ እስከ 16 ተሽከርካሪዎችን የማስተናገድ አቅም ያለው በመሆኑ ለአሽከርካሪዎች ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት ያስችላል፡፡ የዚህ ጣቢያ ወደ ሥራ መግባትም፤ ኩባንያው ቀደም ሲል የገነባቸውን ሁለት ጣቢያዎች ጨምሮ በአጠቃላይ በአንድ ጊዜ ለ48 የኤሌክትሪክ መኪኖች አገልግሎት መስጠት የሚችልበትን አቅም የፈጠረ እንደሆነ ተነግሯል፡፡

የዛሬው 3ተኛው 16 ዲስፔንሮች ያሉት በተመሳሳይ ሰአት 16 መኪኖችን የሚያስተናግድ እንደሆነ የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃሚ ፍሬህይወት ታምሩ ገልጸዋል

ዋና ስራ አስፈፃሚዋ አክለውም በቀጣዩ 3 አመታት ውስጥም በበርካታ ከተሞችም ይህ ዘመናዊ እና ፈጣን የኤሌክትሪክ መኪና መሙያ ጣቢያ እንደሚገነባ ተናግረዋል

የቻርጅ ጣቢያው 24/7 አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን፣ በቴሌብር ሱፐርአፕ ላይ በሚገኝ መተግበሪያ ይከናወናል፡፡ ተገልጋዮች አገልግሎቱን ያለማንም አጋዥነት በራሳቸው ማግኘት እና ክፍያቸውንም በቴሌብር ሱአፐርአፕ መፈጸም እንደሚችሉ ተነግሯል፡፡

ከዚህ ጋር ተያይዞ ከዚህ ቀደም በዚሁ አመት በተገነቡት 2ቱ ዘመናዊ የመኪና ኤሌክትሪክ ኃይል መሙያዎች 165 ሺህ የሚደርሱ የኤሌክትሪክ መኪኖች አገልግሎቱን ተጠቅመዋል ተብሏል

ዩቱብ
https://youtube.com/?si=c6Wc8RignrUhSQp_

ቴሌግራም https://t.me/Habsha_Taem

ፌስቡክ https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL

ሊንክ ዲን https://www.linkedin.com/in/dj-fortin-k-ሐበሻ-ጣዕም-555600202

ዴማ ሆፕ ሪል ስቴት በቦሌ መድኃንያለም ሁለተኛውን ቅርንጫፍ መስሪያ ቤቱን ከፈተ። ዴማ ሆፕ ሪል ስቴት በመሀል ቦሌ መድኃንያለም ሁለተኛ ቅርንጫፍ መስሪያ ቤቱን በታላቅ ድምቀት ከፍቷል።ይህም ...
26/11/2025

ዴማ ሆፕ ሪል ስቴት በቦሌ መድኃንያለም ሁለተኛውን ቅርንጫፍ መስሪያ ቤቱን ከፈተ።

ዴማ ሆፕ ሪል ስቴት በመሀል ቦሌ መድኃንያለም ሁለተኛ ቅርንጫፍ መስሪያ ቤቱን በታላቅ ድምቀት ከፍቷል።

ይህም የመኖሪያ ቤት እና የሱቅ ፈላጊዎችን ፍላጎት ለማሟላት ያለውን ቁርጠኝነት ያሳያል።

አዲሱ ቅርንጫፍ መስሪያ ቤት የዴማ ሆፕ ቦሌ ዳውንታውን በሚባለው ሳይቱ ላይ የከፈተ ሲሆን ልዩ የሪል ስቴት አገልግሎቶችን በመስጠት የዴማ ሆፕ ራዕይን በምሳካት፣ የተለያዩ የደንበኞችን ፍላጎት ያማከሉ ከመኖሪያ ቤቶች እስከ የንግድ ቦታዎች በውስጡ የያዘ አማራጭን አቅርቧል።

በዴማ ሆፕ ሪል ስቴት የማርኬቲንግ ሥራ አስኪያጅ አቶ ናሆም አለማየሁ እንደተናገሩት "ሁለተኛ ቅርንጫፋችንን በቦሌ መድኃንያለም በመክፈት ለህብረተሰቡ ቅንጡ እና ዘመናዊ መኖሪያ ቤቶችን እና ሱቆችን በማቅረባችን ደስተኞች ነን። ጥራት እና ፍጥነት መለያችን ነው’’ ሲሉ ተናግረዋል።

ዴማ ሆፕ ሪል ስቴት ሲግናል ባለው ሳይቱ 100% ገንብቶ ያስረከበ ሲሆን፣ በመሃል ቦሌ በስድስት ወር ውስጥ 90% በማጠናቀቅ፣ ቦሌ አደይ አበባ አከባቢ እንዲሁም 90% በሰባት ወር ውስጥ በማጠናቀቅ፣ በሾላ ገበያ, በቦሌ አትላስ አከባቢ እንዲሁም በሌሎች ለመኖርም ሆነ ለንግድ አመቺ በሆኑ ሰፈሮች ላይ የተጀመረው ግንባታ በጥራት እና በፍጥነት እየተካሄደ ይገኛል።

ዴማ ሆፕ ሪል ስቴት ብዙዎችን የቤት ባለቤት ከማድረግ ባለፈ በማህብረሰቡ ውስጥ ያለውን ትልቅ ሚና በትምህርት ቤት ግንባታ፣ በተለያዩ ጊዜያት በደም ልገሳ እንዲሁ በሌሎች የበጎ ስራዎች ላይ በመሳተፍ ከማህበረሰቡ ጋር ያለውን ቁርኝነት ያሳያል።

ዴማ ሆፕ ሪል ስቴት በአዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ የሚገኝ የሪል ስቴት ኩባንያ ነው።

ዴማ ሆፕ ሪል ስቴት ላለፉት 27 አመታት በተለያዩ የስራ ዘርፎች ላይ ተሰማርቶ ሲሰራ የቆየ ሲሆን ከ 5 አመት ወዲህ ደግሞ የሪል ስቴት ድርጅቱን በማቋቋም ብዙዎችን የቤት ባለቤት በማድረግ ላይ ይገኛል።

ዴማ ሆፕ ሪል ስቴት ቅንጡ የመኖሪያ ቤቶችን እና ሱቆችን በጥራት እና በአጭር ጊዜ ገንብቶ በማስረከብ ለደንበኞቹ ምቹ የመኖሪያ አከባቢን የመፍጠር ትልቅ አቋም አለው።

ዩቱብ
https://youtube.com/?si=c6Wc8RignrUhSQp_

ቴሌግራም https://t.me/Habsha_Taem

ፌስቡክ https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL

ሊንክ ዲን https://www.linkedin.com/in/dj-fortin-k-ሐበሻ-ጣዕም-555600202

የኢትዮጵያ የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማትን ከሀገራዊ ዲጂታል ስነ-ምህዳር ጋር ለማዋሃድ ያለመ ስምምነት ተካሄደበስምምነቱ አሪፍፔይ ከተለያዩ ዲጅታል ባንኮች ጋር እየሰራ እንደሚገኝ የተገለፀ ሲሆን...
26/11/2025

የኢትዮጵያ የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማትን ከሀገራዊ ዲጂታል ስነ-ምህዳር ጋር ለማዋሃድ ያለመ ስምምነት ተካሄደ

በስምምነቱ አሪፍፔይ ከተለያዩ ዲጅታል ባንኮች ጋር እየሰራ እንደሚገኝ የተገለፀ ሲሆን በዛሬው እለት ከአሪፍፔይ ጋር ስምምነት የፈፀመው የኢትዮጵያ ፊንቴክ ኢንዱስትሪ ትራንስፎርሜሽን ፎረም ለማይክሮ ፋይናንሶች አገልግሎት የሚሰጡባቸውን ፎርማቶች የሚያዘጋጅ ነው

የአሪፍፔይ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ረድኤት ፅጌብርሃን እንደገለፁት የዛሬው ስምምነት በኢትዮጵያ ያሉ ማይክሮ ፋይናንሶችን ከዲጂታል ፋይናንስ ፍጥነት እና ቅልጥፍና ጋር ለማዋሀድ ያለመ ነው ብለዋል።

አቶ ረድኤት አክለውም ስምምነቱ የማይክሮ ፋይናንስ ኢንደስትሪዎች ግብይቶችን፣ የብድር ክፍያዎችን እና ቁጠባዎችን በቅጽበት በዲጅታል እንዲያካሂዱ ለማስቻል ያለመ እንደሆነ ተናግረዋል

ከስምምነቱ ባሻገር በዛሬው እለት የአሪፍ ማይክሮ ፋይናንስ ጉባኤ የተካሄደ ሲሆን በዚህም የአሪፍፔይ ዲጂታል ዋሌት (The Arifpay Digital Wallet) የተሰኘ ለመደበኛ ፋይናንስ አዲስ የሆኑ የማይክሮ ፋይናንስ ኢንደስትሪ ደንበኞች ሂሳባቸውን እንዲያስተዳድሩ፣ ብድር እንዲቀበሉ እና ክፍያዎችን በዲጂታል መልክ እንዲከፍሉ የሚያደርግ የሞባይል መተግበሪያ ነው።

ዛሬ ይፋ የሆነው አሪፍ ኮር ባንኪንግ ሲስተም ባህላዊ የባንክ ስራዎችን ዲጂታል ለማድረግ ለሚፈልጉ ባንኮች፣ የኢትዮጵያ ፊንቴክ ኢንደስትሪዎች፣ ለብድርና ቁጠባ ህብረት ስራ ማህበር፣ ለዲጂታል ባንኮች እና ፊንቴክስ የተነደፈ ዘመናዊና ዲጅታል የባንክ ሲስተም ነው

በመርሀገብሩ አሪፍፔይ የማይክሮ ፋይናንሶች በውስጣቸው የተለያዩ ነጋዴዎች ት/ቤቶችንና ሆስፒታሎችን የሚይዙ ሲሆን ለነሱም የሚሆን አሪፍ ኬር የተሰኘ የሜዲካል የዲጅታል ሲስተምን በማዘጋጀት ላይ እንደሚገኝና አሪፍ እስኩል የተሰኘ ለት/ቤቶች የተዘጋጀ ፕላት ፎርምም ይፋ አድርጓል

ይህ ከስምምነቱ ጎን ለጎን የተካሄደው የአሪፍ ማይክሮ ፋይናንስ ጉባኤ አላማ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን እና የገጠር ዜጎችን የሚያገለግሉትን የኢትዮጵያ የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማትን ከሀገራዊ ዲጂታል ስነ-ምህዳር ጋር በማዋሃድ መስራት ነው ተብሏል

ዩቱብ
https://youtube.com/?si=c6Wc8RignrUhSQp_

ቴሌግራም https://t.me/Habsha_Taem

ፌስቡክ https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL

ሊንክ ዲን https://www.linkedin.com/in/dj-fortin-k-ሐበሻ-ጣዕም-555600202

ዩቱብ
https://youtube.com/?si=c6Wc8RignrUhSQp_

ቴሌግራም https://t.me/Habsha_Taem

ፌስቡክ https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL

ሊንክ ዲን https://www.linkedin.com/in/dj-fortin-k-ሐበሻ-ጣዕም-555600202

ተክለሀይማኖት ጠቅላላ ሆስፒታል 25ኛ አመት በዓሉን አከበረአርቲስት ቸርነት ፍቃዱን የብራንድ አምባሳደር አድርጎም ሾመ።ይህ የተገለጸው ሆስፒታሉ የ25ተኛ አመት ክብረ በአሉን ባከበረበት ወቅት...
23/11/2025

ተክለሀይማኖት ጠቅላላ ሆስፒታል 25ኛ አመት በዓሉን አከበረ

አርቲስት ቸርነት ፍቃዱን የብራንድ አምባሳደር አድርጎም ሾመ።

ይህ የተገለጸው ሆስፒታሉ የ25ተኛ አመት ክብረ በአሉን ባከበረበት ወቅት ነው።

ሆስፒታሉ ላለፉት 25 አመታት በሀገራችን የጤና ዘርፍ ላይ የራሱን አስተዋጽኦ ማበርከት ሲሰራ መቆየቱም ተገልጿል።

በእለቱ ተክለሀይማኖት ጠቅላላ ሆስፒታል አርቲስት ቸርነት ፍቃዱን ብራድ አምባሳደር አድርጎ መሾሙ ተነግሯል

ተክለሃይማኖት ጠቅላላ ሆስፒታል በውስጥ ደዌ ፣ በሰሬጀሪ፣ በማህጸን እና ጽንስ ፣ በህጻናት እና ልጆች ህክምናም ፣ ከአንገት በላይ፣ በቆዳ እና አባላዘር ህክምና ከሚሰጣቸው አገልግሎቶች ውስጥ እንደሚገኙበት ተጠቁሟል።

ሆስፒታሉ ዘመናዊ የሆኑ የህክምና መሳሪያዎች በመጠቀም ላለፋት አመታት እየሰራ ነበርም ተብሏል።

ሆስፒታሉ የምስረታ በዓሉን ከህዳር 14 እስከ ግንቦት 18 በተለያዩ በጎ አድራጎት ስራዎች፣ በነጻ ህክምና እንዲሁም በተመረጡ ቀናት ለሚወልዱ እናቶች ልዩ ሽልማትና ልዩ የህክምና ቅናሽ እንደሚኖርም ተገልጿል።

ተክለሃይማኖት በቀጣይ እየገነባ ያለው ኮምፕሬሄንሲቭ ሆስፒታል ሲጠናቀቅ ወደፊት 12 ቀዶ ህክምና ክፍሎች እና 200 አልጋዎችም እንደሚኖሩትም ይጠበቃል

ይህም ለተለያዩ ህመሞች ወደ ውጭ ሀገር ሄደው የሚታከሙ ሰዎችን ድካም በመቀነስ ለጤና ቱሪዝም የድርሻውን እንዲወጣ ያግዘዋል ተብሏል

ዩቱብ
https://youtube.com/?si=c6Wc8RignrUhSQp_

ቴሌግራም https://t.me/Habsha_Taem

ፌስቡክ https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL

ሊንክ ዲን https://www.linkedin.com/in/dj-fortin-k-ሐበሻ-ጣዕም-555600202

Address

Addis Ababa

Telephone

+251923484891

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሐበሻ ጣዕም/Habesha Taem posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ሐበሻ ጣዕም/Habesha Taem:

Share