04/11/2025
አዲስ የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያን ይፋ ሆነ
የሲዳማ ባንክ የሞባይል ባንኪንግአገልግሎት መተግበሪያ ሥራ ማስጀመሩን የባንኩ ዋና ስራ አስፈፃሚ ታደሰ ሐጢያ ተናገሩ።
መተግበሪያው አሁን ላይ ከሲዳማ ባንክ ወደ ሲዳማ ባንክ ገንዘብ ማስተላለፍ፣ወደ ማንኛውም ባንክ ገንዘብ መላክና መቀበል፣ የተለያዩ የአገልግሎት ክፍያዎችን መፈፀም፣ የአየር መሙላትና ሒሳብ ማስተዳደር የሚያስችልአገልግሎት ይሰጣል ብሏል ባንኩ።
በቀጣይ የዲጂታል ብድር አገልግሎት ለደንበኞቹ በዚሁ መተግበሪያ እንደሚያስጀምር የባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተናግረዋል።
ባንኩ ከብሔራዊ ባንክ ፈቃድ አግኝቶ ሥራ ከጀመረ ሦስት ዓመት ያስቆጠረ ሲሆን የተቀማጭ ገንዘብ መጠኑን ወደ 4 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ማድረስ ችሏል።
አጠቃላይ የሀብት መጠኑ ደግሞ ከ6 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር በላይ መድረሱን ባንኩ ይፋ አድርጓል።
የተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥርም 400 ሺህ መድረሱ ነው የተገለፀው።
ዩቱብ
https://youtube.com/?si=c6Wc8RignrUhSQp_
ቴሌግራም https://t.me/Habsha_Taem
ፌስቡክ https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL
ሊንክ ዲን https://www.linkedin.com/in/dj-fortin-k-ሐበሻ-ጣዕም-555600202