ሐበሻ ጣዕም/Habesha Taem

ሐበሻ ጣዕም/Habesha Taem ሐበሻ ጣዕም ስለ ሁሉም የሚያወራ ስለ ሁሉም የሚያነሳሳ #የመዝናኛ , #የመረጃ ,እና, #የቁምነገር ሬዲዮ ፕሮግራም ነው

አዲስ የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያን ይፋ ሆነየሲዳማ ባንክ የሞባይል ባንኪንግአገልግሎት መተግበሪያ ሥራ ማስጀመሩን የባንኩ ዋና ስራ አስፈፃሚ ታደሰ ሐጢያ ተናገሩ። መተግበሪያው አሁን ላይ ከ...
04/11/2025

አዲስ የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያን ይፋ ሆነ

የሲዳማ ባንክ የሞባይል ባንኪንግአገልግሎት መተግበሪያ ሥራ ማስጀመሩን የባንኩ ዋና ስራ አስፈፃሚ ታደሰ ሐጢያ ተናገሩ።

መተግበሪያው አሁን ላይ ከሲዳማ ባንክ ወደ ሲዳማ ባንክ ገንዘብ ማስተላለፍ፣ወደ ማንኛውም ባንክ ገንዘብ መላክና መቀበል፣ የተለያዩ የአገልግሎት ክፍያዎችን መፈፀም፣ የአየር መሙላትና ሒሳብ ማስተዳደር የሚያስችልአገልግሎት ይሰጣል ብሏል ባንኩ።

በቀጣይ የዲጂታል ብድር አገልግሎት ለደንበኞቹ በዚሁ መተግበሪያ እንደሚያስጀምር የባንኩ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ተናግረዋል።

ባንኩ ከብሔራዊ ባንክ ፈቃድ አግኝቶ ሥራ ከጀመረ ሦስት ዓመት ያስቆጠረ ሲሆን የተቀማጭ ገንዘብ መጠኑን ወደ 4 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ማድረስ ችሏል።

አጠቃላይ የሀብት መጠኑ ደግሞ ከ6 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር በላይ መድረሱን ባንኩ ይፋ አድርጓል።

የተጠቃሚ ደንበኞች ቁጥርም 400 ሺህ መድረሱ ነው የተገለፀው።

ዩቱብ
https://youtube.com/?si=c6Wc8RignrUhSQp_

ቴሌግራም https://t.me/Habsha_Taem

ፌስቡክ https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL

ሊንክ ዲን https://www.linkedin.com/in/dj-fortin-k-ሐበሻ-ጣዕም-555600202

"ቶሎ" የተሰኘ የኢንዳክሽን ምድጃ ይፋ ሆነ በሃገር ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ "ቶሎ" በሚል ስያሜ የተገጣጠመዉን የኢንዳክሽን ምድጃ  አምራች የሆነው ግሪን ሲን ኢነርጂ የመጀመሪያዉን የኢንዳክሽን...
04/11/2025

"ቶሎ" የተሰኘ የኢንዳክሽን ምድጃ ይፋ ሆነ

በሃገር ውስጥ ለመጀመሪያ ጊዜ "ቶሎ" በሚል ስያሜ የተገጣጠመዉን የኢንዳክሽን ምድጃ አምራች የሆነው ግሪን ሲን ኢነርጂ የመጀመሪያዉን የኢንዳክሽን ስቶቭ መገጣጠሚያ እና ማምረቻ ተቋም በዛሬዉ እለት ጥቅምት 25/2018 ዓ.ም ስራ አስጀምሯል።

በዉሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር የሚደገፈው በኢትዮጵያ የንፁህ ምግብ ማብሰል ዘርፍ ቁልፍ ሚና ያለው ግሪን ሲን ኢነርጂ ኃ.የተ.የግ.ማህበር በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የኢንዳክሽን ስቶቭ መገጣጠሚያ እና የማምረቻ ፋሲሊቲ ነዉ በዛሬዉ እለት ስራ ያስጀመረዉ።

ዛሬ ይፋ የተደረገዉ ቶሎ ኢንዳክሽን ምድጃ 9ዐ% ኃይል ቆጣቢ ፈጣን ሙቀት ከትክክለኛ የሙቀት መቆጣጠሪያ ጋር ማንኛውንም ቦታ ከፍ አድርጎ ማስቀመጥ የሚያስችል የሚያምር፣ በዘመናዊ ዲዛይን የተሰራ የቴክኖሎጂ ዉጤት ነዉ ተብሏል።

ይህ ቴክኖሎጂ በዓመት 63,000 ለሚገመቱ ሰዎች ሞት ምክንያት የሆነውን የቤት ውስጥ የአየር ብክለትን በመቀነሱ ሴቶችን ከ500 ሰአታት በላይ በመቆጠብ ማገዶን በመሰብሰብ ፣የደን መጨፍጨፍን በመዋጋት የቤትን ደህንነት በማጎልበት እና የአረንጓዴ ልማትን በማስቀጠል እና የከተማ ልማት ፕሮግራሞችን በመደገፍ ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ገልፀዉ የስቶቮቹ ዋጋም ከኢትዮጵያ 6000 ብር ጀምሮ ማግኘት እንደሚቻል የግሪን ሴን መስራች ወ/ሮ ረቂቅ በቀለ ገልፀዋል።

የግሪን ሲን ኢነርጂ ኢንዳክሽን ምድጃ መፍትሄዎች የተነደፉት በፀሃይ ሃይል የሚሰሩ ራቅ ያሉ ቦታዎችን እና ከፍተኛ አቅም ያለው የማብሰያ ፍላጎት ላላቸው ተቋማት ነዉ።

ዩቱብ
https://youtube.com/?si=c6Wc8RignrUhSQp_

ቴሌግራም https://t.me/Habsha_Taem

ፌስቡክ https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL

ሊንክ ዲን https://www.linkedin.com/in/dj-fortin-k-ሐበሻ-ጣዕም-555600202

ሰላም አዲስ አበባ ኢትዮጵያ   የመዝናኛ የመረጃ የቁምነገር ፕሮግራም  .1 ላይ እሁድ ከ8_9 ሰዓት እንደመጣለን ።ከተለያዩ መረጃዎች እና ጣፋጭ ዜማዎች ጋር አብረናቹ እንቆያለን።  #ሽልማት...
02/11/2025

ሰላም አዲስ አበባ ኢትዮጵያ የመዝናኛ የመረጃ የቁምነገር ፕሮግራም .1 ላይ እሁድ ከ8_9 ሰዓት እንደመጣለን ።
ከተለያዩ መረጃዎች እና ጣፋጭ ዜማዎች ጋር አብረናቹ እንቆያለን።

#ሽልማትምአዘጋጅተናል

#ስፖንሰሮቻችን
#ኢትዮቴሌኮም
#ኬናስፔሻሊቲየጥርክሊኒክ
#አቶባባ

ሀሳብ አስታየት ለመስጠት እና በቀጥታ ለማድመጥ
አድራሻችን 👇👇

ዩቱብ https://youtube.com/?si=c6Wc8RignrUhSQp_

ቴሌግራም https://t.me/Habsha_Taem

ፌስቡክ https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL

ሊንክ ዲን https://www.linkedin.com/in/dj-fortin-k-ሐበሻ-ጣዕም-555600202

ፕሬዝደንት ትራምፕ ክርስቲያኖችን በተመለከተ ላስተላለፉት መልእክት አድናቆት አለኝ"  ስትል ራፐር ኒኪ ሚናጅ ገለፀች፡፡ የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ በሶሻል ትሩዝ ገፃቸው ላይ በናይ...
02/11/2025

ፕሬዝደንት ትራምፕ ክርስቲያኖችን በተመለከተ ላስተላለፉት መልእክት አድናቆት አለኝ" ስትል ራፐር ኒኪ ሚናጅ ገለፀች፡፡ የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ በሶሻል ትሩዝ ገፃቸው ላይ በናይጄሪያ የሚገኙ ክርስቲያኖች የህልውና ስጋት እንዳጋጠማቸው ገልፀዋል፡፡

ሲናገሩም ‹‹ክርስትና በናይጄሪያ ውስጥ የህልውና አደጋ ውስጥ ወድቋል፡፡ በሺ የሚቆጠሩ ክርስቲያኖች ተገድለዋል፡፡ ለዚህ ደግሞ ፅንፈኛ ሙስሊሞች ሀላፊነቱን ይወስዳሉ፡፡ ስለዚህም አሁን ናይጄሪያ ልዩ ትኩረት ያስፈልጋታል›› ብለዋል፡፡ ጨምረውም አሜሪካ እንደዚህ አይነት ግፍ ሲፈፀም ቆማ እንደማትመለከት አስታውቀዋል፡፡ የዋሽንግተን አስተዳደር በመላው አለም ከሚገኙ ክርስቲያኖች ጎን እንደሚቆምና እየደረሰባቸው ካለው የህልውና ስጋት እንደሚታደግና የመታደግም አቅም እንዳለው ገልፀዋል፡፡

አሜሪካዊቷ ታዋቂዋ ራፐር ኒኪ ሚናጅ ለዚህ የትራምፕ አስተያየት ትልቅ አድናቆትና ክብር እንዳላት በኤክስ ገጿ ላይ አስታውቃለች፡፡ ራፐሯ በመልእክቷ ‹‹የትራምፕን ፅሁፍ ሳነብ ልዩ ስሜት ተሰምቶኛል፡፡ እኛ በነፃነት እግዚአብሄርን በምናመልክበት አገር ላይ ነን፡፡ ማንም ሰው በሀይማኖታችን የተነሳ አይገድለንም፡፡ እርስ በእርሳችን እየተከባበርን ሀይማኖታችንን የመከተል መብት አለን›› ብላለች፡፡

ራፐሯ በመላው አለም በክርስቲያኖች ላይ ጭቆናና ግፍ እየተደረገ መሆኑን ገልፃ ይህንን የሰብአዊ መብት ጥሰት ችላ ማለት የለብንም የሚል መልእክት አስተላልፋለች፡፡ ስትቀጥልም ‹‹ፕሬዘደንት ትራምፕና ባልደረቦቻቸው ለዚህ ጉዳይ ትኩረት በመስጠታቸው አመሰግናለሁ፡፡ በሀይማኖታቸው የተነሳ የተገደሉ ክርስቲያኖችን እግዚአብሄር ይባርክ፡፡ በፀሎትም እናስባቸው›› ብላለች፡፡

ዩቱብ
https://youtube.com/?si=c6Wc8RignrUhSQp_

ቴሌግራም https://t.me/Habsha_Taem

ፌስቡክ https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL

ሊንክ ዲን https://www.linkedin.com/in/dj-fortin-k-ሐበሻ-ጣዕም-555600202

ኪ ሃውሲንግ ፋይናንስ ሶሉሽን 150 ቤቶችን አስረከበ ኪ ሃውሲንግ ፋይናንስ ሶሉሽን በአዲስ አበባ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው ሃና ማሪያም ፍሬንድሺፕ ስቶር ፊትለፊት ባለ 15 ...
01/11/2025

ኪ ሃውሲንግ ፋይናንስ ሶሉሽን 150 ቤቶችን አስረከበ

ኪ ሃውሲንግ ፋይናንስ ሶሉሽን በአዲስ አበባ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ልዩ ቦታው ሃና ማሪያም ፍሬንድሺፕ ስቶር ፊትለፊት ባለ 15 ወለል ህንፃ አጠናቆ ለ150 ለዕድለኞች በዛሬው ዕለት አስተላልፏል።

ኪ ሃውሲንግ ፋይናንስ ሶሉሽን በአነስተኛ የገቢ ደረጃ የሚገኙ እና በተለመደው መንገድ የቤት ባለቤት መሆን ለማይችሉት የህብረተሰብ ክፍሎች በአነስተኛ ቅድመ-ክፍያ እና ከ 2ሺህ ብር በሚጀምር ዝቅተኛ ወርሃዊ ቁጠባ የቤት ባለቤት እንዲሆኑ ለማስቻል እየሰራ እንደሚገኝ ተነግሯል።

ድርጅቱ ከዚህ ቀደም በአዲስ አበባ ስድስት (6) ሳይቶች እና በባህር ዳር ከተማ በሁለት (2) ሳይቶች ዕድለኞችን የቤት ባለቤት ማድረጉን ተገልጿል።

ዩቱብ
https://youtube.com/?si=c6Wc8RignrUhSQp_

ቴሌግራም https://t.me/Habsha_Taem

ፌስቡክ https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL

ሊንክ ዲን https://www.linkedin.com/in/dj-fortin-k-ሐበሻ-ጣዕም-555600202

የዳሸን ሱፐር አፕ ደንበኞች ቁጥር ከአንድ ሚሊዮን በላይ ተሻገረ በኢትዮጵያ የባንክ ኢንዱስትሪ ፈር ቀዳጅ የሆነውን የዳሸን ሱፐር አፕ መተግበሪያ ያቀረበው ዳሸን ባንክ፣ የሱፐርአፕ ተጠቃሚዎቹ...
30/10/2025

የዳሸን ሱፐር አፕ ደንበኞች ቁጥር ከአንድ ሚሊዮን በላይ ተሻገረ

በኢትዮጵያ የባንክ ኢንዱስትሪ ፈር ቀዳጅ የሆነውን የዳሸን ሱፐር አፕ መተግበሪያ ያቀረበው ዳሸን ባንክ፣ የሱፐርአፕ ተጠቃሚዎቹ ቁጥር ከአንድ ሚሊዮን በላይ መሻገሩን አበሰረ፡፡

ዳሸን ባንክ አንድ እርምጃ ቀዳሚ መሆኑን ያሳየበትና “ሁሉን በአንድ” የሆነው የዳሸን ሱፐር አፕ አንድ ዓመት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በሚሊዮን የሚቆጠር ደንበኛና በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ዕለታዊ የገንዘብ ዝውውር እየተፈፀመበት ይገኛል፡፡

የዳሸን ሱፐር ንቁ ተጠቃሚዎች ቁጥር ከአንድ ሚሊዮን በላይ መድረሱን ምክንያት በማድረግ በዛሬው ዕለት በዳሸን ባንክ ዋና መሥሪያ ቤት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላደረጉ አካላትና የሥራ ክፍሎች የእውቅና አሰጣጥና የፓናል ውይይት መርሃግብር አዘጋጅቷል፡፡

በመርሃግብሩ ንግግር ያደረጉት የዳሸን ባንክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ አስፋው ዓለሙ፣ ዳሸን ሱፐር አፕ ይፋ በተደረገ አንድ ዓመት ውስጥ አንድ ሚሊዮን ተጠቃሚዎች ይኖሩታል የሚለውን ዕቅድ በዘጠኝ ወራት ብቻ ማሳካት መቻሉን ተናግረዋል፡፡አክለውም ዳሸን ሱፐር አፕ ደንበኞችን በልዩ ሁኔታና በአካታችነት አንድ እርምጃ ወደ ፊት የማራመድ ርዕይ ተልዕኮ መሆኑን አስረድዋል፡፡

“በኢትዮጵያ የዲጂታል ጉዞ ተከታይ ሳይሆን ቀዳሚ ሆነን እንደምንጓዝ ማሳየት ይገባናል“ ያሉት አቶ አስፋው፣ የዳሸን ሱፐር አፕን ላበለፀገው የኤግላይን ሲስተም ቴክኖሎጂ ለባንኩና ለአገር ለሚያደርገው አስተዋፅኦ ከፍተኛ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

ዩቱብ
https://youtube.com/?si=c6Wc8RignrUhSQp_

ቴሌግራም https://t.me/Habsha_Taem

ፌስቡክ https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL

ሊንክ ዲን https://www.linkedin.com/in/dj-fortin-k-ሐበሻ-ጣዕም-555600202

አዲሱን አዋጅ በተመለከተ የሲቪል ማህበራት ድጋፋቸውን ሰጡይህ የሰማነው የሲቪል ማህበራት የመራቢያ ጤና ማህበራት ጥምረት (CORHA)፣ የኢትዮጵያ የልብ ማህበር፣ የኢትዮጵያ የስኳር በሽታ ማህ...
30/10/2025

አዲሱን አዋጅ በተመለከተ የሲቪል ማህበራት ድጋፋቸውን ሰጡ

ይህ የሰማነው የሲቪል ማህበራት የመራቢያ ጤና ማህበራት ጥምረት (CORHA)፣ የኢትዮጵያ የልብ ማህበር፣ የኢትዮጵያ የስኳር በሽታ ማህበር እና የኢትዮጵያ የኩላሊት ማህበር የታሸጉ ምግቦችን ለመከላከል በተዘጋጀው አዋጅ ዙርያ በሰጡት መግለጫ ላይ ነው።

የጤናማ ያልሆነ አመጋገብ ቁጥጥር አዋጅ እንዲጸድቅ የሲቪል ማህበረሰቡ ከፍተኛ ድጋፍ ሰጠ

በኢትዮጵያ ጤናማ ያልሆነ አመጋገብ የሚያስከትለው የጤና ቀውስ እየተባባሰ በመምጣቱ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በጤናማ ያልሆነ አመጋገብ ላይ ቁጥጥር የሚያደርገው አዋጅ በጠንካራ ይዘት እንዲጸድቅ ጠንካራ ድጋፋቸውን አሳውቀዋል።

ተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች በአሁኑ ወቅት በአገር አቀፍ ደረጃ ከሚከሰቱ ሞት ውስጥ ከግማሽ በላይ (52%) የሚሆነውን ድርሻ ይይዛሉ።

የተላላፊ ያልሆኑ በሽታዎች ኢኮኖሚያዊ ሸክም ከባድ ሲሆን፣ የኢትዮጵያ መንግስትን በየዓመቱ 31.3 ቢሊዮን ብር እንደሚያስወጣ ይገመታል።

የኢትዮጵያ የምግብ አቅርቦት ሁኔታ በፍጥነት እየተለወጠ፣ በፋብሪካ የተዘጋጁ ምግቦች በስፋት እየተበራከቱ ነው።

ዓለም አቀፍ የምግብ ኩባንያዎች ጤናማ ያልሆኑ ምርቶቻቸውን በተለይም ለህጻናት በኃይል እያስተዋወቁ ይገኛሉ።

የሲቪል ማህበራት የመራቢያ ጤና ማህበራት ጥምረት (CORHA)፣ የኢትዮጵያ የልብ ማህበር፣ የኢትዮጵያ የስኳር በሽታ ማህበር እና የኢትዮጵያ የኩላሊት ማህበር የአዋጁ የመጨረሻ ረቂቅ የሚከተሉትን ዓለም አቀፍ ምርጥ ተሞክሮዎች እንዲያካትት አጥብቀው አሳስበዋል፡፡

ከእነዚህም መካከል ከዓለም ጤና ድርጅት (WHO) ምክረ ሃሳብ ጋር በሚስማማ መልኩ የኢንዱስትሪ ትራንስ-ፋቶችን ማስቀረት እንዲሁም ሸማቾች ስለ ምግቦች የንጥረ ነገር ይዘት (ስኳር፣ ጨው፣ ስብ) ግልጽና በቀላሉ ለመረዳት የሚያስችል መረጃ እንዲያገኙ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ተመላክቷል፡፡

ጤናማ ያልሆኑ ምግቦች ለህጻናት እንዳይተዋወቁ ሙሉ በሙሉ መከልከል እና ጠንካራ የቁጥጥር ስልቶችን መዘርጋት እንደሚያስፈልግ የተመላከተ ሲሆን፤ የመንግስት ተቋማት እና ትምህርት ቤቶች የጤና መስፈርቶችን የሚያሟሉ እና ከአገር ውስጥ የሚመነጩ የተመጣጠኑ ምግቦችን ብቻ እንዲያቀርቡ ማድረግ ያስፈልጋል ተብሏል፡፡

ዩቱብ
https://youtube.com/?si=c6Wc8RignrUhSQp_

ቴሌግራም https://t.me/Habsha_Taem

ፌስቡክ https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL

ሊንክ ዲን https://www.linkedin.com/in/dj-fortin-k-ሐበሻ-ጣዕም-555600202

አዲስ ኢንቨስትመንት ባንክ በይፋ ስራውን ጀመረበኢትዮጵያ ፋይናንስ ኢንዱስትሪ ውስጥ ፈርስት አዲስ ኢንቨስትመንት ባንከ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር (First Addis Investment ...
30/10/2025

አዲስ ኢንቨስትመንት ባንክ በይፋ ስራውን ጀመረ

በኢትዮጵያ ፋይናንስ ኢንዱስትሪ ውስጥ ፈርስት አዲስ ኢንቨስትመንት ባንከ ሃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር (First Addis Investment Bank - FAB) ከባንክ ግሩፕ ከሚቋቋሙ ውጪ ፈቃድ የተሰጠው የመጀመሪያው ኢንዲፔንደንት የኢንቨስትመንት ባንክ ሆኖ በይፋ ስራ መጀመሩን አስታወቋል፡፡

ተቋሙ በ28,000 ሚሊየን ብር መነሻ ገንዘብ በመነሳት የራሱ የዲሬክተሮች ቦርድ ያለው ሲሆን መመሪያው በሚጠይቀው መሰረት ብቃት ያላቸው 11 ባለሙያዎችን በመያዝ ወደ ስራ መግባቱን በይፋ አስታውቋል::

ፈርስት አዲስ ኢንቨስትመንት ባንክ ፍላጎት ተኮር የሆኑ የኢንቨስትመንት መፍትሄዎችን ለግለሰቦች፣ ለድርጅቶች እና ለመንግስት በማቅረብ የካፒታል ተደራሽነትን ማጎልበት እና ዘላቂ የኢኮኖሚ ልማትን ለማምጣት የተቋቋመ ባንክ ነው፡፡

በመግለጫው እንደተገለጸው ፈርስት አዲስ ኢንቨስትመንት ባንክ የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ለገበያ እንደ አዲስ በሚወጡበት ወቅት የማማከር እና የማሳለጥ አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን የተቋማትን ውሕደት እና ግዢ ማማከር ላይም እንደሚሰራ ተነግሯል

እንዲሁም የኢንቨስትመንት እና የኩባንያ ጥናትን መስራትየኩባንያ እና የሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ግመታን መስራትና አዲስ ካፒታል ማፈላለግ እና ማማከር ስራን ይሰራል ተብሏል

በቀጣይነትም ተጨማሪ መሟላት ያለባቸውን መስፈርቶችን በማሟላት በቅርቡ ወደ የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ (ESX) አገበያይ አባል (Trading Member) በመሆን ሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ለማገበያየት እቅድ ይዞ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል ተብሏል፡፡

ፈርስት አዲስ ኢንቨስትመንት ባንክ በኢትዮጵያ እና በተለያዩ ሃገራት ከፍተኛ ልምድ ባላቸው ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን አደራጆች የተቋቋመ ኢንዲፔንደንት ተቋም ነው።

ዩቱብ
https://youtube.com/?si=c6Wc8RignrUhSQp_

ቴሌግራም https://t.me/Habsha_Taem

ፌስቡክ https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL

ሊንክ ዲን https://www.linkedin.com/in/dj-fortin-k-ሐበሻ-ጣዕም-555600202

6 ዓመት የፈጀው የሀይሉ አመርጋ አልበም የፊታችን አርብ ጥቅምት 21 ቀን 2018 ዓ.ም ለአድማጭ ጆሮ ይደርሳል፡፡የቀድሞ የጃኖ ባንድ የሙዚቃ ቡድን አባል የነበረው ሀይሉ አመርጋ አሁን የተሰ...
29/10/2025

6 ዓመት የፈጀው የሀይሉ አመርጋ አልበም የፊታችን አርብ ጥቅምት 21 ቀን 2018 ዓ.ም ለአድማጭ ጆሮ ይደርሳል፡፡

የቀድሞ የጃኖ ባንድ የሙዚቃ ቡድን አባል የነበረው ሀይሉ አመርጋ አሁን የተሰኘ የመጀመሪያ የተናጥል አልበሙን ሰርቶ ማጠናቀቁን አሳውቋል፡፡

አልበሙ አንጋፋና ወጣት ባለሙያዎች የተሳተፉበት ሲሆን መጠኑን መግለጽ ባይቻልም ከፍተኛ ወጪ የወጣበት ነው ተብሏል፡፡

በአልበም ስራው ላይ ሚካኤል ሀይሉ(ሚኪ ጃኖ)፣ ብሩክ አፈወርቅ፣ በረከት ተስፋአፅቂ፣ ኤርሚያስ ሞላ እና ኢብራሂም በቅንብር፣ አበጋዝ ክብረወርቅ ሽዎታ እና ሮቤል ዳኜ በሚክሲንግና ማስሪንግ፣ ሀይሉ አመርጋ፣ አክሊሉ ገ/መድህንና ወንደሰን ይሁብ በግጥምና ዜማ ተሳትፈዋል፡፡

አልበሙ 13 ዘፈኖችን የያዘ ሲሆን ማህበራዊ ህይወት፣ ፍቅር፣ እምነት እና ተስፋ ላይ ያተኮሩ ይዘቶች ተካተውበታል፡፡

አልበሙ ውስጥ ካሉ ዘፈኖች ለሁለቱ የቪዲዮ ክሊፕ ተሰርቶ የተጠናቀቀ ሲሆን አልበሙ ከወጣ ከጥቂት ጊዜ በኋላ እንደሚለቀቁ እና ሶስት የሚሆኑ ዘፈኖቹ ደግሞ ገና እየተሰራላቸው እንደሚገኝ ድምጻዊው ገልጿል፡፡

አልበሙ ከጥቅምት 21 ጀምሮ በሀይሉ አመርጋ የዩቲዩብ ቻናል እና በዓለም አቀፍ ደረጃ በተለያዩ መተግበሪያዎች እንደሚገኝ ነው የተገለጸው፡፡

ዩቱብ
https://youtube.com/?si=c6Wc8RignrUhSQp_

ቴሌግራም https://t.me/Habsha_Taem

ፌስቡክ https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL

ሊንክ ዲን https://www.linkedin.com/in/dj-fortin-k-ሐበሻ-ጣዕም-555600202

ራዲያንስ ፌስት 2025 ተጀመረራዲያንስ ፌስት 2025 የተሰኘው በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የሀገር በቀል የውበትና የጤና ፌስቲቫል በሀያት ሬጀንሲ ሆቴል ተጀምሯል።በፌስቲቫሉ ላይ እንደተገለጸው ይ...
27/10/2025

ራዲያንስ ፌስት 2025 ተጀመረ

ራዲያንስ ፌስት 2025 የተሰኘው በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የሀገር በቀል የውበትና የጤና ፌስቲቫል በሀያት ሬጀንሲ ሆቴል ተጀምሯል።

በፌስቲቫሉ ላይ እንደተገለጸው ይህ ራዲያንስ ፌስት 2025 የግል ጤና አጠባበቅን ወደ ፊት የሚያራምድ፣ ከባህላዊ እስከ ዘመናዊ የኢትዮጵያ ጤና መጠበቂያ መንገዶችን የሚያጎላ የመጀመሪያው ፌስቲቫል ሲሆን በአዲስ ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር ከጥቅምት 21 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ ለሁሉም ክፍት ይሆናል፡፡

ፌስቲቫሉ የቆዳ እንክብካቤ፣ የዕፅዋት መድኃኒቶች፣ የአካል ብቃት፣ የአመጋገብ እና የውበት ዘርፎች ላይ የተሰማሩ የአገር ውስጥ አምራቾችን የሚያቀራርብ ሲሆን የተለያዩ የአገር ውስጥ ምርቶችም በአንድ መድረክ እንዲቀርቡ እድል ይሰጣል ተብሏል፡፡

ፌስቲቫሉ ውበት፣ ጤንነት እና ጥንካሬን መሰረት በማድረግ የተደራጀ ሲሆን የኢትዮጵያን ግብዓቶች የሚጠቀሙ የውበትና የጤና ምርቶች እንዲሁም ዓለም አቀፍ ደረጃዎችን በመከተል የተዘጋጁ አዳዲስ ምርቶች ይቀርቡበታል ፣የአካል ብቃት ማሳያዎች፣ የአመጋገብ ምክሮች እና ባህላዊና ዘመናዊ አቀራረቦችን በማቀናጀት መፍትሄ የሚሆኑ የጤና ልምምዶች እንዲሁም ፀጉርን ወደ ቀድሞ ቦታው ለመመለስ፣በሰው ሰራሽ መንገድ በጥርስ ህክምና ውበትን እስከማስተካከል የረቀቁ በአገር ውስጥ የሚሰጡ የሕክምና ዓይነቶች የሚቀርቡበት ነው።

ዩቱብ
https://youtube.com/?si=c6Wc8RignrUhSQp_

ቴሌግራም https://t.me/Habsha_Taem

ፌስቡክ https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL

ሊንክ ዲን https://www.linkedin.com/in/dj-fortin-k-ሐበሻ-ጣዕም-555600202

በጥቅምት አንድ አጥንት የስጋ ፌስቲቫል መካሄድ ተጀመረለ11ኛ ጊዜ የሚከናወነው በጥቅምት አንድ አጥንት የባህል እና የመዝናኛ ፌስቲቫል በዛሬው ዕለት በኤግዚብሽን ማዕከል ተከፈቷል።በሴንቸሪ ፕ...
25/10/2025

በጥቅምት አንድ አጥንት የስጋ ፌስቲቫል መካሄድ ተጀመረ

ለ11ኛ ጊዜ የሚከናወነው በጥቅምት አንድ አጥንት የባህል እና የመዝናኛ ፌስቲቫል በዛሬው ዕለት በኤግዚብሽን ማዕከል ተከፈቷል።

በሴንቸሪ ፕሮሞሽንና ኤቨንት አዘጋጅነት በቢጂአይ ኢትዮጵያ አጋርነት "በጥቅምት አንድ አጥንት" የተሰኘውን የአበው ባህል በአክብሮትና በክብር ተቀብሎ ባህል በማድረግ በየአመቱ የሚያዘጋጀው ፌስቲቫል በዛሬው እለት ለ11ኛ ጊዜ በኤግዚቢሽን ማዕከል የተከፈተ ሲሆን፣ ከዛሬ ጀምሮ እስከ ነገ ጥቅምት 16 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ ይካሄዳል፡፡

በመክፈቻ መርሐ ግብሩ ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ አመራሮች እና የሴንቸሪ ፕሮሞሽንና ኤቨንት ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ዘውገ ጀማነህን ጨምሮ ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

በፌስቲቫሉ ላይ የከተማችን እውቅ ልኳንዳ ቤቶችን በማሳተፍ ስጋ የሚሸጡበትን ዋጋ ግማሹን ደንበኞች እንዲከፍሉ በማድረግ እንዲገለገሉ እና እንዲዝናኑ ያለመ ፌስቲቫል ስለመሆኑ ተነግሯል።

በዚህም የመዝናኛ ኤግዚብሽን እንግዶች እየበሉ፣ እየጠጡ በባህላዊ ባንድ ተወዛዋዦች እየተዝናኑ ምሽቱን ካሳሁን እሸቱ፣ ሄለን በርሄን ጨምሮ ሌሎች የአገራችን እንቁ ድምፃዊያን የሙዚቃ ስራቸውን እንደሚያቀርቡ ተገልጿል።

ሴንቸሪ ፕሮሞሽን እና ኤቨንት ባለፉት 25 ዓመታት ከመንግስት ፣ መንግስታዊ ካልሆኑ ተቋማት ፣ ከም/ቤቶች ፣ ከማህበራት ዩኒየኖች እንዲሁም የግል ድርጅቶች ጋር በአጠቃላይ ከ 60 የሚበልጡ ሀገር አቀፍና አለም አቀፍ ዝግጅቶችን ለማዘጋጀት መቻሉን የድርጅቱ ዋና ስራአስኪያጅ አቶ ዘውገ ጀማነህ ገልጸዋል፡፡

አንድ ኪሎ ስፔሻል ቁርጥ የሚሸጠው በአንድ ሺህ ሁለት መቶ ብር ለደንበኞች እንደሚቀርብ ነው ለማወቅ የተቻለው።

ይህ ፌስቲቫል ህብረተሰቡን ከሩቅም ከቅርብም በአንድ ቦታ ተሰባስቦ አብሮ እየበላ እየጠጣ የሚተዋወቅበት እና አንድነቱን የሚያጠናክረበት እንደሚሆን ተገልጿል።

ዩቱብ
https://youtube.com/?si=c6Wc8RignrUhSQp_

ቴሌግራም https://t.me/Habsha_Taem

ፌስቡክ https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL

ሊንክ ዲን https://www.linkedin.com/in/dj-fortin-k-ሐበሻ-ጣዕም-555600202

የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት ከታምኮን ሶፍትዌር ሶሎሽንስ ጋር በመሆን የእንቁጣጣሽ ሎተሪ አሸናፊዎችን ሸለመ፡፡የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት ከታምኮን ሶፍትዌር ሶሎሽንስ ጋር በመሆን የእንቁጣጣሽ...
24/10/2025

የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት ከታምኮን ሶፍትዌር ሶሎሽንስ ጋር በመሆን የእንቁጣጣሽ ሎተሪ አሸናፊዎችን ሸለመ፡፡

የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት ከታምኮን ሶፍትዌር ሶሎሽንስ ጋር በመሆን የእንቁጣጣሽ ሎተሪ አሸናፊዎችን በዛሬው እለት ሸልሟል

ይህ ለሁለት ወራት ያህል በዲጂታል እና በወረቀት ሲሸጥ የቆየው የ"እንቁጣጣሽ ሎተሪ" የዕጣ ማውጣት ሥነ-ሥርዓት በስኬት ከተከናወነ በኋላ ዛሬ ለዕድለኞች የሚከተሉት ሽልማቶች ተሰጥተዋል፦

ታላላቅ የገንዘብ ሽልማቶች በዲጂታል እና በወረቀት ለገዙ ፦ 20 ሚሊዮን ብር፣ 10 ሚሊዮን ብር፣ 5 ሚሊዮን ብር፣ 2 ሚሊዮን ብር እና በርካታ የገንዘብ ሽልማቶች ለባለዕድለኛ ተበርክተዋል፡፡

እንዲሁም እንቁጣጣሽ ሎተሪን በዲጂታል ለቆረጡ ብቻ ልዩ የቦነስ ሽልማት- የBYD ተሽከርካሪ እና የኤሌክትሪክ ባጃጅ ለዕድለኞች ተሸልመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት ከታምኮን ሶፍትዌር ሶሉሽን ጋር በመተባበር ባሳለፍነው ዓመት አራት የሎተሪ ዘመቻን በዲጂታል በመሸጥ በስኬት ማጠናቀቁ ተገልጿል፡፡

የቀድሞው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ሎተሪ አስተዳደር የአሁኑ የኢትዮጵያ ሎተሪ አገልግሎት ለ65 ዓመታት ያህል ለበርካታ ኢትዮጵያውያን የደስታ እንዲሁም የለውጥና የዕድል ምንጭ ሆኖ አገልግሏል፡፡

አሁን ላይ ይህ ተቋም ከዘመኑ ጋር እኩል በመራመድ በቴክኖሎጂው እየታገዘ ሎተሪን በወረቀት ብቻ ሳይሆን በዲጂታል አማራጭ በማቅረብ ደንበኞቹ በየትኛውም ቦታ ሆነው በቀላሉ ዕድላቸውን እንዲሞክሩ አስችሏል ተብሏል፡፡

Nobody cared who i was till i put the mask on.

ዩቱብ
https://youtube.com/?si=c6Wc8RignrUhSQp_

ቴሌግራም https://t.me/Habsha_Taem

ፌስቡክ https://www.facebook.com/habeshatae?mibextid=ZbWKwL

ሊንክ ዲን https://www.linkedin.com/in/dj-fortin-k-ሐበሻ-ጣዕም-555600202

Address

Addis Ababa

Telephone

+251923484891

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሐበሻ ጣዕም/Habesha Taem posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ሐበሻ ጣዕም/Habesha Taem:

Share