Zerihun Endale

Zerihun Endale Ethiopia Music Tub6
Follow Like Share Subscribe
(1)

15/07/2025

❤️እኔ ወድሻለሁ❤️

የህይወት ጣዕሙ ቢሆንም እሬት
እድሜ ከሰጠኝ ካለሁ በመሬት
የህልሜ መንገድ ቢሆን አባጣ
ያሰብኩት ባይሆን ያለኝን ባጣ
ልቤ አይሸበር ውስጤ አይደነግጥ
የስኬቴ ቁልፍ አንቺ ነሽ በርግጥ
እውነት ውድዬ!
ካንቺ አይበልጥም የአለም ቁሳቁስ
ባታውቂው እንጂ
የህይወቴ ውድ አንቺ ነሽ እንቁስ
እኔ ወድሻለሁ!
ችጋር ቢገርፈኝ እንደ አለንጋ
ጭለማው ቀኔ ቢለኝ አልነጋ
እጣ ፈንታዬ ቢሆን መባዘን
የልቤን እልፍኝ ቢሞላው ሀዘን
መከራን ባይም ፍቅሬ አያንስም
ያበረታኛል ዘወትር ያንቺ ስም
እኔ ወድሻለሁ!
ህይወት ቢጥመኝ እንደ ጣዝማ ማር
ፊቴ ቢወዛ በኑሮ ማማር
ስኬቴን ባየው ከግብ ደርሼ
የማቱ ሳላን እድሜ ወርሼ
የድሌን ጽዋ ሁሌ ባጣጥም
አግኝቼ ብቆርጥ የገንዘብን ጥም
ደስታ ቢከበኝ ፍቅሬ አያንስም
በልቤ መዝገብ
ታትሞ ይኖራል ዘወትር ያንቺ ስም

አሼ ወንድሜ እንኳን ደስ አለክ ጋብቻችሁ የአብርሃም እና የሳራ ያርግላችሁመልካም ጋብቻ
12/07/2025

አሼ ወንድሜ እንኳን ደስ አለክ ጋብቻችሁ የአብርሃም እና የሳራ ያርግላችሁ
መልካም ጋብቻ

29/06/2025

በጣም አሳዛኝ እና አስተማሪ_ታሪክ ነው

በድህነት ውስጥ የሚኖር አንድ ቤተሰብ ነበር፡፡
በቤተሰቡ ውስጥ እናት፣ አባት እና አንድ ሴት ልጅ ነበረች፡፡

ከቤተሰቡ ውስጥ ገቢ የነበረው አባት ብቻ ነበር፤ ነገር ግን መሰረታዊ ፍላጎትን (ምግብ፣ ልብስ፣ መጠለያ) ለማሟላት በቂ አልነበርም፡፡
አባት ምንም እንኳን በቂ ገንዘብ ባይኖረውም ሁሌም
የሚያልመው ልጁን የአለማችን ምርጥ ዶክተር ማድረግ ነበር፡፡ እጅግ
ከሚባለው በላይ ይወዳታል፡፡ እሷም መልካም ልጅ ነበረች፡፡

የHigh School ውጤቷን በተቀበለችበት ቀን አባት
ከሚባለው በላይ በመደሰቱ "ዛሬ በአንቺ ኩራትና ደስታ
ተሰምቶኛል፤ እንድገዛልሽ የምትፈልጊውን ማንኛውንም ነገር ጠይቂኝ" አላት፡፡ ልጅ መለሰች አባ ባለፈው ያሳየውህን ቀሚስ እፈልጋለው፤ ግን
ዋጋው 1500Dollar ነው፤ የዛኔ እንድትገዛልኝ
አልጠየኩህም፤ ነገር ግን አሁን ትገዛልኛለህ?" አለች፡፡

አባት በመደሰቱ እና ልጁ ተከፍታ ማየት ስለማይፈልግ ብቻ
ያን ቀሚስ የሚገዛ ገንዘብ እንደሌለው እያወቀ እንኳን እንደሚገዛላት ቃል ገባ፡፡ በቀጣዩ ቀን አባት ያንኑ ቀሚስ ገዝቶ ስጦታ ሰጣት፡፡
እናት ይህን ስትመለከት ያን ያህል ገንዘብ እንደሌለው
ስላወቀች ገንዘቡን ከየት እንዳመጣው ጠየቀችው፡፡

አባት እንዲህ ሲል ተደመጠ "ያጠራቀምኩት ትንሽ ገንዘብ
ነበር፤ በተጨማሪ ደሜን ሸጬ ባገኘውት ገንዘብ ነው፡፡
ምክንያቱም ልጄን ማናደድ አልፈልግም፡፡ "ከግዚያት በኀላ
ልጁ የጤና ትምህርት ቤት ገባች፡፡

አባትም ለእሷ የሚያስፈልጉ ክፍያዎችን መክፈል ያስችለው ዘንድ
ከወትሮው በበለጠ ጠንክሮ መስራት ጀመረ፡፡
የመጨረሻ አመቷ ላይ ደረሰች፡፡ ለሁሉም ነገር የሚከፈል
80000 Dollar ያስፈልጋታል፡፡

አባት በቂ ገንዘብ ባይኖረውም እንዴት እንደሆነ ባይታወቅም ያን ገንዘብ
ከፈለ፡፡ እናት አሁንም ያን ያህል ገንዘብ እንደሌላቸው ስለምታውቅ በጥርጣሬ "ያን ገንዘብ ከየት ነው ያመጣኸው? ያን ገንዘብ ለማግኘት መጥፎ ነገር አደረክ

እንዴ?" በማለት ጠየቀች፡፡
"አይደለም የሆነ ኩላሊቱ ከጥቅም ውጭ የሆነበት ሰው
ነበረ፤ እና አንዱን ኩላሊቴን ሸጥኩለት፡፡

አደራ ለልጃችን እንዳትነግሪያት፤ የጥፋተኝነት ስሜት ይሰማታል፡፡" አለ አባት፡፡ ዛሬ የልጃቸው የመመረቂያ ቀን ነው፡፡

እናትና አባት ሴት ልጃቸው ለመጀመሪያ ግዜ ዶክተር ሆና ወደ ቤቷ ልትመጣ በጉጉት እየጠበቋት ነው፡፡ ነገር ግን ልጃቸው ዶክተር ሆና
ሳይሆን አስከሬን ሆና ወደ ቤት መጣች፡፡

የምታፈቅረው ሰው በእሷ ላይ ከሌላ ሴት ጋር ስለማገጠባት ራሷን
አጠፋች፡፡ እስቲ መልሱልኝ አሁን የሞተው ማነው? እሷ ወይስ ቤተሰቦቿ? በተለይ አባቷ የሞት ሞትን ነው የሞተው፡፡
-ወዳጄ ህይወትክ ያንተ ብቻ መስሎህ ከሆነ ተሳስተሀል፡፡

መኖርህ እንኳን ባይጠቅማቸው መሞትክ የሚጎዳቸው ቤተሰቦች አሉህ፡፡ ስለዚህ እራስህን በሲጋራ፣ ጫት፣ አልኮል ውስጥ ደብቀህ
በቁም ሞተህ በቁም አትቅበራቸው፡፡ እህቴ፤ አንቺ እራስሽን ብታጠፊ ፍቅረኛሽ ሌላ ሴት ያገኛል፤ ቤተሰቦችሽ ግን ሌላ ልዕልት ልጅ አያገኙም፡፡

ስለዚህ ሁሌም በህይወታችን ላይ ለመወሰን ስንነሳ እኛን በማሳደግ የጎበጠችው እናታችን ፤ እኛን በማሳደግ በውርጭና በፀሀይ ፊቱ የከሰመው አባታችን ይታወሱን

24/06/2025

💔 ህይወት ለማንም ነፃ ትምህርት አትሰጥም "ህይወት አስተማረኝ" ስትል ዋጋ እንደከፈልክ እርግጠኛ ሁን!።

🐅ስለዚህ ጀግናው ከእያንዳንዱ ዋጋህ ተማር🐅

23/06/2025

አፍቅሬሺ ነውጂ አይደለም አብጄ መኖር እቺላለሁ አዲስ ሰው ለምጄ

23/06/2025

ልረሳሽ ብጠጣ አይኔ እየሰከረ
ጭራሽ ሁለት አርጎሽ 😍
ያሳየኝ ጀመረ 🤗🤗

22/06/2025
1 ሩሐማ፦ምሕረት ማለት ነው።2 ዮዳሔ፦እግዚአብሔር ያውቃል ማለት ነው።3 ቴዎፍሎስ፦የእግዚአብሔር ወዳጅ ማለት ነው።4 ኑኃሚን፦ደስታየ ማለት ነው።5 ናትናኤል፦የእግዚአብሔር ስጦታ ማለት ነው።6...
21/06/2025

1 ሩሐማ፦ምሕረት ማለት ነው።
2 ዮዳሔ፦እግዚአብሔር ያውቃል ማለት ነው።
3 ቴዎፍሎስ፦የእግዚአብሔር ወዳጅ ማለት ነው።
4 ኑኃሚን፦ደስታየ ማለት ነው።
5 ናትናኤል፦የእግዚአብሔር ስጦታ ማለት ነው።
6 አዛሄል፦እግዚአብሔር ያያል ማለት ነው።
7 ኢዮስያስ፦እግዚአብሔር ይደግፋል ማለይ ነው
8 ኢዩኤል፦እግዚአብሔር አምላክ ነው ማለት ነው።
9 በርናባስ፦የመጽናናት ልጅ ማለት ነው።
10 ሶፎንያስ፦እግዚአብሔር ሰውሯል/ጠብቋል ማለት ነው።
11 ሕዝቅኤል፦እግዚአብሔር ብርታትን ይሰጣል ማለት ነው።
12 ኬልቅያስ፦እድል ፈንታየ እግዚአብሔር ማለት ነው
13 ሳሙኤል፦እግዚአብሔር ሰማኝ ማለት ነው።
14 ሚኪያስ፦ እንደ እግዚአብሔር ያለ ማን ነው! ማለት ነው።
15 ሆሴዕ፦እግዚአብሔር ያድናል ማለት ነው።
16 ሔዋን፦የሕያዋን ሁሉ እናት ማለት ነው።
17 ሕዝቅያስ፦እግዚአብሔር ኃይሌ ነው ማለት ነው።
18 መልከጼዴቅ፦የሰላም ንጉሥ ማለት ነው።
19 ሚልኪያስ፦መልእክተኛየ ማለት ነው።
20 ሣራ፦ልዕልት ማለት ነው።
21 ስምዖን፦ሰማ ማለት ነው።
22 ብንያም፦የቀኝ እጄ ልጅ ማለት ነው።
23 ናሆም፦መጽናናት ማለት ነው።
24 ናታን፦ እግዚአብሔር ሰጥቷል ማለት ነው።
25 አልዓዛር፦እግዚአብሔር ረድቷል ማለት ነው።
26 አስቴር፦ኮከብ ማለት ነው፣
27 አቤሜሌክ፦የንጉሥ አገልጋይ ማለት ነው።
28 አቤሴሎም፦አባቴ ሰላም ነው ማለት ነው።
29 አብድዩ፦የእግዚአብሔር አገልጋይ ማለት ነው።
30 አብራም፦ታላቅ አባት ማለት ነው።
31 አብርሃም፦የብዙዎች አባት ማለት ነው
32 አኪያ፦እግዚአብሔር ወንድሜ ነው ማለት ነው።
33 አክዐብ፦የአባት ወንድም ማለት ነው።
34 ባሮክ፦ቡሩክ ማለት ነው።
35 አዳም፦መልካሙ ማለት ነው።
36 ኢሳይያስ፦ እግዚአብሔር ደኅንነት ነው ማለት ነው።
37 ባርቅ፦መብረቅ ማለት ነው።
38 ኢያሱ፦እግዚአብሔር አዳኝ ነው ማለት ነው።
39 ኢዮሳፍጥ፦እግዚአብሔር ፈርዷል ማለት ነው።
40 ኢዮራም፦እግዚአብሔር ከፍ ከፍ አለ ማለት ነው።
41 ኢዮርብዓም፦ሕዝቡ እየበዛ ይሄዳል ማለት ነው።
42 ቤተልሔም፦የእንጀራ ቤት ማለት ነው።
43 ኢዮአስ፦እግዚአብሔር ሰጥቷል ማለት ነው።
44 ኢዮአቄም፦እግዚአብሔር አቆመ ማለት ነው።
45 ኢዮአብ፦እግዚአብሔር አባት ነው ማለት ነው።
46 ኢዮአታም፦እግዚአብሔር ፍጹም ነው ማለት ነው።
47 ኢዮአካዝ፦እግዚአብሔር ይዟል ማለት ነው።
48 ኤልሳዕ፦እግዚአብሔር ደኅንነት ነው ማለት ነው።
49 ኤልያስ፦እግዚአብሔር አምላክ ነው ማለት ነው።
50 ኤልያቄም፦እግዚአብሔር ያስነሳል ማለት ነው።
51 ኤዶም፦ቀይ ማለት ነው
52 እስራኤል፦ከእግዚአብሔር ጋር ይታገላል ያሸንፍማል ማለት ነው።
53 ኤልሳቤጥ፦እግዚአብሔር መሐላየ ነው ማለት ነው።
54 ኤልሻዳይ፦ሁሉን ቻይ አምላክ ማለት ነው።
55 ሀሌሉያ፦እግዚአብሔርን አመስግኑ ማለት ነው።
56 ሰሎሞን፦ሰላማዊ ማለት ነው።
57 ኬብሮን፦ኅብረት ማለት ነው
58 አዛርያስ፦እግዚአብሔር ረድቷል ማለት ነው።
59 ኤደን፦ደስታ ማለት ነው።
60 ዖዝያን፦እግዚአብሔር ኃይሌ ነው ማለት ነው።
61 ዘካርያስ፦እግዚአብሔር ያስታውሳል ማለት ነው።
62 ይሳኮር፦ ዋጋዬ ማለት ነው
63 ይዲድያ፦በእግዚአብሔር የተወደደ ማለት ነው።
64 ዮሐናን፦እግዚአብሔር ጸጋ ሰጪ ነው ማለት ነው።
65 ዮሐንስ፦እግዚአብሔር ጸጋ ነው ማለት ነው።
66 ዮሴፍ፦ይጨምር ማለት ነው።
67 ዮናስ፦ርግብ ማለት ነው።
68 ዮናታን፦እግዚአብሔር ሰጥቷል ማለት ነው።
69 ዮአኪን፦እግዚአብሔር ያቆማል ማለት ነው።
70 ዮካብድ፦እግዚአብሔር ክብር ነው ማለት ነው።
71 ምናሴ፦ማስረሻ ማለት ነው።
72 ዮፍታሔ፦እግዚአብሔር ይከፍታል ማለት ነው።
73 ዲቦራ

21/06/2025

✍️
ለአንድ ዉሻ🐅 ሶስት ቀን ምግብ ብታበላዉው ለ ሶስት ዓመት ያስታውስሃል ለአንድ ሰው 🚶‍♂️ሶስት ዓመት ምግብ ብታበላው በ ሶስት ቀን ይረሰሃል።
እናም ከሰዎች ብዙ አትጠብቅ ...

21/06/2025

እናት ማጣት ምን ማለት እንደሆነ የሚያውቆው እናቱን ያጣ ሰው ነው 🙏

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Zerihun Endale posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Zerihun Endale:

Share