Buche Yogo

Buche Yogo Make better life for You !

ክፍል IX8. አቶ ደስታ ሌዳሞ የክልሉ ፕሬዝዴንት ኃላፍነትዘር በማጥፋትና በዞኑ በስድስት ከተሞች በመቶ ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት ውድመት እንድደርስ  በማድረግ፤ ግለሰቡ ከ2011 ጥር ወ...
02/01/2026

ክፍል IX

8. አቶ ደስታ ሌዳሞ የክልሉ ፕሬዝዴንት ኃላፍነት
ዘር በማጥፋትና በዞኑ በስድስት ከተሞች በመቶ ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት ውድመት እንድደርስ በማድረግ፤
ግለሰቡ ከ2011 ጥር ወር ጀምሮ በቀድሞው ሲዳማ ዞን በአሁኑ ሲዳማ ክልል በሀዋሳ ከተማ "ፖጉማ" የተባለ ህገ ወጥ ቡድን አደራጅቶ በወቅቱ ሲዳማን ሲያስተዳድሩ የነበሩትን አመራሮች ገልብጦ ሥልጣን ለመያዝ ሲያሰር ቆይቶ ሀምሌ 11/11/2011 በዞኑ በሁሉም አካባቢ ግጭት እንዲቀሰቀስ በማድረግ በዚህ ግጭት ብቻ በዕለቱና በተከታታይ ቀናት 156 ንጹሀን ዘጎች እንዲሞቱንና በዞኑ በሰላም ሰርተው የሚኖሩ ግለሰቦችን ብሄር ተለይቶ ንብረት እንድወድም አሰደርጓል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በወቅቱ በዞኑ የተቀሰቀስውን ውጥረት ለማርገብ እራሱ በተወለደበት ወደ ማልጋ ወረዳ እየተንቀሳቀሱ የነበሩ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላት ላይ ጉዳት እንድደርስ አውራ ጎዳና ተቆፍሮ መንገድ ላይ መሰናክል እንድፈጠር በማስደረግ በዕለቱ ቁጥራቸው በርካታ የሆኑ የመከላከያ ሠራዊት አባላት መኪናው በተቆፈረው ጉድጓድ ውስጥ በመግባት ተገልብጦ እንዲያልቁ አስደርጓል፤፡
በመሆኑም ግለሰቡ ለሥልጣን ባለው ጫፍ የወጣ ጥማት ምክኒያት በርከት ያሉ ሰዎች እንዲሞቱ በዞኑ ለተከሰተው ሰብዓዊና የንብረት ጉዳት ግንባር ቀደም ተጠያቂ ነው፡፡በዕለቱ የተከሰተውን ግጭት ሀዋሳ ከተማ ሆኖ ወጣቶች ማስተር ማይንድ(Master Mind) ሆኖ ሲመራ በዕለቱ በደኅንነት ኃይሎች ተደርሶበት በቀድሞው ደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ለአንድ ቀን ታስሮ መለቀቁም ይታወሳል፡፡በዕለቱ ለተፈጠረው ግጭትና የንብረት ውድመት ተጠያቂው እሱና የቡድኑ አባለት ስለሆኑ ተገቢው ምርመራ ተካሂዶ በህግ እንድጠየቅ እንዲደርግ እንጥይቃለን::
በክልሉ ውስጥም ሥልጣኑን ያለ አግባብ በመጠቀምና ለሌሎችም ለዝርፊያ በር በመክፈት አንደኛ ተዋናይና መሪ መሆኑ ማሳያዎች ብዙ ናቸው:: ለምሳሌም ከጀርመን መንግስት ለሀዋሳ ቴክኒክና ሙያ ተቋም የተላከውን ግዙፍ ማሽን ከሥራ ባለደረቦቹ ጋር በመመሳጠር በ2012 ዓ/ም እንደተሰረቀ በማስመሰል ሽጦ ተጠቅሟል፤ማሽኑ የተላከው ለወጣቶች የሙያ ስልጠና እንዲያግዝ ቢሆንም የተሰጠውን የህዝብና መንግስት አደራ ወደ ጎን በመተው እራስን ለማበልጸግ ባለው ጽኑ ፍላጎት የህዝብን ጥቅም የጎዳ በመሆኑ ተገቢ ምርመራ ተካሂዶ በህግ አንዲጠይቅ እንድደረግ እንጥይቃለን::
በ2012 ዓ/ም በሰኔ ወር መጨረሻ ለሠላሳ ስድስት ባለ ሀብቶች ከአንድ ሚሊዮን እስከ ሁለት ሚሊዮን ጉቦ ስብስቦ በመውሰድ የእሸት ቡና ፍቃድ አሰጣጥ መመሪያና ደንብ ባልተከተለ ሁኔታ በሁሉም ቡና አብቃይ ወረዳዎች ፍቃድ ሰጥቷል:: የእሸት ቡና እንዱስትሪ ፍቃድ አስጣጥ አካባቢው የነዋሪዎችን ደኅንነት ለጤና ጉዳት በማያደርስ ሁኔታ መሆን ያለበት ቢሆንም ከዚያነ ጊዜ ጀምሮ በተመሳሳይ ሁኔታ እየተሰጠ በመሆኑ ይህም ከግንዛቤ ውስጥ በማስገባት ተገቢው የማጣራት ሥራ ተሠርቶ ውጤቱ ለህዝብ ይፋ መደረግ አለበት:: በዚህ ምክንያት እስካሁን በዜጎች ላይ የደረሰውንም የጤና ጉዳት ግምት ያስገባ ምርመራ እንዲካሄድም ጭምር እንጠይቃለን::
በተጨማሪም አቶ ደስታ ለዳሞ ሥልጣኑን ያለአግባብ በመጠቀም ከእነዚህ ነጋዴዎች ጋር በመመሳጠር ለራሱ ስድሰት የእሸት ቡና እንዱስትሪ ፍቃድ በመውስድ እያስነገደ ይገኛል::የራሱ የቡና እንዲስትሪ ያሉባቸወ ወረዳዎችም ወንሾ:ሆኮ: በንሳ: ቡራ: እና አለታ ወንዶ ወረዳ መሆኑንና ከአቶ ወርቁ ቡቼ: ከአቶ ንጉሴ ገመዳ: ከአቶ ማቴዎስ ደንኤልና ከአቶ ለገሠ ላሚሶ ከተባሉ ባለሀብቶች ስም እንደሚነግድም ፍንጭ እየሰጠን ተገቢው ምርመራ እንዲካሄድ እንጠይቃለን፡፡
ስልጣኑን ያለአግባብ በመጠቀም የመሬት ሊዝ አዋጅ 721/204ን በመተላለፍ በሀዋሳ ከተማ በልማት ተነሺዎች ስም ስድስት ሺህ (6000) ካሬ ሜትር መሬት በዘመዶቹ ስም ወስዷል፡፡በራሱም ስም ደግሞ ሶስት ሺህ (3000) ካሬ ሜትር መሬት በድምሩ 9000 ካሬ ሜትር መሬት ወስዷል፡፡በእነማን ስም እንደሆነ ከዚህ ማመልካቻ ጋር አባሪ አድርገናል ማዬት ይቻላል፡፡ከዚህ ጋር በተያያዘ በሀዋሳ ከተማ የከተሞች መሬት አሰጣጥ ህግ በመጣስና ሆን ብሎ ግለሰቦችን ለመጥቀም ሲባል ለፓስተሮች እና ለወዳጅ ዘመዶች በርካታ ካሬ ሜትር መሬት እንድታደል በማድረግ የከተማው ማዘጋጃ ቤት የህግ ጥሰት እንድፈጽም አሰደርጓል፡፡ይህም ሥልጣንን ያለአግባብ በመጠቀም የተደረገ ስለሆነ በተገቢው እንዲጣራ እንጠይቃለን፡፡
በ2017 ዓ/ም የእሸት ቡና ዘመን የአርሶ አደሩ ቡና በወረደ ዋጋ እንዲገዛ ትዕዛዝ ለዞኖችና ለወረዳዎች በማስተላለፍ ለውለታው ቡና ነጋዴዎች ኮሚቴ አቋቁመው ከፍተኛ ብር ሰብሰበውለት በሀገረ አሜሪካ በሲያቲል ግዛት ቅንጡ መኖሪያ ቤት እንደተገዛለት በብዙ ታማኝ ምንጮች እየተዘገበ ይገኛል፡፡ይህም በህገ ወጥ መንገድ የተገኘ ሀብት ስለሆነ በህግ አግባብ ተጣርቶ ለህዝብ ግልጽ መደረግ አለበት፡፡ ለዝሁና ለመሳሰሉት ብልሹ አሠራር ገንዘብ ያሰባሰቡ ሰዎች ስም ዝርዝር ምርመራው ሲጀመር ለመርማሪ ቡድን የምናሳውቅ ይሆናል፡፡

ክፍል X ይቀጥላል::

01/01/2026
ክፍል  VIII      7.  የክልሉ አመራር ሁኔታየሲዳማ ከክልል አመራር በሶስት ደረጃ ይከፈላል:: የመጀመሪያዎቹ ተርታ የሚገኙት ለክልሉ ፕረዚደንት ለአቶ ደስታ ሌዳሞ እና ለብልፅግና ፓርት...
01/01/2026

ክፍል VIII

7. የክልሉ አመራር ሁኔታ
የሲዳማ ከክልል አመራር በሶስት ደረጃ ይከፈላል:: የመጀመሪያዎቹ ተርታ የሚገኙት ለክልሉ ፕረዚደንት ለአቶ ደስታ ሌዳሞ እና ለብልፅግና ፓርት ጽ/ቤት ኃላፊ ለአቶ አብርሀም ማርሻሎ ታማኝነታቸው የተረጋገጠላቸው ሥራውችን የሚመሩት ህጋዊ አሠራርን ብቻ ተከትለው ሳይሆን ህገ ወጥ ተግባራትም ስታዘዙ ለምን ሳይሉ በቀጥታ እንደወረደ የሚከውኑ ሲሆኑ እነዚህ በክልሉ በከፍተኛ ሌብነት ቅሌት ውስጥ የገቡም ናቸው፡፡ ከእነዚህ መካከል ቀድሞ በዘመነ ኢህአዴግ በሥርቆትና በስነ ምግባር እንዱሁም በጎሰኝነት የተባረሩ ሲሆን ከላይ ከተጠቀሱት ቁንጮ አመራሮች ጋር ህገ ወጥ ቡድን በማቋቋም በወቅቱ በአመራርነት የነበሩትን አፈናቅለው ሥልጣን የተቆናጠጡና ከእነርሱም ጋር ተመሳሳይ ስነ ልቦና ያላቸው ናቸው፡፡
የተቀሩት ደግሞ አቶ ደስታ ሌዳሞ እና አቶ አብርሀም ማርሻሎ ወደ ሥልጣን ከመጡ ቦኃላ ለራሳቸው ሌብነት እንዲመቹ አድርጎ የሠሩኣቸው ናቸው፡፡እነዚህም በከፍተኛ የሙስና ቅሌት ውስጥ የገቡና ከፖጉማዎቹ ዕኩል ከእነርሱ ጋር የተወዳጁ ናቸው፡፡
በሁለተኛ ተርታ የሚሠለፉ አመራሮች ደግሞ ለስሙ የተማሩ የሚባሉ ነገር ግን በጎሳ ኮታ ብቻ አመራር የተደረጉ ለደስታ ብዙም ሩቅ ብዙም ደግሞ ቅርብ ያልሆኑ ሲፈለጉ ብቻ የሚጠሩ አመራር ሲሰጣቸውም ሳያንገራግሩ የሚከውኑ ለመንግስት አሠራርና ለህዝብ ምንም የማይጨነቁ ለወንበራቸውና ለግል ምቾት ብቻ የሚኖሩ ናቸው፡፡
በሶስተኛ ተርታ የሚሠለፉት ደግሞ በቁንጮ አመራሮች የማይወደዱ ከተቻለም ሰበብ ተፍልጎ ለማባረር የተዘጋጁ በተለይም አቶ ደስታ የሚያውቃቸው ነገር ግን የማያናግራቸው ልክ እንደባለሙያ የሚታዩ ሲሆን እነዚህ አመራሮች ህዝባዊ ወገንተኝነት ያላቸውም ናቸው:: የአቶ ደስታ እና የአቶ አብርሀም ማርሻሎን አመራር ለሚቃወሙት ከውስጥ ሆኖ መረጃም የሚያሾልኩ በክልሉ አመራር በሚፈጽመው ተግባር ደስተኛ ያልሆኑ ናቸው፡፡
በአሁኑ ሰዓት በመጀመሪያ ድረጃ የሚመደቡ አመራሮች ከተቻለ አለቆቻቸውን አድነው የራሳቸውን ሥልጣን ለማሰንበት ወደ ፈደራል በመመላለስ ላይ ይገኛሉ:: በሁለተኛና በሶስተኛ ደረጃ የሚገኙ አመራሮች በመስቀለኛ መንገድ ቆመው ይገኛሉ፡፡በተለይም አቶ ደስታ ሌዳሞና አቶ አብርሓም ማርሻሎ ከኃላፊነት ይነሳሉ የሚል ወረ ከተሠራጨ ጀምሮ በሁለተኛ ደረጃ የሚገኙት ወደት እንደሚወድቁ ግራ የገባቸው ይመስላል፡፡በሶስተኛ ደረጃ የሚገኙት ደግሞ የአባላት የትግል አካል ለመሆን እየተንደደሩ ይገኛሉ፡፡
ሲጠቃለል የሲዳማ ክልል አመራር በተለይም አቶ ደስታ ሌዳሞና አቶ አብርሃም ማርሻሎ ካለፈው የጥቅምት ወር አጋማሽ ጀምሮ ከኃላፊነት የተነሡ መሆኑ በክልሉ ከዳር አስከ ዳር እየተወራ ቆይቷል፡፡በግለሰቦቹ ላይ እየተወራ ያለው ከነባራዊ ሁኔታ ጋር ተደምሮ ነገሩን ወደ እወነታነት የተቃረበ የሚያስመስሉ ብዙ ነገሮች ይስተውላሉ፡፡አንዱና ዋነኛው ራሳቸውን ጥቅም እንዲያስፈጽምላቸው በብርሃን ፍጥነት የሾሙት የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ በፌዴራል መንግስት ጣልቃ ገብነት ከቦታው እንዲነሳ ተደርጎ ለከተማው የሚመጥን ሰው መሾሙ ሲሆን ይህም የአቶ ደስታ ሌዳሞ እና የአቶ አብርሀም ማርሻሎ በከተማዋ ላይ ያለው የጠልቃ ገብነት ሥልጣን ማክተሙ ያሳያል፡፡ በአሁኑ ሰዓት በሲዳማ ክልል ያለው ነባራዊ ሁኔታ እና በሕዝብ ዘንድ ያለው አመነታ አቶ ደስታ ሌዳሞና አብርሀም ማርሻሎ ከስልጣን እንደተነሡ ነው፡፡
በሌላ በኩል እነ ደስታ ሌዳሞ በሥልጣን ላይ ለመሰንበት በለመዱት መንገድ የሲዳማ ሀገር ሽማግሌዎችንና የኦሮሚያ አባገዳዎችን እርስዎን እንድያማለዱአቸው ወደ አዲስ አበባ በመላክ ተጠምደው ይገኛሉ፡፡ እነዚህ የሀገር ሽማግሌዎችና አባገዳዎች ለምልጃ ወደ እርሰዎ መጥተው የብልጽግና ፓርቲ ውሳኔ ያሽራሉ የሚል እምነት ባይኖረንም በተሰጣቸው ኦሬንቴሽን መሠረት "አቶ ደስታ ከክልሉ ከተነሳ ክልሉ እንዳማይረጋጋና ሌላ ከደስታ የተሻለ ሰው ከዬት ይመጣል?" በማለት ከውጪ በማስወራት በእነዚህ ግለሰቦች ላይ የተያዘው አቋም ይሸረሸራል የሚል ስጋት ግን ይኖረናል፡፡በእኛ እምነት ሌላ እሱን የሚተካ ሰው ጠፍቶ እንኳን በሲዳማ ክልል ደስታ ርዕስ መስተዳድር ሆኖ ከሚቀጥል ክልሏ ያለ ርዕሰ መስተዳደር ብትኖር የተሻለ መረጋጋተና ሰላም ይኖራል ብለን እናምናለን፡፡
የተከበሩ ጠ/ሚኒስትር
የክልሉን ነባራዊ ሁኔታ ለማጣራት ከፈለጉ ከጥቁር ውሀ አስከ ጭሬ ድረስ በስውር ሰው አሰማሩና ሲዳማ ያለበትን ሁኔታ ዳሰሳዊ ጥናት ያደርጉ አውነታነቱን ይበልጥ ያረጋግጣሉ፡፡ በአጠቃላይ በአሁኑ ጊዜ የክልሉ አመራር ቁመና በተለይም በአለቆቻቸው ላይ ተሰፋ በመቁረጥ የሚመጣውን በጸጋ ለመቀበል የተዘጋጁ ይመስላሉ፡፡በመሆኑም በአሁኑ ሰዓት በክልሉ ከወረ ሌላ ስራ እየተሠራ ባለመሆኑ የፌዴራል መንግሥት በክልሉ ያለውን አመራር በአስቸኳይ አንዲያነሳልንና በምትካቸው የሲዳማን ህዝብ ንጽህና መምራት በሚችሉ እንዲተካልን አጥብቀን እንጠይቃለን፡፡ለግንዛቤ እንድረዳዎ ምንም እንኳን ከዚህ በፊት ለእርስዎም ሆነ ለሌሎች ጉዳዩ ለሚመለከታቸው ክፍሎች የደረሰ የክልሉ ቁንጮ አመራሮች የዝርፊያና የሌብነት ቅሌት ከዚህ በታች ለማያያዝ ሞከረናል፡፡ይመልከቱ::

ክፍል VIIII ይቀጥላል::

ክፍል  VII 6. በሲዳማ ክልል የመንግሥት ሠራተኛ ሁኔታ በአጭሩ: እንደማንኛውም አካባቢ ዘጎች በክልሉ የሚገኙ መንግስት ሠራተኞች የተለያየ ፖለቲካ አመለካከት ያላቸው በመሆኑ በመንግስት ላይ...
31/12/2025

ክፍል VII

6. በሲዳማ ክልል የመንግሥት ሠራተኛ ሁኔታ በአጭሩ:

እንደማንኛውም አካባቢ ዘጎች በክልሉ የሚገኙ መንግስት ሠራተኞች የተለያየ ፖለቲካ አመለካከት ያላቸው በመሆኑ በመንግስት ላይ ያላቸው አመለካከትም ይለያያል፡፡ለአመራሩ ቅርቤት ያላቸው ሰራተኞች ከአመራሩ የሚወረወርላቸውን ፍርፋሪ ስለሚለቃቅሙ በአመራሩ የሚፈጸመውን ማንኛውንም ህገ ወጥ ተግባር የማይታገሉ ጸጥ ለጥ ብለው ለአመራሩ እያሸረገዱ የሚኖሩ እንዳሉ ሁሉ ሌሎች ደግሞ በአንጻሩ በአመራሩ የሚፈጸመውን ሌብነትና ዘረፋ በግላጭ ስለሚታገሉ በአመራሩ የሚገፉ: ጥቅማ ጥቅምና የተለያዩ ዕድገቶች ሁሉ የሚታገዱና ከሥራ ያለ በቂ ምክንያት የሚፈናቀሉ እየተበራከቱ የመጡበት ክልልም ሆኗል፡፡
በአንጻሩ ደግሞ ምንም የማይሞቃቸውና የማይበርዳቸው ወደነፍሰበት የሚነፍሱ የመንግሥት ሠራተኞችም ይኖራሉ ፡፡በክልሉ ባለፈው ዓመት ከሁሉም የመንግስት ሠራተኞች የብልጽግና ፓርቲ ህንጻ ግንባታ ተብሎ መዋጮ እንድከፍሉ መመሪያ ተላልፎ የነበረ ሲሆን በብዙ አካባቢዎች ተቃውሞ ገጥሞትም እንደነበር ይታወሳል፡፡የሆነ ሆኖ በአብዘኛዎቹ ወረዳዎች መዋጮ ተሳክቶ የህንጻ ግንባታ ተጠናቅቆ ለምረቃ የደረሰ ቢሆንም መዋጮው በሶስት ዓይነት መንገድ የተሰበሰበ መሆኑ ግን መታወቅ አለበት፡፡
አንደኛውና የመጀመሪያው ሠራተኞችን በማግባባትና በጊዜያዊ አበል በመደለል ነበር:: ሁለተኛው መንገድ በማስገደድ ስሆን ሶስተኛው ደግሞ ከበላይ ኃላፊዎች የተሰጠውን ተልዕኮ ብቻ ለማስፈጸም ሲባል ሠራተኞችን ለይስሙላ እንደተስማሙ ተድርገው በማስፈረም መንግሥት ለተለያዩ ጉዳዮች የመደበውን በጀት በቀጥታ ለህንጻ ግንባታ በማዛወር ነበር፡፡ይህንን ጉዳይ በተመለከተ በግዳጅ ከደመወዛቸው እየተቆረጠባቸው የሚገኙ ሰራተኞች እሰከዛሬ ድረስ አቤቱታቸውንና ተቃውሞአቸውን አላቀቋረጡም፡፡
በመሆኑም የክልሉ አብዘኛው ሠራተኞች በግዳጅ እየተቆረጠባቸው በመሆኑ ደስተኛ ሆኖ ሥራቸውን መሥራት አልቻሉም:፡አመራሩ ይህንን ያደረገው በክልሉ በሀሰት የተገነባውን ትርክት በህዝቡ በትክክል ከብልጽግና ፓርቲ ጋር መሆኑን ለማስመሰል ነው፡፡
የተከበሩ ጠ/ሚኒስትር
ይህ እውኔት መሆኑን በማንኛውም መንገድ ማጣራት ይችላሉ፡፡ዛሬ በደቡባዊ ሲዳማ ዞንና በምሥራቃዊ ሲዳማ ዞን መምህራንና ሠራተኞች በየጊዜው ተቋውሞ እያነሱ በጸጥታ ኃይል ተቃውሞአቸው እየታፈነ እንጂ አመራሩ እንደሚያስወራው ሠራተኛው በበጎ ፍቃዱ እንዳልሆነ እንዲረዱ እንፈልጋለን፡፡
እኛም የማንክደው ሀቅ ማንኛውም ሰራተኛ ለአካባቢው ልማት በበጎ ፍቃዱ የቻለውን ቢያድርግ ልዩነት አይኖረንም ፡፡ነገር ግን አመራሩ የራሱን ቆሻሸ በህዝብ ላብ ለመጥረግ መሞከር ግን ከፍተኛ የፖለቲካ ሸፍጥ በመሆኑ መታረመም እንዳለበት ስለምናምን ነው፡፡ስለሆነም የሲዳማ ክልል የመንግስት ሠራተኛ ከፍተኛ ብሶት ያለበት መሆኑን በዚህ አጋጣሚ ለማስታወስም እንወዳለን፡፡
ሌላው ከመንግሥት ሠራተኛ ጋር ያለው ችግርና ግልጽ መሆን ያለበት በክልሉ በህገ ወጥ መንገድ የተቀጠሩ ሠራተኞች ሁኔታ ነው፡፡በክልሉ በሁሉም አካባቢዎች የመንግስት ሠራተኞች ቅጥር አፈጻጸም መመሪያ በሚጻረር መልኩ በአንድ መደብ ላይ በርካታ ሠራተኞች ተቀጥረው ይገኛሉ፡፡ይህም የሆነው አመራሩ ዘመድ አዝማዱን አግበስብሶ በመቅጠሩ ሲሆን የክልሉ ከፍተኛ አመራር ይህንን ችግር ማስተካከል እያለበት እራሱም የችግሩ ባለቤት በመሆኑ በዚህ ዓመት ለተጨመረው ሠራተኞች የደመወዝ ጭማሪ አፈጻጸም ላይ ከፍተኛ ችግር ፈጥሮም ይገኛል፡፡በሲዳማ ክልል ይህ ሁሉ ዝንፈት የመጣው በብቃት ማነስ ሳይሆን የበላይ አመራሩ ለሁሉም ነገር ራሱን ማዕከል አድርጎ ስለሚንቀሳቀስ ነው፡፡በመሆኑም ክልሉ በትክለኛ የመንግስት አሠራር መሠረት እንዲመራ የሚያስፈልግ ከሆነ አውቀው እያበላሹ ያሉትን የክልሉ ከፍተኛ አመራሮችን ገምግሞ ህጋዊና ተገቢውን እርምጃ መውሰድ ያስፈልጋል ብለን እናምናለን፡፡ በመጨረሻም እነዚህ ለህዝብ ሳይሆን ለራሳቸው ጥቅም ብቻ የቆሙ ዘራፊዎችን ከሲዳማ ክልል ዞር እንዲያድርጉልንም አበክረን እንጠይቃለን፡፡

ክፍል VIII ይቀጥላል::

ክፍል  VI 4.  የሲዳማ ወጣቶች ሁኔታ በአጭሩ፤ሲዳማ ክልል ሆኖ ከተደራጀ ወዲህ በሲዳማ ይህ ነው የሚባል የሥራ እድል ለወጣቱ ተፈጥሮ አያውቅም ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡የሥራ ዕድል እየተፈ...
30/12/2025

ክፍል VI

4. የሲዳማ ወጣቶች ሁኔታ በአጭሩ፤

ሲዳማ ክልል ሆኖ ከተደራጀ ወዲህ በሲዳማ ይህ ነው የሚባል የሥራ እድል ለወጣቱ ተፈጥሮ አያውቅም ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡የሥራ ዕድል እየተፈጠረለት ያለው ለባለሥልጣናት ልጆችና ለዘመዶቻቸው ብቻ ስሆን ከዝያ የሚተርፈው ጠርቀም ያለ ጉቦ ለሚሰጡት ለሀብታም ልጆች ብቻ ነው፡፡ የድሃው አርሶ አደር ልጆችና ድሃው የከተሜው ልጆች ሥራ አጥ ሆነው በመንከራተት ላይ ይገኛሉ፡፡በክልሉ ለይስሙላ የተቋቋመው የሥራ ፈጠራና እንተርፕራይዝ ቢሮ ሥራ ዕድል እየፈጠረላቸው ያለው ከላይ ለተጠቀሱ በተሰብ ልጆች ብቻ ነው፡፡ ከላይ ለመጥቀስ እንደተሞከረው ዛሬ በከተሞች" ለወጣቱ የሥራ ዕድል ተፈጠረ"እየተባለ በየመንገድ ዳር የተተከሉ ላሜራዎች ውስጥ የሚንቀሳቀሱ ወጣቶች በፍትሃዊ ውድድር ሥራ የተፈጠረላቸው ሳይሆን በዘመድ አዝማድና በጉቦ የተሰበሰቡ ብቻ መሆናቸውን መላው የሲዳማ ሕዝብ የሚያውቀው ጉዳይ ነው፡፡በሀዋሳ ከተማ አንድ አመራር ከአሥራ ስምንት በላይ ሼድ በራሱ ቤተሰብ ይዞ መገኘቱ በግምገማ መረጋገጡ ለዝሁ አንድ ማሳያ ነው፡፡ ሌላው ደግሞ ከክልሉ ነዋሪዎች ቁጥር በላይ የሆነ የውሸት ሥራ ፈጠራ ርፖርቶች ለፋና ብርድካስትንግ ጭምሮ ተልኮ ተዘግቦ እንደነበር ይታወቃል:: ዛሬ በሲዳማ ክልል ፍትሀዊነት ባለመኖሩ አብዘኛው ወጣት ተስፋ የቆረጠ ስሆን ከዚህ የተነሳ በገጠርም ሆነ በከተሞች ትምህርት የጨረሱ መጣቶች በአሉባሌ ሥፍራ ተሰማርተው መመልከት የተለመደ ሆኗል፡፡የችግሩ ምንጭ የአመራር ጎሰኝነት: ጎጠኝነት: ጉቦኛ ወይም ሙሰኝነት ባጠቃላይም ውድቀት በመሆኑ እርምጃ ተወስዶ መስተካከል አለበት እንላለን::

5. የከተማ ነዋሪው ሁኔታ:-

እንደማንኛውም አካባቢ በሲዳማ ክልል ከተሞች ከመንግስት ሠራተኞች ውጪ ኑሮአቸውን በንግድ የሚገፉ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚኖሩበት ነው፡፡እነዚህ በንግድ ስራ የሚተዳደሩ ነጋዴዎች ህጋዊ ንግድ ፍቃድ አውጥተው የሚነግዱ እንዳሉ ሁሉ በየደረጃው ከሚገኙ አመራሮች ጋር በመሞዳሞድ በህገ ወጥ ተግባር የተሰማሩም ይኖራሉ፡፡በህገ ወጥ ስራ የተሠማሩት ወደ ህጋዊ መስመር ማስገባት የአመራሩ ሚና ቢሆንም አመራሩ ራሱን ጥቅም እሰካገኘ ድረስ ይህንን ተግባር ስለማይፈጽም በክልላችን ህገ ወጥ ንግድ ህጋዊ እየሆነ ይገኛል፡፡በመሆኑም በክልሉ በህጋዊ ነጋዴዎች ይልቅ በህገ ወጥ ንግድ ተሰማርተው ለሀገር ስጋት የሆኑ የጦር መሳሪያና አደንዛዥ ዕጽ ሁሉ የሚያዘዋዉሩ የመንግሥትን ግብር በተገቢው የማይከፍሉ የተባራከቱበት ክልል ሆኗል፡፡

ከዚህ ቀደም በዚህ በህገ ወጥ ተግባር በመሠማራትና ሽፋን በመስጠት የሚታወቀው የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ አቶ አለማየሁ ጢሞቴዎስ አሁን ህጋዊ ሆኖ እስር ቤት ቢሆንም ችግሩ አሁንም አልተቀረፈም፡፡ከተሜው ህጋዊ ፍቃድ አውጥቶ የሚፈለግበት የመንግስት ግብር እየከፈለ መኖር የሚጠበቅበት ቢሆንም ህጋዊ ነጋዴዎች በህገ ወጦች እየተዋጡ በመንግስት ላይ እያማረሩ ይኖራሉ፡፡በዚህ ላይ የኑሮ ዉድነት ተዳምሮ ከተሜው ተስፋ ቆርጦ የሚመጣውን አዲስ ነገር በተስፋ እየተጠባበቀ የሚኖር ነው፡፡የመንግሥት አመራሮች በኮንትሮባንድ ሥራ የተሰማሩትን ተቆጣጥሮ ህጋዊ መሥመር ማስያዝ አቅም ያሳጣው ነገር መመርመርም ይኖርበታል፡ለክልሉ ከኬንያ ጠረፍ ኮንትሮባንድ በስፋት የሚገባበት ሁለት በሮች ማለትም ከሞያሌና ከቦረና የሚገናኙ መንገዶች እንዳሉት ግልጽ ነው፡፡

በእነዚህ መንገዶች የሚገቡ ህጋዊ ቀረጥ ያልተከፈላቸው ሸቀጦች(ቦንዳ) እንዲሁም ሌሎችም ለሀገር ደኄንነት ጭምር ስጋት የሚሆኑ ነገሮች በስፋት እንደምገቡ ጥርጥር የለውም፡፡ይህንን ህገ ወጥ ንግድ መቆጣጠር የክልሉ መንግሥት ኃላፊነት ቢሆንም አመራሩ ግን እራሱ በኮንትሮባን ንግድ ተባባር ሆኖ ይገኛል፡፡ከላይ ለማሳየት እንደተሞከረው የቀድሞው የክልሉ ሰላምና ጸጥታ ቢሮ ኃላፊ በኮንትሮባንድ ንግድ ተሠማርቶ በመገኘቱ እርምጃ ተወስዶበት በህግ ቁጥጥር ሥር ያለ ቢሆንም ዛሬም ችግሮቹ አለመቀረፋቸው የክልሉ መንግሥት ድክመት ብቻ ሳይሆን እጃቸው በዝሁ ተግባር ውስጥ መኖሩን ማሳያ ይሆናል ማለት ነው::

ዛሬ አመራሩ በፈጠረው የኑሮ ቀውስ በሀዋሳና በሌሎችም ከተሞች ነዳጅ ከማዲያዎች ውጪ በኮንትሮባንድ ስለሚሸጥ የአንድ ሌትር ዋጋ በሁለት መቶና ከዚያ በላይ እየተሸጠ ይገኛል፡፡ነዳጅ ከወደብ ወደ ክልሉ እየገባ ቢሆንም ባለማዲያዎቹ ከአመራሩ ጋር በጋራ ስለሚነግዱ በህጋዊ መንገድ መሸጥ አቁመዋል፡፡በከተማ የሚኖሩ ህጋዊ ነጋዴዎች ከባለሥልጣናት ጋር ተመሳጥረው ኮንትሮባንድ በሚነግዱ ኮንትሮባንስቶች ጫና እየደረሰባቸው በህጋዊ መንገድ ተወዳዳሪ መሆን አልቻሉም፡፡


ክፍል VII ይቀጥላል::

ክፍል  V3. በሲዳማ ክልል የግብርና ሰክቴር ውድቀት የወለደው ማህበራዊ ቀውስና የአርሶ አደሩ ሁኔታ በተመለከተ :-ከክልሉ ነዋሪዎች መካከል ከፍተኛውን ቁጥር ይዞ የሚገኘው በግብርና ሥራ የሚ...
30/12/2025

ክፍል V

3. በሲዳማ ክልል የግብርና ሰክቴር ውድቀት የወለደው ማህበራዊ ቀውስና የአርሶ አደሩ ሁኔታ በተመለከተ :-

ከክልሉ ነዋሪዎች መካከል ከፍተኛውን ቁጥር ይዞ የሚገኘው በግብርና ሥራ የሚተዳደሩ አርሶ አደሮች ናቸው:: እነዝህ አርሶ አደሮች በይዞታቸው እንደ አየሩ ፀባይ መሬቱ የሚያበቅለው ሰብል እያመረቱ ለራሳቸው ምግብ ፍጆታና ለገበያ የሚቀርቡ ምርቶችን በማምረት ህይወቱን የሚገፋ ናቸው፡፡ የአርሶ አደሮቹ መሬት ተገቢውን ምርት እንድሰጥ በየደረጃው መንግሥት ያቋቋማቸው የግብርና ባለሙያዎች: በዞኖችና በወረዳዎች የሚገኙ የግብርና ጽ/ቤቶችና አስተዳደራዊ መዋቅሮች አስፈላጊውን ሙያዊ እገዛ የማድረግ ግዴታ እንዳለባቸው ይታወቃል፡፡አርሶ አደሮቹ ከአስተዳደራዊ መዋቅርም ሆነ በየደረጃው ከሚገኙ ባለሙያዎች ተገቢውን ግብዓት አቅርቦት በድህረ ምርት ደግሞ ሚዛናዊና ፍትሃዊ የግብይት ሁኔታ እንዲመቻችለትም ይጠበቃል፡፡
የሲዳማ ክልል ከትናንሽ ጓሮ አትክትል ጀምሮ ለዓለም ገበያ የሚቀርቡ እንደ ቡናና ቦሎቄ የመሳሳሉ ከክልሉ አልፎ ለሀገሪቱም የውጪ ምንዛሪ ለማስገኘት ከፍተኛ ፋይዳ ያላቸው ምርቶች የሚመረቱበት ነው፡፡ነገር ግን የአርሶ አደሮቹ ምርታማነት ከፍ እንዲል መንግሥት ያስቀመጠው አቅጣጫ በክልሉ በትክከል በሥራ ላይ ስለማይውል በግብርና ስራ የተሠማራው አርሶ አደር ለፍቶ መና እየሆነ ይገኛል፡፡
የአርሶ አደሩ ምርት ከፍ እንድል በዘመናዊ ተክኒዮሎጂ መታገዝም አለበት፡ነገር ግን የሲዳማ እርሶ አደር ለዚህ የታደለ አይደለም፡፡መንግሥት ይህንን ዓላማ ለማሳካት ከባንክ እየተበደረ የሚልከው ምርጥ ዘርና የአፈር ማዳበሪያ እንድሁም ምርት ስመክንበት ማካካሻ ዘርና አሰፈላጊ ግብዓት በመንግሥትና መንግስታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች ድጋፍ ሊደረግለት ይገባል፡፡ይህንን ኃላፊነት እንዲወጣ ሥልጣን የተሰጠው የክልሉ የግብርና ልማት ቢሮ ቢሆንም ኃላፊነቱን በአግባቡ እየተወጣ አይደለም፡፡በመሆኑም በክልሉ እየተፈጠረ ላለው ማህበራዊ ቀውስ ቁጥር አንድ ተጠያቂው በየደረጃው ያለ የግብርና ሴክተር አመራር የክልሉ መንግሥት ነው፡፡አመራሩ ሙሉ ጊዜውን ለሌብነት በመሰማራቱ የህዝብ ኑሮ ሊያሻሽሉና የምግብ ዋስትና የሚያረጋግጡ ሥራዎች ስትራቴጂክ አመራር በመስጠት በክልሉ ምርትና ምርታማነት የሚያሳድግ ግብዓቶችን ከማቅረብ ይልቅ ራሱ የምርጥ ዘር: የአፈር ማዳበሪያ: የፍራፍሬ ችግኝና ሌሎችንም በዝናብ እጥረት ወቅት የሚቀርብ የማካከሻ ዘር በመሥረቅ በአዲስ አበባና በሌሎች ክልል ከተሞች ቤት የሚነግድ በመሆኑ ምርታማነትን የሚጨምር ግብዓት ስለማያቀርብለት ዛሬ ህዝባችን ተርቦ ለልመና በወረዳ ከተሞችና በክልሉ ዋና ከተማ ሀዋሳ እንድሁም አደስ አበባና በሌሎች ከተሞች በየለቅሶ ቤቱና ድግስ ቤቶች ልመና ኮሮጆ ይዞ የሚለምን ህዝብ ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሻቀበ ሄዷል፡፡
ለግብርና ሴከተሩ ከመንግስት በጀት በተጨማሪ ለዘላቂ ለልማት ግቦች ማሳኪያ ፕሮግራምና ፕሮጀክት ስም በርካታ ቢሊየን ብር እሰከ ወረዳ ድረስ የሚመደብለት ቢሆንም ህዝባዊ ውግንና ይዞ አንድም መሬት ጾም እንዳያድር ከማሳ ዝግጂት እስከ ምርት መሰብሰብ ድረስ አስፈላጊ ግብዓት ማቅረብና ሙያዊ ዕገዛ በመስጠት የአርሶ አደሩን ኑሮ ከማሻሻል ይልቅ በሲዳማ ባህል እጅግ ነውር ተደርጎ የሚወሰደውን የዘር ሥርቆት ላይ በመሰማራት የሚመደበውን ገንዘብ ዘርፎ ንግድ ላይ የተሰማራ ባለሀብት አመራር ሴክተሩን እየመራ ይገኛል፡፡እንደዚሁም የህዝብ ሥቃይና ችግር የማይሰማው ለግል ገጽታቸው የሚጨነቁ የክልሉ አመራሮች ባደራጁት ሀሰተኛ የማህበራዊ ሚዲያ አንቂዎችና የመንግሥት ልሳኖች አብዘኛው ህዝባችን ተርቦ ጎዳና መውጣቱን ህሊናቸው እያወቀ በክልሉ የቤተሰብ ብልጽግና ተረጋግጧል የሚል ሀሰተኛ ዜና በማሰራጨት በህዝብ ላይ ሲያላግጡ ማየት የተለመደ ሆኗል፡፡
በፓርቲው መሪነትና በቁርጠኛ አመራሮች በአንዳንድ ክልሎች በግብርና ሴክተር የተመዘገቡ አንጸባራቂ ድሎች የክልላቸው ህዝብ የምግብ ዋስትና ማረጋገጥ አልፎ ለዓለም ገበያ ማምረት መጀመራቸው የጸጥታ ሁኔታ ጭምር አሰቸጋሪ በሆነበት ውጤት እየመጣ የሲዳማ ክልል በአንጻሩ ሰላማዊ ሆኖ ሳለ አመራሩ ሙሉ ጊዜውን በሌብነት ላይ ብቻ ስለተሰማራ ክረምት ከበጋ ለማምረት ምቹ ሁኔታም እያለ ህዝባችን በምግብ ራስን መቻልና የቤተሰብ ብልጽግና ማረጋገጥ ውጥን መክኖ ቀርቷል፡፡
ሌሎች ክልሎች የአርሶ አደሮቻቸውን ህይወት ለመቀየር ባስገቡት ዘመናዊ ትራክተርና ማረሻ መሀከል ፎቶ ግራፍ እየተነሡ አርሶ አደሮቻቸውን ሲያበረታቱ የሲዳማ አመራሮች ግን ላለፉት ሰባት ዓመታት የህዝብና የመንግሥት ባጀት ለግላቸው ሀብት ማከማቻ እያደረጉ የቆዩ ፊታቸውን በጥቁር መነጽር ሸፍነው በዱባና በጎመን እንዲሁም በዶሮና በእንቁላል መሀል ፎቶ እየተነሡ ያሰራጫሉ፡፡የአርሶ አደሩ ኑሮ ግን ከድህነት ወለል በታች ነው፡፡

ወደ ክልሉ የሚገባው የአፈር ማዳበሪያ አሁንም እየተሸጠ ለችፑድ ፋብርካ ግብዓትነት መግባት አላቆመም፡፡አመራሮቹ ግን እየሸጡት አርሶ አደሩንም እያፈናቀሉ መሬት ይገዙበታል:-ቪላ ይሰሩበታልም ሥልጣናቸውንለማጽናትም ይጠቀሙበታል፡፡ የሲዳማ ክልል አመራሮች የአርሶ አደሩን ችግር የሚፈቱ ሳይሆኑ የውሸት ሪፖርት እያቀረቡ የህልም እንጀራ የሚያበሉ ናቸው:፡
የሲዳማ አርሶ አደር በግብርና ምርት ላይ ብቻ ሳይወሰን የከብት እርባታንም ከእርሻ ሥራ ጋር አጣምሮ በመያዝ ለራሱ ፍጆታም ይሁን ለአካባቢው ገበያ የራሱን አስተዋጽኦ የሚያደርግ ነው፡፡በክልሉ በአሁኑ ሰዓት በእንስሳት ሀብት ቢሮ በኩል የሚቀርበው የተጋነነ ሪፖርት ከውጪ ሆኖ ለሚመለከትና አመራሩ የፌደራል መንግስት ለማሳሳት ከሚያቀርበው የውሽት ረፖርትና የፎቶ ፖለቲካ ተቃራኒ ነው፡፡
ዘርፉን ለመደገፍ ከመንግስትም ሆነ መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች የሚመደበው ክፍተኛ በጀት የአመራር ሰላባ ስለሚሆን በሚደረገው ድጋፍ ልክ ለውጥ እያመጣ ሳይሆን በውሽት ተሸሞንምኖ በሚቀርብ ሪፖርት ሽፋን እየሞተ የሚገኝ ዘርፍ ነው፡፡በክፍል IV ለመጥቀስ እንደሞከርነው አርሶ አደሩ እንሳስትን አርብቶ ለሚያገኘው ጥቅም አንዱ ማነቆ በክልሉ ያለ ገደብ እየተፈቀዱ በየወንዛ ወንዙ በሚተከሉ የእሸት ቡና እንዱስትሪዎች የተበከለ ውሃ እየጠጡ እየሞቱበትና እየጨነገፉበት ማለቅ ነው፡፡ይህንን ቢሮ የሚመራ አካልና የክልሉ ፕረዝዳንና በየደረጃው የሚገኙ አስተዳዳሪዎች ገንዘብ እየተቀበሉ ስለሚያድሉትና ስለሚሸጡት ፍቃድ ትንፍሽ አይሉም፡፡እንዲያውም ራሳቸው ደላላ ሆነው የሚመሩት ዘርፍ ላይ ውድቀት ይጋብዛሉ፡፡በእነዚህና በሌሎች ምክኒያቶች የሲዳማ አርሶ አደር ህይወት እየጨለመ ይገኛል፡፡ዛሬ በሲዳማ በአመራሩ እየደረሰበት ባለው በደልና ግፍ እንዲሁም መልካም አስተዳደር እጦት እየተማረሩ ነዋሪዎች በአንዳንድ አካባቢዎች በአመራሩ ላይ ማመጽም ጀምረዋል፡፡ለዚህ ማሳያ የሚሆነው ሰሞኑን በምስራቃዊ ሲዳማ ዞን በሚገኙ በንሳ: ቦና ዙሪያ:ቡራና ጭሬ ወረዳዎችን መጥቀስ ይቻላል፡፡ሲጠቃለል በአሁኑ ሰዓት ሲዳማ አርሶ አደር የሥቃይ ኑሮ እየገፋ ይገኛል፡፡ የአፈር ማዳበሪያ ዋጋ መጨመሩ የአርሶ አደሩን ኑሮ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ አድርጎት ይገኛል፡፡ይህ ሁሉ ውድቀት እየመጣ ያለው የክልሉ መንግስት የተቃኘው ህዝብን ባማከለ አሠራር ሳይሆን በሌብነት መንገድ በመሆኑ ይህ ታሪክ እንዲቀየር እነ ደስታ ሌዳሞ የያዙትን ሥልጣን አስረክበው ህዝብን አማክለው መምራት ለሚችሉት መልቀቅ ይኖርባቸዋል፡፡አርሶ አደሩ በችጋር እያለቀ መሪ ነኝ ብሎ ወንበር ላይ መኮፈስ ለራስ ዝና ካልሆነ ሌላ ጥቅም የለውምና፡፡

ክፍል VI ነገ በተመሳሳይ ሰዓት ይቀጥላል::

ክፍል  IV2. በከፍተኛ ጉቦ የመንግሥትን መደበኛ አሠራር በመጣስ እየታደለ ያለ የእሸት ቡና እንዱስትሪ ፍቃድ አሰጣጥና በህዝባችን ላይ ያንዣበበው የደኄንነት  አደጋ በተመለከተ:- እንደሚታወ...
29/12/2025

ክፍል IV

2. በከፍተኛ ጉቦ የመንግሥትን መደበኛ አሠራር በመጣስ እየታደለ ያለ የእሸት ቡና እንዱስትሪ ፍቃድ አሰጣጥና በህዝባችን ላይ ያንዣበበው የደኄንነት አደጋ በተመለከተ:-
እንደሚታወቀው የሲዳማ ክልል ለተለያዩ የእንቬስትመንት ሥራዎች የተመቸ ሁሉንም የአየር ንብረት የያዘ ክልል ነው፡፡ሲዳማ ክልል ከመሆኑ በፊት በርካታ ባለሀብቶች ፍቃድ በመውሰድ በተለያዩ የሥራ መስኮች ተሰማርተው ለወጣቱም የሥራ ዕድል ከፍተው እየተንቀሳቀሱ ይገኛሉ፡፡ክልል ከተኮነ ወዲህም ሌሎች በርካታ ባለሀብቶች ወደ ሥራ ገብተዋል፡፡ሲዳማ ክልል ከሆነ ወዲህ ከተፈቀዱ ፍቃዶች መካከል የእሸት ቡና እንዱስትሪ ፍቃድ: የነዳጅ ማደያና: በከተሞች የሆቴልና በቱሪዝም ዘርፍ የተሰጡ ፍቃዶች በዋናነት የሚጠቀሱ ናቸው፡፡እነዚህ ፍቃዶች የተሰጡበትን አግባብ ከዚህ ቀደም የጠቀስናቸው ቢሆንም አሰጣጡ ላይ ችግር የነበረበት መሆኑን ሳንጠቅስ ግን አናልፍም፡፡ምክንያቱም በዚህ ሰዓት በክልል በእሸት ቡና እንዱስትሪ ፍቃድ አሰጣጥ ያለምንም ባለሙያ ጥናት በጉቦ እየተሰጠ የነዋሪዎችንና የቤት እንስሳትን ጠንነት አደጋ እየጣለ መሆኑን ለማሳየት ነው፡፡
የተከበሩ ጠቅላይ ሚኒስትር!
በእኛ በአመልካቾቹ እምነት ማንኛውም ዜጋ አቅም እሰካለውና መስፈርቱን እስካሟላ ድረስ ከመንግሥት ኃላፊዎች ተገቢውን አገልግሎት የማግኘት መብት እንዳለው እንረዳለን፡፡የብልጽግና ፓርቲ በቅርቡ በአዳማና በአዲስ አበባ ለከፍተኛ አመራሩ ባዘጋጀው ስልጠና በተለይም እርስዎ ያደረጉት ገለጻ (አሁንም በመገናኛ ብዙኃን እየተላለፈ የሚገኘው) በመገናኛ ብዙኃን ሲቀርብ እንደተረዳነው ለህዝብ ተገቢውን አገልግሎት መስጠት ቀዳሚ ተግባራቸው እንደሆነና ይህም ግዴታም ጭምር እንደሆነ ነው፡፡በሲዳማ ክልል ግን ሁሉም አገልግሎቶች በገንዘብ የሚሸጡ መሆናቸው እንደተጠበቀ ሆኖ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በስውር የነበረው የአገልግሎት ግዥ ህጋዊ ሆኖ ይገኛል፡፡
የሲዳማ ክልል ቡና አብቃይ ከልል እንደመሆኑ መጠን በተለይም በዘመነ ኢህአደግ በርካታ ባለሀብቶችና የአገልግሎት ህብረት ሥራ ማህበራት የእሸት ቡና እንዱስትሪ ፍቃድ በማውጣት የታጠበ ቡና ለማዕከላዊ ገበያ በማቅረብ የሀገሪቱን የውጪ ምንዛሪ እየደገፉ ይገኛሉ፡፡የእሸት ቡና እንዱስትሪ ፍቃድ አሰጣጥ የራሱ የሆነ መስፈርት ያለው በመሆኑ ከዚህ ቀደም ፍቃዶች ይሰጡ የነበሩት ህጋዊነቱ ተጠብቆ እንደነበርም ይታወቃል፡፡ሲዳማ ክልል ከሆነ ወዲህ ግን ፍቃድ አሰጣጡ ህግን ያማከለ ሳይሆን አመራሩን( ደስታ ሌዳሞን) ያማከለ እንደሆነ ከበቂ ማስረጃ ጋር ለማሳየት የሚቻል ነው፡፡
ለዚህም በቂ ማሳያ የሚሆነው ሲዳማ ክልል ለመሆን አንድ ቀን ሲቀረው ህግን ባልተከተለ ሁኔታ በአንድ ቀን ብቻ በጉቦ ሳላሳ ስድስት (36) የእሸት ቡና እንዱስትሪ ፍቃድ የተሰጠ ሲሆን ከዚያ ጊዜ ጀምሮ በየዓመቱ የእሸት ቡና ፍቃድ በገፍ ሲቸበቸብ እንደነበር ይወቃል፡፡ከዚህ በፊት ፍቃድ ሲሰጥ በስውር ይሰበስብ የነበረው ጉቦ በዚህ ዓመት በይፋ በመደረጉ ማንኛውም ፍቃድ ጠያቂ ግለሰብ አንድ ሚሊየን ብር ለክልል መንግሥት: አምስት መቶ ሺህ ለዞን አስተዳዳሪዎች: እና ሁለት መቶ ሺህ ለወረዳ አስተዳዳሪዎች ገቢ ማድረግ አለበት የሚል ልክ ህግ የተደነገገ ይመስል ባለጎዳዮች በዚህ መልክ እየተመዘበሩ ናቸው፡፡
ይህ በጎቦ የእሸት ቡና እንዲስትሪ ፍቃድ አሰጣጥ እንደተጠበቀ ሆኖ በሲዳማ ክልል ምን ያህል የእሽት ቡና እንዲስትሪ ፍቃድ መስጠት ይቻላል ?የሚለው ጥያቄ ሌላኛውና ዋናው ጥያቄ ነው፡፡ምክኒያቱም ከህብረተሰቡ ጤና ጋር የተያያዘ በመሆኑ ነው፡፡የእሸት ቡና እንዱስትሪ ፍቃድ ሲሰጥ ትኩረት ከሚደረጉ ነገሮች አንዱ የወንዞች ብክለት ነው፡፡ለዚህም ሲባል አንድ የእሸት ቡና እንዱስትሪ ከሌላኛው የእሸት ቡና እንዱስትሪ መራቅ ያለበት የኪሎ ሜትር መጠን ከመስፈርቶቹ አንዱ ነው፡፡ሲዳማ ዞን በነበረ ጊዜ ለእሸት ቡና እንዱስትሪ ያለውን መጠን አሟጦ የተጠቀመ በመሆኑ በዚህ ህግ ከተከደ በክልሉ ምንም ለእሸት ቡና እንዱስትሪ የሚሆን ቦታ አይኖርም ፡፡
ይሁን እንጂ የሲዳማ ክልል አመራር ለራሳቸው ሲሉ ይህንን መስፈርት ጥሶ በዚህ መስፈርት ምትክ ማንም ለእነርሱ የሚፈልጉትን ያህል ገንዘብ መስጠት ከቻለ "የትም ይሁን የት የእሸት ቡና እንዱስትሪ ማቋቋም ይችላል " የሚል አቅጣጫ በማስቀመጣቸው ጉቦ መክፈል የቻለ ሁሉ የእሸት ቡና እንዱስትሪ ማቋቋም ይችላል ማለት ነው፡፡እየተደረገ ያለውም ይህ ነው፡፡በዝሁ ከቀጠለ ደግሞ የሲዳማ ክልል ህዝብ የጤና ጉዳይ የባሰ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ሊደርስ ይችላል፡፡ይህ ችግር የሰዎች የጤና ችግር ብቻ ሳይሆን መተዳደሪያቸው በሆኑ ከብቶቻቸው ላይም ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳል፡፡እያደረሰም ይገኛል፡፡በአሁኑ ግዜ በክልሉ የእሽት ቡና እንዱስትሪ ባለበት አካባቢ የሚገኙ ነዋሪዎች ከብቶቻቸውን ውሃ የሚያጠጡት በእነዚህ በተበከሉ ወንዞች በመሆኑ ብዙ ከብቶቻቸው ለውርጃ እየተዳረጉም ይገኛሉ፡፡
በክልሉ የንጽህ ውሃ ሽፋን ወደ ስድሳ ፔርሰንት ብቻ በመሆኑ አብዘኛው የገጠር ነዋሪ ህዝብ ለመጠጥ የሚጠቀመውም ይህንን የእሽት ቡና እንዱስትሪ የሚተከልበትን የወንዝ ውሃ ነው፡፡በመሆኑም የቀረው አርባው ፔርሰንት የሲዳማ ህዝብ ጤና አደጋ ላይ ነው ማለት ነው፡፡እሰካሁን ባለን መረጃ መሠረት በክልሉ ምርታማ የሆነና ቡና በትክክል ማልማት የሚችል መሬት 83 000 ሄክታር ነው፡፡እስካሁን በክልሉ አገልግሎት እየሰጠ ያለ የእሽት ቡና እንዱስትሪ ብዛት 439 ነው፡፡ከዚህ ውስጥ 162ቱ አቶ ደስታ ሌዳሞ ወደ ሥልጣን ከመጣ ወዲህ የተሰጠ ፍቃድ ነው፡፡በለፈው ሶስት ሳምንት አካባቢ ደግሞ ምሥራቃዊ ሲዳማ ዞንን ሳያካትት 200 መቶ ያህል ተጨማሪ ፍቃድ የተሰጠ ሲሆን ይህም ቁጥሩን ወደ 639 እንዲያሻቅብ ያደርገዋል፡፡ የምስራቃዊ ሲዳማ ዞን እስካሁን ያልተሰጠውም ለጉቦ በሚሰጥ ገንዘብ ላይ ውዝግብ በመፈጠሩ እንደሆነ አረጋግጠናል፡፡የምሥራቃዊ ሲዳማ ዞንን ጨምሮ ተንጠባጥበው የቀሩትን ደግሞ ወደ ሁለት መቶ የሚቀርቡ ናቸው፡፡ይህ ሲደመር በክልሉ የሚገኘው የእሸት ቡና እንዱስትሪ ቁጥር ወደ ዘጠኝ መቶ ከፍ ይላል፡፡የክልሉ የቡና ምርታማነትና ካለው የእንዱስትሪ ብዛት አንጻር ስለአሰጣጡ ትክክል ነው ወይ ?የሚለውን ለባለሙያዎች ትተን የህዝቡ ጤንነት ጉዳይ አሳሳቢ በመሆኑ የህዝቡ ደኄንነት ለመጠበቅ የተቋቋሙ ተቋማትም ትኩረት የሚሻ ጉዳይ ይሆናል፡፡ከምስራቃዊ ሲዳማ ዞን የቀረውንና በሌሎችም ዞኖች የቀሩትንም ለመስጠት ዝግጅት እያደረጉ ይገኛል፡፡እዚህ ላይ ለማብራራት ሲባል ሰፋ ተደረገ እንጂ መያዝ ያለባቸው ነጥቦች ሶስት ናቸው እነዚህም፤
1 ህብረተሰቡ ከመንግስት አካል በነጻ ማግኘት ያለበትን አገልግሎት በገንዘብ መግዛት ተገቢነት የሌሌውና መወገዝ ያለበት ተግባር ከመሆኑም በላይ ገዥ ፓርቲ የሆነውን ብልጽግናን ከህብረተሰቡ ጋር የሚያቃርን ተግባር ስለሆነ መታረም ብቻ ሳይሆን ይህንን ተግባር የፈጸሙና ያስፈጸሙ የመሩ ሁሉ ህጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃ መወሰድ ይኖርበታል እንላለን፡፡
2 በክልሉ ያለው የእሸት ቡና እንዱስትሪ ማቀነባባሪያ ወንዞች በደንቡ መሠረት መሸከም ከሚችሉት ባላይ እየተሰጠ በመሆኑ የህብረተሰቡን ጤና ጉዳይና ከብቶቻቸውን ከግምት ውስጥ በማስገባት ቅድሚያ ለህብረተሰቡ ጤና የሚል አቋም ስለሚኖረን ከህግ አግባብ ውጪ የተፈቀዱ እንዱስትሪዎች ታግደው የማጣራት ሥራ እንድሠራ አበክረን እንጠይቃለን፡፡ይህንን የህብረተሰቡን ጤና እንድጠብቁ ሥልጣን የተሰጣቸው መንግስታዊም ሆነ መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ለጉዳዩ ልዩ ትኩረት በመስጠት ክትትል እንዲያደርጉ በዚህ አጋጣሚ ለማሳሰብ እንወዳለን፡፡
3 ርዕሰ መስተዳድሩን ጨምሮ ሁሉም በየደረጃው ያሉ አመራሮች ስጋታቸውን በሚገልጹ ዘጎች ላይ የተለያየ ጫና እየፈጠሩ በራሳቸውና ለዘመዶቻቸው ስም ፍቃድ በመውሰድ ላይ ስለሚገኙ ብዙ ግለሰቦች አቤቱታ እያሰሙ ሰሚ ያጡበት ሁኔታ ስላለ ተገቢ የማጣራት ሥራ ተሠርቶ በትክክለኛ መንገድ የሚፈቀድለት አካል ብቻ እንዲያገኝ እንድደረግ እንጠይቃለን፡፡፡

ክፍል V ነገ በተመሳሳይ ሰዓት ይቀጥላል::

ክፍል III  ሌላው የክልሉ አመራር የፌዴራሉን መንግሥትና ፓርቲን እንዲሁም የሲዳማ ህዝብ እያታለለ እንደሚኖር ስናነሳ የቆዬነውጉዳይ ቢሆንም ይህንን ውሸታቸውን ያጋለጠና እራሳቸውም ህዝብንና ...
28/12/2025

ክፍል III

ሌላው የክልሉ አመራር የፌዴራሉን መንግሥትና ፓርቲን እንዲሁም የሲዳማ ህዝብ እያታለለ እንደሚኖር ስናነሳ የቆዬነውጉዳይ ቢሆንም ይህንን ውሸታቸውን ያጋለጠና እራሳቸውም ህዝብንና መንግሥት ሲያታልሉ እንደቆዩ ያመኑበትን ሁኔታ እዚህ ላይ አስረግጠን የሚናልፈው ጉዳይ ይሆናል፡፡ይኸውም በሀምሌ ወር 2017 ዓ/ም አጋማሽ አካባቢ በክልል ደረጃ የአመራር የግምገማ መድረክ ተፈጥሮ ከክልሉ አመራር ፑል ውስጥ በሁለት አመራር ላይ ብቻ እርምጃ ተወስዶ ሌላዉ ሁሉ አመራር ችግር የሌለበት እንደሆነ ተደርጎ እስከታችኛወ መዋቅር ዉጤቱ ደርሶ ሳይጠናቀቅ ከሁለት ወር በኃላ እንደገና የግምገማ መድረክ እንዲፈጠር ተደርጎ በመጀመሪያ ግምገማ ያልወጡ ችግሮች ወጥተው የተወሰኑት ከኃላፊነት እንዲነሱ ተደርጎ እንደነበር የሚታወስ ነው፡፡በሁለተኛው ግምገማ የተነሡ ጉዳዮች በመጀመሪያው ግምገማ ተሸፋፍነው ያለፉ ናቸው፡፡
ዋናው ጥያቄ ያለውም እዚህ ላይ ነው፡፡በዚህ በሁለተኛው የግምገማ መድረክ የተጋለጡ ጉዳዮች በመጀመሪያው ግምገማቸው ተሸፋፍነው የታለፉ ለመሆናቸው ከዚህ በላይ ማረጋገጫ ሊኖርም አይችልም፡፡በዚህ መድረክ ጎልቶ የወጣው የአመራሩ ችግር አቅመ ደካሞችን ከቤት በማፈናቀል በመንግሥት በጀት የመንግስትን ቤት የግላቸው በማድረግ ቅርጽ ቀይረው የራሳቸው ቤትም እያላቸው ወደ እነዝያ የቀሙኣቸው ቤቶች መግባትና ለመግባት ዝግጅት ማድረግ ነው፡፡እዚህ ላይ የክልሉ አመራሮች ምን ያህል ራሳቸውን የሚያስቀድሙ እንደሆኑና ከህዝብ ይልቅ ለራሳቸው እንደቆሙ የሚያሳየው በቅርቡ በተደረገው ግምገማ ማግሥት የተሾመው ከንቲባ በሀያ ስምንት የሥልጣን ቆይታው ቀናቶች የፈጸማቸውን ህገ ወጥ ተግባራት ማሳየት በቂ ይሆናል፡፡በታሪክ ታይቶና ተሰምቶ በማይታወቅ መልኩ ዛሬ ግምገማ ተጠናቅቆ ዛሬውኑ የአመራር ሹመት የተሰጠው በሲዳማ ክልል ነው፡፡
ከግምገማው ማግስት የሀዋሳ ከተማ ከንቲባ ሆኖ የተሾመው አቶ ተክሌ ጆምባ በሀያ ስምንት ቀናት የሥልጣን ቆይታው 53 በመሀንዲስ የተዘለሉ ቦታዎችን ለዘመዶቹና ለአቶ ደስታ ቤተሰቦች ያደለ መሆኑ ነው፡፡ከዚህ ጋር ተያይዞ መነሳትና መታለፍ የሌለለበት ጉዳይ አቶ ተክሌ ጆምባ የክልሉ የእንስሳት ሀብት ቢሮ ኃላፊ ሆኖ በሠራበት ወቅት የመንግስት በጀትንም ሆነ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የሚመድቡትን በጀት ለግሉ እያዋለ እንደነበር በቂ ማስረጃዎችም ይኖራሉ፡፡ግለሰቡ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ፈጠራ የተላከውን ወይንም ከውጪ ዕርዳታ የመጣው ግዙፍ ማሽን ገጠር በሚገኘው በአባቱ መኖሪያ ቀዬ በመትከል እየተገለገለም ይገኛል፡፡ከሀዋሳ ከንቲባነት እንዲነሳና በፌዴራል ደረጃ የተሰጠውን ሹመት አልቀበልም በማለት በወቅቱ ከጠ/ር የተጻፈውን ደብዳቤ ለማጣጣል ሞክሮ እንደነበር ይታወቃል፡፡ለዚህ ዋናው ምክንያት ለሰባት ዓመታት በማን አለብኝነት የክልሉን ሀብት ሲዘርፍ ቆይቶ አዲስ በተሰጠው የከንቲባነት ሥልጣን ደግሞ ሌላ ሌብነት መደላድል በመፍጠር በክልሉ ተጨማሪ ዘረፋ ለማካሄድ እንዲሁም እነ ደስታንና መሰሎቹን ለመጥቀም እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡ይህም የሚያሳየን የክልሉ አመራር ምን ያህል ለራሱ ጥቅም ብቻ የቆመ መሆኑን ነው፡፡በአሁኑ ግዜ በአቶ ተክሌ ጆምባ የተዛባ አመራር የተዘረፉ ቦታዎች በአዲሱ ከንቲባ ወደ መሬት ባንክ እንዲገቡ እንጠይቃለን፡፡
በዚህ ርዕስ ሥር በደንብ እንዲያዝልን የምንፈልጋቸው ነጥቦችን እንደሚከተለው እናቀርባለን::
1ኛ. አመራሩ የራሱ የግል መኖሪያ ቤት በዚሁ ከተማ እያለው የመንግሥት ቤቶች አስተዳደር መመሪያዎችን በራሱ ማነጅሜት ብቻ አስወስኖ በመሻር የቀበሌ ቤቶችን መቀራመት ህገ-ወጥ ተግባርና ወንጀልም በመሆኑ ይህንን መመሪያና ደንብ ሌላ አዋጅ ሳይኖር ለራሱ በሚያመች መልኩ እንዲሻር ያደረገና በጉዳዩ በቀጥታ ተሳታፊ የሆነ የክልል ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ አሻግሬ ጀንበሬ ላይ ቢሮ ከመቀየር ውጪ እና አቅመ ደካሞችን ከቤት አፈናቅላ ላባረረችው በክልሉ ሥራ ፈጠራና እንተርፕራይዝ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሀረገጽዮን አበበ ላይ ህጋዊና አስተዳደራዊ እርምጃ አለመኖሩ አባላትን ብቻ ሳይሆን መላው የሲዳማን ህዝብ ያስገረመ ጉዳይ ነው፡፡በመሆኑምበዚህ ድርጊት የተሳተፉ አመራሮች ላይ ተመጣጣኝ እርምጃ እንዲወሰድ እንጠይቃለን፤
2ኛ.የግል መኖሪያ ቤት እያላቸውም ከመንግስት ካዝና የቤት አበል እየተከፈላቸው የመንግሥትን ቤቶች አፍርሶ ቅርጽ በመቀየር የግል ማድረግ እራሱ የተደራራቢ ወንጀል ስለሆነ ያለ አግባብ እየተከፈላቸው የቆዬው የቤት አበል እንዲመለስ ተደርጎ ለመንግሥት ገቢ እንዲደረግ እንጠይቃለን፤
3ኛ. በአመራሩ ያለ አግባብ የተወሰዱ መንግሥት ቤቶች የተወሰኑት ብቻ ለቀድሞ ባለመብቶች ተመለሱ ሲሆን የማስመለሱ እንቅስቃሴ አሁን የቆመ ስለሚመስል አዲሱ ከንቲባ በህገ-ወጥ መንገድ ከቤታቸው የተፈናቀሉ ነዋሪዎች በአፋጣኝ ወደ ነበሩበት እንዲመለሱ እንዲደረግ እንጠይቃለን፡፡

ክፍል IV ነገ በተመሳሳይ ሰዓት ይቀጥላል::

አስቸኳይ የእርዳታ ጥሪ ለመምህር ተሾመ ሰፎንያስ ደብሶ:-መምህር ተሾመ ሶፎንያስ በአርጎና ወረዳ ከአንደኛ ደረጃ እስከ 2ኛ ደረጃ ድረስ በመምህርነት አገልግሏል፤ በቦና ወረዳ ቦና ሁለተኛ ደረ...
28/12/2025

አስቸኳይ የእርዳታ ጥሪ

ለመምህር ተሾመ ሰፎንያስ ደብሶ:-

መምህር ተሾመ ሶፎንያስ በአርጎና ወረዳ ከአንደኛ ደረጃ እስከ 2ኛ ደረጃ ድረስ በመምህርነት አገልግሏል፤ በቦና ወረዳ ቦና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በእንግልዝኛ መምህርነት እና በርዕሰ መምህርነት አገልግሏል፤ በአለታ ጩኮ 2ኛ ደረጃ በእንግልዝኛ መምህርነት ለ10 ዓመት አገልግሏል፥ በደቡብ ክልል እና ሲዳማ ክልል ደረጃ ከፍተኛ የእንግሊዝኛ አሰልጣኝ ሆኖ አገልግሏል ፥ በአሁኑ ወቅት ከ2017ዓ/ም ጀምሮ በሀዋሳ ታቦር ከፍተኛ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በእንግልዝኛ መምህርነት በማገልገል ላይ እያለ ባጋጠመው የጤና እክል በቤተሰቡና በሀዋሳ ታቦር ከፍተኛ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መምህራን እርዳታ ስታከም ቆይቶ ከፍተኛ ገንዘብ በመጠየቁ በገንዘብ እጥረት ህክምና አቋርጦ በቤቱ ተኝቶ ይገኛል። ስለዚም መምህሩ በቂ የሚረዳ ዘመድ እና ንብረት የለው ስለሆነ መምህር ተሾመ ሰፎንያስን የምታውቁም የማታውቁም ጓደኞቹ ተማሪዎቹ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገር ያላችሁ ከዚህ በታች በስሙ ባለው አካውን ያላችሁን በመርዳት የመደጋገፍ ባህላችንንና ኢትዮጵያዊ ርሁርህነታችንን በመግለጽ ህክምናውን እንዲቀጥል እንድታደርጉ በእግዚአብሔር ፍቅር እንጠይቃችኋለን።

ይህንን መልዕክ ለሌሎችም ሼር በማድረግ እንዲትተባበሩን እንጠይቃለን።
1000095958487 ተሾመ ሰፎንያስን ደብሶ

ክፍል IIእስካሁን የሚመደቡ ከንቲባዎችና የክልል አመራር ዋና ትኩረት ሌብነት ስለነበር የልማት ሥራዎች ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ቆሞ ቆይቷል ለማለት ያስደፍራል፡፡በተለይም አቶ መኩሪያ መርሻዬ...
27/12/2025

ክፍል II

እስካሁን የሚመደቡ ከንቲባዎችና የክልል አመራር ዋና ትኩረት ሌብነት ስለነበር የልማት ሥራዎች ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ቆሞ ቆይቷል ለማለት ያስደፍራል፡፡በተለይም አቶ መኩሪያ መርሻዬ የተባለ ግለሰብ ከንቲባ ተደርጎ ከተመደበ ወዲህ ምንም የልማት እንቅስቃሴ አልነበረም፡፡በአቶ መኩሪያ ጊዜ የነበረው ዋኛው ትኩረት ዝርፊያና የመንግሥት ወይም የቀበሌ ቤቶች ሽሚያ ብቻ ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም፡፡፡እዚህ ላይ ሳይጠቀስ የማይታለፈው ጉዳይ ቢኖር ግለሰቡ ለሀዋሳ ከተማ ከንቲባነት የሚያበቃ ብቃት ኖሮት ተሹሞ የቆዬ ሳይሆን ማንኛውንም ትዕዛዝ ከአቶ ደስታ ሌዳሞ እየተቀበለ ሳያላምጥ ተግባራዊ እንዲያደርግ ታልሞ ነበር፡፡ለአቶ ደስታ ሌዳሞም እንዳቀደው በሁለት ዓመት ቆይታው መቶ በመቶ የተሳካለት ይመስላል፡፡
ነገር ግን ምስጋና ለፌዴራል መንግስት ይሁንና አቶ ጥራቱ በየነ ከእንደገና ወደ ከንቲባነት ተመልሶ መምጣታቸው ከእንግዲህ እነ ደስታ ሌዳሞ በሀዋሳ ከተማ እንደፈለጉ የሚፈነጩበት ጊዜም ያበቃ ይመስላል፡፡ከእሳቸው በፊት የነበረው ከንቲባ ለከተማዋ የሚመጥን ዕውቀት ባያንሰውም የእነ ደስታ ሌዳሞ ተልዕኮ በማስፈጸም በርካታ የእንቬስትሜንትና የልማት ተነሺ ስም መሬት እንዲዘረፍ አድርገዋል፡፡ሆኖም በሥልጣን ዘመናቸው ማብቂያ አንዳንድ የልማት ሥራዎች እንቅስቃሴ እንዳደረጉ የማይካድ ነው፡፡
ከንቲባውን ጨምሮ የክልሉና ከተማ አስተዳደሩ አመራሮች ጭምር የራሳቸው ቤት እያላቸው በየወሩ የቤት አበል ከመንግስት በጀትም እየተከፈላቸው በቁጥር 89 አባወራ ከ800 በላይ ቤተሰብ አባላትን ከቀበሌ ቤቶች በማፈናቀል በመንግስት በጀት አዲስ ግንባታ በማሰገንባት የሲዳማ አቃፊነት ባህል በሚቃረን መልኩ ዜጎችን በዘር በመለየት ጎዳና አውጥተው የጣሉ በህግ መጠየቅ የሚገባቸው በሥልጣን ላይ መቆየታቸው በአሁኑ ሰዓት መነጋገሪያ ሆኖ ይገኛል፡፡
ዜጎች ለዘመናት ከኖሩበት ቤት አፈናቅለው የገቡ የተወሰኑ አመራሮች በግምገማ ተለይተው እርምጃ በተወሰደ ማግሥት እነ ደስታ ሌዳሞ የራሳቸው ዓላማ ለማሳካት ሲሉ በብርሃን ፍጥነት የሾሙት ከንቲባ በፌዴራል መንግስት ጣልቃ ገብነት እንዲነሳ ተድርጎ ከዚህ በፊት የተገፋ ክቡር ከንቲባ አቶ ጥራቱ ተመልሶ መምጣታቸው የእነ ደስታ ሌዳሞን ወሽመጥ የሰበረ ከመሆኑም ሌላ የፌደራል መንግሥትና ፓርቲ የመደበው ከንቲባ እንደይመጣ ብዙ ጥረት አድርገው ሳይሳካላቸው ቀርቷል፡፡የአቶ ጥራቱ በየነ ዳግም ከንቲባ ሆኖ መመደባቸው ለከተማውና ለመላው ሲዳማ ህዝብ ከፍተኛ ደስታ ፈጥሮም ይገኛል፡፡በመሆኑ ብልጽግና ፓርቲ የከተማውን ወደ ቁልቁል ማደግ በመረዳት እጅ አስገብቶ ወደ ነበረበት እንዲመለስ የተደረገውን ጥረት በዚህ አጋጣሚ አድንቀን ማለፍ እንወዳለን፡፡የክልሉ አመራር ሀዋሳ ከተማን ለራሱ በሚመች ሁኔታ በማዋቀሩ የሚሰበሰበው ገቢ የሚፈስሰውም ወደ እነርሱ ጓዳና ክስ እንጅ ለሕዝቡ በዕለታዊ ኑሮያቸው ላይ አንዳችም ጠብ ያለ ነገር የለም፡፡ሌላው ቀርቶ በከተማው በቀድሞዎቹ ከንቲባዎች የተጀመሩ ፕሮጀክቶች እንኳን ቆመው ቀርተዋል፡፡የተጀምረው ቆመው ከቀሩ ፕሮጀክቶች መካካል ታቦር ተራራን የማልማት ፕሮጀክት: አቶቴ አሊቶ የአስፋልት መንገድ ፕሮጄክት: ከቴክኒክና ሙያ ወደ ትምባሆ ሞኖፖል የአስፋልት መንገድ ፕሮጀክት: ...ወዘተ በዋናነት የሚጠቀሱ ሲሆኑ እነዚህ ፕሮጄክቶች በፋይናንስ እጥረት ምክንያት የቆሙ ናቸው፡፡ፋይናንስ ያጠረውም እነ ደስታ ሌዳሞ ረዥም እጃቸውን አስገብተው ስለምመዘብሩ ነው፡፡ምስጋና ለፌዴራል መንግስት ይሁንና ከእንግዲህ እነ ደስታ ሌዳሞ በሀዋሳ ከተማ እንደፈለጉ የሚፈነጩበት ጊዜም ያበቃ ይመስላል፡:
አቶ ጥራቱን ከዝሁ ቀደም በሥራቸው ወይም በተግባራቸው ጠንቅቀን ስለምናቃቸው በከተማው የተያዙ ፕሮጀክቶች ከእንግዲህ በበጀት እጥረት ምክንያት እየተሳበቡ አይቆሙም የሚል ጽኑ እምነት አለን ፡፡የማይጠናቀቁ ፕሮጀክቶችም አይጀመሩም የሚል ተስፋም ይኖረናል፡፡ዛሬ የሲዳማ አመራር የሀዋሳ ከተማ ነዋሪዎች ሥጋት ሆኖ በሚገኝበት ወቅት ነው የፌዴራል መንግስት የደረሰለት!"ባለቤቱን ካልናቁ አጥር አይነቀንቁ"እንደሚባለው ተረት ዛሬ የሲዳማና የሀዋሳ ከተማ አመራሮች ዜጎችን በብሄር በመለየት አካል ጉዳተኞች እንኳን ሳይቀሩ ከቤታቸው እያፈናቀሉ በማፍረስ ቅርጽና ይዘትም እየቀየሩ በመንግስት በጀት በመጠገን ከገቡበት የፌዴራሉ መንግስት የዜጎችን ጩኄት በመስማት የታደጋቸው ቢሆንም አሁንም ተፈናቅለው ያሉ ዜጎች መኖራቸው የአዲሱ ከንቲባ የቤት ስራ ይሆናል የሚል እምነት አለን፡፡እዚህ ላይ ሳይጠቀስ ማይታለፈው ሌላው ጉዳይ ቢኖር ዜጎችን ዘር ቆጥረው ለዘመናት ከኖሩበት ቤት ያፈናቀሉ አመራሮች ላይ የተወሰደው የተለሳለሰ እርምጃ የክልሉ ከፍተኛ አመራሮች በጉዳዩ እጃቸው ያለበት እንደሆነም የሚያሳብቅ መሆኑ ነው፡፡የሚገርመው ነገር አካል ጉዳተኛ እንኳን ሳይቀር ከቤት ያፈናቀሉ አመራሮች ለምን ተነካን በማለት ሰሞኑን ማንን ለመክሰስ እንደሆነ ባይታወቅም ወደ አራት ኪሎ (ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት)ያቀኑ መሆናቸው ነው፡፡በእኛ እምነት ህዝብን እንዲመራና እንድያስተዳድር በተሰጠው ሥልጣን የዚህ አይነት አሰነዋሪና አሳፋሪ ደርጊት ላይ የተሳተፈ አመራር አይደለም ለምን ተነካሁ ብሎ ያዙኝ ልቀቁኝ እያሉ የማህበራዊ ሚዲያ ቀለብተኞችን በመላክ ህዝብን መሳደብና ወደ አራት ኪሎም መመላለስ (ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ) ይቅርና ከተነቃበት ጊዜ ጀምሮ ሥልጣኑን በገዛ እጁ መልቀቅ ነው ያለበት፡፡
የክልሉ መንግሥት ለከተማዋ የከተማ ልማት ፖሊሲና ስትራቴጂ የከተሞች መንሰራራት አቅዶ ብቁ ሀብት መድቦ የአመራርና የባለሙያ ድጋፍ ፓኬጅ ቀርጾ ተወዳዳሪነቷን ከማስቀጠል ይልቅ በተገኘ አጋጣሚ ሁሉ በእንቬስትሜንት ስም መሬትና የመንግሥት ቤቶች መዝረፍ እንዲሁም ከተማ አስተዳደሩን ገንዘብ መዝረፍ ዓላማ ያደረገው የደስታሌዳሞአስተዳደር ለከተማው የማይመጥን እንኳን ለከንቲባነትና የክፍለ ከተማ አመራርነት የማይታጭ ግለሰብ በመመደብ የግል ፍላጎቱን እያሳካና የከተማዋ ዕድገት እንዲቆም ከተማዋ የዝርፊያ ማዕከል ሆና ዜጎች ያለጥፋታቸው ከሚኖሩበትቤቶች ዘራቸው ተለይቶ የሚፈናቀሉበት ከተማ እንዲትሆን አድርጎ ቆይቷል፡፡

ክፍል III ነገ በተመሳሳይ ሰዓት ይቀጥላል::

ክፍል I                      ቀን 24/03/2018      ለተከበሩ ለዶ/ር አብይ አህመድ  ለኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትርና ለብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝዴንት:ለተከበሩ ለአቶ ተመስገን ጥ...
26/12/2025

ክፍል I

ቀን 24/03/2018

ለተከበሩ ለዶ/ር አብይ አህመድ ለኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስትርና ለብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝዴንት:
ለተከበሩ ለአቶ ተመስገን ጥሩነህ ለኢፌዴሪ ም/ል ጠ/ሚኒስትርና ለብልጽግና ፓርቲ ም/ል ፕሬዝዴንት:

ለተከበሩ ለአቶ አደም ፋራህ ለብልጽግና ፓርቲ ም/ል ፕሬዝዴንትና የድሞኪራሲ ሥርዓት ግንባታ ማዕከል ማስተባባሪያ ጽ/ቤት ኃላፊ:

ለብሔራዊ መረጃና ደኄንነት ዋና አገልግሎት:

አዲስ አበባ

ለሁሉም የብልጽግና ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት:
በያሉበት

ጉዳዩ፤በሲዳማ ክልል የሚፈጸመውን ሌብነትና ዘረፋ ለአሥራ አምስተኛ ጊዜ ማጋለጥ ይሆናል፤

ከላይ በርዕሱ ለመጥቀስ እንደተሞከረው በሲዳማ ክልል አመራሩበህዝቡ ላይ የሚፈጸመውን በደል ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ ስናሳውቅ የቆዬን ቢሆንም ቶሎ ምላሽ ባለመሰጠቱ እየደረሰ ያለው ግፍና በደል አሁን አልቆመም፡፡ የክልሉ አመራሮች የህዝቡን ሀብት መዝረፋቸውና በዘረፉት ገንዘብ ሀገር ቤት እንኳን መኖር ተጸይፈው ቤተሰቦቻቸውን ባህር ማዶ በማሻገር እየተመቻቹ ዜጎች እዚሁ እንዳይኖሩ ለዘመናት ከሚኖሩበትና ወልደው ከከበሩበት ቀዬአቸው ብሄር በመለዬት ማፈናቀል ጀምረዋል፡፡እነዚህ ለህዝብ ሳይሆን ለራሳቸው ብቻ የቆሙ የክልሉ አመራሮችከድርጊታቸው እስካልተመለሱና ብልጽግና ፓርቲ ተገቢውን እርምጃ እስከሚወስድ ድረስ ትግላችንን እንቀጥላለን፡፡በመሆኑምእኛ በክልሉ በተለያዩ ዞኖችና ወረዳዎች የምንኖር የብልጽግና ፓርቲ አባላት በአሁኑ ሰዓት በክልሉ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ የሚያትት ይህንን አጭር ሰነድ ሲናቀርብልዎ በክልሉ ሌብነትና ዘረፋ እንዲሁም ጎሴኝነትና ጎጤኝነትን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ እንደሚያስወግዱልን በመተማመንም ጭምር ነው ፡፡

የተከበሩ ጠ/ሚኒስትርና የብልጽግና ፓርቲ ፕሬዝዴንት!
ከሁሉ በማሰቀደም የሲዳማ ህዝብና የክልሉ ፓርቲ አባላትበየጊዜው ሲያቀርቡ የቆዩትን አቤቱታ በከፊልም ቢሆን አዳምጠው በሀዋሳ ከተማ ላይ ፓርቲዎ ለወሰደው እርምጃ አድናቆታችንን እየገለጽን በሀዋሳ ከተማ የተወሰዱት እርምጃ በክልሉ አመራር ላይ እንድቀጥል ስናሳስብ በክልሉ ያለውን የአመራር ችግር በተጨባጭ በማሳዬት ጭምር ነው፡፡ የሲዳማ ህዝብ በፓርቲዎና በራስዎ ያለው አክብሮት ወደር እንደለሌው ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ ያወሳነው ጉዳይ ነው፡፡ ይህ ደግሞ ያለ ምክኒያትም አይደለም፡፡ ለዘመናት በህዝብ ውስጥ ጥያቄ ሆኖ የቆዬው የሲዳማ ክልልነት ጥያቄ በእርስዎ ዘመን ምላሽ ማግኘቱ ብቻ ሳይሆን ለሲዳማ ህዝብ በየጊዜው በሚያሳዩት ፍቅርና አክብሮትም ነው፡፡ በሌላ አንጻር ሲዳማ ክልል ሲሆን የህዝብ ወገንተኛ በመምሰል እርስዎንም ሆነ ፓርቲዎን በማሳሳት የክልሉንቁንጮ ሥልጣን የያዙ ግለሰቦች ህዝቡን አማክለው መምራትና የወከሉትን ህዝብ ተጠቃሚ የሚያድርግ ሥራ መሥራት እየተገባቸው ለራሳቸው ብቻ የቆሙ መሆናቸውን ከዚህ ቀደም በተከታታይ በቀረበልዎ አቤቱታዎች የተገለጹ ጉዳዮች ናቸው፡፡በዚህ ሰነድ ላይ ከዚህ በፊት የተዘረዘሩ ጉዳዮች እየጠቀስን ጊዜዎንም ለማባከን አንፈልግም፡፡ ስለሆነም ከዚህ ቀደም ባልተዘረዘሩ ጉዳዮች ላይ ትኩረት በመስጠት ክልሉ ምን ያህል ኣሳሳቢ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ለማሳወቅ እንወዳለን፡፡ በመሆኑንም በእያንዳንዱ በተጠቀሱ ጉዳዮች ላይ ልዩ ትኩረት በመስጠት ህዝቡንና ፓርቲዎንም እንድታደጉ እንጠይቃለን፡፡

1 አመራሩ በሀዋሳ ከተማ መሬትና በመንግሥት ቤቶች ላይ ሲፈጸም የቆዬው ቅርምት በሚመለከት፤
ሀዋሳ ከተማ እስከ ከ2013 ዓ/ም ድረስ በሀገሪቱ ከሚገኙ ከተሞች ተወዳዳሪና በግንባር ቀደምትነት የሚትመደብ ከተማ ነበረች፡፡ከተማዋ ከ2013 ዓ/ም ጀምሮ ከዕድገት ጎዳና ሀዲድ ከመውጣቷናየዝርፊያ ማዕከል ከመሆኗ በፊት ከአሥር በላይ ከንቲባዎች የተፈራረቁባት ሲሆን እነዚህ ከንቲባዎች አቅማቸው በፈቀደ መጠን አሻራቸውን በማኖር ከተማዋ የቱሪዝም የእንቬስትሜንትና የአስተዳደር ማዕከል ሆና እንድትይቆይ አድገርውም ነበር፡፡ ነዋሪዎቿንም ያለ አድልዎ የሚታስተናግድ አሳታፊ አካታች የልማትና የዕድገት ማዕከል ሆና በርካታ እንግዶችን ተቀብላ በማስተናገድ የፍቅር ከተማ የሚል ስያሜ የተጎናጸፈች ጽዱ አረንጓዴና ለኑሮ ምቹ ከተማ ነበረች፡፡የኢትዮጵያ የልማትና የዕድገት ተምሳሌትም ነበረች፡፡

ክልሉ ከተዋቀረና አሁን የክልሉን ሥልጣን የተቆናጠጠው ቡድን ለዘመናት የከተማዋን ሀብት ለመዝረፍ ነበረውን ዓላማ ለማሳካት ለከተማዋ ዕድገት የሚመጥን የልማት ሥራዎችን እየሠራ የነበረውን የአሁኑ ከንቲባ አቶ ጥራቱ በየነን በ2013 ዓ/ም አካባቢ ተረጋግቶ ሥራውን እንዳይሠራ ሁከት ፈጣሪ የሚዲያ ሠራዊት እያደራጁ ከቆዩ በኃላ በመጨረሻም የከተማውን ዕድገት የሚገታ የተሳሳተ ውሳኔ ሆን ብለው በመወሰን ከቦታው እንዲነሳ ማድረግ የራሳቸውን ዓላማ ሊያሳካ የሚችል አመራር እየመደቡ የከተማዋ የዕድገት ጉዞ እንዲገታ አድርገዋል፡፡ በሌላ በኩል የክልሉ አመራሮች ለከተማዋ ዕድገት እየተጋ የነበረውን ከንቲባ በዚህ መንገድ ተገቢ ያልሆነ ውሳኔ በመወስን ከቦታው ቢያነሱም የፌዴራል መንግስት ግለሰቡን ለህዝብ የተሻለ አገልግሎት የሚሰጥ ሥፍራ አስቀምጦታል፡፡

የክልሉ አመራር አቶ ጥራቱ በየነን ቦታውን ካስለቀቁ በኃላ ከ2013 ዓ/ም ጀምሮ ከተማዋ የሥራ ልምድ የሌላቸው የከተማውን ህዝብ ስነ ልቦና መረዳት የማይችሉ እጃቸው ንጹህ ያልሆኑ ታዛዥ ከንቲባዎችን በመመደብ የከተማዋን ሀብት ሲመዘብሩ ቆይተዋል፡፡ በዚህ መሠረት ከከተማዋ ከመዘበሩአቸው ዋና ዋና ሀብቶች መካካል የከተማ መሬትና የመንግሥት ቤቶች መቀራመትከከተማው የሚሰበሰበውን ገቢ እንዲሁም ለልማት የሚመደበውገንዘብ ለከተማዋ ልማትና ዕድገት ለማይጠቅሙ ጉዳዮች አያዋሉ ማባከን ነው፡፡የሌሎች አመራሮች ዘረፋ እንደተጠበቀ ሆኖ አቶ ደስታ ሌዳሞ ብቻ በሥልጣን ዘመኑ በልማት ተነሺ ስም ምንም መፈናቀል ያልደረሰባቸው ዘመዶቹን በማስመዝገብ በተለይም አራተኛና አምስተኛ ዙር የልማት ተነሺዎች አካል አድርጎ 9000 ካሬ ሜትር በላይ መሬት በመውስድ ነበር በከተማ አስተዳደሩ ላይ የነበረውን የረዥም ጊዜ ህልሙን እውን ማድረግ የጀመረው፡፡

አቶ አብርሃም ማርሻሎም ቢሆን ምንም መፈናቀል ባልደረሰባቸውና የሀዋሳ ከተማ ነዋሪ ባልሆኑ ዘመዶቹ ስም ከ6000 ካሬ ሜትር መሬት በመውሰድ እሱም የድርሻውን በዚህ መልክ በመቋደስ ከተማ ሀብት ተቀራምቷል፡፡ከዚህም በተጨማሪ ዛሬ የእነ ደስታ ሌዳሞን ሥልጣን ለማስጠበቅ አዲስ አበባ አባገዳ ማዕከልና ጠ/ሚኒስትር ጸ/ቤት የሚመላለሱ በሀገር ሽማግሌዎች ስም የሚነግዱ አካላት በቁጥር 29 የሚሆኑ እያንዳንዳቸው ባላቸው ተደማጭነትና ተጽዕኖ ፈጣሪነት ደረጃ ከአንድ እስከ ስድስት ባለሁለት መቶ ካሬ ሜትር መሬት የታደላቸው ሲሆንለወዳጅ ዘመዶቻቸው ለቄስ ለፓስተር እገሌ እየተባለ በእነዚሁ ግለሰቦች ትዕዛዝ አሁን አቶ ጥራቱ በየነ ዳግመኛ ከንቲባ ሆኖ እስከሚመጣበት ዕለት ድረስ ሲዘረፍ ኖሯል፡፡

ክፍል II ነገ በተመሳሳይ ሰዓት ይቀጥላል::

በሲዳማ ክልል ላለፉት ዓመታት በክልሉ ቁንጮ አመራሮች ስደረግ የነበረውን አይን ያወጣ ለብነትና ዘረፋን በተመለከተ በክልሉ የተለያዩ ዞኖችና ወረዳዎች የሚኖሩ የብልፅግና የራሱ አባላት ለጠ/ር ...
26/12/2025

በሲዳማ ክልል ላለፉት ዓመታት በክልሉ ቁንጮ አመራሮች ስደረግ የነበረውን አይን ያወጣ ለብነትና ዘረፋን በተመለከተ በክልሉ የተለያዩ ዞኖችና ወረዳዎች የሚኖሩ የብልፅግና የራሱ አባላት ለጠ/ር እና ለም/ል
ጠ/ር ጽ/ቤት: ለብልፅግና ጽ/ቤት: እና ለብሔራዊ ደህንነትና መረጃ አገልግሎት ለ15ኛ ግዜ መረጃዎችን በማስረጃ አስደግፎ ያቀረቡትን አቤቱታ ከዛሬ ማታ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ጀምሮ በተለያየ ክፍል በማድረግ አቀርብላችኃለሁ::

ቅድሜ ማሳሰቢያ:
ጽሑፉ ወይም መልዕክቱ በክልሉ ውስጥ ሆኖ የመናገርና የመጻፍ መብት ስላጡና ለደህንነታቸው ስጋት ስላደረባቸው እንጅ እኔ የጻፍኩት እንዳልሆነ እንድትገነዘቡልኝ ልንግራችሁ እወዳለሁ::

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Buche Yogo posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Buche Yogo:

Share