02/01/2026
ክፍል IX
8. አቶ ደስታ ሌዳሞ የክልሉ ፕሬዝዴንት ኃላፍነት
ዘር በማጥፋትና በዞኑ በስድስት ከተሞች በመቶ ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት ውድመት እንድደርስ በማድረግ፤
ግለሰቡ ከ2011 ጥር ወር ጀምሮ በቀድሞው ሲዳማ ዞን በአሁኑ ሲዳማ ክልል በሀዋሳ ከተማ "ፖጉማ" የተባለ ህገ ወጥ ቡድን አደራጅቶ በወቅቱ ሲዳማን ሲያስተዳድሩ የነበሩትን አመራሮች ገልብጦ ሥልጣን ለመያዝ ሲያሰር ቆይቶ ሀምሌ 11/11/2011 በዞኑ በሁሉም አካባቢ ግጭት እንዲቀሰቀስ በማድረግ በዚህ ግጭት ብቻ በዕለቱና በተከታታይ ቀናት 156 ንጹሀን ዘጎች እንዲሞቱንና በዞኑ በሰላም ሰርተው የሚኖሩ ግለሰቦችን ብሄር ተለይቶ ንብረት እንድወድም አሰደርጓል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በወቅቱ በዞኑ የተቀሰቀስውን ውጥረት ለማርገብ እራሱ በተወለደበት ወደ ማልጋ ወረዳ እየተንቀሳቀሱ የነበሩ የሀገር መከላከያ ሰራዊት አባላት ላይ ጉዳት እንድደርስ አውራ ጎዳና ተቆፍሮ መንገድ ላይ መሰናክል እንድፈጠር በማስደረግ በዕለቱ ቁጥራቸው በርካታ የሆኑ የመከላከያ ሠራዊት አባላት መኪናው በተቆፈረው ጉድጓድ ውስጥ በመግባት ተገልብጦ እንዲያልቁ አስደርጓል፤፡
በመሆኑም ግለሰቡ ለሥልጣን ባለው ጫፍ የወጣ ጥማት ምክኒያት በርከት ያሉ ሰዎች እንዲሞቱ በዞኑ ለተከሰተው ሰብዓዊና የንብረት ጉዳት ግንባር ቀደም ተጠያቂ ነው፡፡በዕለቱ የተከሰተውን ግጭት ሀዋሳ ከተማ ሆኖ ወጣቶች ማስተር ማይንድ(Master Mind) ሆኖ ሲመራ በዕለቱ በደኅንነት ኃይሎች ተደርሶበት በቀድሞው ደቡብ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን ለአንድ ቀን ታስሮ መለቀቁም ይታወሳል፡፡በዕለቱ ለተፈጠረው ግጭትና የንብረት ውድመት ተጠያቂው እሱና የቡድኑ አባለት ስለሆኑ ተገቢው ምርመራ ተካሂዶ በህግ እንድጠየቅ እንዲደርግ እንጥይቃለን::
በክልሉ ውስጥም ሥልጣኑን ያለ አግባብ በመጠቀምና ለሌሎችም ለዝርፊያ በር በመክፈት አንደኛ ተዋናይና መሪ መሆኑ ማሳያዎች ብዙ ናቸው:: ለምሳሌም ከጀርመን መንግስት ለሀዋሳ ቴክኒክና ሙያ ተቋም የተላከውን ግዙፍ ማሽን ከሥራ ባለደረቦቹ ጋር በመመሳጠር በ2012 ዓ/ም እንደተሰረቀ በማስመሰል ሽጦ ተጠቅሟል፤ማሽኑ የተላከው ለወጣቶች የሙያ ስልጠና እንዲያግዝ ቢሆንም የተሰጠውን የህዝብና መንግስት አደራ ወደ ጎን በመተው እራስን ለማበልጸግ ባለው ጽኑ ፍላጎት የህዝብን ጥቅም የጎዳ በመሆኑ ተገቢ ምርመራ ተካሂዶ በህግ አንዲጠይቅ እንድደረግ እንጥይቃለን::
በ2012 ዓ/ም በሰኔ ወር መጨረሻ ለሠላሳ ስድስት ባለ ሀብቶች ከአንድ ሚሊዮን እስከ ሁለት ሚሊዮን ጉቦ ስብስቦ በመውሰድ የእሸት ቡና ፍቃድ አሰጣጥ መመሪያና ደንብ ባልተከተለ ሁኔታ በሁሉም ቡና አብቃይ ወረዳዎች ፍቃድ ሰጥቷል:: የእሸት ቡና እንዱስትሪ ፍቃድ አስጣጥ አካባቢው የነዋሪዎችን ደኅንነት ለጤና ጉዳት በማያደርስ ሁኔታ መሆን ያለበት ቢሆንም ከዚያነ ጊዜ ጀምሮ በተመሳሳይ ሁኔታ እየተሰጠ በመሆኑ ይህም ከግንዛቤ ውስጥ በማስገባት ተገቢው የማጣራት ሥራ ተሠርቶ ውጤቱ ለህዝብ ይፋ መደረግ አለበት:: በዚህ ምክንያት እስካሁን በዜጎች ላይ የደረሰውንም የጤና ጉዳት ግምት ያስገባ ምርመራ እንዲካሄድም ጭምር እንጠይቃለን::
በተጨማሪም አቶ ደስታ ለዳሞ ሥልጣኑን ያለአግባብ በመጠቀም ከእነዚህ ነጋዴዎች ጋር በመመሳጠር ለራሱ ስድሰት የእሸት ቡና እንዱስትሪ ፍቃድ በመውስድ እያስነገደ ይገኛል::የራሱ የቡና እንዲስትሪ ያሉባቸወ ወረዳዎችም ወንሾ:ሆኮ: በንሳ: ቡራ: እና አለታ ወንዶ ወረዳ መሆኑንና ከአቶ ወርቁ ቡቼ: ከአቶ ንጉሴ ገመዳ: ከአቶ ማቴዎስ ደንኤልና ከአቶ ለገሠ ላሚሶ ከተባሉ ባለሀብቶች ስም እንደሚነግድም ፍንጭ እየሰጠን ተገቢው ምርመራ እንዲካሄድ እንጠይቃለን፡፡
ስልጣኑን ያለአግባብ በመጠቀም የመሬት ሊዝ አዋጅ 721/204ን በመተላለፍ በሀዋሳ ከተማ በልማት ተነሺዎች ስም ስድስት ሺህ (6000) ካሬ ሜትር መሬት በዘመዶቹ ስም ወስዷል፡፡በራሱም ስም ደግሞ ሶስት ሺህ (3000) ካሬ ሜትር መሬት በድምሩ 9000 ካሬ ሜትር መሬት ወስዷል፡፡በእነማን ስም እንደሆነ ከዚህ ማመልካቻ ጋር አባሪ አድርገናል ማዬት ይቻላል፡፡ከዚህ ጋር በተያያዘ በሀዋሳ ከተማ የከተሞች መሬት አሰጣጥ ህግ በመጣስና ሆን ብሎ ግለሰቦችን ለመጥቀም ሲባል ለፓስተሮች እና ለወዳጅ ዘመዶች በርካታ ካሬ ሜትር መሬት እንድታደል በማድረግ የከተማው ማዘጋጃ ቤት የህግ ጥሰት እንድፈጽም አሰደርጓል፡፡ይህም ሥልጣንን ያለአግባብ በመጠቀም የተደረገ ስለሆነ በተገቢው እንዲጣራ እንጠይቃለን፡፡
በ2017 ዓ/ም የእሸት ቡና ዘመን የአርሶ አደሩ ቡና በወረደ ዋጋ እንዲገዛ ትዕዛዝ ለዞኖችና ለወረዳዎች በማስተላለፍ ለውለታው ቡና ነጋዴዎች ኮሚቴ አቋቁመው ከፍተኛ ብር ሰብሰበውለት በሀገረ አሜሪካ በሲያቲል ግዛት ቅንጡ መኖሪያ ቤት እንደተገዛለት በብዙ ታማኝ ምንጮች እየተዘገበ ይገኛል፡፡ይህም በህገ ወጥ መንገድ የተገኘ ሀብት ስለሆነ በህግ አግባብ ተጣርቶ ለህዝብ ግልጽ መደረግ አለበት፡፡ ለዝሁና ለመሳሰሉት ብልሹ አሠራር ገንዘብ ያሰባሰቡ ሰዎች ስም ዝርዝር ምርመራው ሲጀመር ለመርማሪ ቡድን የምናሳውቅ ይሆናል፡፡
ክፍል X ይቀጥላል::