The Kings Page

The Kings Page Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from The Kings Page, News & Media Website, addis ababa, Addis Ababa.

“አዲሱ የአማራ ትውልድ የራሱን መሪ ፈጥሮ የጠላቶቹን ሰንሰለት በጣጥሶ ወደ ነፃነት የሚሻገርበትን ሁኔታ የማደላደል ዓላማ ሰንቆ የተቋቋመወ የአማራ ሕዝባዊ ኃይል በተመሰረተ በአንድ ዓመት ግዜ...
28/09/2022

“አዲሱ የአማራ ትውልድ የራሱን መሪ ፈጥሮ የጠላቶቹን ሰንሰለት በጣጥሶ ወደ ነፃነት የሚሻገርበትን ሁኔታ የማደላደል ዓላማ ሰንቆ የተቋቋመወ የአማራ ሕዝባዊ ኃይል በተመሰረተ በአንድ ዓመት ግዜ ውስጥ ለአማራ ህዝብ ትልቅ ተስፋ የጣሉ በርካታ ተግባራትን መፈፀም ችሏል።
በበርካታ መሰናክሎችን አልፈን የመሰረትነው አደረጃጀት እና ለትውልዱ ያስተዋወቅነው የተደራጀ እና የሰለጠነ የፋኖ መዋቅር የመውለድ ሂደት በአራቱም ማዕዘናት የፋኖ አደረጃጀቶችን እንዲፈጠሩ እና እንዲያብቡ የህዝባዊ ኃይሉ አስተዋፅኦ ከፍተኛ በመሆኑ ኩራት ይሰማኛል።
መንግስት በህግ ማስከበር ስም የጀመረው የማሰር እና የማሳደድ ተግባር በሺዊች የሚቆጠሩትን ከህይወት መስዋዕትነት እስከ አፈና እና መዋከብ የሚያጥቃልል ዋጋ ያስከፈለ ሲሆን በተለይም የመሪያችን የአርበኛ ዘመነ ካሴ መታፈን የስርዓቱን አደገኛነት ያረጋገጠ እና ህዝባችንን ያስቆጣ ድርጊት ነው::
የአርበኛ ዘመነ ካሴን መታፈን ተከትሎ የታየው ህዝባዊ ቁጣ እና እንቅስቃሴ ትዉልዱ የኔ የሚለውን መሪ በማዳመጥ እና መሪውን በመጠበቅ በኩል ቁርጠኛ መሆኑን ያረጋግጣል።
ለመላው ህዝባችን፣ ለደጋፊወቻችን እና ለህዝባዊ ኃይሉ አባላት የአርበኛ ዘመነ ካሴን ከአፈና ነፃ መውጣት ጨምሮ ጉልህ የሆኑ የአማራ ህዝብ ጥያቄዎች እስከሚመለሱ ድረስ የአማራ ሕዝባዊ ኃይል ስራ አስፈፃሚ ትግሉን ለመምራት የሚያስችል ቁመና ላይ መሆኑን አረጋግጥላችኋለሁ።
አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ! አዲስ ተስፋ!”
ካፕቴን ማስረሻ ሰጤ
የአ/ሕ/ኃ/ ምክትል ሰብሳቢ

የአማራ ሕዝባዊ ኃይል (ፋኖ) የአማራ ህዝብ የህልውና ስጋት የወለደው አደረጃጀት ነዉ። ህዝባዊ ኃይሉ ነባሩን የፋኖነት ፍልስፍና እና ተግባር ከግዜው እና ከትግሉ ባህሪ ጋር በሚጣጣም መልኩ ለ...
23/09/2022

የአማራ ሕዝባዊ ኃይል (ፋኖ) የአማራ ህዝብ የህልውና ስጋት የወለደው አደረጃጀት ነዉ። ህዝባዊ ኃይሉ ነባሩን የፋኖነት ፍልስፍና እና ተግባር ከግዜው እና ከትግሉ ባህሪ ጋር በሚጣጣም መልኩ ለማስኬድ የተተለመ አደረጃጀት ነው::
ይህንን አደረጃጀት ስንመሰርት ታሳቢ ያደረግነውን የአማራን ህዝብ የህልውና አደጋ የመቀልበስ ታሪካዊ ኃላፊነት መወጣት የሚቻለው ደግሞ የነቃ እና የሰለጠነ ኃይል ሲኖር ብቻ መሆኑን ስለምናምን ከምስረታችን ጀምሮ ወጣቶችን በማሰልጠን እና በማደራጀት በኩል በርካታ ተግባራትን መፈፀም ተችሏል።
በተመሰረትን በአጭር ግዜ ውስጥም ከመንግስት ጎን ተሰልፈን ህዝቡን ከጥቃት ለመከላከል ባደረግነው ጥረት በርካታ ጓዶቻችን መሪር መስዋዕትነት ከፍለዋል::
ዓላማችን በአማራ ህዝብ የህልውና ትግል ውስጥ የበኩላችንን ድርሻ ከመወጣት እና ትውልዱን የትግሉ ባለቤት ከማድረግ የዘለለ አለመሆኑን በተደጋጋሚ ይፋ ከማድረጋችንም ባሻገር ከተመሰረትንበት ዓላማ ውጭ የሆነ አንዳችም ህገ-ወጥ ተግባር ባለመፈፀም ቃላችንን በተግባር አረጋግጠናል::
ይሁን እንጅ ሀቀኛ የአማራ ትግል ለጥቅማችን አደጋ ይሆናል ያሉ የመንግስት ኃይሎች እና የአማራ ህዝብ ጠላቶች ባከናወኑት የተቀናጀ ሴራ የብልፅግና መንግስት በህልውናችን ላይ ስጋት የሚደቅን ዘመቻ ከከፈተብን አራት ወራት ተቆጥረዋል::
የአማራ ህዝባዊ ኃይልን ጨምሮ ሁሉም የፋኖ አደረጃጀቶች ላይ እንዲህ ዓይነት ዘመቻ እንደሚከፈት አስቀድመን በመገንዘባችን አክሳሪ ያልሆነ መውጫ መንገድ የቀየስነው ዘመቻው ከመጀመሩ ጥቂት ቀናትን አስቀድመን ነበር::
በዚህም ምክንያት የዘመቻው ዒላማ የተደረጉ የፋኖ አደረጃጀቶች በሀገሪቱ የፀጥታ መዋቅር የአመራር እርከን ቁንጮ ላይ በደረሱ ግለሰቦች የተመራውን ኦፕሬሽን ፊት ለፊት ከመጋፈጥ ይልቅ ራስን መከላከል ላይ ብቻ የተመሰረተ የትግል ስልት እንዲከተሉ ማድረግ ተችሎ ነበር።
በዚህ ምርጫችንም ወንድማማች የሆኑትን ፋኖ እና የክልሉ ልዩ ኃይል በታቀደው ልክ እንዳይጠፋፉ ማድረግ ከመቻሉም በላይ ኦፕሬሽኑ በታሰበው መጠን አውዳሚ ውጤት እንዳይኖረው ማድረግ ተችሏል።
በወሰድነው አማራጭ ህዝቡን የእርስ በእርስ ግጭት ሰለባ ከመሆን፣ ቀጠናውን ከቀውስ እና ትርምስ ነፃ ማድረግ ተችሏል። ይህንን ኃላፊነት የተሞላበት አቅጣጫ ማስቀመጣችንም ትክክለኛ ውሳኔ እንደነበር ገምግመናል::
በመሆኑም ላለፉት 126 ቀናት በተደረገው የግድያ እና የእስር ዘመቻ ከ10 ሺህ በላይ የሚሆኑ ደጋፊወቻችን እና አባላት ለእስራት የተዳረጉ፣ ጥቂቶች ደግሞ መስዋዕትነት የተቀበሉ ቢሆንም በትንሽ መስዋዕትነት ዘመቻውን ጉልህ በሆነ መልኩ (Significantly) ማክሸፍ በመቻሉ ጉዳዩን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት በአንዳንድ ቅን አሳቢ ወገኖች የተጀመረውን እንቅስቃሴ በቀናነት ስንመለከት ቆይተናል:
ይህ በእንዲህ እንዳለ አካላዊ እና ስነ ልቦናዊ ብቃት ያለው ትውልድ ለመፍጠር የምናደርገው ጥረት ፈተና ላይ በወደቀበት እና ክልሉ ለሶስተኛ ዙር አውዳሚ ጦርነት ሰለባ በሆነበት በዚህ ወቅት የህዝባዊ ኃይሉ ሰብሳቢ አርበኛ ዘመነ ካሴ በተፈፀመበት መንግስታዊ ክህደት ምክንያት በመንግስት በመንግስት ሃይሎች እጅ ስር ወድቋል።
በህግ ማስከበር ስም ዘመቻ ከተከፈተብን ግዜ አስቀድሞም ቢሆን የድርጅታችን አመራር እና አባላት ሰላማዊ ኑሯችንን የምንመራ እና ምንም አይነት የወንጀል ተሳትፎ የሌለን እንደመሆኑ መጠን ለሰላም እና ለህዝብ አንድነት የምንሰጠውን ዋጋ በጉልህ በሚያሳይ መልኩ መሪያችን ያለ ጦር መሳሪያ ለሰላም ጥሪው የታመነ ሆኖ ከመገኘቱም በተጨማሪ በመሃል ከተማ የተኩስ ልውውጥ እንዳይደረግ በማሰብ በወሰነው ኃላፊነት የተሞላበት ተግባር ምክንያት በመንግስት ኃይሎች ሊታፈን ችሏል::
በመሆኑም:-
1/ ህዝቡ ከተደጋጋሚ ጥቃት መትረፍ እና ዓለም አቀፍ ተደማጭነት ማግኘት የሚችለው ራሱን ከጥቃት የሚከላከልበት ጉልበት ሲፈጥር እና አንድነቱን የሚሸረሽሩ ድርጊቶችን በጋራ ማውገዝ እና መታገል ሲችል ብቻ መሆኑን በመገንዘብ አርበኛ ዘመነ ካሴ ከእስር እንዲፈታ ሁሉን አቀፍ ትግል እንዲያደርግ ጥሪ እናቀርባለን::
2/ የክልሉ መንግስት ልዩነትን በጠረጴዛ ዙሪያ መፍታት ለአማራ ህዝብ ትግል የማይተካ ሚና ያለው መሆኑን እንዲገነዘብ እና በድርድር ሽፋን ያፈነውን አርበኛ ዘመነ ካሴን በአስቸኳይ በመፍታት ለህዝብ ጥያቄ እና ለሀገር ሰላም ከፍ ያለ ዋጋ እንዲሰጥ እግረ መንገዱንም የፖለቲካ ልዩነት አጥር ያልገደበው አዲስ መንገድ እንዲከተል ጥሪ እናቀርባለን::
3/ መላው የአደረጃጀታችን አመራሮች፣ አባላት እና ደጋፊወች አርበኛ ዘመነ ካሴን ጨምሮ ያለ ህጋዊ ምክንያት የታሰሩ ሁሉም የአማራ ህዝብ ታጋዮችን ለማስፈታት የምናደርገዉ ትግል እንደከዚህ በፊቱ ስክነት እና ብልሃት ያልተለየው እንዲሁም የህዝባችንን አንድነት አደጋ ላይ የማይጥል እንዲሆን ኃላፊነት በተሞላበት መንገድ እንድትንቀሳቀሱ እናሳስባለን!!!
4/ በመጨረሻም የተነሳንለት እና መስዋዕትነት የከፈልንለት ዓላማ እንደመሆኑ መጠን የአማራ ህዝብ እረፍት የሚያገኝበትን ሀገራዊ መደላድል በመፍጠር በኩል በነቢብም ሆነ በገቢር የሚኖረንን ሁለንተናዊ ሚና አጠናክረን የምንቀጥል መሆኑን እናረጋግጣለን።
የአማራ ህዝብ ህልውና በጠንካራ ህዝባዊ ተጋድሎ ይረጋገጣል!!!
አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ! አዲስ ተስፋ!
የአማራ ሕዝባዊ ኃይል (ፋኖ)

የአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ ለአቶ ሠማ ጥሩነህ ማስጠንቀቂያ መስጠቱ ተሠማየፍትሕ ቢሮው ለአቶ ሠማ ጥሩነህ ማስጠንቀቂያውን የሠጠው የኢትዮ 360 ሚዲያ ቅዳሜ መስከረም 8/2015 የአቶ ሠማን የት...
20/09/2022

የአማራ ክልል ፍትህ ቢሮ ለአቶ ሠማ ጥሩነህ ማስጠንቀቂያ መስጠቱ ተሠማ
የፍትሕ ቢሮው ለአቶ ሠማ ጥሩነህ ማስጠንቀቂያውን የሠጠው የኢትዮ 360 ሚዲያ ቅዳሜ መስከረም 8/2015 የአቶ ሠማን የትምህርት ማስረጃ ማጭበርበር አስመልክቶ በሠጠው ጥቆማ መነሻነት ተመስርቶ መሆኑ ተሰምቷል። የፍትህ ቢሮው የሙስና ወንጀሉን ማጣራት ከመጀመሩ በፊት አቶ ሰማ ተምሮበታል ከተባለው የቻይና ዩንቨርስቲ ኢንተርናሽናል ቢዝነስ ኤንድ ኢኮኖሚክስ ተምሮ የተሠጠው የ(PHD) የምስክር ወረቀት ካለ በኢትዮጵያ የትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን የአቻ ግምቱን በማሠራት እስከ መስከረም 12/01/2015 ዓ/ም ማስረጃውን ለሶስት ተቋማት እንዲያስገባ አዝዟል።
በዚህም አንደኛ ለክልሉ ፍትሕ ቢሮው፣ ሁለተኛ ለክልሉ ሲቪል ሠርቪስ ኮሚሽን፣ ሦስተኛ ለክልሉ የብልፅግና ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ማረጃውን የማያቀርብ ከሆነ ምርመራ ማጣራት እንደሚጀምር ማስታወቁ ተሠምቷል። ይህንን የሠሙ የትምህርት ማስረጃ ያጭበረበሩ ሌሎች ባለ ስልጣናት ጭምር ጭንቅ ውስጥ መግባታቸው ታውቋል።

If America and Europe cared about humanity, they would have condemned and fought against this terrorist work of the OLf,...
10/09/2022

If America and Europe cared about humanity, they would have condemned and fought against this terrorist work of the OLf, but they are political gamblers and extreme terrorists, not for humanity. God's creation must condemn this Amhara massacre and genocide in welega oromiya .

28/08/2022

ትናንት በህውሃት ወረራ የተፈፀመባቸው የደቡብ ቆቦ አካባቢዎች ሮቢትን ጨምሮ ዛሬ በጥምር ጦሩ ቁጥጥር ስር መዋላቸው ታውቋል። ወደ ወልዲያ አሰፍስፎ እየመጣ የነበረው ወራሪ ሃይል በመከላከያ፣ልዩ ሃይሉ እና ፋኖ በተወሰደበት ፈጣን የመልሶ ማጥቃት እርምጃ ፊቱ አዞሮ ቆቦን ለቆ ወደ አላማጣ በመውጣት ላይ እንደሚገኝ ተሰምቷል።በግዳን በኩል ጠዋት 4:30 ሙከራ ቢያደርግም ተመቶ መመለሱን ከስፍራው የደረሰኝ መረጃ ያመለክታል።ባለንበት ተረጋግተን አካባቢያችንን እንጠብቅ።ጥምር ጦሩን እናግዝ‼ከሌላ አቅጣጫ ሌላ ሰበር መረጃ እየተሰማ ነው።እመለሳለሁ።

28/08/2022

#የሰሜን ወሎ ዞን ዋና አስተዳዳሪው ሁሉም ካዳር ዳር በመነሳት እንዲታገል ጥሪ አቀረቡ!!!
@የሕወሃት የሽብር ቡድን በአማራ ክልል ሰሜን ወሎ ዞን ዳግም ወረራ ከከፈተ ቀናት ተቆጥረዋል፡፡
@ሕዝብን ጠላት አድርጎ የተነሳው የሽብር ቡድኑ ወረራ በከፈተባቸው አካባቢዎች በደሎችን እየፈጸመ ነው፡፡ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆችም የጠላትን ሕልም ለማምከንና ሀገራቸውን ለማጽናት እየተዋደቁ ነው፡፡
የሰሜን ወሎ ዞን ዋና አስታዳደሪ ዲያቆን ተስፋው ባታብል የሕወሃት የሽብር ቡድኑ ለሰላም የቀረበለትን አማራጭ ወደጎን በመተው ዳግም ጦርነት መክፈቱን ገልጸዋል፡፡
ጦርነቱን ጀምሮ መንግሥትን መክሰሱንም ተናግረዋል፡፡ ጠላት ከጦርነት ውጭ ሌላ ሥራ እንደሌለው ጠንቅቀን እናውቃለን ያሉት ዋና አስተዳደሪው፤ ዋነኛ ጠላታችን እንደሆነ በማንሳት መመከት የሚያስችል ውይይትና ዝግጅት ስናደርግ ቆይተናልም ብለዋል፡፡
የሽብር ቡድኑ የከፈተውን ዳግመኛ ወረራ ለመመከት የመከላከያ ሠራዊት አስደናቂ ተጋድሎ ማድረጉንም ተናግረዋል፡፡
የመከላከያ ሠራዊት፣ የአማራ ልዩ ኃይል፣ ሚሊሻውና ፋኖው ጠላትን እያረገፈው እንደሆነም ገልጸዋል፡፡
ሕዝቡ ለጀግናውን ተዋጊ ኃይል እውነተኛ ደጀን እንዲሆን እየሠሩ መሆናቸውንም አስታውቀዋል፡፡
ማኅበረሰቡ እያደረገው ያለው አስተዋጽዖ የሚደነቅ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡ የፈለገው ቢሆን ጠላት ሊያሸንፈን አይችልም፣ ጠላት የትም አይደርስም፣ ይህን የሚያደርግ ሥራ እየሠራን ነው ብለዋል፡፡
ጦርነቱ ባለበት አካባቢ ያለው ማኅበረሰብ በእልህና በወኔ ተነስቶ ጠላትን እየተፋለመ መሆኑንም ገልጸዋል፡፡
የዞኑ የሥራ ኃላፊዎች ከጸጥታ ኃይሉ ጋር በቅንጅት እየሠሩ መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ የራያ ጀግኖች አካባቢያችንን አንለቅም ብለው ከጠላት ጋር እየተዋደቁ መሆናቸውንም አንስተዋል፡፡
አብዛኛው ማኅበረሰብ ከአሁን ቀደም ከነበረው ወረራ ትምህርት በመውሰድ ከጠላት ፕሮፓጋንዳና የሐሰተኛ መረጃዎች ራሱን እየጠበቀ እንደሆነ የተናገሩት ዋና አስተዳደሪው።
ጠላት ደረሰብን እንጂ አልደረስንበትም፣ የትኛውም ማኅበረሰብ አካባቢውን ለቅቆ የትም መሄድ የለበትም፣ በጀግንነት መታገል አለበት፣ ታግሎ ማሸነፍ አማራጭ የሌለው ምርጫ ነውም ብለዋል፡፡
ሁሉም ካዳር ዳር በመነሳት መታገል እንደሚገባውም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ጀግኖቻችን በማጀገንና ከአሉባልታ በመቆጠብ ጠላትን መምታት ይገባልም ብለዋል፡፡
ለሕዝብ መድረስ ያለበትን መረጃ እናደርሳለን ያሉት ዲያቆን ተስፋ፤ ከዚያ ውጭ ባሉ ጠላት በሚያሰራጫቸው አሉባልታዎች መደናገር እንደማይገባም ገልጸዋል፡፡ ጠላት በተቀላቢ የማኅበራዊ ሚዲያ አርበኞቹ የተሳሳተ የጦርነት ዘገባና ሌሎች አሉባልታዎችን እንደሚያስተላልፍ መታወቅ አለበትም ብለዋል፡፡
በማኅበራዊ ሚደያ አሉባልታዎችን የሚያስተላልፉ ግለሰቦች ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡም አሳስበዋል፡፡ ማኅበረሰቡ ከበሬ ወለደ ወሬ ራሱን እንዲጠብቅም ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ጦርነት ወደ ፊትም፣ ወደ ኋላም ሊል ይችላል ያሉት ዋና አስተዳዳሪው፤ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ከፍተኛ ተጋድሎ እያደረጉ ነው፣ ከማኅበረሰቡ የሚጠበቀው ተዋጊውን ኃይል ማጀገን ነው፣ የፈለገ ቢሆን ጠላት የትም ሊደርስ አይችልም ነው ያሉት፡፡
ማኅበረሰቡ ከደጀንነት ባለፈ ተዋጊ ኾኖ ጠላቱን መቅጣት አለበት ብለዋል፡፡ ያለ መስዋዕትነት ድል እንደማይመጣም ገልጸዋል፡፡
በአሸናፊነት ስነ ልቦና የተገነባ ማኅበረሰብ ማሸነፉ አይቀርምም ብለዋል፡፡

28/08/2022

🙏ጥብቅ ማሳሰቢያ ለሰሜን ወሎ እና ለደቡብ ወሎ ከፍተኛ አመራሮች የተላለፈ መልእክት🙏
=================================
(ሼር ማረግ አይረሳ ሼር ይደረግ)
✅ ከትናንት ከሰአት ጀምሮ በተለይ መንግስት ቆቦን አሳልፎ ከሰጠ ቡሀላ በርካታ የከተማችን ህዝብ ሆነ የደቡብ ወሎ የሰሜን ወሎ ማህበረሰብን ያስደነገጠ መረጃ ቢሆንም ህዝባችን ግን ከመደናገጥ አልፎ በአለበት በመቀመጥ የተቻለውን እያረገ እንዳለ ከወልዲያ የደረሰ መረጃ ያመላክታል እንዲህ በእንዲህ እያለ እስካሁን ጦርነቱ በራያ ምድር ላይ እየተደረገ ይገኛል ወደ ሰሜን ወሎ ዞኖች ላለማስገባት ጥምር ጦሩ ትልቅ ተጋድሎ እያረገ መሆኑን ከስፍራው መረጃ አሁን ደርሶናል!!
✅ አሁን ከባለፈው ጊዜ አሁን መማሪያ ሰአት ላይ ተደርሷል ይህ ሰአት ለደሴ ከተማ ብቻ ሳይሆን የጦርነት ስጋት ላለባቸው አካባቢዎች በሙሉ አሁን ቅድመ ጥንቃቄ ማረግ አለብን ህውሀት እንደባለፈው ስለሆነ አሁንም የሚያረገው አሁን ከተማ መስተዳደሩ ይህን አውቃችሁ በተፈናቃይ ስም የሚመጡትን የህውሀት የፊት ደጀኖችን ልንከላከል ይገባል ስራዎች ከአሁኑ መሰራት አለባቸው!!!
✅በተጨማሪ ወሬ የሚያናፍሱ ሰዎች በዚህ ገባ በዚህ ወጣ እያሉ የሚያደናግሩ ስላሉ በአስቸኳይ እነዚህ ሰዎች በመያዝ የህውሀትን የፊት ደጀን በማቋረጥ መረጃ የሚያገኝበትን መንገድ መዝጋት ይኖርብናል!!!
✅ይህን ጥብቅ ስራ ሳይሰራ በመዘናጋት ለሚመጣ ማንኛውም ችግር ተጠያቂ መሆናችሁ ስለማይቀር ከባለፈው ስህተት በመማር አስፈላጊው ተግባር በማረግ ህዝባችንን ከባለፈው መከራ እንታደግ!!!
🙏ይህን ጥብቅ የሆነ ነገር ዛሬ ነገ ሳይባል በቶሎ ወደ ስራ በመግባት ከተሞቻችንን ከወረራ እንታደግ🙏
✅ድል ለጥምር ጦሩ እና ለእናት ሀገር ኢትዮጵያ ይሁን!!

28/08/2022

የወልዲያ ከተማ አስተዳደር
የሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ የአማራ ልዩ ኃይል፣ ፋኖ እና ሚኒሻው እየተፋለሙ ነው።
የአካባቢው ማኅበረሰብ አካባቢውን ተረጋግቶ በመጠቅ ለጥምር ጦሩ የተለመደ ሁለተናዊ ደጀንነቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል የወልድያ ከተማ አስተዳደር ጥሪውን አቅርቧል።
የጦርነቱ የፍልሚያ ቦታ እስከ አሁኗ ሰዓት ድረስ ከራያ ሚዳ አልዘለለም።
ሾልኮ ለማለፍ እና በወሬ ለመፍታት የተደረገው የጠላት ስልት እስከ አሁን ድረስ አልሰመረም።
ወልድያ ከተማ ኮሙኒኬሽን

30/04/2022
በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን አደአ በርጋ ወረዳ የኦሮሚያ ልዩ ኃይል ፖሊስ አባላት በርካታ ንጹሃን ሰዎችን መግደላቸውን ነዋሪዎች ለቢቢሲ ተናገሩ። እንደ ነዋሪዎች ከሆነ የኦሮሚያ ልዩ ፖሊ...
30/04/2022

በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን አደአ በርጋ ወረዳ የኦሮሚያ ልዩ ኃይል ፖሊስ አባላት በርካታ ንጹሃን ሰዎችን መግደላቸውን ነዋሪዎች ለቢቢሲ ተናገሩ። እንደ ነዋሪዎች ከሆነ የኦሮሚያ ልዩ ፖሊስ አባላት ትናንት አርብ ሚያዚያ 21/2014 ዓ.ም. በነዋሪዎች ላይ ግድያ የፈጸሙት ከአንድ ቀን በፊት ታጣቂዎች የኦሮሚያ ልዩ ኃይል አባላትን ከገደሉ በኋላ ነው። ቢቢሲ ያነጋገራቸው ሁለት የአካባቢው ነዋሪዎች ትናንት የተገደሉ ሰዎች ቁጥር ቢያንስ 21 ይሆናሉ ሲሉ ሌላኛው ነዋሪ ደግሞ የሟቾች ቁጥር ወደ 40 ይጠጋል ብለዋል።
https://bbc.in/3vWXr6H

በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን አደአ በርጋ ወረዳ የኦሮሚያ ልዩ ኃይል ፖሊስ አባላት በርካታ ንጹሃን ሰዎችን መግደላቸውን ነዋሪዎች ለቢቢሲ ተናገሩ። እንደ ነዋሪዎች ከሆነ የኦሮሚያ ል...

የባልደራሱ ቢንያም ታደሰ በድጋሜ ታሰረ/የአድዋና የካራማራ የድል በዓላትን ሰበብ በማድረግ ከአንድ ወር በላይ በግፍ በአባ ሳሙኤል ወህኒ ቤት ታስሮ የቆየው የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓር...
30/04/2022

የባልደራሱ ቢንያም ታደሰ በድጋሜ ታሰረ
/
የአድዋና የካራማራ የድል በዓላትን ሰበብ በማድረግ ከአንድ ወር በላይ በግፍ በአባ ሳሙኤል ወህኒ ቤት ታስሮ የቆየው የባልደራስ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ፓርቲ (ባልደራስ) አባሉ ቢንያም ታደሰ በድጋሜ በፖሊስ ታስሯል። ቢንያም ከሰሞኑ በስልጤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አማኞችና አብያተ ክርስቲያናት ላይ እየደረሰ ያለውን ሃይማኖታዊ ጥቃት ሲያወግዝና አንድነትን ሲሰብክ ቆይቷል። ወጣቱ ከዚህ ቀደም ኦርቶዶክሳውያን ሲታሰሩም ታስሮ ቆይቷል።
ቢንያም በአሁኑ ጊዜ በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የታሠረ ሲሆን በቀድሞው ማዕከላዊ፣ 3ኛ ፖሊስ ጣቢያ ይገኛል።

ኦነግ ሸኔ ከሶማሌ ክልል ሊባን ዞን ፊልቱ ወረዳ በኦሮሚያ እና በሶማሌ ክልል ድንበር አከባቢ በደርቁ ሥራ ላይ ተሰማሪቶ እየሰሩ ከነበሩ ጤና በለሞያዎች እጅ የዘረፈው አምፑላንስ ተ.ቁጥር ሱማ...
11/04/2022

ኦነግ ሸኔ ከሶማሌ ክልል ሊባን ዞን ፊልቱ ወረዳ በኦሮሚያ እና በሶማሌ ክልል ድንበር አከባቢ በደርቁ ሥራ ላይ ተሰማሪቶ እየሰሩ ከነበሩ ጤና በለሞያዎች እጅ የዘረፈው አምፑላንስ ተ.ቁጥር ሱማ 01692 በምስል የምትመለከቱት መኪና ነው::

Address

Addis Ababa
Addis Ababa
1212

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when The Kings Page posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to The Kings Page:

Share