Al ሀበሻ TV

Al ሀበሻ TV Al Habesha TV

ሁለት የነዳጅ ማጣሪያ ብቻ ያላት እዝ ራኤል የሀይፋው በኢራን ነዷል:: የዚህ ዓለም ሕግ በትክክል የሚፈርደው እኩል ቀበቶ ስትታጠቅ እንጂ "ልብ አድርጉልኝ" ስትል አይደለም:: > እንዲል መን...
15/06/2025

ሁለት የነዳጅ ማጣሪያ ብቻ ያላት እዝ ራኤል የሀይፋው በኢራን ነዷል:: የዚህ ዓለም ሕግ በትክክል የሚፈርደው እኩል ቀበቶ ስትታጠቅ እንጂ "ልብ አድርጉልኝ" ስትል አይደለም:: > እንዲል መንጊዬ መንጌዋ እየተደበደብክ ከመሞት እየተደባደብክ የሚሆነውን አብሮ መጠባበቅ ይሻላል::

ስያሜ ብቻ ሳይሆን አምሳያም የታጣላቸዉ የህገወጦች ጉዳጉድ ከመስጂድ ፈረሳ እስከ ሁከት ቅስቀሳ !!የወላይታ ህዝብ አንድ ተረት አለዉ "ከገደሉት ሬሳ የጎተቱት የበለጡት ጨካኞች ናቸዉ " ይላሉ...
01/06/2023

ስያሜ ብቻ ሳይሆን አምሳያም የታጣላቸዉ የህገወጦች ጉዳጉድ ከመስጂድ ፈረሳ እስከ ሁከት ቅስቀሳ !!

የወላይታ ህዝብ አንድ ተረት አለዉ "ከገደሉት ሬሳ የጎተቱት የበለጡት ጨካኞች ናቸዉ " ይላሉ ታዲያ ምን ለማለት ነዉ ብዙ ሌባ አይተናል ብዙ የማፍያ ፊልምም ታይቷል ምድር ላይ ግን በሂወት ዘመን ራሱ ነፃ አዉጪ ግንባር አድርጎ ለአመታት ሙስሊሙን ሲያሞኝ የነበረዉ ዛሬ መጅሊስ ግቢ በአሙዝ የተረከበዉ አይነት አምሳያ የለሽ አስመሳይ ቲያትረኛ ታይቶ አይታወቅም ፡፡

የተውኔቱን አለም በማስመሠልም የማይጨበጥ ልቦለድ ላይ ጎበዝ መሆናቸዉ መቼም ለሚከተለዉ ዑማ በተግባር አሳይተዉ እጅን በአፍ አስጭነዋል ።

መስጂድ ካፈረሰዉ በላይ መስጂድ ፈረሳዉ በመጠቀም የራሱን ኦፖርቹኒቲ ለመጠቀም ከሚሠራ በላይ ፀያፍ ነገር የለምና ነዉ ፡፡ ነገርን ከስሩ እንዲል ሁሉንም ከስሩ ለማሳየት ወደናል ፡፡

ካፈርኩ አይመልስኝ ይላችሗል ይሄ ነው ።የተደራጀ ሌባ ለመጀመርያ ጊዜ እራሱን ያጋለጠበት በታሪክም የነዚህ ሰዎች ታሪክ ይመስላል ።ሀጂ ሱልጣን አማንና መሀመድ አባተ መሳጂዶች ከባለሀብት ጋር አንዴ በናዚርነት አንዴ በልማት ሲሉ የመቸርቸራቸዉና ከመንፈሳዊነት ይልቅ የዱንያ መወዳደሪያ ማዕከል ማድረጋቸዉና እያደረጉ እንደሚገኝ ፀሀይ የሞቀዉ ሀቅ ነዉ ፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ዋናዉ ነገር ግን ላለፉት አመታት አዲስ አበባ መጅሊስን የመራው ሱልጣን አማን ና መሀመድ አባተ ናቸው የሰሩት በደል ያፈጠጠና ያገጠጠ የአደባባይ የሚታይ የሚሠማ ሀቅ መሆኑ ነው ።

ይኸዉ እነ ሀጂ ሱልጣንና መሀመድ አባተ የሚመራዉ የአዲስ አበባ መጅሊሱ እኔ በስያሜ እኛ ሙስሊም ነን አስተዳደራዊ ጉዳዮች ስለሆነ ሁሉም በእኩል ያለ አድሎና መድሎ እናስተዳድራለን ሲሉ ሲለፍፉ የከረሙቱ ዛሬ ግን ተቋሙ በእጃቸዉ ከገባበት ዕለት አንስቶ ሙስሊሙን አንድ ከማድረግ ይልቅ ተከባብሮ አስተምህሮ ሲሠጥባቸዉ የነበሩ መሳጂዶችና መድረሳዎች እነ ሱልጣን አማንና መሀመድ አባተ በሚፅፉት ደብዳቤ የሰዉ ደም መፍሰሻ ፣ ከዲን ቦታነት ይልቅ የሁከት የረብሻ የጥል ሜዳ ሆነዉ መሳጂዶች ሰላም ከራቃቸዉ ሰንበትበት ብሏል ፡፡

በዚህ ረገድ በከተማዋ በተለያዩ ቦታዎች ክፍለከተሞች ሀጂ ሱልጣን አማንና መሀመድ አባተ በየ ፖሊስ ጣቢያዉ በመሄድ ሙስሊሞች በጅምላም በተናጠልም በማሣሠር ከምንግዜዉም በላይ የሙስሊሙ አንድነት እያላላዉ ወደ መበጠስ እየሄደ ይገኛል ፡፡

ቁርዓኑ ችግሮቻችሁ አጥብቡ እንደ ገመድም በላኢላሃኢለላህ ቃል ተያያዙ አትለያዩ ቢልም ገመዷን ቆርጠዉ ሙስሊሙን እገደል ለመክተት እየተንደረደሩ ይገኛል ፡፡

በዚህ ህገወጥ መጅሊስ ሳቢያ በርካታ ኢማሞች ፣ ሙዓዚኖች ከስራ ገበታቸዉ ተፈናቅለዋል አሳስረዉም የተለቀቁ መኖራቸዉ የምንሰማዉ ሀቅ ሆኗል ፡፡ የአዲስ አበባ መጅሊስ ከአስተዳደራዊ አጀንዳ አልፎ በሙስሊሙ አይነኬ የሚባሉ የልዩነት አጀንዳዎችን በማንገብ ተቻችሎ የመኖር እሴትን ጭምር በመጣስ ሙስሊሙን አዋኪ ድርጊት በመፈፀም በአዲስ አበባም የሰላምና መረጋጋት እንዳይኖር እያደረገ የሚገኝ ጉዳይ ሆኗል ፡፡

በዚህም የከተማ የፀጥታ አካላት በአዲስ አበባ መጅሊስ በሚፃፉላቸዉ ደብዳቤ ከህግ አግባብ ዉጪ መስጂዶች አካባቢ በሚደረጉ ከመጅሊሱ ተልዕኮ ዉጪ የሆኑ ተግባራት የቀኖና ጉዳይ ዉስጥ መግባትና ማስፈፀም ተከትሎ ሙስሊሙ በአንድነት ፊቱ መንግስታዊ ወደሆኑ ልማቶችና ሀይማኖታዊ ልማቶች ላይ እንዳያተኩር በማድረግ ረገድ የሱልጣን አማንና መሀመድ አባተ አፍራሽና በታኝ እንቅስቃሴ ዋና መንስኤ ነዉ ማለት ይቻላል ፡፡ በመሠረቱ ይህን ስንል አቅል ያለው ከቡድንተኝነት ወጥቶ ትክክለኛዉን ሀቅ በህሊናው ሚዛን ላይ እንዲያስቀምጥ ብቻ ነዉ ፡፡

በስትክክልም ማንሳት የፈለግነዉም የሀቅ ጉዳይ እንጂ የመነሀጅ የሱፊ ሰለፊ ጉዳይ አይደለም ፡፡ ይልቅ ትላንት ዛሬ የማያዩ የመሠላቸዉ አንድ ነን ከሱፊ ሰለፊ በላይ እስልምና ያሰባስበናል በማለት ሲያራግቡ ሀቅ ነዉ ብላችሁ ተከትላችሗቸዉ የነበራቹ ያሰባሰባቹ ኢስላም ሀቀኝነትንና ፍትሀዊነትን ከቸራቹ የህሊና ፍርዱን ለናንተ ልንሰጥም ወደናል ።

በቀድሞ መጅሊሶች ታሪክ ኢማም ሙዓዚን አንተ ሰለፊያ ነህ ተብሎ ፣ በቢስሚላ አትጀምርም ዱዓ አታደርግም ተብሎ የታሰረበት ታሪክ አለ ወይ ? ወጣቶችን በስም ዝርዝር ለየፀጥታ ጣቢያ በመስጠት ለማሣሠር የሚሠራ በዚህ የተጠመደ መጅሊስስ ነበረን ወይ ?

ይሄ ሁሉ በየትኛዉም የሊቃዉንቶቹ መጅሊስ ታሪክ አልተሰራም ተሰርቶም አይታወቅም ፡፡ ታዲያ ከዚህ በላይ ሙስሊም ከፋፋይነት ከየት ሊመጣ ? አምሳያስ ሊኖረዉ ? .....ድንቄም የአንድነት መጅሊስ እዉነታዉ የሙስሊሙ ክፍተት ከለት ተለት እየሰፋ ከመቼዉም ግዜ በበለጠ ለያዥና ለገናዥ አስቸጋሪ የሆነበት ደረጃ ደርሷል ፡፡

ምናልባት በዚህ የቀጠለ የሚሄድ ከሆነ በቀጣይ ለመስጂድ ለሀይማኖቱ እሴቶች ግድ የማይሰጠዉ አለፍ ሲልም ቀጣዩ Generation/ትዉልድ ወደ Ethiest አቋም እንዳይነጉድ እንደ ሙስሊም ስጋቶች አሉን ፡፡አሁን እያየነዉ ያለዉ እየታዩ ያሉ ነገሮች የሚያሳዩ ምልክቶች ስላሉ ፡፡

ስለዚህ ይህንን መጅሊስ አምርረን ልንታገለዉ የሚገባዉ ለዚህም ጭምር ለወደፊቱ ለሙስሊሞች ስጋት የመሆን እድሉ ሰፊ በመሆኑ ነዉ ፡፡

በዚህ ረገድ መጅሊሶቹ አምሳል የሌላቸዉ የህገወጥ ቁንጮ በመሆናቸዉ የሚያስተዳድሩት ህዝብም ይሁን ሀይማኖት ግድ አይሰጣቸዉም ይህንን በተመለከተ ህዝቡን የሚመጥኑ ዑለሞች የሚመሩት ህዝባዊ መጅሊስ በፍጥነት ለሙስሊሙ ያስፈልጋል ፡፡

!!

!!

የወሀቢያ መጅሊስ ይፍረስ
31/05/2023

የወሀቢያ መጅሊስ ይፍረስ

7 ሰው ታሰረበዛሬው እለት ጀርመን አደባባይ አቅራቢያ በሚገኘው ፈላህ መስጊድ ውስጥ ህገወጡ የአዲስ አበባ መጅሊስ መልምሎ ለሁከት  ያሰማራቸው ግለሰቦች ባስነሱት ረብሻ የአካባቢው ሙስሊም ላይ...
19/05/2023

7 ሰው ታሰረ

በዛሬው እለት ጀርመን አደባባይ አቅራቢያ በሚገኘው ፈላህ መስጊድ ውስጥ ህገወጡ የአዲስ አበባ መጅሊስ መልምሎ ለሁከት ያሰማራቸው ግለሰቦች ባስነሱት ረብሻ የአካባቢው ሙስሊም ላይ ድብደባ ፈፅመዋል። መስጊዳቸውን ከወራሪው ህገወጥ ቡድን ለመከላከል ወደ መስጊድ እየመጡ የነበሩ 7 ሰዎች ታስረዋል። 2 ልጅ የሚያጠቡ እናቶች ሲሆኑ 5 ወንዶች ናቸው።

መሀመድ አባተ እና ሱልጣን አማን ከዚህ ቀደም ከ20 በላይ የቢላል ቁጥር 2 እናቶችን ማሳሰራቸው የሚታወስ ሲሆን በዛሬው እለት 2 ጡት የሚያጠቡ እናቶችን አሳስረዋል። እነዚህ ህገወጥ ሙስሊሙ ያልወከላቸው አረመኔዎች በእያንዳንዱ በሚሰሩት ወንጀል ህግ ፊት ቀርበው የሚጠየቁበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም።

13/04/2023

የረመዳን 20ኛ ቀን ዋነኛ ትዉስታ ‹‹ፈትህ መካ›› የተባለዉ ታሪካዊ ድል ነዉ፡፡ በስምንተኛዉ ዓመተ ሂጅራ (ጃንዋሪ/630) በነብያችን (ሶ.ዐ.ወ) የተመራዉ የሙስሊሞች ሀይል የመካ ከተማን የተቆጣጠረበት ዕለት ሲሆን በዐረብያ ምድር የጣኦት አምልኮ ዋነኛ ምሽግ ተደርምሶ እስልምና በቀጠናዉ የበላይነቱን ያረጋገጠበት ክስተት ነዉ፡፡ በዘመቻዉ 10 ሺ ያህል ሙስሊሞች ተሳትፈዋል፡፡ መካን ለመቆጣጠር ባደረጉት በዚህ እንቅስቃሴ ከተቃራኒ ወገን ይህ ነዉ የሚባል ተቃዉሞ አልገጠማቸዉም፡፡ የዘመቻዉ ምክንያት ቁረይሾች ‹‹ሁደይቢያ›› የተሰኘዉን በጦርነት ያለመፈላለግ ዉል ማፍረሳቸዉ ነበር፡፡ ድሉን ተከትሎ በሺዎች የሚቆጠሩ ጣኦታዉያን እስልምናን ተቀላቅለዋል፡፡ ሀይማኖቱ በፍጥነት ተስፋፍቷል፡፡ ከዐረብያ ምድር ዉጭ የሚያደርገዉን ግስጋሴ ፍጥነቱን ጨምሮለታል፡፡ በዕለቱ ከታዩ ትኩረት ሳቢ ክስተቶች መሀል፡-

 አሸናፊዉ የሙስሊሞች ሠራዊት ወደመካ የገባዉ እንደድል አድራጊ ሀይል እየፎከረና እየሸለለ ሳይሆን ልክ እንደተሸናፊ አንገቱን ደፍቶ፣እያለቀሰና አምላኩን እያመሰገነ በከፍተኛ ዲሲፕሊን ነበር፡፡ ይህ ድርጊቱ የሺዎችን መካዉያን ልብ ማረከ፡፡ ብዙም ሳይቆዩ ‹‹አፍዋጀን›› ወደአላህ ዲን ጎረፉ፡፡

 ‹‹ወለላዬ›› (ሶ.ዐ.ወ) ለዓመታት ያሳደዷቸዉን፣የወጓቸዉን፣የበደሏቸዉን የመካ ባላባቶች በሙሉ ይቅር በማለት አስደደናቂ የምህረት ጀብዱ ፈጸሙ፡፡ ‹‹ረህመተን ሊልዐለሚን›› የተሰኘዉ ዋነኛ ገጽታ ከነሙሉ ዉበቱና ግዝፈቱ ተገለጠ፡፡

 ሰይድ ቢላል እብን ረባህ ከካዕባ አናት ላይ ወጥተዉ አዛን እንዲያሰሙ የተደረገበት ሁነት የሰብአዊ እኩልነትን ዕሴት ያጸና እጅግ ማራኪ ትእይንት ነበር፡፡ ሀበሻ የዚህ ትዕይንት ዋነኛ ባለቤት ሆና በታሪክ ተመዝግባለች፡፡ ያበሻ አካል መሆናችንን ለምንቀበልና በዚህም ለምንኮራ ሁሉ ክስተቱ ልባችንን በሀሴት የሚሞላ፣ በኢትዮጵያዊነት ኩራት የሚያንጎማልል ነዉ፡፡

 ዉዳችን (ሶ.ዐ.ወ) ወደካዕባ በማምራት ከዉስጡ የነበሩ ጣኦታትን ሰባበሩ፡፡ በነብዩ ኢብራሂምና በልጃቸዉ በኢስማዔል ለ‹‹ተዉሂድ›› ዓላማ ዳግም የታነጸዉ ካዕባ ከጣኦታት ጉድፍ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ጸዳ፡፡ የሰዉ ልጅ ከአምላክ የተቸረዉን ክብርና ማዕረግ ትቶ ለእንጨት፣ ለዲንጋና ለተፈጥሮ ክስተቶች ሲሰግድ የመባጀቱ ነገር ሲያስቡት የሚደንቅ ነዉ፡፡

 ‹‹ዘይኑል ዉጁድ›› (ሶ.ዐ.ወ) የዚህን ሀይማኖት መሠረታዊ ዕሴቶች ያሰመረ መሳጭ መልዕክት አስተላለፉ፡፡

 በዕለቱ በርካታ ታዋቂ ሰዎች የሰለሙ ቢሆንም ‹‹ያልቃሻዉ ዛሂዱ›› የሰይድ አቡበክር ሲዲቅ አባት አቡቁሀፋ መስለማቸዉ ለኔ የተለየ ስሜት ይሰጠኛል፡፡ ሰይድ አቡበክር በእጅጉ ሲጓጉለት የነበረ ጉዳይ ስለሆነ የርሳቸዉ ደስታ ከሰይዲ ደስታ ቀጥሎ ሊገመት የማይችል ዋጋ አለዉ፡፡

በአካልም ባይሆን በዕምነትና በስሜት የዚህ ድንቅ ትዕይንት አካልና የመልካም ዉጤቱም ተቋዳሽ መሆን፣ የተቀደሰ ሀይማኖቱን መሸለም መታደል ነዉ፡፡ ለኛ ለሀበሾች ደግሞ ከዚህ በተጓዳኝ ከካዕባ አናት ላይ የመዉጣት የኢትዮጵያዊነት ክብርና ሞገስ ስላጎናጸፈን ዕለቱ የተለየ ትርጉም አለዉ፡፡ ስለሀገራችን ያለንን አተያይ ከተሰጣት ክብርና ሞገስ አኳያ በመፈተሸ እንድናስተካክልም ዓመታዊ ማስታወሻ ነዉ፡፡ ሀበሻ ለሶሀቦች ስደት መመረጧ፣ በታላቁ ነብይ፡ ‹‹የዕዉነት ምድር›› መባሏ፣ ‹‹የጀነት ወንዝ›› የተሰኘዉ የአባይ (የጊዮን) መፍለቂያ መሆኗ፣በአንድ ወይም በሌላ መንገድ ከኛ ጋር የሚገናኙ ከ20 በላይ የቁርአን አንቀጾችና ከ30 በላይ ሀዲሶች መነገራቸዉ ያጋጣሚ ጉዳይ አይመስለኝም፡፡

እናማ የዚህ ሁሉ ታሪክ ቋትና ባለቤት ስለሆነችዉ ሀገራችን ሠላምና አንድነት እንትጋ፤ ለህልዉናዋ ስጋት የሆነንና የህዝቧን ደህንነት አደጋ ላይ የሚጥልን ማንኛዉም አካል በፅናት እንፋለም፤ ክብሯን የሚመጥን የመንግስት ሥርዓት ዕዉን እንዲሆን ያለመታከት እንታገል፡፡ ‹‹ፈትህ መካ››ን ዕዉን ያደረገ አምላክ ለሙስሊሙ ዓለም ዘመኑን የዋጀ ሌላ ‹‹ፈትህ›› እንዲለግስ፣ እንዲሁም በሀገራች የሚስተዋሉ ያልተገቡ ነገሮችን አስወግዶ፣ ጀርባዋን ያደቀቀውን የመከራ ሸክም አንስቶ፣አድማሷን የሸፈነዉን ጽልመት ገፎ ‹‹ሀገራዊ ፈትህ›› እንዲያጎናጽፋት ዱዐ እናድርግ፡፡

Lebawechu ባለፈው አምት በሙፍቲ የሚመራው መጅሊስ ለሀጅ የሚያስፈልገው ገንዘብ 185,000 ብር ነው ሲል የወሀቢያው ኡመት ጮኸ ኡ ኡ ኡ ኡ ያዙን ልቀቁን አለ:: ጋሽ ጡልቅም መጅሊሱን ...
31/03/2023

Lebawechu ባለፈው አምት በሙፍቲ የሚመራው መጅሊስ ለሀጅ የሚያስፈልገው ገንዘብ 185,000 ብር ነው ሲል የወሀቢያው ኡመት ጮኸ ኡ ኡ ኡ ኡ ያዙን ልቀቁን አለ:: ጋሽ ጡልቅም መጅሊሱን ለኛ ስጡን የሀጅ ዋጋ በደምብ እንቀንሳልን አሉ::

ዘንድሮ ጋሽ ቱፋ ጡሉቅ ብለው መጅሊስ ገቡና ለሐጅ 315,000 ካላመጣቹ መንገድ የለም አሉ የወሀብያው ኡመት አፉን ሸብቦ ዝም ጪጭ አለ

የሚገርመው ደግሞ በተለያዩ ምክንያቱች ምንዛሬ ከዘንድሮ ያለፈው አመት ይበልጥ ተወዶ ነበር

በሀገራችን ከተከሰቱ የረመዳን ጸጋዎች  መካከል የታላቁ የሀበሻ ሊቅ የከቢር አህመድ መወለድ ይገኝበታል፡፡ በ1295 ሂጅሪ በወርሀ ረመዳን 5 ቀን በዕለተ ሀሙስ ንጋት ላይ (የዛሬ 149 ዓመታ...
31/03/2023

በሀገራችን ከተከሰቱ የረመዳን ጸጋዎች መካከል የታላቁ የሀበሻ ሊቅ የከቢር አህመድ መወለድ ይገኝበታል፡፡ በ1295 ሂጅሪ በወርሀ ረመዳን 5 ቀን በዕለተ ሀሙስ ንጋት ላይ (የዛሬ 149 ዓመታት አካባቢ) ነበር የተወለዱት፡፡ ከትግራይ (ዐዲ ከርቢ) አባትና ከወሎየ እናት የተገኙ፣ ለሀበሻ የተሰጡ የረመዳን ችሮታ ናቸዉ፡፡ ከሙፍቲ ዳዉድ ጋር በእናታቸዉ በኩል ይዛመዳሉ፡፡ በተለያዩ የሸሪዐ ዕዉቀቶች አንቱ የተባሉ ሊቅ ነበሩ፡፡ በተለይ በሀዲስ ዕዉቀት አቻ አልነበራቸዉም፡፡ ዝናቸዉ በሀገራችን ሊቃዉንት ዘንድ ከዳር ዳር ናኝቷል፡፡ በማስተማር ሂደት በርካታ ሊቃዉንትን አፍርተዋል፡፡ የኖሩት በ‹‹ደዌ››/ ‹‹ገዶ›› በተባለዉ ቀዬ ዉስጥ ነዉ፡፡ ከድርሳኖቻቸዉ መካከል ‹‹ጦርፈቱል ሙሂብ›› የተሰኘዉ ይገኝበታል፡፡ ድንቅነቱ ተመስክሮለታል፡፡ በርከት ያሉ የዉዳሴ ነቢ (መድህ) መድብሎችንም አዘጋጅተዋል፡፡ በአበልቃሲም የተሰጣቸዉ ተከታዩ እማኝነት ከፍታቸዉን ይመሰክራል (ኢዕላም…ገጽ 232)፡-

كان من أكابرأعيان الحبشة، فقيها محدثا مفسرا أصوليا عالما بالفنون العربية، عارفا بعلم القراءة والتجويد، قوالا بالحق محاربا للبدع، زاهدا عابدا حافظا للقرءان الكريم … وانتهت إليه الرحلة والرياسة في الحديث في الحبشة بأسرها من غير مزاحم.

‹‹ካበሻ ጉሉሀን መካከል አንዱ ነበሩ፡፡ የፊቅህ፣ሀዲስ፣ተፍሲር፣ ኡሱል፣የዐረብኛ ቋንቋ የዕዉቀት ዘርፎች ሊቅ፣የቁርአን ንባብ ህግጋት አዋቂ፣ሀቅን ተናጋሪ፣ ብልሹ ፈጠራን ተዋጊ፣ዓለማዊ ህይወትን የናቁ፣የተቀደሰዉን ቁርአን በአዕምሯቸዉ የያዙ፣….በሀዲስ የዕዉቀት ዘርፍ በሀበሻ በሞላ ያለተጋሪ የዘመናቸዉ ቁንጮ፤››

ከባድ ምስክርነት ነዉ፡፡ ለዚህች ሀገር ሀይማኖታዊና ሀገራዊ ዕሴቶች መጽናት የበዛ አበርክቶ አላቸዉና ስማቸዉን ማዉሳት ሊደረግላቸዉ ከሚገባዉ ነገር በጣም ትንሹ በመሆኑ እነሆ የወርሀ ረመዳንን አጋጣሚ በመጠቀም ዘክረናቸዋል፡፡ አላህ ጀነተል ፊርደዉስ ይወፍቃቸዉ፡፡ እነርሱ ያጸኗቸዉን ዕሴቶች የመጠበቅ፣ያቆዩትን ‹‹ዲን›› የማስቀጠል፣ ዘመንን ከዋጀ ጥበባቸዉ የመማር አቅም ይስጠን፡፡

‹‹ታሪኬ አልተጻፈም›› ከሚል አጓጉል ሙሾና የሌሎችን ጥረት ከማጣጣል አሉታዊነት ይልቅ የጎደለዉን በማሟላት በጎ መንፈስ ከነርሱ በኩል የሚጠበቀዉን በማደድረግ ይህንና ሌሎች ታሪኮችን ላሻገሩልን ሊቃዉንቶቻችንም አላህ ጀዛቸዉን ይክፈላቸዉ፡፡

በተወዳጁ ነብይ (ሶዐወ) ላይ ሰላዋት ማበርከቱ ጥቅሙን ክቡርነታቸው ዛሬ ጁሙዓ ላይ ተናግረው ነበርዛሬ ዒፍጣር ከሳቸው ጋ አሏህ አድሎኝ ነበረና ስለሰላዋቱ ጠየኳቸውተወዳጁ ነብይ (ሶዐወ)የኑር...
31/03/2023

በተወዳጁ ነብይ (ሶዐወ) ላይ ሰላዋት ማበርከቱ ጥቅሙን ክቡርነታቸው ዛሬ ጁሙዓ ላይ ተናግረው ነበር
ዛሬ ዒፍጣር ከሳቸው ጋ አሏህ አድሎኝ ነበረና ስለሰላዋቱ ጠየኳቸው
ተወዳጁ ነብይ (ሶዐወ)የኑር ሳጥን አላቸው
በተወዳጁ ነብይ (ሶዐወ)ላይ አንድ ሰው ሁሌም ሰላዋት ሲያበረክት ስሙ ከነ አባቱ እናቱ አጎቱ ቤተሰቦቹ ጭምር በተወዳጁ ነብይ (ሶዐወ) የኑሩ ሳጥን ውስጥ ይቀመጣል
የአሏህ ስራ ይህን እየፃፍኩ ሳልጨርስ የተወዳጁ ነብይ (ሶዐወ) ስጦታ ደረሰኝ
Jaza akum ALLAH heyr habibi 💚
💚አላሁማ ሰሊ ዓላ ሙሀመድ ወዓላ ዓሊ ሰይዲና ሙሀመድ💚

ምንም የማያውቁ መሻኢኮቻችንን ዒማሞቻችንን ከመስጂድና ከዒልም ማዓድ ላይ አስነስቶ በደህንነቶች ማሳፈን ያውም በዚህ በራህመተኛው ወር በረመዷን 😭ህገወጡ መጅሊስ የሚመክረው አጥቷል ምናለ ረመዷ...
24/03/2023

ምንም የማያውቁ መሻኢኮቻችንን ዒማሞቻችንን ከመስጂድና ከዒልም ማዓድ ላይ አስነስቶ በደህንነቶች ማሳፈን ያውም በዚህ በራህመተኛው ወር በረመዷን 😭

ህገወጡ መጅሊስ የሚመክረው አጥቷል ምናለ ረመዷኑን እንኳን ሰው በሰላም እንዲፆም ቢፈቅዱለት😭

የምንለቃቸው መረጃዎች ህዝብ ጋር ተደራሽ እንዲሆን ሁላችንም ሼር በማድረግ እንተባበር

በዚህ ፔጅ የሚለቀቁ መረጃዎች ተደራሽ እንዳይሆን የሚቻላቸውን እያደረጉ ስለሆነ እኛም በቻልነው አቅም እንረባረብ!

ጾም ሶስት እርከኖች እንዳሉት ‹‹ዐሪፎች›› ይናገራሉ፡-1. ዝቅተኛዉ እርከን፡- ከምግብ፣ከመጠጥና ከፍትወት ታቅቦ መዋል፤ ‹‹ሶዉሙል ዑሙም›› (የአብዛኛዉ ሰዉ ጾም) ይሉታል፡፡ 2. መካከለኛ...
23/03/2023

ጾም ሶስት እርከኖች እንዳሉት ‹‹ዐሪፎች›› ይናገራሉ፡-

1. ዝቅተኛዉ እርከን፡- ከምግብ፣ከመጠጥና ከፍትወት ታቅቦ መዋል፤ ‹‹ሶዉሙል ዑሙም›› (የአብዛኛዉ ሰዉ ጾም) ይሉታል፡፡

2. መካከለኛ እርከን፡- ዐይንን ክፉ ከማየት፣ ጆሮን ክፉ ከማድመጥ፣አንደበትን ክፉ ከመናገር፣እጅን ሀራም ከመጨበጥ፣ እግርን ወደሀራም ከመጓዝ ማቀብ፤ ‹‹ሶዉሙል ኹሱስ›› (የተመረጡ ሰዎች ጾም) ወይም ‹‹ሶዉሙ ሷሊሂን›› (የደጋጎች ጾም) ሲሉ ይጠሩታል፡፡

3. ከፍተኛዉ እርከን፡- ቀልብን ከክፉ ሀሳብ፣ከዚያም አልፎ ከአላህ ዉጭና ለአላህ ካልሆኑ፣ብሎም ግባቸዉ ዓለማዊ ብቻ ከሆኑ ሀሳቦች ማቀብ፡፡ ‹‹ሶዉሙ ኹሱሲል ኹሱስ›› (በጣም የተመረጡ ሰዎች ጾም) ሲሆን ዑለሞች ‹‹የነብያት፣የሲዲቆችና የሙቀረቦች እርከን›› ብለዉታል፡፡

የመጀመሪያዉን እርከን አብዛኛዉ ሙስሊም ይጋራል፡፡ ጥቂቶች ተነጥለዉ ወደሁለተኛዉ እርከን ከፍ ይላሉ፡፡ በጣም ጥቂቶቹ ብቻ ነጥረዉ በመዉጣት ከሶስተኛዉ እርከን ላይ ይነግሳሉ፡፡

እያንዳንዱ ሰዉ የሚገኝበትን እርከን በሚገባ ያዉቃል፡፡ እናም ሰዎች ስለኛ ያላቸዉን ግምት ወደጎን ትተን ‹‹መን ተሸበሀ ቢቀዉሚን…›› እንደተባለዉ ከ‹‹ሷሊሆች›› ለመመሳሰል ከመትጋት በስተቀር ሌላ ምን አማራጭ አለ?!


اللَّهُمَّ أعِنَّا عَلَى ذِكْرِكَ، وَشُكْرِكَ، وَحُسْنِ عِبَادَتِكَ

ለክቡር ዶ/ር ሙፍቲ ሀጅ ዑመር እድሪስ፣ረመዳን ሙባረክ፤ እንኳን በሰላም አደረስዎት፤ አላህ እድሜና ጤና ይስጥልኝ፤
23/03/2023

ለክቡር ዶ/ር ሙፍቲ ሀጅ ዑመር እድሪስ፣

ረመዳን ሙባረክ፤ እንኳን በሰላም አደረስዎት፤ አላህ እድሜና ጤና ይስጥልኝ፤

22/03/2023

Address

Merkato
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Al ሀበሻ TV posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category