ብስራት ሚዲያ

ብስራት ሚዲያ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ብስራት ሚዲያ, News & Media Website, Addis Ababa.
(1)

ብስራት ሚዲያን ማገዝ ለምትፈልጉ
ንግድ ባንክ👉1000404574241
ማስታወቂያ ማሰራት የምትፈልጉ በስልክ ጥራችን 0916725040 በመደወል ያነጋግሩን !!

ብስራት ሚዲያ፦ዜና ፣ መዝናኛ ፣ ታርክ ፣ ጤና ፣ ማህበራዊ ጉዱይ .ወ.ዘ.ተ
ታማኝ እና ፈጣን ፣ የሁሉም ለሁሉም !!

በሴቶች 3ሺህ ሜትር መሰናክል ሳይጠበቅ ለሀገራችን የብር ሜዳልያ ያመጣችው ሲምቦ አለማየሁ😍
17/09/2025

በሴቶች 3ሺህ ሜትር መሰናክል ሳይጠበቅ ለሀገራችን የብር ሜዳልያ ያመጣችው ሲምቦ አለማየሁ😍

ጌቾን አለማድነቅ ይከብዳል!360 የዞረ ሁሉ ጌቾ በ360 መዞር ሲከሱት ይገርማል!!አቶ ግርማ ሰይፉ
17/09/2025

ጌቾን አለማድነቅ ይከብዳል!
360 የዞረ ሁሉ ጌቾ በ360 መዞር ሲከሱት ይገርማል!!

አቶ ግርማ ሰይፉ

ኢትዮጵያ ሰላምን ታስቀድማለች፤ ድህነትን ትፋለማለች፤ መውጫ፣ መግቢያ በሯን ታበጃለች፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ********************ኢትዮጵያ ሰላምን ታስቀድማለች...
17/09/2025

ኢትዮጵያ ሰላምን ታስቀድማለች፤ ድህነትን ትፋለማለች፤ መውጫ፣ መግቢያ በሯን ታበጃለች፡- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
********************

ኢትዮጵያ ሰላምን ታስቀድማለች፤ ድህነትን ትፋለማለች፤ መውጫ፣ መግቢያ በሯን ታበጃለች ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፤ ወንድም እህቶቻችንም ይህ አይቀሬ መንገድ መሆኑን ተገንዝበው በፈጠነ ጊዜ ለድርድር ራሳቸውን ዝግጁ እንዲያደርጉ እንጠይቃለን ሲሉ መልዕክት አስተላልፈዋል።

ኢትዮጵያን የምታክል ሀገር በሯ ተዘግቶ ለልጆቻችን መተላለፍ አለባት ብሎ ማመን ተገቢ እሳቤ አይደለም ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በመደመር መንግሥት መጽሐፍ ምረቃ ሥነ-ሥርዓት ላይ ባሰሙት ንግግር።

የኛ የሆነውን ቀይ ባህርን መልሶ ለመጠየቅ የሚሰጋ፣ የሚጠራጠር ትውልድ መፈጠሩ የሥነ ልቦና ስብራት አካል መሆኑን ያነሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ኢትዮጵያ የጂኦግራፊ እስረኛ ሆና ለዘለዓለም ትኖራለች ብሎ የሚያስብ ኢትዮጵያዊ ካለ እርሱ የሞተ ነው ብለዋል።

የቀይ ባህርን ጉዳይ ይህ ትውልድ አይችለውም ብለው የሚያስቡ አሉ፤ እኔ ግን ኢትዮጵያ እንደምትችል አረጋግጥላችኋለሁ ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ።

ይህን በምሳሌ ሲያስረዱም፥ የዛሬ 155 ዓመት ስዊዝ ካናልን በጀግኖች ልጆቻቸው ያሳኩ ሰዎች ዛሬ እፎይ ብለው በዓመት 10 ቢሊዮን ዶላር ያገኛሉ፤ ስዊዝ ካናል ሲሰራ ኢትዮጵያ፣ ደቡብ አፍሪካ ወይም ናይጄሪያ ውስጥ የሞቱ ሰዎች ነበሩ፣ ግን ታሪክ የላቸውም፤ ስዊዝ ካናልን እየሰሩ በሐሩር፣ በምግብና በመድኃኒት እጥረት የሞቱ ሰዎች ግን ዛሬም ድረስ ታሪካቸው ሕያው ነው ብለዋል።

ከእኔ እና ከናንተ መካከል ዘለዓለማዊ የሆነ፣ የማይሞት አንድም ሰው የለም፣ እኔም እናንተም ሟቾች ነን፤ ታሪክ ሰርቶ የሞተ ሰው ግን ስሙ በትውልድ መካከል ሲተላለፍ ይኖራል ነው ያሉት።

የቀይ ባህርን ጉዳይ ለማሳካት ግጭት ውይም ውጊያ ያስፈልጋል ብለን አናምንም፣ ለዚህም ነው ለ5 ዓመታት ስንለማመጥ የኖርነው፤ ይሁን እንጂ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ ሕግ መሠረት የተዘጋባትን በር ለማስከፈት እና ድሃ ያስባላትን መጠሪያ ለመፋቅ ትግሏን ትቀጥላለች ብለዋል።

በዚህ ዙሪያ በየትኛውም መድረክ ከኢትዮጵያ ጋር በሰላማዊ መንገድ ለመነጋገር የሚፈቅድ አካል ካለ ከምን ጊዜውም በላይ እጃችን የተዘረጋ ነው ሲሉ አረጋግጠዋል።

በመሀመድ ፊጣሞ

የምድር ገነቷ ሌጲስ‎  ፦ በአስደናቂ የተፈጥሮ መስህቦች፣ በፏፏቴ፣ በዱር እንስሳቶቹ በአዕዋፋቱ እንዲሁም በጥብቅ ደኑ ይታወቃል። ሌጲስ የኢኮ ቱሪዝም መንደር። ‎‎በዕደ ጥበብ ስራዎች የሚታወ...
16/09/2025

የምድር ገነቷ ሌጲስ
‎ ፦ በአስደናቂ የተፈጥሮ መስህቦች፣ በፏፏቴ፣ በዱር እንስሳቶቹ በአዕዋፋቱ እንዲሁም በጥብቅ ደኑ ይታወቃል። ሌጲስ የኢኮ ቱሪዝም መንደር።

‎በዕደ ጥበብ ስራዎች የሚታወቁት የአካባቢው ማህበረሰቦች ሌጲስን ጠብቀው ለዚህ ትውልድ አድርሰዋል።

‎በኢትዮጵያ ማዕከላዊ ስምጥ ሸለቆ ውስጥ የሚገኘውን የሌጲስ ኢኮ ቱሪዝም በተባበሩት መንግስታት የዓለም ቱሪዝም ድርጅት መንደር በዓለም ድንቅ የቱሪዝም መንደርነት ዕውቅና ያገኘው በ2016 ዓ.ም ነበር።

‎ይሁንና ምን ያህሎቻችን እናውቀዋለን? ምን ያህሎቻችንስ ጎብኝተነዋል?

‎ሌጲስ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ አርሲ ዞን ነገሌ አርሲ እና ቆሬ ወረዳዎች መካከል የሚገኝ መንፈስን የሚያድስ ድንቅ የተፈጥሮ መስህብ ስለመሆኑ የውጭ ሀገራት ጎብኚዎች ይመሰክራሉ።

‎ለዘመናት ተጠብቆ የቆየው ዓመታዊ የፈረስ ጉግስ የሚካሄድበት ስፍራ ሲሆን፤ በጫካ የተከበበው ወንተሼ ሜዳ የብዙዎችን ቀልብ የሚገዛው የሌጲስ መንደር መስህብ ነው።

‎ከወንጪና እና ከጮቄ የኢኮቱሪዝም መንደሮችን ቀጥሎ በዓለም ድንቅ የቱሪዝም መንደርነት የተመዘገበችው ሌጲስ ለእግር ጉዞና ተራራ መውጣት ለሚፈልጉ ጎብኚዎች ምቹ ስፍራ ነች።

‎ውጤቴን ስሰማ በጣም ደንግጫለው ፥ ተማሪ ካሊድ በሽር ‎‎  ፦ የዶዶላ ኢፈ ቦሩ ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ት/ት ተማሪ የሆነው ካሊድ በሽር በ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና 591 በማምጣት በሀገ...
15/09/2025

‎ውጤቴን ስሰማ በጣም ደንግጫለው ፥ ተማሪ ካሊድ በሽር

‎ ፦ የዶዶላ ኢፈ ቦሩ ልዩ አዳሪ 2ኛ ደረጃ ት/ት ተማሪ የሆነው ካሊድ በሽር በ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና 591 በማምጣት በሀገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛ ውጤት አስመዝግቧል፡፡

‎ተማሪ ካሊድ በሽር በ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ፈተና ከ600 ነጥቦች 9 ብቻ በማጣት ነው በሀገር አቀፍ ደረጃ ከፍተኛውን ውጤት ያስመዘገበው።

‎ተማሪ ካሊድ በሽር
‎እንግሊዘኛ 96🔥
‎ሒሳብ 100🔥
‎ፊዚክስ 100🔥
‎ኬሚስትሪ 98🔥
‎ባዮሎጂ 99🔥
‎አፕቲትዩድ 98🔥 ውጤት አምጥቷል፡፡

‎ውጤቴን ስሰማ በጣም ደንግጫለው የሚለው ተማሪ ካሊድ፥ ማንኛውም ተማሪ ዓላማ ሊኖረው ይገባል፤ ለዓላማ መድከም ካለ ከድካም በኋላ ጥሩ ውጤት እንደሚመጣ ገልጿል፡፡

ከ585,882 የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች መሀል ያለፉት 48,920፣ የወደቁት ደግሞ 536,962 ሆነዋል። በሌላ አገላለፅ 91.6% ተማሪዎች ወድቀው 8.4% ብቻ አልፈዋል ነው። ለዚህ የ...
14/09/2025

ከ585,882 የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ ተማሪዎች መሀል ያለፉት 48,920፣ የወደቁት ደግሞ 536,962 ሆነዋል። በሌላ አገላለፅ 91.6% ተማሪዎች ወድቀው 8.4% ብቻ አልፈዋል ነው።

ለዚህ የትምህርት ስርዐቱን የሚመሩት አካላት በዋነኝነት፣ መንግስትም በየደረጃው ሀላፊነት ወስዶ ምን እየሆነ እንደሆነ ለህዝብ ሊያስረዱ ይገባል።

ይህ ከግማሽ ሚሊዮን በላይ ትውልድ ምን ሊሆን ነው? ከሰሞኑ እየታፈሰ ወደ ጦር ማሰልጠኛ እንደሚገባው ትውልድ እጣ ፈንታቸው ይሆን?

ያሳዝናል!

የወንዶች 10 ሺ ሜትር የመጨረሻዋ ቅፅበት በፎቶ🔥🔥Photo Aman
14/09/2025

የወንዶች 10 ሺ ሜትር የመጨረሻዋ ቅፅበት በፎቶ🔥🔥

Photo Aman

 #ዓለም ሲኒማ በመገናኛ ከመስከረም 4 - 8 የፊልም እና ቴአትር ፕሮግራም 🍿 🥤 09 86 95 95 95
13/09/2025

#ዓለም ሲኒማ በመገናኛ ከመስከረም 4 - 8 የፊልም እና ቴአትር ፕሮግራም 🍿 🥤 09 86 95 95 95

የኢትዮጵያውያን ቁጭት በደስታ የተቀየረበትን ቀን የሚያስታውስ ስራ በመስራቴ ደስተኛ ነኝ - አርቲስት ነዋይ ደበበ************************የዘመናት የኢትዮጵያውያን ቁጭት በደስታ ...
13/09/2025

የኢትዮጵያውያን ቁጭት በደስታ የተቀየረበትን ቀን የሚያስታውስ ስራ በመስራቴ ደስተኛ ነኝ - አርቲስት ነዋይ ደበበ
************************

የዘመናት የኢትዮጵያውያን ቁጭት በደስታ የተቀየረበትን ቀን የሚያስታውስ ስራ በመስራቱ ደስተኛ መሆኑን አንጋፋው አርቲስት ነዋይ ደበበ ገለፀ፡፡

የኢትዮጵያውያን የዘመናት ሕልም የሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ 14 ዓመታትን የተሻገረው የግንባታ ሂደት ተጠናቆ ባሳለፍነው ሳምንት ጳጉሜ 4 ቀን 2017 ዓ.ም መመረቁ ይታወሳል።

ይህን ተከትሎ የተሰማቸውን ደስታ በጥበባዊ ስራዎቻቸው ከገለፁት ባለሙያዎች መካከል አንዱ የሆነው አንጋፋው አርቲስት ነዋይ ደበበ፤ የግድቡ ምርቃትን ምክንያት በማድረግ በዓባይ ዙሪያ አቀንቅኖ ሙዚቃውን ለህዝብ ያደረሰ ሲሆን በሥራው ዙሪያ ከኤፍ ኤም አዲስ 97.1 መሰንበቻ ሬዲዮ ፕሮግራም ጋር ቆይታ አድርጓል።

አርቲስት ነዋይ በቆይታውም፤ በሙዚቃው የተሰማውን ስሜት እንደገለፀ ጠቅሶ፤ ሥራው በአጭር ጊዜ ውስጥ ተሰርቶ መጠናቀቁን ተናግሯል፡፡

"እንቅልፍ አጣሁ ተጨነኩ ከዛም ለዓባይ ተቀኝሁ" ሲልም ሙዚቃው የተሰራበትን ሂደት አብራርቷል::

የብዙ ሺህ ዘመን ምኞት ለውጤት የበቃበትን አጋጣሚ ማየት ትርጉሙ ቀላል አይደለም ያለው አርቲስት ነዋይ፤ ዕድሉን አግኝቶ የዘመናት የኢትዮጵያውያን ቁጭት በደስታ የተቀየረበትን ቀን የሚያስታውስ ስራ በመስራቱም ደስተኛ መሆኑን ገልጿል::

ሙሉ ቆይታውን ለመከታተል በኮሜንት ሴክሽን ላይ ያለውን ሊንክ ይጫኑ

በናትናኤል ሀብታሙ

★ የኢትዮጵያ ስካይላይት ሆቴል የስራ ማስታወቂያ [Ethiopian SkyLight Hotel Vacancy]♦Deadline: September 18, 2025Ethiopian Skylight Hotel i...
13/09/2025

★ የኢትዮጵያ ስካይላይት ሆቴል የስራ ማስታወቂያ [Ethiopian SkyLight Hotel Vacancy]

♦Deadline: September 18, 2025

Ethiopian Skylight Hotel invites qualified applicants for the following position.

✅ Position: QMS (QUALITY MANAGEMENT SYSTEM ) & SMS (SAFETY MANAGEMENT SYSTEM) OFFICER

● EDUCATION & EXPERIENCE: BSC degree in Food Science/Biology/ or any related field of study from a recognized college/university with a minimum of two years’ experience in food services/Food Quality Assurance/Cook capacity with HACCP standards.
OR
A Minimum of College Diploma/10+3/Level III Certificate per the old/new curriculum in Food preparation/Foreign Dish Cooking/Ethiopian Cultural Food Preparation/ Confectionery, Baking and Pastry Making/Hotel Operation or any related field of study from a recognized TVET/College/University with a Minimum of Four years relevant experience in food service/Food Quality Assurance/Cook capacity with HACCP standards.

How to Apply??
👇👇👇
https://effoysira.com/ethiopian-skylight-job-vacancy/
:
🎈Telegram:- https://t.me/effoyjobs

የሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅን ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበባ "በህብረት ችለናል" በሚል መሪ ሀሳብ የተካሄደው የስፖርት ፌስቲቫልና የጎዳና ላይ ትርዒት በፎቶ፦
13/09/2025

የሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅን ምክንያት በማድረግ በአዲስ አበባ "በህብረት ችለናል" በሚል መሪ ሀሳብ የተካሄደው የስፖርት ፌስቲቫልና የጎዳና ላይ ትርዒት በፎቶ፦

ዶ/ር ፍፁም አሰፋ የብሔራዊ ባንክ ገዢ ሆነው በጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ ተሹመዋል!ዶ/ር ፍፁም አሰፋ በመንግሥት በተለያዩ የስልጣን ዘርፍ ያገለገሉ ሲሆን የብሔራዊ ባንክ ገዢ ከመሆናቸው በፊ...
12/09/2025

ዶ/ር ፍፁም አሰፋ የብሔራዊ ባንክ ገዢ ሆነው በጠ/ሚ ዶ/ር አብይ አህመድ ተሹመዋል!

ዶ/ር ፍፁም አሰፋ በመንግሥት በተለያዩ የስልጣን ዘርፍ ያገለገሉ ሲሆን የብሔራዊ ባንክ ገዢ ከመሆናቸው በፊት የፕላንና ልማት ኮሚሽን ሚኒስተር እንደነበሩ ይታወቃል! የቀድሞ የብሔራዊ ባንክ ገዢ የነበሩ አቶ ማሞ ምህረቱ በገዛ ፍቃዳቸው ከስልጣን መልቀቃቸው እና የአፍሪካ ልማት ባንክ ምክትል ፕሬዚዳንት ሆነው መሾማቸው የሚታወስ ነው!


ዶ/ር ፍፁም አሰፋ መልካም የስራ ዘመን

Address

Addis Ababa
0000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ብስራት ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ብስራት ሚዲያ:

Share