ብስራት ሚዲያ

ብስራት ሚዲያ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from ብስራት ሚዲያ, News & Media Website, Addis Ababa.
(1)

ብስራት ሚዲያን ማገዝ ለምትፈልጉ
ንግድ ባንክ👉1000404574241
ማስታወቂያ ማሰራት የምትፈልጉ በስልክ ጥራችን 0916725040 በመደወል ያነጋግሩን !!

ብስራት ሚዲያ፦ዜና ፣ መዝናኛ ፣ ታርክ ፣ ጤና ፣ ማህበራዊ ጉዱይ .ወ.ዘ.ተ
ታማኝ እና ፈጣን ፣ የሁሉም ለሁሉም !!

ከዋን ቲቪ ጋር የሥራ ውል ተፈራረመች‎‎  ፦  የቀድሞዋ የኢቢኤስ የመዝናኛ ፕሮግራም አቅራቢ እና ጋዜጠኛ ናፍቆት ትዕግስቱ ከአዲሱ ቻናል ዋን ቲቪ ጋር የሥራ ውል ተፈራረመች። ‎‎ናፍቆት በማ...
24/07/2025

ከዋን ቲቪ ጋር የሥራ ውል ተፈራረመች

‎ ፦ የቀድሞዋ የኢቢኤስ የመዝናኛ ፕሮግራም አቅራቢ እና ጋዜጠኛ ናፍቆት ትዕግስቱ ከአዲሱ ቻናል ዋን ቲቪ ጋር የሥራ ውል ተፈራረመች።

‎ናፍቆት በማህበራዊ ሚዲያ ገጾቿ ላይ ስለ ስራ ስምምነቱ እንዳጋራቸው "በልዩነት እየመጣ ካለው ቻናል ዋን ጋር አብሮ ለመስራት ስምምነት መፈረሜን ሳበስራችሁ እጅግ ደስ እያለኝ ነው" ብላለች

‎የቻናል ዋን ቲቪ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሳሙኤል ደበበ ተመራጭ እና አዳዲስ ፕሮግራሞችን በማዘጋጀት ጣቢያው በልዩነት ስርጭቱን ለመጀመር ዝግጅቱን እንዳጠናቀቀ ገልፀዋል።

‎ ቻናል ዋን ቴሌቪዥን ታዋቂ እና አዳዲስ ጋዜጠኞች በመያዝ በቅርቡ ስርጭቱን ለመጀመር መሰናዳቱን ጠቅሰው፣ ናፍቆት ትዕግስቱ ከጣቢያው ጋር አብራ ለመስራት ስምምነት በመፈጸሟ ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል ።

በባንካችን ላይ የተቃጣውን የዝርፊያ ወንጀልን ተቆጣጥረነዋል 7.735 ቢሊየን ብሩን ገንዘቡን ከወሰዱት ሰዎች አካውንት ተመላሽ አድርገናል  በባንካችን ላይ ተቃጥቶ ከነበረው ብር 7.735 ቢሊ...
24/07/2025

በባንካችን ላይ የተቃጣውን የዝርፊያ ወንጀልን ተቆጣጥረነዋል

7.735 ቢሊየን ብሩን ገንዘቡን ከወሰዱት ሰዎች አካውንት ተመላሽ አድርገናል

በባንካችን ላይ ተቃጥቶ ከነበረው ብር 7.735 ቢሊየን ገንዘብ ከባንኩ የውስጥ ሂሳቦች ያለሕጋዊ ምክንያትና ሥልጣን በባንካችን በሚገኙ 10 የሌሎች ግለሰቦች ሂሳብ በማዛወር ገንዘቡን ለማይገባው ሰው ጥቅም ወይም ለራሳቸው ለተጠርጣሪዎች ለማዋል የማመቻቸት ተግባርን ባንኩ ባለው ጠንካራ የውስጥ ቁጥጥር ስርዓት ደርሶበት ምንም አይነት ገንዘብ ወጪ ሳይደረግ ገንዘቦቹን ከተላለፉባቸው ሂሳቦች ወደ ትክክለኛዎቹ የውስጥ ሂሳቦቹ ተመላሽ አድርጓል።

ባንካችንም ለሚመለከተው የሕግ አካል ወዲያውኑ የወንጀል ተግባሩን ጥቆማ በማቅረቡ ምርመራዎች ሲካሄዱና ማስረጃዎች ሲሰባሰቡ ቆይቶ በ14 ተጠርጣሪዎች ላይ ለራስ ወይም ለሌላ ሰው የማይገባ ጥቅም ለማግኘት አስቦ ስልጣንን አላግባብ የመገልግል ከባድ የሙስና ወንጀል በዋና ወንጀል አድራጊነትና በልዩ ወንጀል ተሳታፊነት በፌደራል ዓቃቢ ሕግ የሙስና ወንጀል ዳይሬክቶሬት በኩል በ14 ተጠርጣሪዎች ላይ የወንጀል ክስ ተመስርቷል።

በሌላ በኩል ግንቦት 19 ቀን 2017 ዓ.ም. “በኢትዮጵያ ንግድ ባንከ የውስጥ አካውንት ውስጥ ተቀምጦ የነበረ ከ7 ቢሊየን ብር በላይ መዘረፉ ተገለፀ” በማለት ባንካችን ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ እንደተዘረፈ፣ ዘራፊዎቹ እንዳልተያዙ እና ባንካችንም ጉዳዩን አድበስብሶ እንዳለፈው የሚገልጽ የሐሰት መረጃ መሰራጨቱን ተከትሎ ባንካችን ትክክለኛውን እውነታ በመግለፅ ግንቦት 20 ቀን 2017 ዓ.ም. በይፋዊ የማህበራዊ ሚድያ ገፆቹ ባስተላለፈው መልዕክት:-

➢ ባንካችን ሙከራው በተደረገ በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ በጠንካራው የውስጥ ቁጥጥር ስርዓታችን አጠራጣሪ ግብይት መፈፀሙን ስለደረሰበት ምንም ዓይነት ገንዘብ ወጪ ሳይደረግ (ሳይመዘበር) ሙከራው ወዲያውኑ እንዲከሽፍ መደረጉን፣

➢ ሙከራው በጥቂት ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት ባሰቡ ተጠርጣሪዎች የተፈፀመ እንጂ የባንካችንን ሲስተም ተላልፎ የተፈፀመ ጥቃት አለመሆኑን፣

➢ ባንካችን ሙከራ የተደረገበትን ገንዘብ ባለው ጠንካራ የቁጥጥር ስርዓት አማካኝነት ከጥቃት ከተከላከለ በኋላ ጉዳዩን ለሚመለከተው የሕግ አካል በማሳወቅ ተጠርጣሪዎቹ በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋሉና የምርመራ ስራውም ተጠናክሮ እየተከናወነ የሚገኝ መሆኑን መግለፁ ይታወሳል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በፖሊስ በኩል ተገቢው ምርመራ ተደርጎ በ14 ተጠርጣሪዎች ላይ በፌዴራል ዓቃቤ ህግ በኩል ክስ መመስረቱን ተከትሎም ገንዘቡ “በተጠርጣሪዎቹ ወጪ ተደርጎ እንደተወሰደ” በማስመሰል፤ “ባንካችን አጭበርብረውኛል ባላቸው ግለሰቦች ላይ ክስ እንደመሰረተ” እንዲሁም “ተመዘበረ የተባለው ገንዘብ ባንካችን ከፖሊስ ጋር በመተባበር ማሳገዱን” በመጥቀስ ሀሰተኛ መረጃዎች በጥቂት የማህበራዊ ሚድያዎች መሰራጨቱንና የዚህን መረጃ ትክክለኛነት ሳያጣሩ ሌሎች የተወሰኑ ሚዲያዎችም ይህንኑ ሀሰተኛ መረጃ ደግመው እያሰራጩ የሚገኙ እንዳሉም ተገንዝበናል።

ቀደም ብለንም እንዳሳወቅነው ባንካችን እንደማንኛውም የፋይናንስ ተቋም በተለይም እንደ ግዙፍ የፋይናንስ ተቋምነቱ ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት አስበው ለሚንቀሳቀሱ አካላት ኢላማ መሆኑ እሙን ቢሆንም እንዲህ አይነቱን ሕገ ወጥ ተግባር ለመከላከል የሚያስችል ጠንካራ የውስጥ ቁጥጥር ስርዓትና የዘመነ ሲስተም ያለው ለመሆኑ ይህ የሙከራ ድርጊት መክሸፉና ተጠርጣሪዎች ላይም ምርመራ ተጣርቶ የወንጀል ክስ መመስረቱ አንዱ ማሳያ ነው፡፡

በመሆኑም የባንካችንን መልካም ስምና ዝና ለማጠልሸትና ሀሰተኛ መረጃ ለማሰራጨት ሆን ብለው የተዛባና ትክክለኛ ያልሆነ መረጃ በሚያሰራጩ ግለሰቦችም ሆኑ ተቋማት ላይ በአፋጣኝ ተገቢውን የእርምት ማስተባበያ ካልሰጡ ባንካችን ቀጣይ ሕጋዊ እርምጃዎችን ለመውሰድ የሚገደድ መሆኑን እያሳወቅን ክቡራን ደንበኞቻችንም ባንካችንን የሚመለከቱ መረጃዎችን ከታአማኒ የመረጃ ምንጮችና ከባንካችን ይፋዊ የመረጃ ምንጮች ላይ ማግኘት የሚችሉ መሆኑን እያሳወቅን የመረጃዎችን ትክክለኛነታቸውን ሳያጣሩ ሀሰተኛ መረጃዎችን እንዳይቀበሉ በአክብሮት እንጠይቃለን።

አሜሪካ ትንኮሳ እየፈፀመችብኝ ነዉ ! / ቴህራን /ኢራን በኦማን ባሕረ ሰላጤ በመንቀሳቀስ ላይ የነበረን የአሜሪካ መርከብ መከልከሏ ተነገረ ።የኢራን ሃይሎች ረቡዕ እለት አንድ የዩናይትድ ስቴ...
24/07/2025

አሜሪካ ትንኮሳ እየፈፀመችብኝ ነዉ ! / ቴህራን /

ኢራን በኦማን ባሕረ ሰላጤ በመንቀሳቀስ ላይ የነበረን የአሜሪካ መርከብ መከልከሏ ተነገረ ።

የኢራን ሃይሎች ረቡዕ እለት አንድ የዩናይትድ ስቴትስ የባህር ኃይል ንብረት የሆነ የአሜሪካ አጥፊ መርከብ ቴህራን የዉሐ ክልል ዘልቆ ለመግባት ሲሞክር እንዳገኘች ገለፀች ።

የኢራን መንግስት ቲቪ እንዳስታወቀው ዩኤስኤስ ፌዝጀራልድ መርከቧ በኢራን ቁጥጥር ስር ወደ ሆነዉ ውሀ ክልል በመቅረብ ለመግባት ስትሞክር የኢራን ጦር ሄሊኮፕተር ማስጠንቀቂያ በመስጠት ማባረሩን ገልጿል ።
በተዘገበው የቪዲዮ ተገግፎ በወጣዉ መረጃ ምስል ላይ አንድ ሄሊኮፕተር ከመርከቡ ጋበቅርበት ሲበር ታይቷል ። እናም አንድ የኢራናዊ መርከበኞች በእንግሊዘኛ የሬዲዮ ማስጠንቀቂያ ለጦር መርከብ ሲሰጥ መንገዱን እንዲቀይር ትእዛዝ ሲሰጥ ይሰማል።

የአሜሪካ አጥፊ 'Fitzgerald' መርከብ በኢራን ቁጥጥር ስር ወደ ሆነዉ ውሃ ለመቅረብ መሞከሩ፣ ግጭት ቀስቃሽ እርምጃ ነው" ሲል የኢራን መንግስት ቴሌቪዥን ገልጿል።

የአሜሪካ መከላከያ ባለስልጣን የአሜሪካው መርከብ በአለም አቀፍ ውሃ ውስጥ በሚንቀሳቀስበት ወቅት ከኢራን SH-3 'Sea King' ሄሊኮፕተር ጋር ደህንነቱ የተጠበቀ እና ሙያዊ ግንኙነት ነበረው ብለዋል ።

የዩኤስ ጦር ባለፈው ወር የኢራንን የኒውክሌር ቦታዎችን ባደበደበ ጊዜ እስራኤል ከኢራን ጋር ባደረገችው ጦርነት ውስጥ እራሱን ማስገባቱ ተከትሎ የሁለቱ ሀገራት ግኑኝነት እየሻከረ ሲሄድ ኢራንም የኒኩሊየር መርሀ ግብሯን እንደማታቆም ደጋግማ እየገለፀች ይገኛል ።

የኢራኑ ፕሬዝዳንት ማሱድ ፔዜሽኪያን ረቡዕ እለት በሰጡት ቃለ ምልልስ ቴህራን የኒውክሌር መርሃ ግብሯን ለሰላማዊ ዓላማ ለማስቀጠል ቁርጠኛ መሆኗን እና ሀገራቸው ወደፊት እስራኤል ለምታደርገው ጦርነት ዝግጁ መሆኗን ተናግረዋል። ሲል ያስነበበው አልጀዚራ ነዉ ።

የኔቲ ቲዩብ ዘጋቢ፦ ታዴ የማመይ ልጅ

https://youtu.be/5m-csHXOlDw?si=1C8pCKrvJxHb-b70
24/07/2025

https://youtu.be/5m-csHXOlDw?si=1C8pCKrvJxHb-b70

‎🎬 Yefikirzema Amharic Drama Recap | ሙሉ ታሪኩን በአንድ ድምፅ እንደተመለከቱ!‎Welcome back to Bisrat Media ! In this video, we break down the powerful and emotional story...

‎ከአዲስ አበባ ከተማ ኮሙኒኬሽን ቢሮ የተሰጠ መግለጫ‎‎  ፦ ትላንትናው ዕለት በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት በአዲስ አበባ በተከሰተው ጎርፍ ዙሪያ አንዳንድ ያልተገቡ አስተያየቶች መሰጠታቸውን...
24/07/2025

‎ከአዲስ አበባ ከተማ ኮሙኒኬሽን ቢሮ የተሰጠ መግለጫ

‎ ፦ ትላንትናው ዕለት በጣለው ከባድ ዝናብ ምክንያት በአዲስ አበባ በተከሰተው ጎርፍ ዙሪያ አንዳንድ ያልተገቡ አስተያየቶች መሰጠታቸውን የአዲስ አበባ ከተማ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ገለጸ።

‎ቢሮው እንዳብራራው፣ ትላንትና የተከሰተው ጎርፍ ወቅቱን በጠበቀ ከባድ ዝናብ ምክንያት በወንዝ ዳርቻ ልማት ግንባታ ላይ በነበረው ጊዮን ሆቴል አካባቢ የውሃ መጠን በመጨመሩ እና ለጊዜው የተሰራለትን ግድብ ጥሶ በመውጣቱ ነው።

‎ይሁን እንጂ፣ አንዳንድ ግለሰቦች ሁኔታውን ያላገናዘበ እና ከእውነት የራቀ አስተያየት መስጠታቸውን ቢሮው አስታውቋል።

‎አዲስ አበባ የነበራትን አስቸጋሪ የፍሳሽ ማስወገጃ ስርዓት ለማሻሻል በከፍተኛ ደረጃ እየተሰራ ያለውን ስራ ወደ ጎን በመተው፣ አንዳንዶች ያልተገባ ስያሜ መስጠታቸው ተገቢ እንዳልሆነም ተገልጿል።

‎ጥሪ ለህብረተሰቡ:-

‎የአዲስ አበባ ከተማ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ለመላው ህብረተሰብ እና የከተማዋ ነዋሪዎች የሚከተለውን ጥሪ አቅርቧል፦

‎ * ወቅቱንና ከተማዋ አሁንም በበርካታ ግንባታዎች ላይ መሆኗን ከግምት ውስጥ እንድታስገቡ።

‎ * ምንጩ ካልታወቀ የተዛባ መረጃ ራሳችሁን እንድትጠብቁ።

‎ * ትክክለኛውንና ሚዛናዊ የሆነውን መረጃ እንድትመረምሩ።

‎ * የኢትዮጵያ ሜቴዎሮሎጂ ኢንስቲትዩት ወቅቱን አስመልክቶ የሚሰጣቸውን ማሳሰቢያዎች ከግምት ውስጥ በማስገባት ራሳችሁን ከጎርፍ አደጋ እንድትጠብቁ።

‎የጎርፍ መከላከል ስራ እና የህብረተሰቡ ተሳትፎ
‎በመጨረሻም፣ ማህበረሰቡ እየጣለ ያለውን ዝናብ እና ወቅቱን እንዲሁም በከተማዋ እየተሰራ ያለውን ግንባታ ከግምት ውስጥ በማስገባት፣

‎የጎርፍ መከላከል ስራው ተጠናክሮ እንዲቀጥል እና ከተማው በሚያደርገው የመከላከል ስራ ተባባሪነቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል ቢሮው ጠይቋል።

‎Via Addis Ababa City Communication

‎ዣቪ  ሲመንስን ወደ ቼልሲ ቤት‎‎  ፦ በአዲሱ የውድድር ዘመን በልጦ ለመገኝት  ተጫዋቾችን በማስፈረም የተጠመዱት ክለቦች ተፍ ተፍ እያሉ ነው::‎‎ሰሞኑን የአርሰናል ልጅ ለመሆን የፊርማ ም...
24/07/2025

‎ዣቪ ሲመንስን ወደ ቼልሲ ቤት

‎ ፦ በአዲሱ የውድድር ዘመን በልጦ ለመገኝት ተጫዋቾችን በማስፈረም የተጠመዱት ክለቦች ተፍ ተፍ እያሉ ነው::

‎ሰሞኑን የአርሰናል ልጅ ለመሆን የፊርማ ምስክርነቱን በውል ሰነዱ ላይ ያኖረው ዩክሬሽ ሌላኛውን ሰፈር ሳያሸብር አልቀረም::

‎ሆላንዳዊው ተጫዋች ዣቪ ኪውንተን ሻይ ሲመንስን እስከ 2023 በቼልሲ ቤት የሚያቆየውን ኮንትራት ለመፈራረም መቃረቡ ተሰምቷል::

‎ተጫዋቹ 70 ሚሊየን ይከፈለኝ ያለ ሲሆን ቼልሲም ለመክፈል ችግር እንደሌለበት ገልፆል::

‎ቼልሲ ተጫዋቹን ገቢ ለማድረክ ፍላጎት ያለው እንደሆነ ያቀረበለት ዳጎስ ያለ ገንዘብ ሊነገረን ይችላል::

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቀደም ሲል ሰርተነው ለነበረው የዜና ዘገባ ተከታዩን ማስተካከያ ልኳል 👇***የ7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብሩ ጉዳይ!...የኢትዮጽያ ንግድ ባንክ  በጠንካራ የውስጥ አሰራሩ በ...
24/07/2025

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቀደም ሲል ሰርተነው ለነበረው የዜና ዘገባ ተከታዩን ማስተካከያ ልኳል 👇
***

የ7 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብሩ ጉዳይ!...

የኢትዮጽያ ንግድ ባንክ በጠንካራ የውስጥ አሰራሩ በሕገ ወጥ መንገድ በባንኩ በሚገኙ 10 ሂሳቦች ተላልፎ የነበረ 7.5 ቢሊዮን ብር ወጪ ሳይደረግ ማዳን መቻሉን ገልጿል። የድርጊቱ ፈፃሚዎች ላይም በስልጣን አላግባብ የመገልገል የሙስና ክስ ተመስርቷል።
***
ከሰባት ቢሊዮን ብር በላይ በሕገወጥ መንገድ ከባንኩ የውስጥ ሂሳብ በባንኩ በሚገኙ ሌሎች ሂሳቦች በማስተላለፍ ለራሳቸው ጥቅም ለማዋል ሲሞክሩ ባንኩ ደርሶባቸው ገንዘቡን ተመላሽ ቢያደርግም በድርጊቱ በተሳተፉ 14 ግለሰቦች ላይ በሥልጣን አላግባብ በመገልገል የሙስና ወንጀል ዋና አድራጊነትና የልዩ ወንጀል ተሳታፊነት ክስ ተመስርቷል። የወንጀል ክሱ የተመሰረተውም በ3 የባንኩና 2 የደህንነት ሠራተኞች በ9 ሌሎች ግብረአበሮቻቸው ላይ ነው።

ከተከሳሶቹ መካከል በኢትዮጲያ ንግድ ባንክ የንፋስ ስልክ ዲስትሪክት የኮንዶሚኒየም ብድር ክትትል ባለሙያ አቶ ደጉ አሸናፊ በየነ ፥ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወለጋ ሆሮ ጉዱሩ የሆሮ ቅርንጫፍ ስራ አስኪያጅ ተፈሪ ዲንቄሳ በለጠ፣ አቶ እሱባለው ሽመልስ በኢትዮጲያ ንግድ ባንክ የኢፕሊኬሽን ኦፊሰር፥ በብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት የኢኮኖሚ ኢንተለጀንት ኦፊሰሮች መሀመድ ነጋሽ ገሰሰና ንጉሱ ኡምሩ ጉሪኖ ይገኙበታል፡፡

በተጨማሪም በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የለሚ ኩራ ክፍለ ለተማ ስራና ክህሎት ጽ/ቤት የሥራ ስምሪት ባለሙያ አቶ ገብረሃና አለሙ ቸሩ፥ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የማህበራዊ ትረስት ፈንድ ጽ/ቤት የፕሮጀክት ዝግጅትና ሃብት ማፈላለጊያ ባለሙያ አቶ አንተነህ ካሳ መኮንን፥ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የማህበራዊ ትረስት ፈንድ ጽ/ቤት የፕሮጀክት ዝግጅትና ሃብት ማፈላለጊያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ዮናስ ሸዋዬ እንዳለማውም እንደሚገኙበት በፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ወንጀል ጉዳዮች ዳይሬክተር ጀነራል አቃቤ ሕግ ለፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ያቀረቡት ክስ ያስረዳል፡፡

ሌሎች ሙሉጌታ ቀሪዓለም ደሴ፣ ሞላ ሽፈራው እጅጉ፣ ኤባኤል ተሻተ ፣ አንተነህ ካሳ መኮንን፣ ገላና አዴሳ ቦና የተባሉ ተከሳሾች በአዲስ አበባ እና ሸገር ከተማ የሚኖሩ ናቸው።

እንደ ክስ መዝገቡ በኢትዮጲያ ንግድ ባንክ ይሰሩ የነበሩ በክስ መዝገቡ የተጠቀሱ ሠራተኞች ከሌሎች በክሱ ከተካተቱ ግብራበሮቻቸው ጋር በመሆን፥ በሥልጣን አላግባብ በመገልገል የጥቅም ትስስር በመፍጠር በኢትዮጲያ ንግድ ባንክ 3 የውስጥ ተቀማጭ ሂሳቦች ላይ ከሰባት ነጥብ አምስት (7.5) ቢሊዮን ብር በላይ በሕገ-ወጥ መንገድ በባንኩ ወደሚገኙ የተለያዩ የ10 ግለሰቦች ሂሳቦች ውስጥ ገቢ በማድረጋቸው ነው ለራስ ወይም ለሌላ ሰው ጥቅም ለማስገኘት ስልጣንን አላግባብ በመገልገል በዋና ወንጀል አድራጊነትና በልዩ ወንጀል ተሳታፊነት የተከሰሱት።
በክስ መዝገቡ የተካተቱ የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ሥራና ክህሎት ጽ/ቤት የስራ ስምሪት ባለሙያዉ አቶ ገብረሃና አለሙ ቸሩ ከሌሎች በክሱ ከተጠቀሱ በግል ስራ ከሚተዳደሩ 3 ተከሳሾች ጋር በ 2017 አመተ ምህረት በጥር እና የካቲት ወራት በተለያዩ ጊዜያት ይህንን ገንዘብ ከባንክ እንዴትና በማን አማካኝነት እንደሚያወጡ ሲነጋገሩ ቆይተው ባንኩ ለሕጋዊ ሥራ በስጠው የሂሳብ ማንቀሳቀሻ ይለፍ ቃልን ተጠቅሞ ያለ ሕጋዊ አግባብና ሥልጣን ገንዘቡን ተቀናሽ አድርገው ወደ ሌሎች አስር ሂሳቦች ቢያስተላልፉም ባንኩ በዘረጋውን ጠንካራ የውስጥ ቁጥጥር ገንዘቡን ወጪ ሳያደርጉ በፊት ወደ ትክክለኛው የባንኩ የውስጥ ሂሳቦች ተመላሽ መደረጉን ባንኩ ጉዳዩን አስመልክቶ በሰጠው መግለጫ ማሳወቁ ይታወሳል።

ይህ የባንኩ ሰራተኛ ከባንክ ተቀማጭ ገንዘብ በአቶ ኢያሱ ለማ ፀጋዬ ስም ወደተከፈተ የባንክ ሂሳብ አምስት ሚሊየን (5,000,000)ብር ገቢ በማድረግ፥ ሌሎች በክስ መዝገቡ የተጠቀሱ ሁለቱ የብሔራዊ መረጃና ደህንነት የኢኮኖሚ ኢንተለጀንስ ሰራተኞችም ሁኔታዎችን በማመቻቸት በአቶ እስራኤል ደገፋ ስሜ ስም በተከፈተ ሁለት የተለያዩ አካውንቶች በድምሩ አራት ቢሊየን (4,000,000,000) ብር ገቢ በማድረግ፥ አቶ ጌታቸው ተገኝ አባዳማ በሚሰኝ ስም አንድ ቢሊየን (1,000,000,000)ብር እንዲሁም የአቶ ግዛቸው ዳምጠው ባለቤት በሆኑት በወ/ሮ ያለምዘርፍ ቢተው ገሰሰ ስም በተከፈተ እና ተከሳሹ በውክልና በሚያስተዳድሩት የባንክ ሂሳብ ቁጥር ሰላሳ ሚሊየን (30,000,000) ብር በተጨማሪም በተከሳሽ አቶ ሞላ ሽፈራው እጅጉ ስም በተከፈተ ሂሳብ ሁለት ቢሊየን (2,000,000,000)ብር፥ በክስ መዝገቡ በተካተተ ተከሳሽ ግዛቸው ዳምጠው ሽፈራው ስም በተከፈተ የባንክ ሂሳብ አምስት መቶ ሚሊየን (500,000,000) ብር ገቢ በማድረግ፥ በአፍራ መሳሊክ ወይም አርዝቱልስ ኢምፖርተር ስም ሀመሳ ሚሊየን ሚሊየን (50,000,000) ብር እና በአቶ ሙባረክ ሀሰን አብዱ ስም በተከፈተ የባንክ ሂሳብ ቁጥ አንድ መቶ ሚሊየን (100,000,000) ብር በሕገ ወጥ መንገድ በባንክ ይሰሩ የነበሩ ተከሳሾች ሁኔዎችን በማመቻቸት የተጠቀሰውን ከሰባት ነጥብ አምስት ቢሊየን ብር በላይ አስተላልፈው ተገኝተዋል በሚል በክስ መዝገቡ ተገልጿል።

በአጠቃላይ ተከሳሶቹ ከፍተኛ የባንክ ተቀማጭ ገንዘብ ለማስወጣት አስቀድመው በማዘጋጀት የማይገባቸውን ጥቅም ለራሳቸው ለማግኘት ወይም ለሌሎች ለማስገኘት በማሰብ የተጠቀሰውን ገንዘብ በማስተላለፍ በፈፀሙት በስልጣን ያለአግባብ መገልገል ከባድ የሙስና ወንጀል ተከሰዋል፡፡

ሁሉም ተከሳሾች በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አንደኛ የጸረ ሙስና ወንጀል ችሎት ቀርበው የዋስትና መብታቸው ተነፍጎ ጉዳያቸውን በማረሚያ ሆነው በመከታተል ላይ ናቸው፡፡

ተከሳሾቹ በሕገወጥ መንገድ ከባንኩ 3 የውስጥ ሂሳቦች በዚያው በባንኩ ወደሚገኙ 10 የተለያዩ ሂሳቦች ቢያስተላልፉም ባንኩ በዘረጋው ጠንካራ የውስጥ ቁጥጥር ከተላለፈው ገንዘብ ላይ ምንም ወጪ ሳይደረግ የተደረገው ማስተላለፍ ተቀልብሶ ገንዘቡ ወደ ነበረበት ትክክለኛዎቹ የባንኩ የውስጥ ሂሳቦች ተመላሽ መደረጉን ባንኩ መግለፁ ይታወሳል።

ሃዋሳ : የቴዲ ግቢ‎‎  ፦ ቴዎድሮስ መሳይ (ቴዲ ግቢ) በሀዋሳ ከተማ ጥንቀቅ፥ እምር፥ ፅድት ያለ ቤት ይዞ በክብር እየጠበቃችሁ ነው።‎‎ እንኳን አደረሳችሁ ...‎‎አድራሻ:- ‎ከቀድሞ ቴዲ...
23/07/2025

ሃዋሳ : የቴዲ ግቢ

‎ ፦ ቴዎድሮስ መሳይ (ቴዲ ግቢ) በሀዋሳ ከተማ ጥንቀቅ፥ እምር፥ ፅድት ያለ ቤት ይዞ በክብር እየጠበቃችሁ ነው።

‎ እንኳን አደረሳችሁ ...

‎አድራሻ:-
‎ከቀድሞ ቴዲ ቤት ጎን

‎ለበለጠ መረጃ
‎09-12-60-55-20

ቱርክ አዲስ ቴክኖሎጂ ለአለም አስተዋወቀች !ቱርክ በጦር ሜዳ ላይ የሚደርሰውን የድሮን ስጋቶችን ለመዋጋት ለመከላከልና ለማክሸፍ የሚያስችል አልካ-ካፕላን የተባለውን በቴክኖሎጂ የረቀቀ ተሽከር...
23/07/2025

ቱርክ አዲስ ቴክኖሎጂ ለአለም አስተዋወቀች !

ቱርክ በጦር ሜዳ ላይ የሚደርሰውን የድሮን ስጋቶችን ለመዋጋት ለመከላከልና ለማክሸፍ የሚያስችል አልካ-ካፕላን የተባለውን በቴክኖሎጂ የረቀቀ ተሽከርካሪ አስተዋወቀች ።

ይህ በአይነቱ የመጀመሪያው የተባለው ከአየር፣ ከመንገድ ዳር የሚደርሱ ቦምቦች፣ ፈንጂዎች፣ እና ያልተፈነዱ ቦምቦች በውጊያ ዞኖች የሚመጡ ስጋቶችን ለማስወገድ ይረዳል የተባለው ተሽከርካሪ አንካራ ዘመናዊ ቴክኖሎጅዎችን የደረሰችበትን ልህቀት ያሳያል ተብሏል ።

አለም አሁን እየተጠቀመባቸዉ ካለዉ የአየር መከላከያ ዘዴዎች ይልቅ ድሮኖችን፣ ሄሊኮፕተሮችን እና ሌሎች የበረራ መሳሪያዎችን ለማጥቃት ኤሌክትሮማግኔቲክ መጨናነቅ እና ጠንካራ ሌዘርን ይጠቀማል የተባለው ይህ ተሽከርካሪ የአየር ላይ ስጋቶችን ለማስወገድ እንደሚያስችል ተነግሯል ።

በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ የታገዘ ክትትል እና የጠላት ማስጠንቀቂያዎችን መለየትን እንደሚችል የተነገረለት መኪና የላቀ መመሪያ ቴክኖሎጂዎችን የሚጠቀሙ ከራዳር ዉጭ የሆኑ ሰዉ አልባ ድሮኖች ፈንጂዎችን በፍጥነት ለማወቅ እና ለማስወገድ የሚያስችሉ ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች የተገጠሙለት ሲሆን የከተማ ቦታዎችን፣ ክፍት ቦታዎችን እና ኮንቮይዎችን ለመጠበቅ ሁለገብ በሆነ መንገድ ሊሰማራ ተገልጿል ።

ራስን መከላከል የሚያስችሉ የኃይል ስርዓቶች ፍላጎት በአለም አቀፍ ደረጃ እያደገ ሲሄድ፣ ቱርክ ራሷን በዚህ የወታደራዊ ቴክኖሎጂ ዘርፍ ለመወዳደር እያዘጋጀች ነው። ሲል የዘገበዉ ሮይተርስ ነዉ ።

አሁን ላይ ዮክሬሽ የህክምና ምርመራውን ለማድረግ ከስፖርቲንግ ፍቃድ እየጠበቀ ነው ፤ ይህንን ውስብስብ ዝውውር ለማጠናቀቅ ክለቦቹ ዶክሜንት እየተለዋወጡ ነው።- Fabrizio Romano 🎖
23/07/2025

አሁን ላይ ዮክሬሽ የህክምና ምርመራውን ለማድረግ ከስፖርቲንግ ፍቃድ እየጠበቀ ነው ፤ ይህንን ውስብስብ ዝውውር ለማጠናቀቅ ክለቦቹ ዶክሜንት እየተለዋወጡ ነው።

- Fabrizio Romano 🎖

የፌዴራል በቶች ኮርፖሬሽን ለሁለት ቀናት ሲያካሂድ የነበረውን የማጠቃለያ ግምገማ አጠናቀቀየኮርፖሬሽኑ ዓመታዊ ገቢ 9 ነጥብ 34 ቢሊየን ብር ሆኖ ተመዘገበየፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ለሁለት ቀ...
23/07/2025

የፌዴራል በቶች ኮርፖሬሽን ለሁለት ቀናት ሲያካሂድ የነበረውን የማጠቃለያ ግምገማ አጠናቀቀ

የኮርፖሬሽኑ ዓመታዊ ገቢ 9 ነጥብ 34 ቢሊየን ብር ሆኖ ተመዘገበ

የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን ለሁለት ቀናት ሲያካሂድ የነበረውን የ2017 በጀት ዓመት የማጠቃለያ ግምገማ የ2018 በጀት ዓመትን እቅድና የአፈጻጸም አቅጣጫ በማስቀመጥ አጠናቋል፡፡

በኮርፖሬሽኑ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ክቡር አቶ ረሻድ ከማል በተመራው በዚህ የማጠቃለያ ግምገማ ተቋማዊ ሪፎርሙ ከአገራዊ ሪፎርሙ እኩል ግለቱን ጠብቆ እንዲጓዝ ባማስቻል ረገድ እየተከናወኑ ያሉ ሥራዎች ስኬታማ መሆናቸውን ያረጋገጡ ውጤቶች በሁሉም መስክ መገኘታቸው ተገምግሟል፡፡

ኮርፖሬሽኑ ያገኘው የ9 ነጥብ 34 ቢሊየን ብር ገቢ ተቋማዊ ሪፎርሙ ሲጀመር ከነበረበት ተመሳሳይ ወቅት የ2010 በጀት ዓመት (300 ሚሊየን ብር ገቢ ) ጋር ሲነጻጸር ከ 30 ጊዜ በላይ እጥፍ የገቢ አድገት ተመዝግቧል፡፡

ለገቢ እድገቱ ፡- የገቢ ማግኛ መሰረቱና ዓይነቱ በመስፋቱ ፣ ከአማካሪነት በተቋራጭነት የተገኘው ገቢ ፣ በሪኖቬሽንና ሥራ እና ከቤት ሽያጭ የተገኘው ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ እድገት በማሳያታቸው እንደሆነ ተመላክቷል፡፡ ከ 4 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር በላይ የሚገመት ተጨማሪ ሀብት (ASSET) መፍጠሩም ተችሏል፡፡

በኮርፖሬሽኑ እንዲሁም በደንበኞች ሙሉ በሙሉ ወጪ በርከታ ሱቆች በመገንባታቸው ከፍተኛ ገቢ ከማስገኘታቸው ባሻገር ኮርፖሬሽኑ ከ4 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር በላይ ተጨማሪ ሀብት መፍጠር ተችሏል፡፡

የተፈጠረው ሀብት በኮሪደር ልማት ስታንዳርድ መሰረት እንዲነሱ ከተደረጉት የኮርፖሬሽኑ ቤቶች በላይ ግምት ያለው ሀብት በአጭር ጊዜ መፍጠር መቻሉ በጥንካሬ ተገምግሟል፡፡

በተያዘው በጀት ዓመት የተገኘው ንጹህ የኦዲት አስተያየት ፣ በሥራ ላይ ካለው የአልሙኒም ፎርምወርክ ቴክኖሎጂ በተጨማሪ የ3ዲ ኮንስትራክሽን ፕሪንት ቴክኖሎጂ እና የፕሪካስት ቴክኖሎጂን ወደ ሀገር ለማስገባትና ለማላመድ በበጀት ዓመቱ የተከናወነው የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መጠናቀቁም ተገልጿል፡፡

በተመሳሳይ በፕሮጀክት አፈጻጸምና አስተዳደር ፣ አዲዳስ ፕሮጀክትን ለመጀመረ እየተከናወኑ ያሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ፣ የመፈጸምና የማስፈጸም አቅም ግንባታ ፣ በትብብር የሚከናወኑ አገራዊ ፋይዳ ያለቸውን ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ተግባራዊ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት እና ሌሎች ስትራቴጂካዊ ሥራዎች ላይም ትኩረት ያደረገ ግምገማ ተከናውኗል፡፡

ዘመናዊ አፓርትመንት ሕንጻዎችን ወደ ሥራ ማሰገባት መቻሉና ግዙፉን የግብዓት ማምረቻ ማዕከል አጠናቆ በአጭር ጊዜ ወደ ምርት ሥራ ማስገባት መቻሉና አሁን ላይ በሙሊ አቅሙ ወደ ምርት እንዲገባ ለማስቻል እየተሰሩ ያሉት ሥራዎች ውጤታማ መሆናቸውም ተጠቁሟል፡፡

ከተለያዩ አካለት እየመጡ ያሉ አብረን እንሰራ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ሚያስችል የመፈጸምና የማስፈጻም አቅም ግንባታ ሥራዎችን የበለጠ ውጤታማ እንዲሆኑ የሚያስችል የአፈጻጸም አቅጣጫም ተቀምጧል፡፡

በ2018 በጀት ዓመት ኮርፖሬሽኑ ያስቀመጠውን የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ የሚያስችለውን ሰፊ እቅድ ቀርቦ ውይይት ከተደረገበት በኋላ ከአፈጻጸም አቅጣጫ ጋር በማጽደቅ ለሁለት ቀናት ሲያካሂድ የቆየውን ውጤታማና ታሪካዊ የማጠቃለያ ግምገማ በስኬት አጠናቋል፡፡

https://youtu.be/bKjh8cBrmvE?si=jNzPmvTHGwvxm4dz
23/07/2025

https://youtu.be/bKjh8cBrmvE?si=jNzPmvTHGwvxm4dz

‎🎬 Yeterasu Amharic Drama Recap | ሙሉ ታሪኩን በአንድ ድምፅ እንደተመለከቱ!‎Welcome back to Bisrat Media ! In this video, we break down the powerful and emotional story of...

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ብስራት ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ብስራት ሚዲያ:

Share