ዜና ኢትዮጵያ Zena Ethiopia

ዜና ኢትዮጵያ Zena Ethiopia This is media company

በፓሪስ 2024 ኦሊምፒክ ኢትዮጵያን በውሃ ዋና የወከለችው ሊና አለማየሁ በ50 ሜትር ነፃ ቀዘፋ አዲስ የኢትዮጵያ ክብረወሰን አስመዝግባለች፡፡ ሊና አለማየሁ የመጀመሪያ ውድድሯን በአራተኛነት ...
04/08/2024

በፓሪስ 2024 ኦሊምፒክ ኢትዮጵያን በውሃ ዋና የወከለችው ሊና አለማየሁ በ50 ሜትር ነፃ ቀዘፋ አዲስ የኢትዮጵያ ክብረወሰን አስመዝግባለች፡፡

ሊና አለማየሁ የመጀመሪያ ውድድሯን በአራተኛነት ማጠናቀቅ ችላለች። በዚህም በ50 ሜትር ሴቶች የነጻ ቀዘፋ ውድድር ወደ ግማሽ ፍጻሜ ለማለፍ ሳትችል ቀርታለች።

በውድድሩ የገባችበት ሰዓት 31 ሴኮንድ ከ87 ማይክሮ ሴኮንድ ከዚህ በፊት በያኔት ስዩም ተይዞ የነበረውን የኢትዮጵያ ክብረወሰን እንድታሻሽል አስችሏታል።

በ2012 በለንደን ኦሊምፒክ ዋናተኛ ያኔት ስዩም በ50 ሜትር ይዛው የነበረው ክብረወሰን 32:41 ሰከንድ ነበር።

በርካቶችን የቀጠፈው የመሬት ናዳ አደጋበደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጎፋ ዞን በገዜ ጎፋ ወረዳ በኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ ትናንት ጠዋት በደረሰ የመሬት ናዳ አደጋ የበርካቶች ህይወት ማለፉ ተገልጿል...
23/07/2024

በርካቶችን የቀጠፈው የመሬት ናዳ አደጋ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል በጎፋ ዞን በገዜ ጎፋ ወረዳ በኬንቾ ሻቻ ጎዝዲ ቀበሌ ትናንት ጠዋት በደረሰ የመሬት ናዳ አደጋ የበርካቶች ህይወት ማለፉ ተገልጿል።

በድንገተኛ የመሬት ናዳ አደጋ እስካሁን የሟቾች ቀጥር ከ200 በላይ መድረሱንና የሟቾች ቁጥር ከዚህ በላይ ሊያሻቅብ እንደሚችል የጎፋ ዞን አስታውቋል።

“ ራሴን በይፋ  አግልያለሁ “                   ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ አባል የነበረው ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ በወረቀት ላይ ብቻ ከተካተትኩበት የኦ...
18/07/2024

“ ራሴን በይፋ አግልያለሁ “
ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ

የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ አባል የነበረው ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ በወረቀት ላይ ብቻ ከተካተትኩበት የኦሎምፒክ የኮሚቴ አባልነት በይፋ መልቀቄን ህዝብ ይወቅልኝ ሲል ተናግሯል።

አሁን ያለው የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ አባል የስራ ዘመኑ ሊጠናቀቅ ስምንት ወይም ዘጠኝ ወራት እንደሚቀሩት የገለፀው ኃይሌ " እኔ በወረቀት ላይ ብኖርም ጥዬ የወጣሁት ግን ከቶኪዮ ኦሎምፒክ በፊት ነው " ብሏል።

ከሶስት አመታት በፊት ከአባልነት መልቀቁን ለህዝብ ያላሳወቀው የባሰ ብጥብጥ ውስጥ እንዳይገባ በመስጋት መሆኑን ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ ከሸገር ኤፍ ኤም ጋር በነበረው ቆይታ ገልጿል።

" በድጋሜ ያለ አግባብ ሌላ ምርጫ ማድረግ እና ሌላ ስህተት ግን ተቀባይነት የለውም ያንጊዜ ማድረግ የነበረብኝ ነው አሁን ከአባልነት መልቀቄን በይፋ አሳውቃለሁ።" ሲል ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ ተናግሯል።

ሻለቃ ኃይሌ ገብረ ሥላሴ አያይዞም በቅርቡ በዝግ በተደረገው ምርጫ ጋር በተያያዘ የተነሳውን ውዝግብ ለአዲሷ የባህል እና ስፖርት ሚኒስቴር ወ/ሮ ሸዊት ሻንካ አቅርበው መልስ እየተጠበቀ መሆኑን አስረድቷል።

" የተከበሩ ዶክተር አሸብር የትም ሂዱ ብለውናል የትም እንሄዳለን " ያለው ኃይሌ " በኋላ ግን ለምን ሄዳችሁ ለምን ይህንን አደረጋችሁ እንዳይሉ እፈራለሁ ፣ እንኳን ይሄን 42 ኪ.ሜ በሞት እና በህይወት ውስጥ ሆነን ሮጠናል " በማለት ተናግሯል።

"እንወያይ" - ዶ/ር አሸብር

የዶ/ር አሸብር ኦሎምፒክ ኮሚቴ ለአትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ የ"እንወያይ" ደብዳቤ መላኩ አነጋግሯል

ሀትሪክ ከኦሎምፒክ ኮሚቴ ታማኝ ምንጮቿ እንዳገኘችው መረጃና ደብዳቤ ከሆነ የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ በቀን 10/11/2016 ዓ.ም በቁጥር ኢ/ኦ/ኮ/21117/16 በፅ/ቤት ኃላፊው በአቶ ዳዊት አስፋው ለአትሌት ሀይሌ ገብረስላሴ በስሙ ተፅፎ በተላከው ደብዳቤ "እንወያይ" የሚል ጥያቄ አቅርቧል።

የኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ለአትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ በቀጥታ በስሙ የላከውና ሀትሪክ ከታማኝ ምንጮቿ ያገኘችው ደብዳቤ ላይ እንደሠፈረው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከኢትዮጵያ ኦሎምፒክ ኮሚቴ ጋር መግባባት እንደሌልዎትና በአሠራሩም ቅሬታ እንዳልዎት ለእኛ በቀጥታ በፅሁፍ፣ ወይንም በተለመደ አሠራር ያቀረቡት ነገር ባይኖርም ከመገናኛ ብዙሃን እየሠማን እንገኛለን።ይህንን ተከትሎ "ጀግናውን አትሌታችንን ማዳመጥ አለብን ብለን ስላመንን ዓርብ ሐምሌ 12/11/16 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 በኦሎምፒክ ፅ/ቤት ተገኝተው እንድንወያይ በአክብሮት ጥሪያችንን እናስተላልፋለን ይላል።

በእርግጥ ኃይሌ የፈለገበት ድረስ መሄድ ይችላል የሚል ግትር አቋም በየሚዲያውና በየጋዜጣዊ መግለጫው ሲያንፀባርቁ የቆዩት ዶክተር አሽብርና በእሳቸው የሚመራው ተቋም አሁን ምን ተገኝቶ የሃሳብ ና የአቋም ለውጥ አሳይቶ "ኃይሌ ናና እንወያይ"ማለትን እንደመረጠ ግልፅ የሆነ ነገር ባይገኝም ከጀግናው አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ ጋር የፊታችን አርብ ከቀኑ በ9:00 ለመወያየት ፍላጎት እንዳላቸው በላኩት ደብዳቤ አሳውቀዋል።

የውይይት ግብዣው የቀረበለት አትሌት ሻለቃ ኃይሌ ገብረስላሴ ኦሎምፒክ ባደረገለት ጥሪ ወንበር ስቦ ይቀመጥ ይሆን?ለሚለውን ለማወቅ የእጅ ስልኩ ላይ ደጋግመን ብንደውልም ምላሽ ማግኘት አልቻልንም።

በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገርናቸውና የኦሎምፒክ ኮሚቴ የህግ ጥሠት ፈፅሞ ምርጫ አከናውኗል በሚል ተቋውሞ በማሠማት ላይ የሚገኙ አንዳንድ ወገኖች በሠጡን አስተያየት "በማንአለብኝነት ታብዮ የትም ድረሱ፣የትም ይሂዱ ሲል የነበረው

በአዲስ አበባ የተቃውሞ ድምፅ ለማሰማት ሲዘጋጁ የነበሩ ሁለት አሜሪካውያን እና አንድ እንግሊዛዊ በቁጥጥር ስር ዋሉ ግለሰቦቹ ትናንት በፖሊስ የተያዙት ብሄራዊ አካባቢ በሚገኘው የኢትዮጵያ አየ...
18/07/2024

በአዲስ አበባ የተቃውሞ ድምፅ ለማሰማት ሲዘጋጁ የነበሩ ሁለት አሜሪካውያን እና አንድ እንግሊዛዊ በቁጥጥር ስር ዋሉ

ግለሰቦቹ ትናንት በፖሊስ የተያዙት ብሄራዊ አካባቢ በሚገኘው የኢትዮጵያ አየር መንገድ የቲኬት ቢሮ በመገኘት አየር መንገዱ "ጨካኝ የጦጣ ጭነቶችን ያቁም" የሚል ፅሁፍ ያለበት ፖስተር በመያዝ እና የእስረኛ ልብስ በመልበስ ለተቃውሞ በመዘጋጀት ባሉበት ወቅት እንደነበር የደረሰኝ መረጃ ይጠቁማል።

ከሰሞኑ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለምርምር የሚውሉ ጦጣዎችን እያጓጓዘ ነው የሚሉ ክሶች ሲቀርቡ ነበር። እነዚህ ክሶች እንደሚሉት ጦጣዎቹ ከተጓጓዙ በኋላ "በጭካኔ ተቆራርጠው ተገድለው ለላቦራቶሪ ምርምር ይውላሉ"።

ትናንት በቁጥጥር ስር የዋሉት የእንስሳት መብት ተከራካሪው PETA ምክትል ፕሬዝደንት ጄሰን ቤከር እና የ11 አመት ልጁ እንዲሁም የእንግሊዝ PETA ፋውንዴሽን የዘመቻ ንቅናቄ ሀላፊው ሩበን ስኪትስ ናቸው።

የወደፊቱ የሲቲ ተጨዋች አዲስ ታሪክ ፅፏል !     ማንችስተር ሲቲዎች ከወዲሁ ያስፈረሙት የወደፊት ተስፈኛ ታዳጊ ካቫን ሱሊቫን ትላንት በአሜሪካ ሜጀር ሊግ ሶከር ውድድር ለፊላደልፊያ ዩኒየን...
18/07/2024

የወደፊቱ የሲቲ ተጨዋች አዲስ ታሪክ ፅፏል !

ማንችስተር ሲቲዎች ከወዲሁ ያስፈረሙት የወደፊት ተስፈኛ ታዳጊ ካቫን ሱሊቫን ትላንት በአሜሪካ ሜጀር ሊግ ሶከር ውድድር ለፊላደልፊያ ዩኒየን ተሰልፎ ተጫውቷል።

ታዳጊው በ 14ዓመቱ በአሜሪካ ሜጀር ሊግ ውድድር ላይ ተሰልፎ መጫወት የቻለ በታሪክ በእድሜ ትንሹ ተጨዋች በመሆን አዲስ ታሪክ መፃፍ ችሏል።

ማንችስተር ሲቲዎቹ ባለ ትልቅ ተሰጥኦ ባለቤቱን ታዳጊ ካቫን ሱሊቫን በቅርቡ አንድ ሚልዮን ዶላር አውጥተው ለቡድናቸው አስፈርመውታል።

አሜሪካዊው ታዳጊ ካቫን ሱሊቫን በሚቀጥለው አመት በ2025 ማንችስተር ሲቲን እንደሚቀላቀል ይጠበቃል።

ባለፉት አስርት ዓመታት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ጉልህ ሚና ይዞ የቆየው ህወሓት (ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ) “በ50 ዓመት ታሪኬ ከባዱ ፈተና ተጋርጦብኛል” አለ።ፓርቲው በትግራይ ክልል ...
18/07/2024

ባለፉት አስርት ዓመታት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ጉልህ ሚና ይዞ የቆየው ህወሓት (ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ) “በ50 ዓመት ታሪኬ ከባዱ ፈተና ተጋርጦብኛል” አለ።
ፓርቲው በትግራይ ክልል መዲና መቀለ ለቀናት ሲያካሂድ የነበረውን የከፍተኛ አመራሮች ጉባኤ ካጠናቀቀ በኋላ ባወጣው መግለጫ የግል ጥቅምን ማስቀደም የፓርቲውን ህልውና አደጋ ላይ መጣሉን አስታውቋል።
ፓርቲው ትናንት ማክሰኞ ሐምሌ 9/2016 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ “በማዕከላዊ ኮሚቴው ውስጥ ከሕዝባዊ ወገንተኝነት ያፈነገጠ እና ለግል ጥቅም መሰባሰብ” በተደራጀ መልኩ መሥራት እንዳላስቻለው ገልጿል።
ፓርቲው በማዕከላዊ ኮሚቴው ውስጥ ያጋጠመው የችግር ምንጭ “ቡድናዊነት፣ ፀረ-ዴሞክራሲያዊነት፣ ጎጠኝነት፣ ሕዝበኝነት እና ሙስና” ናቸው ብሏል።

ስፔን አዘጋጇን ጀርመንን በማሸነፍ ወደ ግማሽ ፍጻሜ ገባች አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአውሮፓ ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ መርሐ ግብር እጅግ ተጠባቂ በነበረው ጨዋታ አዘጋጇ ጀርመ...
05/07/2024

ስፔን አዘጋጇን ጀርመንን በማሸነፍ ወደ ግማሽ ፍጻሜ ገባች

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) በአውሮፓ ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ መርሐ ግብር እጅግ ተጠባቂ በነበረው ጨዋታ አዘጋጇ ጀርመን በስፔን 2 ለ 1 ተሸንፋ ከውድድሩ ውጪ ሆነች።

የ17ኛው የአውሮፓ ዋንጫ የሩብ ፍጻሜ መርሐ ግብር ዛሬ ምሽት 1:00 ሰዓት ላይ በስቱትጋርት አሬና ስታዲየም በተካሄደው የጀርመንና ስፔን ጨዋታ ጀምሯል።

ብሔራዊ ቡድኖቹ ባደረጉት ጨዋታ መደበኛ ሰዓቱን 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ማጠናቀቃቸውን ተከትሎ ወደ ተጨማሪ ሰዓት አምርተዋል።

በዚህም ስፔን አንድ ተጨማሪ ግብ በማስቆጠሯ 2 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፋ ወደ ግማሽ ፍጻሜው ገብታለች።

በስፖርቱ ቤተሰብ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው ይህ ጨዋታ ዳኒ ኦልሞ እና ሚኬል ሜሪኖ ባስቆጠሯቸው ጎሎች ስፔን ለድል ስትበቃ፤ አዘጋጇ ጀርመን ከሽንፈት ያላዳነቻትን ብቸኛ ግብ ፍሎሪያን ቨርትዝ አስቆጥሯል።

የሩብ ፍጻሜው ጨዋታ ምሽት 4:00 ላይ ሲቀጥል ፖርቹጋል እና ፈረንሳይ በቮልክስፓርክ ስታዲየም ጨዋታቸውን ያካሂዳሉ።

ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት 10. 5 ቢሊዮን ዶላር ልታገኝ እንደምትችል ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ገለጹ ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) እና ከዓለም ባንክ ጋር ...
04/07/2024

ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት 10. 5 ቢሊዮን ዶላር ልታገኝ እንደምትችል ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ገለጹ

ኢትዮጵያ ከዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት (IMF) እና ከዓለም ባንክ ጋር የምታደርገው ድርድር ከተሳካ፤ 10.5 ቢሊዮን ዶላር እንደምታገኝ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ተናገሩ። መንግስታቸው ገንዘቡን ካገኘ፤ ዛሬ በጸደቀው የፌደራል መንግስት በጀት ላይ ማሻሻያዎች ሊደረጉ እንደሚችሉ ጥቆማ ሰጥተዋል።

የፌደራል መንግስት ለ2017 ያዘጋጀው በጀት 971.2 ቢሊዮን ብር ነው። በጀቱ ዛሬ ሐሙስ ሰኔ 27፤ 2016 በተካሄደው የተወካዮች ምክር ቤት ስብሰባ በሙሉ ድምጽ ጸድቋል።

በዚሁ ስብሰባ ላይ የተገኙት ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ፤ መንግስታቸው የኢኮኖሚ ጉዳዮችን በተመለከተ ከዓለም አቀፍ ተቋማት ጋር ስለሚያደርገው ድርድር ማብራሪያ ሰጥተዋል። መንግስታቸው ከIMF እና ከዓለም ባንክ ጋር ላለፉት አምስት ዓመታት “ሰፊ ንግግር፣ ድርድር እና ውይይት” ሲያደርግ መቆየቱንም አብይ አስታውሰዋል።

ኢትዮጵያ ተግባራዊ በምታደርጋቸው “የሪፎርም አጀንዳዎች” ላይ የተደረገው ድርድር ይህን ያህል ጊዜ የወሰደው “እኛም አስቸጋሪዎች፤ እነሱም አስቸጋሪዎች በመሆናቸው ነው” ብለዋል። “አሁን አንዳንድ ወዳጅ ሀገራት ባደረጉልን ድጋፍ፤ አብዛኛው ሃሳቦቻችን ተቀባይነት እያገኙ ይመስላል” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ መንግስታቸው ጠቀም ያለ ገንዘብ ሊያገኝበት የሚችለው ድርድር እየተገባደደ ነው የሚል ተስፋ እንዳላቸው ጠቆም አድርገዋል።

“ይህ ጉዳይ ተሳክቶ ሪፎርሙን ካጸደቅን፤ ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት ዓመታት ተጨማሪ 10.5 ቢሊዮን ዶላር ታገኛለች” ሲሉ አብይ ለፓርላማ አባላት ተናግረዋል። ተስፋ የተደረገበት ገንዘብ ከተገኘ፤ በፌደራል መንግስት በጀት ላይ “ይህን ታሳቢ ያደረገ ማሻሻያዎች ሊደረጉ ይችላሉ” ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ። (ኢትዮጵያ ኢንሳይደር)

ኢትዮጵያ ስለ አንካራው ውይይት ምን አለች ?የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በአንካራው ውይይት ጉዳይ የፕሬስ መግለጫ አውጥቷል።በመግለጫው በቱርኪዬ ሪፐብሊክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሀካን ፊዳን ጋባዥነት...
02/07/2024

ኢትዮጵያ ስለ አንካራው ውይይት ምን አለች ?

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር በአንካራው ውይይት ጉዳይ የፕሬስ መግለጫ አውጥቷል።

በመግለጫው በቱርኪዬ ሪፐብሊክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሀካን ፊዳን ጋባዥነት የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ እና የሶማሊያ የውጭ ጉዳይና ዓለምአቀፍ ትብብር ሚኒስትር አህመድ ሞአሊም ፊቂ ትላንት ሰኔ 24 ቀን 2016 ዓ.ም በአንካራ ተገናኝተው መወያየታቸውን አረጋግጧል።

„ በቱርኪዬ መንግስት አመቻቺነት የተካሄደው የሁለቱ ሚኒስትሮች ውይይት በሁለቱ አገራት መካከል ላሉ አለመግባባቶች መፍትሄ ሊያመጡ በሚችሉ ጉዳዮች ላይ ግልፅና ወዳጅነት የተሞላበት የሀሳብ ልውውጥ የተደረገበት ነበር „ ብሏል።

ሁለቱ ሚኒስትሮች ያሉ አለመግባባቶችን በሰላማዊ መንገድ እልባት ለመስጠት ቁርጠኝነታቸውን መግለጻቸውን አመልክቷል።

የቱርኪዬ መንግስት ውይይቱን ለማመቻቸት ስለተጫወተው ገንቢ ሚናም ምስጋና እንደቀረበ ገልጿል።

ሁለቱ ሚኒስትሮች መልካም ጉርብትናን እና ቀጠናዊ መረጋጋትን ከግምት በማስገባት መፍትሄዎችን ለማመላከት ያለሙ ምክክሮችን ለመቀጠልም እንደተስማሙ አረጋግጧል።

ሁለቱም ሚኒስትሮች የቱርኪዬ ፕሬዚዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ምከከሩን አገራቸው ለማስተናገድ የወሰዱትን ተነሳሽነት በማድነቅ ሁለተኛ ዙር ውይይታቸውን ነሐሴ 27 ቀን 2016 ዓ.ም በአንካራ ለመቀጠል እንደተስማሙ የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳውቋል።

አንቺ ሴት ከቻልሽ ወደ ቀልብሽ ተመለሺ❌❌መቼም በዚህ እድሜሽ ተሳስቼ ነው ገለመሌ አትይንም አይደል የሆነ ዩቲዩብ ላይ ቀርበሽ???❌❌❌አይንሽን ማየት አንፈልግም❌❌❌
06/05/2024

አንቺ ሴት ከቻልሽ ወደ ቀልብሽ ተመለሺ❌❌

መቼም በዚህ እድሜሽ ተሳስቼ ነው ገለመሌ አትይንም አይደል የሆነ ዩቲዩብ ላይ ቀርበሽ???

❌❌❌አይንሽን ማየት አንፈልግም❌❌❌

ተቋርጦ የነበረው የቅርንጫፎች አገልግሎት ስራ ጀምሯል - የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በሲስተም ችግር ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የቅርንጫፎች አገልግሎት ስራ መጀመሩን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታ...
16/03/2024

ተቋርጦ የነበረው የቅርንጫፎች አገልግሎት ስራ ጀምሯል - የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ

በሲስተም ችግር ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የቅርንጫፎች አገልግሎት ስራ መጀመሩን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አስታወቀ፡፡

ባንኩ ባስተላለፈው መልዕክት ቅርንጫፎች አገልግሎት መስጠት የጀመሩ ሲሆን በዚህም ዛሬ እስከ ምሽቱ 2፡00 ሰዓት አገልግሎት እንደሚሰጡ አስታውቋል፡፡

በተመሳሳይ ዲጂታል የባንክ አገልግሎቶችን (ኢንተርኔት ባንኪንግ፥ ሞባይል ባንኪንግ፥ እንዲሁም ሲቢኢ ብር) ለማስጀመር እየሠራ መሆኑን ገልፆ ለተፈጠረው የአገልግሎት መስተጓጎል በድጋሚ ይቅርታ ጠይቋል፡፡

በቱርክ የደረሰ የአውሮፕላን አደጋየቱርክ የአየር ትርዒት አቅራቢ (ኤሮባቲክ) አውሮፕላን በልምምድ ላይ እያለ መከስከሱን የሀገሪቱ መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል።አውሮፕላኑ መንስኤው ባልታወቀ ...
15/03/2024

በቱርክ የደረሰ የአውሮፕላን አደጋ

የቱርክ የአየር ትርዒት አቅራቢ (ኤሮባቲክ) አውሮፕላን በልምምድ ላይ እያለ መከስከሱን የሀገሪቱ መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል።

አውሮፕላኑ መንስኤው ባልታወቀ መክንያት አየር ላይ መጨስ ከጀመረ በኋላ መከስከሱ የተነገረ ሲሆን፤ በምድር ላይ የነበረ የአቪዬሽን ሰራተኛ ህይወቱ ሲያልፍ የአብራሪው ግን አየር ላይ እያለ በማስፈንጠሪያ ወጥቶ ህይወቱ መትረፉ ተነግሯል።

የገጻችን ቤተሰብ ይሁኑ!

Address

Bole
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ዜና ኢትዮጵያ Zena Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share