AFTA MEDIA አፍታ ሚዲያ

AFTA MEDIA አፍታ ሚዲያ Afta Media ‘Voice of Reason’ is your Ethiopian idea platform.

29/05/2025

💔💔💔

ሆርቲ ካምፓስ የተሰኘ ኢ-ለርኒንግ ፕላትፎርም ይፋ ሆነ የኢትዩጵያ ሆርቲካልቸር አምራች ላኪዎች ማህበር  ተደራሸነቱን ለማስፋት እና ዓለም የደረሰበትን የዲጂታል ቴክኖሎጂን ተግባራዊ ለማድረግ ...
29/05/2025

ሆርቲ ካምፓስ የተሰኘ ኢ-ለርኒንግ ፕላትፎርም ይፋ ሆነ

የኢትዩጵያ ሆርቲካልቸር አምራች ላኪዎች ማህበር ተደራሸነቱን ለማስፋት እና ዓለም የደረሰበትን የዲጂታል ቴክኖሎጂን ተግባራዊ ለማድረግ ሆርቲ-ካምፓስ የተሰኘውን E-learning platform ከትሬድማርክ አፍሪካ ጋር በመተባበር በኢዮሮፕያን ዩንየን ድጋፍ ማዘጋጀቱን አስታውቋል፡፡

ማህበሩ ከተመሰረተበት ዓመት ጀምሮ አባላቶቹ ዓለም አቀፍ ደረጃዎችን ከማሟላት አንጻርም የራሱን የሆነ የነሀስ፣ የብርና ወርቅ አሰራር ደንቦችን በማቋቋም ለአባላቱ አቅም ማጎልበት ጉልህ አስተዋጾ ሲያበረክት የቆየ ሲሆን እ፡አ.አ ከ2019ዓ.ም ጀምሮ የስልጠና ክፍሉ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የትምህርት እና ስልጠና ጥራት ቁጥጥር ባለስልጣን እውቅና በማግኘት አገልግሎቱን አስፍቶ በስራ ላይ ይገኛል።

ኢትዮጲያ በሆርቲካልቸር ኤክስፖርት ኢንዱስትሪ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ተፎካካሪ እንድትሆን ዘርፉን _ በተለያዩ _ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎችን ላለፉት 18 ዓመታት ሲሰጥ ቆይቷል:: በዚህም ከ50000 በላይ የዘርፉ ባለሙያዎችና ሰራተኞች ተጠቃሚ ሆነዋል።

ማህበሩ የሚሰጠውን ስልጠና ለማዘመን እና ደረጃውን የጠበቀ እንዲሆን E-learning platform በመላ አገሪቱ ላሉ ባለሙያዎች፣ ሰራተኞች፣ የልማት ጣቢያ ሰራተኞች እንዲሁም በዘርፉ ፍላጎት ያላቸው ተቋማት ወቅታዊ እና ከፍተኛ ጥራት ያለው ስልጠና በመስጠት የሃገሪቷን የሆርቲካልቸር ዘርፍ የአቅም ግንባታን ለመለወጥ የሚጠቅም ነው ተብሏል፡፡

ከዚህም በተጨማሪ የሆርቲ-ካምፓስ E-leaming platform ስራ መጀመር _ ኢትዮጵያ በሆርቲካልቸር ኢንደስትሪ የበለጠ ተፎካካሪ እንድትሆን ተጨማሪ አቅም የሚፈጥር ሲሆን በግብርና የሰው ኃይልን በመለወጥ ረገድ የዲጂታል ትምህርት ያለውን ተፅዕኖ እና የወደፊት እምቅ አቅም በመጋራት ረገድ ወሳኝ ሚና ይጫወታል፡፡

ሹመት‼️የኦነግ ሸኔ ሰራዊት ምክትል አዛዥ የነበሩት እና በቅርቡ ከክልሉ መንግስት ጋር የሰላም ስምምነት የፈፀሙት አቶ ጃል ሰኚ ነጋሳ የኦሮሚያ ክልል ሚሊሻ ቢሮ ኃላፊ በመሆን በዛሬው መሾሙ ...
29/12/2024

ሹመት‼️

የኦነግ ሸኔ ሰራዊት ምክትል አዛዥ የነበሩት እና በቅርቡ ከክልሉ መንግስት ጋር የሰላም ስምምነት የፈፀሙት አቶ ጃል ሰኚ ነጋሳ የኦሮሚያ ክልል ሚሊሻ ቢሮ ኃላፊ በመሆን በዛሬው መሾሙ ተዘግቧል።

29/12/2024

😥😥

የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሓኖም ገብረ እየሱስ እስራኤል ጥቃት እየፈጸመች በነበረችበት በየመኑ ሰንዓ አውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ እንደነበሩ ገለጹ። በጥቃቱ አንድ የ...
26/12/2024

የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴድሮስ አድሓኖም ገብረ እየሱስ እስራኤል ጥቃት እየፈጸመች በነበረችበት በየመኑ ሰንዓ አውሮፕላን ማረፊያ ውስጥ እንደነበሩ ገለጹ። በጥቃቱ አንድ የአውሮፕላኑ ሰራተኛ ተጎድቷል።
"ከሁለት ሰዓታት በፊት፣ ከሰንዓ ለመብረር ወደ አውሮፕላኑ ልንሳፈር ስንል አየር ማረፊያው የአየር ጥቃት ተፈጸመበት" ብለዋል።

''ምርጫው ፍትሀዊ አይደለም''  የተከበሩ አቶ ዱቤ ጁሎለኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ምርጫ እጩ ሆነው የተወዳደሩት ዱቤ ጁሎ(የተከበሩ) ምርጫው ፍትሀዊ አይደለም ሲሉ  ተናግረዋል...
22/12/2024

''ምርጫው ፍትሀዊ አይደለም'' የተከበሩ አቶ ዱቤ ጁሎ

ለኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ምርጫ እጩ ሆነው የተወዳደሩት ዱቤ ጁሎ(የተከበሩ) ምርጫው ፍትሀዊ አይደለም ሲሉ ተናግረዋል።

በሀገር ላይ ከፍተኛ ደባ እየተሠራ ነው፤እኔ ይሄንን ፍትሃዊ ምርጫ ነው ብዬ አልቀበልም ያሉት አቶ ዱቤ ምርጫው ያለቀለት ነው ወደ ጉባኤው አትሂድ ተብዬ ነበር፤ በጉባኤውም የገጠመኝ ይኸው ነው ሲሉ አስረድተዋል።

ሌላው ቢቀር የወከለኝ ክልል እንዴት አንድ ድምፅ ይነፍገኛል፤ይሄ ራሱ የምርጫውን ፍትሃዊ አለመሆን ያሳያል ባለመመረጤ አልበሳጭም በአትሌቲክሱም ተስፋ አልቆርጥም ሲሉ ከውጤቱ በኋላ ምልከታቸውን ለሀትሪክ ስፖርት አጋርተዋል።

18/12/2024

ጋዜጠኛዋ ከ ሥራ ታገደች

ሰሞኑን የኢሳት ቴሌቪዥን የዜና አንባቢ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቆሴ ወረዳ የተመለከተ ዜና ስታነብ ቆሴ የሚለውን ስም ለመጥራት ሲያስቸግራት ያለውን ቪዲዮ በቲክቶክ ገጿ ላይ በመለጠፍ የተለያዩ ትችቶችን ስታስተናግድ ነበር ኢሳት ቴሌቪዥን ይህን ተመልክቶ ዜና አንባቢዋን እና የተቆረጠውን ቪዲዮ አሳልፎ የሰጣትን ባልደረባ ከስራ ማገዱ ተሰምቷል

 አርቲስት ሀረገወይን አሰፋ ሀሳብ ቀይራ ስራ ጀመረች።የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌደሬሽን አቃቢ ነዋይ ሆና ተመርጣ ጉዳዩን አላቅም ብላ የነበረችው አርቲስቷ ዛሬ ስብስቡን ተቀላቅላለች።አዲሱ ስ...
10/12/2024



አርቲስት ሀረገወይን አሰፋ ሀሳብ ቀይራ ስራ ጀመረች።

የአዲስ አበባ እግር ኳስ ፌደሬሽን አቃቢ ነዋይ ሆና ተመርጣ ጉዳዩን አላቅም ብላ የነበረችው አርቲስቷ ዛሬ ስብስቡን ተቀላቅላለች።

አዲሱ ስራ አስፈፃሚ የትውውቅ ፕሮግራም ዛሬ ሲያካሄድ በሀገር ውስጥ የሌለው ዶ/ር ወገኔ ዋልተንጉስ ብቻ በመጀመሪያ ስብሰባ ላይ ያልተሳተፈ አባል ነው።

በፕሬዝዳንት ኢንጂነር ሀይለየሱስ የሚመራው ስራ አሰፈፃሚው የስራ ክፍፍል በማድረግ ወደ ስራ መግባቱን ለማወቅ ችለናል።

#ዋይን ስፖርት

የባለቤቱን  እጅ በመቁረጥ የአካል ጉዳት ያደረሰው ግለሰብ እስራት ተቀጣ በሲናና ወረዳ ወልቲኢ አርጆ  ቀበሌ  ነዋሪ እና  የሁለት ልጆች ወላጆች የሆነዉ ጎሳ በላቸው ከኮከቤ ዳምጤ ጋር ትዳር...
09/12/2024

የባለቤቱን እጅ በመቁረጥ የአካል ጉዳት ያደረሰው ግለሰብ እስራት ተቀጣ

በሲናና ወረዳ ወልቲኢ አርጆ ቀበሌ ነዋሪ እና የሁለት ልጆች ወላጆች የሆነዉ ጎሳ በላቸው ከኮከቤ ዳምጤ ጋር ትዳር መስርቶ አብረው ሲኖሩ የቆየ ቢሆንም በአካባቢያቸው ያሉ ሴቶች አረብ ሀገር ሄደው ሰርተው ሲመጡ በመመልከት እኔም መሄድ አለብኝ በሚል ጥያቄ በመካከላቸው ግጭት ይፈጠር የነበረ መሆኑ ተገልጿል።

በዚህም በተፈጠረ ግጭት ወደ ቤተሰቦቿ ጋር ኮከቤ ዳምጤ ትሄዳለች፡፡ ባለቤቷ ሳያውቅ በድብቅ ወደ አረብ ሃገር ለመሄድ የሚያስፈልጋትን ዝግጅት ትጀምራለች ። ሀምሌ 28ቀን 2016 ዓ.ም ኮከቤ ዳምጤ ወደ ቀበሌ በመሄድ የልደት ካርድ ስታወጣ ለባለቤቷ መረጃው ይደርሰዋል ። ይህንንም ሲሰማ በመበሳጨት ስለታም ባንጋ በመያዝ ከቀበሌ ስትመለስ የበቆሎ እርሻ ውስጥ ጠብቆ ሃሳቤን አላከበርሽም በማለት የጆሮ ግንዷን መቶ ከጣላጥ በኋላ ግራ እጇን ሙሉ በሙሉ መቁረጡ ተገልጿል ።

ስትጮህ የሰሙ የአካባቢው ነዋሪዎች ተጎጂዋን ወደ ሮቤ ሆስፒታል በመውሰድ እርዳታ እንድታኝ አድርገዋል፡፡ ፖሊስ ጉዳቱን በመመልከት ተከሳሹን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራውን በማጣራት ለዓቃቢህግ ይልካል። ዓቃቢህግ ሰው በመግደል ሙከራ እና በአካል ማጉደል ክስ በመመስረት ለፍርድ ቤት ያቀርባል ።

የባሌ ዞን ፍርድ ቤትም ህዳር 25 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሽ ጎሳ ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ በ15 ዓመት እስራት እንዲቀጣ ውሳኔ የተላለፈበት መሆኑን የሲናና ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት የወንጀል ምርመራ ክፍል ሃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ፍቅሩ ቦጃ ተናግረዋል።

በጥንቆላ ተግባር የተሰማሩ 110 ሰዎች መገደላቸው ተሰማበሄይቲ ዋና ከተማ ዝቅተኛ ገቢ ባላቸዉ አካባቢዎች ቢያንስ 110 ሰዎች በሳምንቱ መጨረሻ ተገድለዋል ሲል አንድ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ...
09/12/2024

በጥንቆላ ተግባር የተሰማሩ 110 ሰዎች መገደላቸው ተሰማ

በሄይቲ ዋና ከተማ ዝቅተኛ ገቢ ባላቸዉ አካባቢዎች ቢያንስ 110 ሰዎች በሳምንቱ መጨረሻ ተገድለዋል ሲል አንድ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ቡድን ገልጿል፡፡ ግድያው በአካባቢው የወሮበሎች ቡድን የተፈጸመ ነዉ፡፡የብሄራዊ የሰብአዊ መብት መከላከያ ኔትዎርክ (አርኤንዲኤች) እሁድ እለት እንዳስታወቀው የወንጀለኛ ቡድኑ መሪ "ሚካኖ" ፌሊክስ ልጁ ከታመመ በኋላ በፖርት-አው-ፕሪንስ ውስጥ የተንሰራፋው ጥንቆላን ምክንያት በማድረግ የጅምላ ጭፍጨፋዉ እንዲፈጸም አዟል።

ፌሊክስ ሕፃን ልጄን የገደለብኝ ጥንቆላ ተጠቅመዉ ነዉ በማለት በአካባቢው ያሉ በጥንቆላ የተሰማሩ አዛውንቶችን እንዲያጠፋ ምክር የሰጡትን ቄስ ቃል ተግባራዊ አድርጓል፡፡የወሮበሎች ቡድን አባላት አርብ ዕለት ቢያንስ 60 ሰዎችን እና ቅዳሜ 50 ሰዎችን ቢላዋ ተጠቅመዉ ገድለዋል ሲል የመብት ተሟጋች ድርጅቱ አስታዉቋል፡፡ሁሉም ተጎጂዎች ከ60 በላይ እድሜ ያላቸው መሆናቸውን የመብት ቡድኑ ገልጿል።

ከፍተኛ የህዝብ አሰፋፈር ባለበት ሲቲ ሶሌይል ከሄይቲ በጣም ድሃ እና ብጥብጥ ካሉባቸዉ አካባቢዎች አንዱ ነው።በፖለቲካዊ ሽኩቻ የተነሳ በዋና ከተማው እና በአካባቢው እያደገ የመጣውን የታጠቁ የወንበዴ ቡድኖችን ሃይል ለመቆጣጠር የሄይቲ መንግስት ከአቅሙ በላይ ሆኗል፡፡

ሃላል" የተሰኘ ኬተሪንግ በይፋ ሥራውን ጀመረ ሃላል የተሰኘ ኬተሪንግ በይፋ ስራ መጀመሩን በሰጠው መግለጫ አስታወቀ።ሃላል የተሰኘ ባህላዊን ከዘመናዊ ምግቦች በማጣመር የሚሰራ  የምግብ አዘጋጅ...
08/12/2024

ሃላል" የተሰኘ ኬተሪንግ በይፋ ሥራውን ጀመረ

ሃላል የተሰኘ ኬተሪንግ በይፋ ስራ መጀመሩን በሰጠው
መግለጫ አስታወቀ።

ሃላል የተሰኘ ባህላዊን ከዘመናዊ ምግቦች በማጣመር የሚሰራ የምግብ አዘጋጅ ተቋም(ኬተሪንግ) ለ ህብረተሰቡ አገልግሎት መጀመሩን በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታወቀ።

ሃላል ኬተሪንግ በኃይማኖት እና በሳይንስ ሃላል ያልሆኑ( ያልተፈቀዱ) ምግቦችን ህብረተሰብ እንዳይመገብ በማሰብ ጥራቱን በጠበቀ መልኩ የሚሰራ መሆኑን ተጠቁሟል።

የ"ሃላል" ኬተሪንግ መስራች የሆኑት ወ/ሮ መዲሃ ሰይድ እንደተናገሩት ሃላል ኬተሪንግ የሰዎችን ጤና በጠበቀ መልኩ ለመጀመርያ ግዜ በኬተሪንግ የተለያዩ የሐበሻ እና የአረብ ምግቦችን ከሀገር ውስጥ እና ከውጪ በመጡ ባለሙያዎች እንደሚዘጋጁ ገልጸዋል።

"ሃላል" ኬተሪንግ የተለያዩ ምግቦችን ለ፣ሰደቃ፣ኢፍጣር፣ ሰርግ፣ለሀቂቃ፣ለሂና እንዲሁም ኮርፖሬት ኩባንያዎች እና ሌሎች ሻይ ቡናን ጨምሮ የተለያዮ ፓኬጆች አሉት ተብሏል።

Address

Addis Ababa
1000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when AFTA MEDIA አፍታ ሚዲያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Your Voice

Ethio Anchor Media ‘your voice’ Ethiopian multi-platform entertainment and media company ,Powered by its own proprietary technology We provide you with the latest breaking news, recent affairs, discussions with different prominent Ethiopian individuals and more.

is the go-to source for technology, digital culture and entertainment content for its dedicated and influential audience around the nation as well for the world.