Lemi Kura Wereda 14 Communication

Lemi Kura Wereda 14 Communication ይህ የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት ገጽ ነው

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ  የብልፅግና ፓርቲ  '' ከቃል እስከ ባህል " በሚል መሪ ቃል  ሁለተኛው የብልፅግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ቅድመ ጉባኤ ውይይት በክፍለ ከተማ ደረጃ የማጠቃለያ ኮንፍራን...
15/01/2025

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ '' ከቃል እስከ ባህል " በሚል መሪ ቃል ሁለተኛው የብልፅግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ቅድመ ጉባኤ ውይይት በክፍለ ከተማ ደረጃ የማጠቃለያ ኮንፍራንስ እየተካሄደ ይገኛል።

"የጥምቀት በዓል ሀገራችንን ኢትዮጵያ በአለም አቀፍ ደረጃ ያስተዋወቀ የጋራ የአብሮነት መገለጫ በዓላችን ነው"አቶ አድማሱ ደቻሳየለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚበለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ...
15/01/2025

"የጥምቀት በዓል ሀገራችንን ኢትዮጵያ በአለም አቀፍ ደረጃ ያስተዋወቀ የጋራ የአብሮነት መገለጫ በዓላችን ነው"

አቶ አድማሱ ደቻሳ
የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የ2017 ዓ.ም ጥምቀት በዓል አከባበር ማስፈፀሚያ እቅድን አስመልክቶ የክፍለ ከተማ ጠቅላላ አመራር፣የአስሩም ወረዳዎች አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት፣የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ አመራሮች፣ የየደብሩ አስተዳዳሪዎች፣ የሀይማኖት አባቶች፣አባገዳዎች፣የፀጥታ አካላት፣የደንብ ማስከበር ኦፊሰሮች የሠንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች እንዲሁም ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው አካላት በተገኙበት በዓሉ በሠላም እንዲከበር በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት አካሄዷል።

የውይይት መድረኩን የመሩት የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አድማሱ ደቻሳ እንዳሉት የጥምቀት በዓል ሀገራችንን ኢትዮጵያ በአለም አቀፍ ደረጃ ያስተዋወቀ፣በርካታ የሀይማኖቱ ተከታይ የሆኑና ያልሆኑ የተለያዩ የውጭ ሀገራት ዜጎች የሚታደሙበት እንዲሁም በክፍለ ከተማችን በርካታ ሀይማኖታዊ ተቋማት የሚበዙበት በመሆኑ ከሀይማኖት መሪዎች ጋር ተባብሮ መስራቱ እጅግ ወሳኝ ነው ሲሉ አክለውም ስለሠላም መከበር መስራት ያለበት ስራ የመንግስት ብቻ ሳይሆን ሁሉም የማህበረሰብ ክፍል በቅንጅት መሆን አለበት ብለዋል።

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑ አቶ ፈንታሁን ሌማንቾ በበኩላቸው በዓሉ ሀይማኖታዊ ትፊቱን እንደጠበቀ ከፍ ብሎ ለማክበር በክፍለ ከተማው ከመቼው ጊዜ በላይ እንደ ኮሪደር ልማትና በኮሪደር ልማት ምክንያት ከመሀል ከተማ ተነስተው ወደ ክፍለ ከተማችን የመጡ ነዋሪዎች በጋራ ደምቀን የምናከብረው ምቹ ሁኔታዎችን የፈጠረ በመሆኑ በዓሉን ታላቅ ያደርገዋል ሲሉ በዓሉን ተከትሎ እምነትን ከእምነት ብሔርን ከብሔር ለማጋጨት ፀብ አጫሪ መልዕክቶችን በመያዝ በዓሉ በሠላም እንዳይጠናቀቅ ለማድረግ የሚሠሩ አካላት ደግሞ በፅኑ የማወገዝ ስራ የፀጥታ አካሉና የሀይማኖት አባቶች ተግባር ብቻ ሳይሆን የሁሉም ማህበረሰብ ስራ ሊሆን ይገባል ብለዋል።

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የፖሊስ ማህበረሰብ አቀፍ ዲቪዚዮን ኃላፊ ኮማንደር ካሳሁን ፍቃዱ በዓሉ ሀይማኖታዊ ቱፊቱን ጠብቆ እንዲከበር የፀጥታ አካሉ በበቂ ሁኔታ ዝግጅት አድርጓል ብለው ማህበረሰቡ ከፀጥታ አካሉ ጋር በተናበበ መልኩ እንዲሳተፉም አበክረው መልዕክት አስተላልፈዋል።

የለሚ ኩራ ኮሚኒኬሽን
ጥር /7/2017 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ በከተማው የነዳጅ አቅርቦት፣ ስርጭትና የቁጥጥር ሂደቶች ላይ መግለጫ ሰጠ፡፡የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ሀላፊ ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ ለአዲ...
14/01/2025

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ በከተማው የነዳጅ አቅርቦት፣ ስርጭትና የቁጥጥር ሂደቶች ላይ መግለጫ ሰጠ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ንግድ ቢሮ ሀላፊ ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ ለአዲስ አበባ ከተማ እየቀረበ ባለው ነዳጅ አቅርቦት፣ ስርጭት እና ቁጥጥር ሂደትን በሚመለከት ከማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ትግበራ አንስቶ ልዩ የክትትል እና ድጋፍ ስርዓት በመዘርጋቱን ይፋ አድርጓል።

በዚህም በከተማዋ 125 ማደያዎች ቀርቦ በመሰራጨት ላይ ያለ የነዳጅ ምርት መጠን በሊትር ናፍጣ በአማካኝ በቀን 2.0 ሚሊዮን ፣ ቤንዚን በአማካኝ በቀን 1.45 ሚሊዮን ሊትር በድምሩ ባለፉት ስድስት ወራት በቀን በአማካኝ 3.45 ሚሊዮን ሊትር ነዳጅ በበቂ መጠን መቅረቡን አመላክተዋል፡፡

ለፕሮጀክቶች እና ነዳጅ ለሚጠቀሙ ለተፈቀደላቸው 234 ተቋማትም አሰራሩን በጠበቀ አግባብ ናፍጣ 1,047,422 እና ቤንዚን 978,071 በድምሩ 2,025,493 ሊትር ነዳጅ ለተቋማቱ መሰራጨቱን የቢሮ ሀላፊ ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ ጠቅሰዋል፡፡

በቁጥጥር ሂደት ህገ-ወጥ ተግባር ውስጥ የገቡ ነዳጅ ማደያዎች ላይም እርምጃ መወሰዱን ያስታወሱት የቢሮው ኃላፊ ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ በዚህም በህገ-ወጥ ሲዘዋወር የተወረሰ የነዳጅ መጠን ቤንዚን 18985 ሊትር፣ ናፍጣ 9434.5 እና ነጭ ጋዝ 189 በድምሩ 28608.5 ሊትር ነዳጅ መወረሱን እና የዋጋ ጭማሪ በመጠባበቅ ሳይሰራጭ የቆየ አንድ ቦቲ ቤንዚን የዋጋ ጭማሪውን ተከትሎ በመደበኛው ገበያ 19000 ሊትር እንዲሸጥ በማድረግ ጭማሪው ለመንግስት ገቢ እንዲሆን ተደርጓል ብለዋል፡፡ በጥቅሉም 47608.5 ሊትር ነዳጅ ምርቱ ተሽጦ 2,600,649.94 ብር ለመንግስት ገቢ መደረጉም በመግለጫቸው አውስተዋል፡፡

በቀጣይም ቢሮው የነዳጅ አቅርቦትና ስርጭቱን ጤናማ ለማድረግ በሚያስችሉ ጉዳዮች ላይ አበክሮ እንደሚሰራ የገለጹት ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ ቢሮው በፍጹም የማይታገሳቸውንና በህጉ መሰረት ጠበቅ ያለ እርምጃ ለመውሰድ የሚገደድባቸውንም ነጥቦች አብራርተዋል ። ለአብነት ነዳጅን በኮንትሮባንድ በመሸጥ ከከተማ እንዲወጣ የሚያደርጉ ማደያዎችን ፣ ከኤሌክተሮኒክስ የመገበያያ አማራጮች ውጪ ነዳጅን በጥሬ ገንዘብ ሽያጭ የሚፈጽሙ እንዲሁም በማደያቸው የሚገኙ ማሽኖችን ሁሉንም አገልግሎት ላይ ባለማዋል ተገቢ ያልሆነ ሰልፎችን የሚፈጥሩትንና በመጨረሻም በንግድ ፍቃድ አሰጣጥ መስፈርቱ ላይ በተቀመጠው መሰረት የ24 ሰዓት አገልግሎት በማይሰጡ ማደያዎች ላይ በህጉ በተቀመጠው አግባብ እርምጃዎችን እንደሚወስድ አሳስበዋል፡፡

በመግለጫቸው ማጠቃለያም ማደያዎች በመንግስት የሚቀርበውን ነዳጅ ስርዓቱን በጠበቀና በህጋዊ አግባብ ማሰራጨት እንደሚገባቸውና ማህበረሰቡም ይህን አውቆ አገልግሎቱን በፍትሀዊነት ማግኘት እንዲችል ሁሉም ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት እንደሚገባ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

"ከቃል እስከ ባህል" በፎቶ ማህደራችን!
14/01/2025

"ከቃል እስከ ባህል" በፎቶ ማህደራችን!

"ከቃል እስከ ባህል" በሚል መሪ ቃል  የመሰረታዊ ፓርቲ ቅድመ ጉባኤ ውይይት  በወረዳ ደረጃ ተጠቃለለ"   በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14  ብልጽግና ፓርቲ  ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስተባ...
14/01/2025

"ከቃል እስከ ባህል" በሚል መሪ ቃል የመሰረታዊ ፓርቲ ቅድመ ጉባኤ ውይይት በወረዳ ደረጃ ተጠቃለለ"

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስተባባሪነት "ከቃል እስከ ባህል"በሚል መሪ ቃል 2ኛው የብልፅግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ቅድመ ጉባኤ ኮንፈረንስ የወረዳው ኮር አመራሮች እና በወረዳ ደረጃ ጉባኤውን እንዲሣተፉ የተለዩ የመሠረታዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት በተገኙበት የቅድመ ጉባኤ ኮንፈረንሱ የማጠቃለያ ውይይት በዛሬው ዕለት በልዩ ድምቀት ተከናውኗል።

የቅድመ ጉባኤ ኮንፈረንሱ "ከቃል እስከ ባህል"በሚል መሪ ቃል ተቋማዊ ባህል እንዲሰፍን ስርዓታዊ ልዕቀት ለዘላቂ ሀገረ መንግስት ያለውን ፋይዳ በሚያስተጋባ መልኩ የተካሄደ ሲሆን በወረዳ ደረጃ በዕለቱ በተካሄደው 2ኛው የብልፅግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ቅድመ ጉባኤ ኮንፈረሱ የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ብርሃኑ ትርፌ፣የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌቴ ቢሠጠኝ እና የወረዳው ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚና የስራና ክህሎት ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ረጅብ አክመል እንዲሁም በወረዳው የብልፅግና ፓርቲ ኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሲሣይ ቤተ ማርያም በተገኙበት የተካሄደ ሲሆን በውይይቱም በለውጥ ሂደት የተገኙ ስኬቶችን በተባበረ ክንድ ለማስቀጠል ብሎም የተስተዋሉ ክፍተቶችን በተቀናጀ መልኩ ለማረም በሚያስችል መልኩ በወረዳ ደረጃ የማጠቃለያ ኮንፈረንሱ ተካሂዷል።

የማጠቃለያ ኮንፈረንሱ በበርካታ አባላት ታጅቦ የተካሄደ ሲሆን በመድረኩም "ከቃል እስከ ባህል"በሚል መሪ ቃል 2ኛው የብልፅግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ቅድመ ጉባኤ ውይይት የተመዘገቡ ለውጦችን የሚያትት ሰነድ በወረዳው የብልፅግና ፓርቲ ምክትልና የፓለቲካ ዘርፍ ኃላፊ በአቶ ታገስ ታምሩ እና ፓርቲው "ጠንካራ ኢንስፔክሽን ለጠንካራ ፓርቲ"በሚል መርህ በወረዳው ኢንስፔክሽንና ሥነ ምግባር ኮሚሽን በኩል የተከናወኑ ዝርዝር ተግባራት አፈፃፀም በፓርቲው የኢንስፔክሽንና ስነ ምግባር ኮሚሽን ፅህፈት ቤት ኃላፊ በአቶ ሲሣይ ቤተ ማርያም አማካኝነት ቀርበው ለውይይት የበቁ ሲሆን በተሳትፎ ሂደቱም የተገኙ ስኬቶችን በመዘከር በሂደቱ የተስተዋሉ ክፍተቶችን ብሎም ልዩ ትኩረት በሚሹ የህዝብ የመልካም አስተዳደር መጠይቆችን በመመለስ ሁለንተናዊ ብልፅግናን የማረጋገጥ ተቋማዊ ህልም ማሳካት እንደሚገባ አመላክተዋል።

በመጨረሻም በወረዳው ኮሙኒኬሽን ፅህፈት ቤት በኩል የ2017 በጀት አመት የፓርቲና የመንግስት ተግባራት የአፈፃፀም ማሣያ ፎቶ አውደ ርዕይ ለእይታ ቀርቦ የተጎበኘ ሲሆን በተጨማሪም የኢንስፔክሽንና ስነ- ምግባር ኮሚሽኑ አመራሮችን እና ለውይይት የቀረቡ ሰነዶችን በማፅደቅ በተከታታይነት በክፍለ ከተማ ብሎም በከተማ ደረጃ በድምቀት በሚካሄደው 2ኛው የብልፅግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ የሚሳተፉ አመራሮችና አባላትን በመምረጥ ኮንፈረንሱ ተቋጭቷል።

ለሚ ኩራ ወረዳ 14 ኮሙኒኬሽን
ጥር 06-2017 ዓ.ም

➤ለበለጠ መረጃ ሊንኮቹን ይጠቀሙ
👇👇👇

➤ቲክ ቶክ https://vt.tiktok.com/ZS6QsHeTt/

➤ቴሌግራም
https://t.me/yekawereda14media

➤ፌስቡክ https://www.facebook.com/share/p/19hwsRMq4x/

➤ዩቲዩብ
https://youtu.be/UNqKupF3dlU?si=KVlP8d1E6xefiIjt

➤ቲውተር
https://x.com/ZuryashY?t=d4TDOTa2wR1N1bblIH8R8A&s=08

➤ኢንስታ ግራም
https://www.instagram.com/p/Cvhto_Xspod/?igsh=MjhnZ3h1N2xtZDhv

➤ትግረኛ ፌስቡክ ገጽ
https://www.facebook.com/share/p/19qmJf5DXf/

➤ኦሮምኛ ፌስቡክ ገጽ
https://www.facebook.com/share/p/1DEM6DQ1eN/

"ከቃል እስከ ባህል" በሚል መሪ ቃል ሰ የመሰረታዊ ድርጅት ቅድመ ጉባኤ በወረዳ ደረጃ የማጠቃለያ ውይይት እየተካሄደ ነው"በወረዳው ብልጽግና ፓርቲ  ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስተባባሪነት "ከቃ...
14/01/2025

"ከቃል እስከ ባህል" በሚል መሪ ቃል ሰ የመሰረታዊ ድርጅት ቅድመ ጉባኤ በወረዳ ደረጃ የማጠቃለያ ውይይት እየተካሄደ ነው"

በወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት አስተባባሪነት "ከቃል እስከ ባህል"በሚል መሪ ቃል 2ኛው የብልፅግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ቅድመ ጉባኤ ኮንፈረንስ የወረዳው ኮር አመራሮች እና በወረዳ ደረጃ እንዲሣተፉ የተለዩ የመሠረታዊ ፓርቲ አባላት በቅድመ ጉባኤው የወረዳ ተሳታፊዎች በማጠቃለያ ውይይቱ ተካፋይ መሆን ችለዋል።

"ከቃል እስከ ባህል"በሚል መሪ ቃል የተካሄደው 2ኛው የብልፅግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ቅድመ ጉባኤ ኮንፈረስ በለውጥ ሂደት የተገኙ ስኬቶችን ለማስቀጠል እናም የተስተዋሉ ክፍተቶችን በተቀናጀ መልኩ ለማረም ያለመ መሆኑም በኮንፈረንሱ ተገልጿል።

ለሚ ኩራ ወረዳ 14 ኮሙኒኬሽን
ጥር 06-2017 ዓ.ም

➤ለበለጠ መረጃ ሊንኮቹን ይጠቀሙ
👇👇👇

➤ቲክ ቶክ https://vt.tiktok.com/ZS6QsHeTt/

➤ቴሌግራም
https://t.me/yekawereda14media

➤ፌስቡክ https://www.facebook.com/share/p/19hwsRMq4x/

➤ዩቲዩብ
https://youtu.be/UNqKupF3dlU?si=KVlP8d1E6xefiIjt

➤ቲውተር
https://x.com/ZuryashY?t=d4TDOTa2wR1N1bblIH8R8A&s=08

➤ኢንስታ ግራም
https://www.instagram.com/p/Cvhto_Xspod/?igsh=MjhnZ3h1N2xtZDhv

➤ትግረኛ ፌስቡክ ገጽ
https://www.facebook.com/share/p/19qmJf5DXf/

➤ኦሮምኛ ፌስቡክ ገጽ
https://www.facebook.com/share/p/1DEM6DQ1eN/

"የተቀናጀ የልምድ ልውውጥ እና የተሞክሮ ማስፋት ተግባር በወረዳ 14"    በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር በወረዳው ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ፅህፈት ቤት አቀናጅነት...
13/01/2025

"የተቀናጀ የልምድ ልውውጥ እና የተሞክሮ ማስፋት ተግባር በወረዳ 14"

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር በወረዳው ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ፅህፈት ቤት አቀናጅነት የክፍለ ከተማው ዘርፍ ፅህፈት ቤት ቡድን መሪዎችና ባለሙያዎችን ጨምሮ ከአስሩም(10) ወረዳ የተውጣጡ ኃላፊዎችና ቡድን መሪዎች በወረዳው በተከናወኑ ተግባራት የልምድ ልውውጥ እና ተሞክሮ የማስፋት ተግባር በተቀናጀ መልኩ በዛሬው ዕለት ተካሂዷል።

በወረዳው በተካሄደው የልምድ ልውውጥ እና የተሞክሮ ማስፋት ተግባርም የወረዳው ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚና የስራና ክህሎት ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ረጅብ አክመልን ጨምሮ የወረዳው ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ታምራት ታደሰ፣የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ደረጄ ቀነአ እና ተሞክሮ የሚያጋሩ የተቋም ኃላፊዎችና ቡድን መሪዎች በተገኙበት የተካሄደ ሲሆን የተሞክሮ ልውውጥ ሂደቱም በወረዳው ከተቋማት ሪፎርም አኳያ የመጡ ለውጦችን እና በአንድ ማዕከል የአገልግሎት አሰጣጥ የተመዘገቡ ለውጦችን ተጨባጭነት በማረጋገጥ ለተሞክሮው ቅመራው አስቻይ ሁኔታን በሚፈጥር መልኩ ተከናውኗል።

ቅንጅት አዘሉ የልምድ ልውውጥ ቡድኑም ከተቋማት የሪፎርም ስራዎች እና ከአንድ ማዕከል የአገልግሎት አሰጣጥ ውጤታማነት አኳያ መድረክ ፈጥሮ መረጃን በማስረጃ ከመለዋወጥ ባሻገር አገልግሎት ሰጭ ተቋማት ለተገልጋዬች የሚሰጡትን ግልጋሎት በተጨባጭ የማረጋገጥ ስራም ማከናወን ችሏል።

በመጨረሻም የክፍለ ከተማ ዘርፍ ፅህፈት ቤት ቡድን መሪዎችን ጨምሮ ከአስሩም ወረዳ የተውጣጡ ኃላፊዎችና ቡድን መሪዎች በተሞክሮ ልውውጥ ሂደቱ ያስተዋላቸውን ጥንካሬዎች በማድነቅ ተጠናክረው ሊቀጥሉና ፈጥኖ ማስተካከል የሚሹ ተግባራትንም አመላክተዋል።

ለሚ ኩራ ወረዳ 14 ኮሙኒኬሽን
ጥር 05-2017 ዓ.ም

➤ለበለጠ መረጃ ሊንኮቹን ይጠቀሙ
👇👇👇

➤ቲክ ቶክ https://vt.tiktok.com/ZS6QsHeTt/

➤ቴሌግራም
https://t.me/yekawereda14media

➤ፌስቡክ https://www.facebook.com/share/p/19hwsRMq4x/

➤ዩቲዩብ
https://youtu.be/UNqKupF3dlU?si=KVlP8d1E6xefiIjt

➤ቲውተር
https://x.com/ZuryashY?t=d4TDOTa2wR1N1bblIH8R8A&s=08

➤ኢንስታ ግራም
https://www.instagram.com/p/Cvhto_Xspod/?igsh=MjhnZ3h1N2xtZDhv

➤ትግረኛ ፌስቡክ ገጽ
https://www.facebook.com/share/p/19qmJf5DXf/

➤ኦሮምኛ ፌስቡክ ገጽ
https://www.facebook.com/share/p/1DEM6DQ1eN/

"ከጥምቀት በዓል ሰላማዊ የበዓል ድባብ አሰቻይ ሁኔታዎች ዙሪያ ከሴት አደረጃጀቶች ጋር ውይይት ተካሄደ"   በዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር ሰላምና ጸጥታ ጽህፈት ...
13/01/2025

"ከጥምቀት በዓል ሰላማዊ የበዓል ድባብ አሰቻይ ሁኔታዎች ዙሪያ ከሴት አደረጃጀቶች ጋር ውይይት ተካሄደ"

በዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር ሰላምና ጸጥታ ጽህፈት ቤት አስተባባሪነት በወረዳው ከሚገኙ ሴት አደረጃጀቶች ጋር ከከተራ እና የጥምቀት በዓላት ሰላማዊ አከባበር ዙሪያ የውይይት መድረክ ተካሂዷል።

የውይይት መድረኩን የወረዳው ሰላምና ጸጥታ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሚሊዮን ቅናቱ እና የጸጥታእና መረጃ ቡድን መሪ ወይዘሮ አብዮት ተሾመ
የተመራ ሲሆን በውይይቱም በዓላቱን በሰላማዊ ድባብ ለማጠናቀቅ በሚያስችሉ የቅንጅት ተግባራት ዙሪያ ተግባባቦት መፍጠር ተችሏል።

የጥምቀት በዓል ከሀገር ከሃይማኖታዊ እሴቱ እና ፋይዳው ባሻገር አለማቀፋዊ ቅርስ በመሆኑ በልዩ ድምቀት የሚከበር ክብረ በዓል ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ፍፁም ሰላማዊ የበዓል ድባብ ለማሳለፍ ሴት አደረጃጀቶች ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት መሰራት እንደሚገባቸው በውይይት ተገልጿል።

ለሚ ኩራ ወረዳ 14 ኮሙኒኬሽን
ጥር 05-2017 ዓ.ም
➤ለበለጠ መረጃ ሊንኮቹን ይጠቀሙ
👇👇👇

➤ቲክ ቶክ https://vt.tiktok.com/ZS6QsHeTt/

➤ቴሌግራም
https://t.me/yekawereda14media

➤ፌስቡክ https://www.facebook.com/share/p/19hwsRMq4x/

➤ዩቲዩብ
https://youtu.be/UNqKupF3dlU?si=KVlP8d1E6xefiIjt

➤ቲውተር
https://x.com/ZuryashY?t=d4TDOTa2wR1N1bblIH8R8A&s=08

➤ኢንስታ ግራም
https://www.instagram.com/p/Cvhto_Xspod/?igsh=MjhnZ3h1N2xtZDhv

➤ትግረኛ ፌስቡክ ገጽ
https://www.facebook.com/share/p/19qmJf5DXf/

➤ኦሮምኛ ፌስቡክ ገጽ
https://www.facebook.com/share/p/1DEM6DQ1eN/

"የጥምቀት እና የከተራ በዓልን ሰላማዊ  አከባበር በተመለከተ ከወጣቶች ጋር መድረክ ተካሄደ"  በለሚ ኩራ  ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 ሰላምና ፀጥታ ጽህፈት ቤት  ከፊታችን በድምቀት የሚከበሩት ...
13/01/2025

"የጥምቀት እና የከተራ በዓልን ሰላማዊ አከባበር በተመለከተ ከወጣቶች ጋር መድረክ ተካሄደ"

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 ሰላምና ፀጥታ ጽህፈት ቤት ከፊታችን በድምቀት የሚከበሩት የከተራ እና የጥምቀት በዓላት ሀይማኖታዊ እሴታቸውን እና ባህላዊ ትውፊታቸውን በጠበቀ መልኩ ያለምንም የፀጥታ ችግር እንዲከበሩ የሚያስችል ውይይት በዛሬው ዕለት የጽህፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ሚሊዮን ቅናቱ እና የማህበረሰብ አቀፍ ፖሊስ ኃላፊ ኢንስፔክተር ታለጌታ ሰጤ በተገኙበት ተካሂደዋል።

በዓላቱ በሰላም ተከብረው እንዲጠናቀቁ በማስቻል ረገድም የወጣት አደረጃጀቶች ሚና የጎላ በመሆኑ ከባለድርሻ አካላት ጋር ከመረጃ ልውውጥ ጀምሮ የተቀናጀ ሰራ መስራት እንደሚጠበቅ በመድረኩ ተገልጿል።

የጥምቀት ዓላል አለማፋዊ ቅርስ በመሆኑም ሁሉም አካል በአንድ አይነት ስሜት በልዩ ድምቀት ሊከበር እንደሚገባም በመጠቆም በዓሉ ሃይማኖታዊ እሴቱን እና ባህላዊ ትውፊቱን ጠበቆ እንዲከበር ብሎም ያለምንም የፀጥታ ችግር ተከናውኖ እንዲጠናቀቅ ማድረግ እንደሚገባም በመድረኮቹ ተመላክቷል።

ለሚ ኩራ ወረዳ 14 ኮሙኒኬሽን
ጥር 05-2017ዓ.ም

➤ለበለጠ መረጃ ሊንኮቹን ይጠቀሙ
👇👇👇

➤ቲክ ቶክ https://vt.tiktok.com/ZS6QsHeTt/

➤ቴሌግራም
https://t.me/yekawereda14media

➤ፌስቡክ https://www.facebook.com/share/p/19hwsRMq4x/

➤ዩቲዩብ
https://youtu.be/UNqKupF3dlU?si=KVlP8d1E6xefiIjt

➤ቲውተር
https://x.com/ZuryashY?t=d4TDOTa2wR1N1bblIH8R8A&s=08

➤ኢንስታ ግራም
https://www.instagram.com/p/Cvhto_Xspod/?igsh=MjhnZ3h1N2xtZDhv

➤ትግረኛ ፌስቡክ ገጽ
https://www.facebook.com/share/p/19qmJf5DXf/

➤ኦሮምኛ ፌስቡክ ገጽ
https://www.facebook.com/share/p/1DEM6DQ1eN/

"ከቃል እስከ ባህል" የቅድመ ጉባኤ ውይይት ከቢሮ መሠረታዊ ፓርቲዎች ጋር እየተካሄደ ነው"  በዛሬ ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት አስተባባሪነት ...
13/01/2025

"ከቃል እስከ ባህል" የቅድመ ጉባኤ ውይይት ከቢሮ መሠረታዊ ፓርቲዎች ጋር እየተካሄደ ነው"

በዛሬ ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት አስተባባሪነት የብልፅግና ፓርቲ 2ኛው መደበኛ ጉባኤ የቅድመ ጉባኤ ኮንፍረስ "ቃል እስከ ባህል"በሚል መሪ ቃል የቢሮ መሰረታዊ ፓርቲ የጉባኤ ቅድመ ውይይት ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው።

ለሚ ኩራ ወረዳ 14 ኮሙኒኬሽን
ጥር 05-2017 ዓ.ም

➤ለበለጠ መረጃ ሊንኮቹን ይጠቀሙ
👇👇👇

➤ቲክ ቶክ https://vt.tiktok.com/ZS6QsHeTt/

➤ቴሌግራም
https://t.me/yekawereda14media

➤ፌስቡክ https://www.facebook.com/share/p/19hwsRMq4x/

➤ዩቲዩብ
https://youtu.be/UNqKupF3dlU?si=KVlP8d1E6xefiIjt

➤ቲውተር
https://x.com/ZuryashY?t=d4TDOTa2wR1N1bblIH8R8A&s=08

➤ኢንስታ ግራም
https://www.instagram.com/p/Cvhto_Xspod/?igsh=MjhnZ3h1N2xtZDhv

➤ትግረኛ ፌስቡክ ገጽ
https://www.facebook.com/share/p/19qmJf5DXf/

➤ኦሮምኛ ፌስቡክ ገጽ
https://www.facebook.com/share/p/1DEM6DQ1eN/

"በጎነት ለዘላቂ ማህበረሰባዊ ለውጥ"በዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር የሚገኙ የኢትዮጵያ  ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የየካ አባዶ በጎ አድራጎት ማህበር በቁ...
12/01/2025

"በጎነት ለዘላቂ ማህበረሰባዊ ለውጥ"

በዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር የሚገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የየካ አባዶ በጎ አድራጎት ማህበር በቁጥር 670 ለሚሆኑ ድጋፍ ለሚሹ የማህበረሰብ ክፍሎች ማዕድ የማጋራት እናም የአልባሳት ድጋፍ በተቀናጀ መልኩ ተበርክቷል።

በወረዳው ደረጃ በተበረከተው የማዕድ ማጋራት የበጎ አድራጎት መርሃ ግብሩም በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሃገረ ስብከት ሊቃነ ጳጳስ አቡነ ሄኖክን ጨምሮ የቤተ ክርስቲያኗ ሊውቃውንት፣በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ብርሀኑ ገ/ጊዮርጊስ፣የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የሴቶች ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ሙሉእመቤት ስራህብዙ እና የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ብርሃኑ ትርፌ በተገኙበት በልዩ ድምቀት ተከናውኗል።

በኘሮግራሙም በቁጥር 670 ለሚሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎች የምሳ ግብዣን ጨምሮ"በጎነት ለማህበረሰባዊ ለውጥ" ያለውን ሚና በሚያጎላ እናም በሚያስተጋባ መልኩ የማዕድ ማጋራትና የአልባሣት ልዩ አበርክቶ የሃይማኖት ተቋማት ከተቋቋሙበት ቀጥተኛ ተልዕኮ ባሻገር በሰው ተኮር ተግባራትም ጭምር እያበረከቱ ያሉትን አርአያነት ያለው መልካም ተግባር ይበልጥ አጠናክሮ ማስቀጠል በሚያስችል መልኩ ተካሂዷል።


ለሚ ኩራ ወረዳ 14 ኮሙኒኬሽን
ጥር 04-2017 ዓ.ም

➤ለበለጠ መረጃ ሊንኮቹን ይጠቀሙ
👇👇👇

➤ቲክ ቶክ https://vt.tiktok.com/ZS6QsHeTt/

➤ቴሌግራም
https://t.me/yekawereda14media

➤ፌስቡክ https://www.facebook.com/share/p/19hwsRMq4x/

➤ዩቲዩብ
https://youtu.be/UNqKupF3dlU?si=KVlP8d1E6xefiIjt

➤ቲውተር
https://x.com/ZuryashY?t=d4TDOTa2wR1N1bblIH8R8A&s=08

➤ኢንስታ ግራም
https://www.instagram.com/p/Cvhto_Xspod/?igsh=MjhnZ3h1N2xtZDhv

➤ትግረኛ ፌስቡክ ገጽ
https://www.facebook.com/share/p/19qmJf5DXf/

➤ኦሮምኛ ፌስቡክ ገጽ
https://www.facebook.com/share/p/1DEM6DQ1eN/

"ከቃል እስከ ባህል" በሚል መሪ ቃል የመሰረታዊ ድርጅት ቅድመ ጉባኤ ተጠናክሮ ቀጥሏል"በዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ  ወረዳ 14 ብልጽግና ፓርቲ  ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት "ከቃል እስከ...
12/01/2025

"ከቃል እስከ ባህል" በሚል መሪ ቃል የመሰረታዊ ድርጅት ቅድመ ጉባኤ ተጠናክሮ ቀጥሏል"

በዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት "ከቃል እስከ ባህል"በሚል መሪ ቃል 2ኛው የብልፅግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ቅድመ ጉባኤ ኮንፈረንስ የወረዳው ኮር አመራሮች በተገኙበት በመሠረታዊ ድርጅት መሪነት የተከናወነው የቅድመ ጉባኤ በልዩ ድምቀት በመካሄድ ላይ ነው።

"ከቃል እስከ ባህል"በሚል መሪ ቃል የተካሄደው 2ኛው የብልፅግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ቅድመ ጉባኤ ኮንፈረስ በለውጥ ሂደት የተገኙ ስኬቶችን ለማስቀጠል እናም የተስተዋሉ ክፍተቶችን በተቀናጀ መልኩ ለማረም ያለመ መሆኑ በኮንፈረሱ ተገልጿል።

የቅድመ ጉባኤ ኮንፈረሱ በሁሉም ማህበራዊ መሠረቶች የተካሄደ ሲሆን በመድረኮቹም የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ብርሀኑ ትርፌ እና የወረዳው የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ጌቴ ቢሰጠኝ ተገኝተው መልዕክት አስተላልፈዋል።

ለሚ ኩራ ወረዳ 14 ኮሙኒኬሽን
ጥር 04-2017 ዓ.ም

➤ለበለጠ መረጃ ሊንኮቹን ይጠቀሙ
👇👇👇

➤ቲክ ቶክ https://vt.tiktok.com/ZS6QsHeTt/

➤ቴሌግራም
https://t.me/yekawereda14media

➤ፌስቡክ https://www.facebook.com/share/p/19hwsRMq4x/

➤ዩቲዩብ
https://youtu.be/UNqKupF3dlU?si=KVlP8d1E6xefiIjt

➤ቲውተር
https://x.com/ZuryashY?t=d4TDOTa2wR1N1bblIH8R8A&s=08

➤ኢንስታ ግራም
https://www.instagram.com/p/Cvhto_Xspod/?igsh=MjhnZ3h1N2xtZDhv

➤ትግረኛ ፌስቡክ ገጽ
https://www.facebook.com/share/p/19qmJf5DXf/

➤ኦሮምኛ ፌስቡክ ገጽ
https://www.facebook.com/share/p/1DEM6DQ1eN/

  በሚል መሪ ቃል መሰረታዊ ድርጅት ቅድመ ጉባኤ ኮንፈረንስ መካሄድ ጀመረ።በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ  ወረዳ 14 ብልጽግና ፓርቲ  ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት 'ከቃል እስከ ባህል!' በሚል መሪ ሀሳብ...
12/01/2025

በሚል መሪ ቃል መሰረታዊ ድርጅት ቅድመ ጉባኤ ኮንፈረንስ መካሄድ ጀመረ።

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት 'ከቃል እስከ ባህል!' በሚል መሪ ሀሳብ 2ኛው የብልፅግና ፓርቲ አጠቃላይ መደበኛ ጉባኤ ቅድመ ጉባኤ ኮንፈረንስ መሰረታዊ ድርጅት የወረዳው ኮር አመራሮች በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ መካሄድ ላይ ነው።

➤ለበለጠ መረጃ ሊንኮቹን ይጠቀሙ
👇👇👇

➤ቲክ ቶክ https://vt.tiktok.com/ZS6QsHeTt/

➤ቴሌግራም
https://t.me/yekawereda14media

➤ፌስቡክ https://www.facebook.com/share/p/19hwsRMq4x/

➤ዩቲዩብ
https://youtu.be/UNqKupF3dlU?si=KVlP8d1E6xefiIjt

➤ቲውተር
https://x.com/ZuryashY?t=d4TDOTa2wR1N1bblIH8R8A&s=08

➤ኢንስታ ግራም
https://www.instagram.com/p/Cvhto_Xspod/?igsh=MjhnZ3h1N2xtZDhv

➤ትግረኛ ፌስቡክ ገጽ
https://www.facebook.com/share/p/19qmJf5DXf/

➤ኦሮምኛ ፌስቡክ ገጽ
https://www.facebook.com/share/p/1DEM6DQ1eN/

"ከቃል እስከ ባህል"በሚል መሪ የተካሄደው ሁለተኛው የብልፅግና ፓርቲ  መደበኛ ጉባኤ  ቅድመ ጉባኤ የውይይት መድረክ ተጠናቀቀ"በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር "ከቃል እስከ ባህ...
10/01/2025

"ከቃል እስከ ባህል"በሚል መሪ የተካሄደው ሁለተኛው የብልፅግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ቅድመ ጉባኤ የውይይት መድረክ ተጠናቀቀ"

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር "ከቃል እስከ ባህል " በሚል መሪ ቃል ለተከታታይ ሶስት ቀናት ሲካሄድ የቆየውን የሁለተኛው የብልፅግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ቅድመ ጉባኤ ውይይት የወረዳው ጠቅላላ አመራር በተገኙበት በዛሬው ዕለት ተካሂዷል።

በመድረኩም በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የመልካም አስተዳደር ቅሬታና አቤቱታ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ እዮብ እሸቱን ጨምሮ የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ብርሃኑ ትርፌ እና የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌቴ ቢሠጠኝ በተገኙበት የተካሄደ ሲሆን በውይይቱም በከተማና በክፍለ ከተማ ደረጃ ለሁለት ተከታታይ ቀናት የተካሄደውን የቅድመ ጉባኤ የውይይት መድረክ መነሻ ሰነድ እና የወረዳውን ነባራዊ ሀቆች አፈፃፀም የሚያሳይ መረጃ ቀርቦ ለውይይት በቅቷል።

በዕለቱ በወረዳ ደረጃ በተካሄደው የውይይት መድረክም በ2017 በጀት አመት በፓርቲ እና የመንግስት ተቋማት የተከናወኑ ዝርዝር ተግባራት የአፈፃፀም ልክ የቀረበ ሲሆን በዋናነትም በሂደቱ የተስተዋሉ ክፍተቶችን በሚደፍን እና ጥንካሬዎችን ይበልጥ አጠናክሮ በሚያስቀጥሉ ብሎም ልዩ ትኩረት በሚሰጣቸው የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎች ዙሪያ የጋራ ተግባቦት ፈጥሮ መውጣት ተችሏል።

በመጨረሻም በአፈፃፀም ሪፓርቶችን መነሻነት የጠቅላላ አመራር ሂስ ግለሂስ የምዘና አግባብ በወረዳ ደረጃ ተከናውኖ ሁለተኛው የብልፅግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ የቅድመ ዝግጅት የውይይት መድረኩ ተቋጭቷል።

ለሚ ኩራ ወረዳ 14 ኮሙኒኬሽን
ጥር 02-2017 ዓ.ም

➤ለበለጠ መረጃ ሊንኮቹን ይጠቀሙ
👇👇👇

➤ቲክ ቶክ https://vt.tiktok.com/ZS6QsHeTt/

➤ቴሌግራም
https://t.me/yekawereda14media

➤ፌስቡክ https://www.facebook.com/share/p/19hwsRMq4x/

➤ዩቲዩብ
https://youtu.be/UNqKupF3dlU?si=KVlP8d1E6xefiIjt

➤ቲውተር
https://x.com/ZuryashY?t=d4TDOTa2wR1N1bblIH8R8A&s=08

➤ኢንስታ ግራም
https://www.instagram.com/p/Cvhto_Xspod/?igsh=MjhnZ3h1N2xtZDhv

➤ትግረኛ ፌስቡክ ገጽ
https://www.facebook.com/share/p/19qmJf5DXf/

➤ኦሮምኛ ፌስቡክ ገጽ
https://www.facebook.com/share/p/1DEM6DQ1eN/

ከቃል እስከ ባህል" በሚል መሪ ቃል ሲካሄድ የቆየው ሁለተኛው የብልፅግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ቅድመ ጉባኤ ውይይት መጠናቀቁ ተገለፀ።የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ  የክፍለ ከተማ እና የወረዳ የብልፅ...
09/01/2025

ከቃል እስከ ባህል" በሚል መሪ ቃል ሲካሄድ የቆየው ሁለተኛው የብልፅግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ቅድመ ጉባኤ ውይይት መጠናቀቁ ተገለፀ።

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የክፍለ ከተማ እና የወረዳ የብልፅግና ፓርቲ አመራሮች የተሳተፉበት '' ከቃል እስከ ባህል " በሚል መሪ ቃል ለተከታታይ ሁለት ቀናት ሲያካሂዱት የቆየውን የሁለተኛው የብልፅግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ቅድመ ጉባኤ ውይይት ማጠቃለላቸው ተገለፀ።

በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ የተገኙት የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አድማሱ ደቻሳ ፓርቲያችን ብልፅግና ኢትዮጵያን በሚመጥን ከፍታ ለማስቀመጥ በማህበራዊ ፣ በኢኮኖሚያዊ ፣ በፓለቲካዊ እና በዉጭ ጉዳይና በሌሎችም ጉዳዮች ከፍተኛ ስራን ሰርቷል። በዚህም አስደማሚ ውጤት አስመዝግቧል። ይህንን ውጤት ለማስቀጠል ሁሉም አመራር ባለበት የስራ መደብ በጠራ መረጃ ቀጣይነት ያለው ውጤት ማስመዝገብ ፤ በጎ ተግባር በመስራት የብልፅግናን መልካም ስሙ መትከል፤የሰው ተኮር ስራን በእምነት መያዝ በጠንካራ በፓርቲ እሳቤ የሚሰሩ ውጤታማ ስራዎች በማጎልበት በሀሳብም በተግባርም የብልፅግና ፓርቲ አመራር መሆን እንደሚያስፈልግ አፅንኦት በመስጠት የቀጣይ አቅጣጫም አስቀምጠዋል።

ባሳለፍነው አምስት የለውጥ አመታት በርካታ ለመስራት አይቻልም የሚባሉና ይከብዳሉ ተብለው የሚታሰቡትን ተግባራትን በድፍረት ጀምሮ በጥራት ሰርቶ በውጤት የተመዘገቡ ሀገራችንን በአለም አደባባይ እውቅና እንድታገኝ ያደረገው ፓርቲያችን በተሰጠው የጊዜ ገደብ ለህዝብ የገባውን ቃል በተግባር አሳይቷል። በዚህም ሀገር ከፓርቲ በላይ በመሆኗ ከሀሳብ ልዕልና ተነስቶ የበለፀገች ሀገር ወደ መገንባት በከፍተኛ ቁርጠኝነት ከችግር በላይ አርቆ በማሰብ አልቆ የሰራ ፓርቲው የጠራ ግንዛቤ በመያዙ ነው። የዚህ ፓርቲ አባላት በሙሉ ከሰራነው ስራ የሚቀረው ይበረታልና ልንተጋ ይገባል ሲሉ ገልፀዋል።

የክፍለ ከተማው ምክትል ስራ አስፈፃሚ እና ስራና ክህሎት ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ልመንህ ምህረቱ በበኩላቸው
ፓርቲያችን ብልፅግና በአምስት አመት ጉዞው በርካታ ስኬቶችን ያስመዘገበ እና ሀገራችንን ከውድቀት የታደገ ብሎም በአለም አደባባይ መብቷን በሰራው ስራ እውቅና የተቸረ ፓርቲ ነው። በዚህ ፓርቲ ያለን አመራሮች በቀጣይ ፓርቲያችን በመስራትና ውጤት በማስመዝገብ የማይታማ ነውና ይህንን በሙሉ አቅም ተግቶ በመስራት ከህገ ወጥነት ተግባር ራስን በማራቅና በተቀላጠፈ አገልግሎት ለህዝቡ በመስጠት መትጋት ያስፈልጋል ብለዋል።

ለሚ ኩራ ኮሚኒኬሽን
01/05/2017 ዓ.ም

ከቃል እስከ ባህል!! በለሚ ኩራ ክፍለ  ከተማ ብልፅግና  ፓርቲ ቅርንጫፍ  የክፍለ  ከተማና ወረዳ አመራሮች  "ከቃል እስከ ባህል" በሚል መልዕክት  እየተካሄደ  ያለው  2ኛው የብልፅግና  ...
09/01/2025

ከቃል እስከ ባህል!!

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ የክፍለ ከተማና ወረዳ አመራሮች "ከቃል እስከ ባህል" በሚል መልዕክት እየተካሄደ ያለው 2ኛው የብልፅግና ፓርቲ አጠቃላይ መደበኛ ጉባኤ ቅድመ ጉባኤ ውይይት የ2ኛ ቀን በቡድን ውይይት ተጠናክሮ እንደቀጠለ ይገኛል።

መድረኩ ላይ በተመዘገቡ ስኬቶችና ፓርቲውን የበለጠ የሚያጠናክሩ ሀሳቦችን በማንሳት በሁሉም ቡድኖች ጠንካራ ውይይት እየተደረገ መሆኑ ተገልጿል ።

ለሚ ኩራ ኮሙኒኬሽን
ጥር 01/2017 ዓ.ም

ከቃል እስከ ባህል በሚል መሪ ቃል የሚደረገው 2ኛው የብልፅግና  ፓርቲ   መደበኛ ጉባኤ ቅድመ  ውይይት  በለሚ ኩራ ክፍለ  ከተማ የክፍለ  ከተማ እና ወረዳ አጠቃላይ  አመራሮች  በተገኙበት...
08/01/2025

ከቃል እስከ ባህል በሚል መሪ ቃል የሚደረገው 2ኛው የብልፅግና ፓርቲ መደበኛ ጉባኤ ቅድመ ውይይት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የክፍለ ከተማ እና ወረዳ አጠቃላይ አመራሮች በተገኙበት ውይይት ተጀምሯል ።

ለሚ ኩራ ኮሙኒኬሽን
ታህሳስ 30/2017 ዓ.ም

"የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ከወረዳው ፓርቲ ፅህፈት ቤት ሃላፊ"    ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዬች እንኳን ለጌታችን ለመድሃኒታችን ለእየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳች...
06/01/2025

"የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት ከወረዳው ፓርቲ ፅህፈት ቤት ሃላፊ"

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዬች እንኳን ለጌታችን ለመድሃኒታችን ለእየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ሲሉ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የወረዳ 14 ፓርቲ ፅህፈት ቤት ሃላፊ አቶ ጌቴ ቢሠጠኝ የእንኳን አደረሳችሁ የመልካም ምኞት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

የወረዳው ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ሃላፊው በእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸው በዓሉ በክርስትና እምነት ተከታዬች ዘንድ በልዩ ድምቀት የሚከበር በዓል በመሆኑን በዓሉን ሲናከብርም አንዱ ለሌላው ያለው ለሌለው በማካፈል ሊሆን እንደሚገባ አሳስበዋል።

በመጨረሻም በዓሉ በኢትዮጵያውያን ፍፁም የአብሮነት መንፈስ ታጅቦ በሀይማኖታዊ አስተምህሮ ፀንቶ እንደሚከናወን በማመን ሁለንተናዊ መስተጋብርን ፈጥሮ የሚያልፍ እንዲሆን በመመኘት ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለጌታችን ለመድሃኒታችን ለእየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል በሰላም አደረሳችሁ ሲሉ የመልካም ምኞት መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

መልካም የልደት በዓል!!
አቶ ጌቴ ቢሠጠኝ

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የወረዳ 14 ፓርቲ ፅህፈት ቤት ሃለፊ

ለሚ ኩራ ወረዳ 14 ኮሙኒኬሽን
ታህሳስ 28-2017 ዓ.ም

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Lemi Kura Wereda 14 Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Videos

Share