Lemi Kura Wereda 14 Communication

Lemi Kura Wereda 14 Communication ይህ የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት ገጽ ነው

መልክ-አዲስ፥ ተምሳሌተ አዲስ ትውልድ፣ የብልፅግና መንገድ፤ ከለዉጡ ማግስት ጀምሮ፥ የስኽበት ማዕከል በሆነችዉ አዲስ አበባ፣ በፍጥነትና በጥራት ከተጠናቀቁ መሰረተ-ልማቶች መካከል፥ ወጣቱን በ...
14/11/2025

መልክ-አዲስ፥ ተምሳሌተ አዲስ ትውልድ፣ የብልፅግና መንገድ፤

ከለዉጡ ማግስት ጀምሮ፥ የስኽበት ማዕከል በሆነችዉ አዲስ አበባ፣ በፍጥነትና በጥራት ከተጠናቀቁ መሰረተ-ልማቶች መካከል፥ ወጣቱን በአዕምሮ፤በአካል እና በስነ-ልቦና የሚገነቡ፤ የከተማዋን ገፅታ የሚቀይሩ፤ በዓለም ተወዳዳሪነትን የሚያጎናፅፉ እና የትዉልዱን መፃኢ ዕድል የሚያመላክቱ፣ ዘመን ተሻጋሪ ዘመናዊ የስፖርት ማዘዉተሪያዎችና መዝናኛዎች በጥራት ገንብታ እንኾ ብላለች። እንዲሁም፤ ለኪነጥበቡ ዕድገት፣ ለተተኪ ከያኒ ምቾት፣ አንፊዎች እና በዓይነታቸው ልዩ የሆኑ ሲኒማ ቤቶች፣ ቴአትር ቤቶች እነኆ ብላለች። ቃል ወደ ተግባር የመቀየር ባህል በውል የታየባቸው የመንግስት እና የህዝብ ድምር ዉጤቶች ናቸዉ፡፡

ኑ! ተጠቀሙባቸው።

"በወረዳው የክረምት በጎ ፍቃድ መዝጊያና የበጋ በጎ አድራጎት ማስጀመሪያ ኘሮግራም ተካሄደ"በዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር በወረዳው ህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ አድራ...
14/11/2025

"በወረዳው የክረምት በጎ ፍቃድ መዝጊያና የበጋ በጎ አድራጎት ማስጀመሪያ ኘሮግራም ተካሄደ"

በዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር በወረዳው ህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ አድራጎት ፅህፈት ቤት አስተባባሪነት"የክረምት በጎ ፍቃድ መዝጊያና የበጋ በጎ አድራጎት ማስጀመሪያ ኘሮግራም ተካሂዷል።

የክረምቱ የበጎ ፍቃድ መዝጊያና የበጋ በጎ አድራጎት ማስጀመሪያ ኘሮግራሙም የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ምክትልና የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ታገስ ታምሩ እና የወረዳው ህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሚዛን ኪዳኔ በተገኙበት የተካሄደ ሲሆን በመድረኩም የ2017 በጀት አመት የክረምት በጎ አድራጎት የአፈፃፀም ልክ እና የ2018 የዕቅድ ክንውን ሂደት በሰነድ ማሳያነት ቀርቦ ለውይይት በቅቷል።

በጎነት ለዘላቂ የማህበረሰብ ለውጥ በሚል መርህ በክረምቱ መርሃ ግብር በስኬታማነት ተግባራትን በተቀናጀ መልኩ ማሳካት መቻሉን የገለፁት የወረዳው ህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሚዛን ኪዳኔ በተግባር ስምሪት ሂደት የተመዘገቡ ስኬቶችን አጉልቶ ማስቀጠል ብሎም የተስተዋሉ ክፍተቶችን ማረም እንደሚጠበቅ አስገንዝበዋል።

በመጨሻም በክረምቱ የበጎ ፍቃድ አድራጎት መርሃ ግብር በጎ አስተዋፅኦ ላበረከቱ ግለሰቦች እና ተቋማት የእውቅና ሰርተፍኬት በማበርከት የክረምት በጎ ፍቃድ መዝጊያና የበጋ በጎ ስራዎች ማስጀመሪያ መድረኩ ተቋጭቷል።

ለሚ ኩራ ወረዳ 14 ኮሙኒኬሽን
ህዳር 05-2018 ዓ.ም

"የተቀናጀ ስራ የተሳለጠ አገልግሎት" በዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር"የተቀናጀ ስራ የተሳለጠ አገልግሎት"በሚል የአገልጋይነት መርህ የባለጉዳይ ቀናት ለታለመላቸው ...
14/11/2025

"የተቀናጀ ስራ የተሳለጠ አገልግሎት"

በዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር"የተቀናጀ ስራ የተሳለጠ አገልግሎት"በሚል የአገልጋይነት መርህ የባለጉዳይ ቀናት ለታለመላቸው የአገልግሎት ልክ አየዋሉ ስለመሆናቸው ተገለፀ።

ዕለቱ "የተቀናጀ ስራ የተሳለጠ አገልግሎት" በሚል መርህ በተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎት እና በአገልግሎት ሰጭ ተቋማት አማካኝነት የሰላ የአገልግሎት አሰጣጥ ለተገልጋዬች እየተሰጠ ስለመሆኑም ከተገልጋዬች አንደበት ማድመጥ ተችሏል።

ባለጉዳዬች በአገልግሎት መስጫ የተሳለጠ አገልግሎት እንዲያገኙ ብሎም የባለጉዳይ ቀነት ለታለመላቸው የህዝብ ግልጋሎት መሰጫነት ብቻ እንዲውሉ የማድረግ ተግባሩም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት ተገልጿል።

ለሚ ኩራ ወረዳ 14 ኮሙኒኬሽን
ህዳር 05- 2018ዓ.ም

"በመልካም አስተዳደር  ፅንሰ ሃሳብ ዙሪያ የሚያትት የአቅም ግንባታ ስልጠና ለባለድርሻ አካላት ተሰጠ"በዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር በወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ ...
13/11/2025

"በመልካም አስተዳደር ፅንሰ ሃሳብ ዙሪያ የሚያትት የአቅም ግንባታ ስልጠና ለባለድርሻ አካላት ተሰጠ"

በዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር በወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ ፅህፈት ቤት አዘጋጅነት በመልካም አስተዳደር ፅንሰ ሃሳብ ዙሪያ የሚያትት የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጥቷል።

የአቅም ግንተባታ ስልጠናውም የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አለሙ ጨመዳ እና የወረዳው ምክትል ስራ አስፈፃሚ እና የስራና ክህሎት ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ረጅብ አክመል እንዲሁም የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ደረጄ ቀነዓ በተገኙበት የተካሄደ ሲሆን በስልጠና መድረኩም የወረዳው ጠቅላላ አመራርን ጨምሮ የብሎክ ኮሚቴዎች፣የእድር ኮሚቴዎች እናም የዘርፉ ባለድርሻ አካላት በተገኙበት ተካሂዷል።

የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አለሙ ጨመዳ ባስተላለፉት ግንዛቤ አዘል መልዕክትም ስልጠናው ለባለድርሻ አካላት ተደማሪ አቅምን ፈጥሮ ማለፍ የሚያስችል መሆኑን በመጠቆም የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በተቀናጀ መልኩ ለመፍታትም የችግር ምንጮችን ብሎክን መነሻ በማድረግ ደረጃ በደረጃ በመለየት ለተለዩ ችግሮቹ የመፍትሔ ሰጭነት አቅምን እያዳበሩ መሄድ ይጠይቃል ብለዋል።

በመልካም አስተዳደር ፅንሰ ሃሳብ ዙሪያ የሚያትት የስልጠና ሰነድ በማቅረብ ስልጠናውን የሰጡት የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የመልካም አስተዳደር እና የቅሬታና አቤቱታ ፅህፈት ቤት የመልካም አስተዳደር ዘርፍ ቡድን አስተባባሪ የሆኑት አቶ ናፍ ጋዲሳ እንደገለፁትም የመልካም አስተዳደር ምንነትን የተረዳ የህብረተሰብ ክፍል በመፍጠር ችግሮችን ከምንጫቸው ለማድረቅ የባለድርሻ አካላትን ተናባቢነትና ልዩ ቅንጅት እንደሚጠይቅ አስገንዝበዋል።

የስልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው ስልጠናው እጅግ በጣም አስፈላጊ መሆኑን በመጠቆም ደረጃ በደረጃ የሚለዩ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ከማሳየት ባሻገር በራስ አቅም መፍትሔ በማበጀት በርካታ ስራዎችን እንደሚያከናውኑ በመተማመን ልዩ ቅንጅት የሚጠይቁት የመልካም አስተዳደር መጠይቆችም ልዩ ትኩረት በመስጠት እልባት መስጠት እንደሚገባ ጠቁመዋል።

ለሚ ኩራ ወረዳ 14 ኮሙኒኬሽን
ህዳር 04-2018 ዓ.ም

ሠላም የሚረጋገጠው በህዝብ ተሳትፎ መሆኑ በአንድ ማዕከል የሮንድ ስምሪት ወቅት ተገለፀበለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የሠላምና ፀጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ከአጎራባች የሸገር ከተማ ክፍለ ከተማ ጥምር ሀ...
12/11/2025

ሠላም የሚረጋገጠው በህዝብ ተሳትፎ መሆኑ በአንድ ማዕከል የሮንድ ስምሪት ወቅት ተገለፀ

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የሠላምና ፀጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ከአጎራባች የሸገር ከተማ ክፍለ ከተማ ጥምር ሀይል በጋራ በመቀናጀት የአንድ ማዕከል የሮንድ ስምሪት አካሄዷል።

ስምሪቱ በሸገር ከተማ አጎራባች ከሆኑ ወረዳ 2፣ወረዳ 13 እና ወረዳ 14 ሲደረግ የሠላምና ፀጥታ የአካባቢ ቅኝት ደግሞ በወረዳ 3 እና ወረዳ 9 መካሄዱ ተገልጿል።

በስፍራው በመገኘት ስምሪት የሠጡት የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የሠላምና ፀጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አየለ ተስፋዬ እንደተናገሩት ሠላም የሚረጋገጠው በህዝብ ተሳትፎ ነው ስለዚህ ከመቼውም ጊዜ በላይ በተባበረ ክንድ በጋራ በመሆን አካባቢያችንን በመጠበቅ ብሎም እንደ ሀገርና ከተማ ማንኛውንም የፀጥታ ደጀን ሆነን ሠላምን የማስከበር ስራ መስራት ይኖርብናል ብለዋል።

በተለይም ደግሞ በመኖሪያ አካባቢዎች የሚፈጠሩ ወንጀሎችንም ለመቀነስ በየብሎኩ የተጀመረው የመንገድ መብራት የማብራት ተግባር ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።

የለሚ ኩራ ኮሙኒኬሽን
ህዳር 3/2018 ዓ.ም

"በወረዳው የ2018 በጀት አመት የስፖርት ምክር ቤት ጠቅላላ ጉባኤ ተካሄደ"በዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር በወረዳው ወጣቶችና ስፖርት ፅህፈት ቤት አስተባባሪነት ...
12/11/2025

"በወረዳው የ2018 በጀት አመት የስፖርት ምክር ቤት ጠቅላላ ጉባኤ ተካሄደ"

በዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር በወረዳው ወጣቶችና ስፖርት ፅህፈት ቤት አስተባባሪነት የ2018 በጀት አመት የስፖርት ምክር ቤት ጠቅላላ ጉባኤ ተካሂዷል።

በጠቅላላ ጉባኤውም የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ እና የስፖርት ምክር ቤቱ ሰብሳቢ አቶ አለሙ ጨመዳ እና የወረዳው ወጣቶችና ስፖርት ፅህፈት ቤት ኃላፊና የስፖርት ምክር ቤቱ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ለማ አብዲሳን ጨምሮ የስፖርት ምክር ቤቱ አባላትና የዘርፉ አሰልጣኞች ባለሙያዎች በተገኙበት የተካሄደ ሲሆን በመድረኩም የ2017 በጀት አመት የዕቅድ ክንውን ሪፖርት እና የ2018 የስፖርት ምክር ቤት ዕቅድ ቀርቦ ለውይይት በቅቷል።

ስፖርት ምክር ቤቱን በሙሉ አቅም ማጠናከር ተቀዳሚ የሌለው ተግባር መሆኑን የገለፁት የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አለሙ ጨመዳ ዘርፉን ለዘላቂ የአብሮነት ምንጭና ለትውልድ ግንባታ ሂደት ሁነኛ አማራጭ አድርጎ መውሰድ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።
በዘርፉ ለሚነሱ ሁለንተናዊ ምላሽ የሚሹ መጠይቆች ፈጣን ምላሽ መስጠት እንደሚገባ የገለፁት የወረዳው ወጣቶችና ስፖርት ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ለማ አብዲሳ በበኩላቸው የምክር ቤቱ አባላት ለዕቅድ አተገባበሩ የተቀናጀ እናም ውጤት የተግባር ስምሪት ሊኖራቸው እንደሚገባ ጠቁመዋል።


ለሚ ኩራ ወረዳ 14 ኮሙኒኬሽን
ህዳር 03-2018 ዓ.ም

"ከዛሬ የተሻረው የነገ ፍሬዎች የህፃናት ማቆያ ግብረ ሰናይ ድርጅት ድጋፍ"በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር  የነገ ፍሬዎች የህፃናት ማቆያ ግብረ ሰናይ ድርጅት ልዩ ድጋፍ ለሚሹ ...
12/11/2025

"ከዛሬ የተሻረው የነገ ፍሬዎች የህፃናት ማቆያ ግብረ ሰናይ ድርጅት ድጋፍ"

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር የነገ ፍሬዎች የህፃናት ማቆያ ግብረ ሰናይ ድርጅት ልዩ ድጋፍ ለሚሹ እናቶች እና ህፃናት ለተከታታይ (6)ወራት እፎይታን ማረጋገጥ የሚያስችል የግብአት ድጋፍ ተደረገ።

ግብረ ሰናይ ድርጅቱ ልዩ ድጋፍ ለሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎች በተሰጠው የስጦታ ኘሮግራሙም በየደረጃው ያሉ የድርጅቱ ኃላፊዎችን ጨምሮ የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አለሙ ጨመዳ እና የወረዳው ሴቶች ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አይዛቤል ሃ/ሚካኤል በተገኙበት የተካሄደ በድጋፍ አግባቡም ለርካታ የህብረተሰብ ክፍሎች የአብሮነት ማዕድ ማጋራት ተችሏል።

ግብረ ሰናይ ድርጅቱ ልዩ ድጋፍ ለሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎች ያበረከተው አስተዋፅኦ በእጅጉ የሚደነቅ መሆኑን የገለፁት የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አለሙ ጨመዳ መሰል የድጋፍ አግባቦች ተጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባ ገልፀዋል።

ድርጅቱ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የልማትና ክርስቲያናዊ ተራድኦ ኮሚሽን የስደተኞችና ከስደት ተመላሾች ጉዳይ መምሪያ የተቋቋመ ሲሆን በልዩ ትኩረት ሰጭነትም የነገ ፍሬዎች የህፃናት ማቆያ ግብረ ሰናይ ድርጅት ሙያ ለሚሹ እናቶችና ልዩ ድጋፍ ለሚሹ ህፃናት የአለኝታ ምንጭ መሆኝ የቻለ ድርጅት ነው።

ለሚ ኩራ ወረዳ 14 ኮሙኒኬሽን
ህዳር 03-2018 ዓ.ም

"አገልግሎት ሰጭ ተቋማት የመፍትሔ ምንጮች ናቸው"በዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር የአገልግሎት አሰጣጥ ቅኝቱም የወረዳው ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃይል ልማት ፅህፈት...
12/11/2025

"አገልግሎት ሰጭ ተቋማት የመፍትሔ ምንጮች ናቸው"

በዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር የአገልግሎት አሰጣጥ ቅኝቱም የወረዳው ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሃይል ልማት ፅህፈት ቤት ከወረዳው ኮሙኒኬሽን ፅህፈት ቤት ጋር በመቀናጀት"አገልግሎት ሰጭ ተቋማት የመፍትሔ ምንጮች ናቸው"ሚል መሪ ቃል በአገልግሎት መስጫ ቀናት የተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ጨምሮ በሁሉም ተቋማት የሰላ አገልግሎት እየተሰጠ ስለመሆኑ በምልከታ ማረጋገጥ ተችሏል።

"አገልግሎት ሰጭ ተቋማት የመፍትሔ ምንጮች ናቸው"በሚህ መርህ በዕለቱ በተካሄደው የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደቱም በአገልግሎት ሰጭ ተቋማት በመገኘት የአገልግሎት ቅኝት የተደረገ ሲሆኝ "ህዝብን ማገልገል ክብር ነው"ግልጋሎቱም በፍትሃዊነት እየተሰጠ መሆኑ ተገልጿል።

ባለጉዳይ ቀናት ለታለመላቸው የህዝብ ቀና አገልግሎት መስጫነታቸው በተቋማት በኩል መተግበራቸውን ለማረጋገጥ ያለመው የቅኝት ሂደት በሁሉም ተቋማት የሰረተኛ ስምሪት ሂደትና የአገልግሎት ውጤታማነት ያተኮረ ሲሆን ተገልጋዬች የተሳለጠ አገልግሎት በማግኘት ላይ መሆናቸውንም በአንፃሩ ማረጋገጥ ተችሏል።

የተቃና አገልግሎት መስጠት ከክብርም በላይ መከበር በመሆኑ ለህብረተሰቡ የሚሰጡትን ዘወትራዊ ግልጋሎት በእጅጉ እንደሚያስደስታቸው የተቋማት ባለሙያዎች ገልፀዋል።

ለሚ ኩራ ወረዳ 14 ኮሙኒኬሽን
ህዳር 03-2018 ዓ.ም

በሀሳብ የበላይነት የሚያምን ትዉልድ መገንባት የምንግዜም ስራችን  መሆን አለበት::አቶ በትግሉ ኪታባ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ቢሮ የበጀት ዓመቱን የ 3 ወራት እቅድ አፈፃፀ...
11/11/2025

በሀሳብ የበላይነት የሚያምን ትዉልድ መገንባት የምንግዜም ስራችን መሆን አለበት::አቶ በትግሉ ኪታባ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ቢሮ የበጀት ዓመቱን የ 3 ወራት እቅድ አፈፃፀም እና የቅንጅታዊ አሰራር ስራዎችን ገምግሟል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ም/ቢሮ ኃላፊ አአቶ በትግሉ ኪታባ እንደተናገሩት ሃሳብ መሸጥ፤የሀሳብ የበላይነትን መያዝ እና በሀሳብ የበላይነት የሚያምን ትዉልድ መገንባት የምንግዜም ስራችን መሆን አለበት በማለት ፤በበጀት ዓመቱ ጠንካራ ጎኖችን ይበልጥ በማስቀጠል ክፍተቶችን ፈጥኖ በማረም በቀጣይ የላቀ ዉጤት የምናስመዘግብበት ጊዜ እንዲሆን ሁላችንም መትጋት አለብን ብለዋል።

ምክትል ቢሮ ሃላፊው አክለውም በዘርፉ የተፈጠሩ ምቹ ሁኔታዎችን በመጠቀም ከማዕከል እስከ ወረዳ እንዲሁም ከሌሎች ተቋማት ጋር ተቋማዊ እና ቅንጅታዊ አሰራርን ይበልጥ ማጠናከር የተደራጀና ዘመናዊ አሰራርን መከተል፣የሚዲያ ፕላት-ፎርሞችን ማስፋትና ተከታዮችን ማብዛት ይገባል ነው ያሉት፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ም/ቢሮ ኃላፊ አቶ ዘዉዱ ከበደ በበኩላቸዉ በክረምት ወራት በከተማዋ በተከናወኑ ከተማ አቀፍ እና ሀገር አቀፍ የተለያዩ ህዝባዊ ንቅናቄዎች፣በተለያዩ የልማት ስራዎች፣በበጎ ፈቃድ ተግባራት እና መንግስት ባስመረቃቸዉ ትላልቅ እና ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ላይ ከአመራር ጀምሮ በተደራጀና በተናበበ ቅንጅታዊ አግባብ ትኩረት አድርጎ የማስፈፀሚያ ዕቅድ ከማዘጋጀት ጀምሮ አጀንዳዎችን እና መልዕክቶችን በመቅረፅ፤ መረጃዎችን በመሸጥና ለህዝብ በማስረፅ ሀገራዊ የጋራ መግባባት በመፍጠር ረገድ ቢሮዉ የሚጠበቅበትን ሚና በላቀ ሁኔታ በመፈፀም ኃላፊነቱን መወጣት መቻሉን ተናግረዋል።

በ2018 ይህን የላቀ ትጋትና አፈፃፀም የበለጠ ለማስቀጠልና ዉስንነቶች ለማረም ከማዕከል እስከ ወረዳ ያለዉ የኮሙኒኬሽን መዋቅር በተደራጀ አግባብ በሙሉ አቅም ወደ ስራ መግባቱን አስታዉሰዉ በዚህ በጀት ዓመት ድርብ ድርብርብ ተልዕኮ ያለብን በመሆኑ ከመቸዉም ጊዜ በተሻለ ተግቶ በመስራት እና በሁለንተናዊ መልኩ የበለጠ ነጥረን በመዉጣት በኮሙኒኬሽን አግባብ ስራዎቻችንን በመሸጥ ከተማችንን ብሎም ሀገራችንን ወደ ላቀ ከፍታ ለማሻገር የሚመጥን ስራ መስራት ከእኛ ይጠበቃል በማለት መልዕክታቸዉን አስተላልፈዋል።

በበጀት ዓመቱ 1ኛ ሩብ ዓመት ከማዕከል እስከ ወረዳ ባሉ መዋቅሮች የዝግጅት ምዕራፉ ተግባር ጨምሮ የዉስጥና የዉጪ ተቋማዊ እና ቅንጅታዊ አሰራርን ይበልጥ በማጠናከርና በማዘመን የከተማዋን ሁለተናዊ እንቅስቃሴዎች በአጀንዳ እና በመልዕክት፤በተደራጀና በተናበበ መንገድ በመምራት እና የህዝቡን የመረጃ ፍላጎት በማርካት ዉጤታማ ስራዎች መሰራታቸዉን በቀረቡት ሪፖርቶች ተመላክቷል፡፡

"ወረዳ አስተዳደሩ መደበኛ የመንግስትና የፓርቲ ስራዎችን አፈፃፀም በመገምገም የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ አስቀመጠ"በዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የወረዳ 14 አስተዳደር  መደበኛ የመንግ...
11/11/2025

"ወረዳ አስተዳደሩ መደበኛ የመንግስትና የፓርቲ ስራዎችን አፈፃፀም በመገምገም የቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ አስቀመጠ"

በዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የወረዳ 14 አስተዳደር መደበኛ የመንግስትና የፓርቲ ስራዎችን ጥቅል አፈፃፀም የወረዳው ጠቅላላ አመራሮች በተገኙበት በጥልቀት በመገምገም አቅጣጫ አስቀመጠ።

ስኬቶችን ይበልጥ ለማላቅ ብሎም ክፍተቶችኝ ደግሞ በጊዜ የለኝም መንፈስ ለማረም ያለመውን የጠቅላላ አመራር የውይይት መድረኩም የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አለሙ ጨመዳ እና የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌቴ ቢሠጠኝ በተገኙበት የተካሄደ ሲሆን በመድረኩም መደበኛ የመንግስት እና የፓርቲ ስራዎች የአፈፃፀም ሪፖርት በተቋምና በክላስተር ደረጃ ቀርቦ ለውይይት በቅቷል።

በቀረበውን የተቋማት የስራ አፈፃፀም ግምገማ መነሻ በማድረግም በአፈፃፀም የተሻሉ የሚባሉ ተግባራትን አልቆ በማስቀጠል ብሎም በሂደቱ የተስተዋሉ ዝንፈቶችን ፈጥኖ ማረም በሚያስችል መልኩ በላቀ ፍጥነት እና ውጤት በሚያመጣ የአመራር ስምሪት ተግባራትን መከወን እንደሚገባ ግልፅ ተግባቦት በመፍጠር በቀጣይ ጊዜያት ልዩ ትኩረት በሚሹ ጉዳዬች ዙሪያ የጋራ አቅጣጫ በማስቀመጥ መድረኩ ተቋጭቷል።

ለሚ ኩራ ወረዳ14 ኮሙኒኬሽን
ህዳር 02-2018 ዓ.ም

የከተማው አስተዳደር አመራሮች አቶ ጥራቱ በየነን በአዲስ አበባ የአመራርነት ቆይታቸዉ ለነበራቸዉ አስተዋፆ አመስግነዉ  በሄዱበት መልካሙን ሁሉ በመመኘት በክብር ሸኝተዋል ።እንዲሁም በምክትል ...
11/11/2025

የከተማው አስተዳደር አመራሮች አቶ ጥራቱ በየነን በአዲስ አበባ የአመራርነት ቆይታቸዉ ለነበራቸዉ አስተዋፆ አመስግነዉ በሄዱበት መልካሙን ሁሉ በመመኘት በክብር ሸኝተዋል ።

እንዲሁም በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የስራ እና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ በመሆን የተሾሙት አቶ ሚሊዮን ማቲዎስን እንኳን ደህና መጡ ብለዋል ።

"ስነ ምግባርን መቅረፅ ብሎም ሙስናና ብልሹ አሰራሮች መከሰቻ አውድ እንዳይኖራቸው ማድረግ የጋራ ተግባራችን ነው" በዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ...
10/11/2025

"ስነ ምግባርን መቅረፅ ብሎም ሙስናና ብልሹ አሰራሮች መከሰቻ አውድ እንዳይኖራቸው ማድረግ የጋራ ተግባራችን ነው"

በዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኢንስፔክሽንና ስነ-ምግባር ኮሚሽን ፅህፈት ቤት ከወረዳው የስነ-ምግባር እና ፀረ-ሙስና መከታተያ ቡድን ጋር የጋራ በሚያደርጉ ተቋማዊ አጀንዳዎች ዙሪያ የጋራ የስምምነት ሰነድ ተፈራርመዋል።

የጋራ ስምምነት ሰነዱም የወረዳው ኢንስፔክሽንና ስነ ምግባር ኮሚሽን ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሲሣይ ቤተማርያም እና የወረዳው ስነ ምግባርና ፀረ ሙስና መከታተል ቡድን መሪ የሆኑት አቶ አራርሶ ገደታ በተገኙበት የተካሄደ ሲሆን በኘሮግራሙም የኮሚሽኑ አመራሮች በተቋማቱ መካከል በጋራ ስለሚከወኑ ተግባራት ዙሪያ ግንዛቤ አዘል ስልጠና ተሰጥቷል።

የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናውን የሰጡት የወረዳው ስነ ምግባርና ፀረ ሙስና መከታተያ ቡድን መሪ የሆኑት አቶ አራርሶ ጉደታ እንደገለፁትም ስነ ምግባርን መቅረፅ ብሎም ሙስናና ብልሹ አሰራሮች መከሰቻ አውድ እንዳይኖራቸው ማድረግ የጋራ ተግባራችን ነው"ሲሉ አብራርተዋል።


ለሚ ኩራ ወረዳ 14 ኮሙኒኬሽን
ህዳር 01-2018 ዓ.ም

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Lemi Kura Wereda 14 Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share