Lemi Kura Wereda 14 Communication

Lemi Kura Wereda 14 Communication ይህ የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት ገጽ ነው

"ኢትዮጵያ ትችላለች"  በሚል መሪ ቃል የታላቁን ህዳሴ ግድብ የ14 ዓመት ጉዞ የሚያስቃኝ የፎቶ እና የስዕል አውደ ርዕይ   በአድዋ ድል መታሰቢያ ተከፈተየአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የታላ...
13/09/2025

"ኢትዮጵያ ትችላለች" በሚል መሪ ቃል የታላቁን ህዳሴ ግድብ የ14 ዓመት ጉዞ የሚያስቃኝ የፎቶ እና የስዕል አውደ ርዕይ በአድዋ ድል መታሰቢያ ተከፈተ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የታላቁን የህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ አስመልክቶ በከተማ ደረጃ በማዘጋጀት የፎቶ እና የስዕል አውደ ርዕይ በአድዋ ድል መታሰቢያ ለእይታ ክፍት አድረጓል።

በዚህ በተዘጋጀዉ የፎቶ እና የስዕል አውደ ርዕይ መክፈቻ ስነስርዓት ላይ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ እና የኢንዱስትሪ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ጃንጥራር ዓባይ፣የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ብልፅግና ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ ፣ ፣ናየታላቁ የኢትዮጽያ ህዳሴ ግድብ ህዝባዊ ማስተባበሪያ ፅ/ቤት ዋና ስራ አስፈፃሚ አረጋዊ በርሔ(ዶ/ር ፣ እና ሌሎች ከፍተኛ የፈሬደራልና የከተማ ክፍተኛ የመንግስት አመራሮች ተገኝተዋል።

"የተከናወኑ የንቅናቄ ተግባራት አፈፃፀም እና በቀጣይ ልዩ ትኩረት በሚሹ ተግባራት ዙሪያ የጠቅላላ አመራር መድረክ ተካሄደ"   በዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር ቀደ...
13/09/2025

"የተከናወኑ የንቅናቄ ተግባራት አፈፃፀም እና በቀጣይ ልዩ ትኩረት በሚሹ ተግባራት ዙሪያ የጠቅላላ አመራር መድረክ ተካሄደ"

በዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር ቀደም ብለው የተከናወኑ የንቅናቄው ተግባራት የአፈፃፀም ልክ እና በቀጣይነት በልዩ ትኩረት በሚተገበሩ ንቅናቄ አዘል ተግባራት ዙሪያ የጠቅላላ አመራር መድረክ ተካሂዷል።

ቀደም ብለው የተከናወኑ የንቅናቄው ተግባራት አፈፃፀም እና በቀጣይነት ልዩ ትኩረት በሚሹ ተግባራት ዙሪያ የተካሄደው ግምገማ አዘል የውይይት መድረኩም በወረዳው ምክትል ዋና ስራ አስፈፃሚና የስራና ክህሎት ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ረጅብ አክመል እና በወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ምክትልና የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ታገስ ታምሩ የተመራ ሲሆን በመድረኩም የተከናወኑ ተግባራትን የአፈፃፀም ልክ መነሻ በማድረግ በቀጣይ ልዩ ትኩረት የሚሹ ተግባራትን በስኬት ለመቋጨት አቅም ፈጥሮ ማለፍ በሚያስችል መልኩ ተግባቦት በመፍጠር መድረኩ ተቋጭቷል።

ለሚ ኩራ ወረዳ 14 ኮሙኒኬሽን
መስከረም 03-2018 ዓ.ም

የለሚ ኩራ ክፍለ ፈርጦች ወረዳ 14  ወረዳው  ነዋሪዎች   ! በሚል መሪ ቃል በመስቀል አደባባይ በተዘጋጀው ማህበረሰብ-አቀፍ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ
12/09/2025

የለሚ ኩራ ክፍለ ፈርጦች ወረዳ 14 ወረዳው ነዋሪዎች ! በሚል መሪ ቃል በመስቀል አደባባይ በተዘጋጀው ማህበረሰብ-አቀፍ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ

"በህብረት ችለናል"በለሚ ኩራ  ክ/ከተማ የወረዳ 14  አስተዳደር ወጣቶችና  ነዋሪዎች የታላቁን የህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ ምክንያት በማድረግ በመስቀል አደባባይ እየተካሄደ ባለው ብዙሃን የአካል...
12/09/2025

"በህብረት ችለናል"

በለሚ ኩራ ክ/ከተማ የወረዳ 14 አስተዳደር ወጣቶችና ነዋሪዎች የታላቁን የህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ ምክንያት በማድረግ በመስቀል አደባባይ እየተካሄደ ባለው ብዙሃን የአካል ብቃት እንቅስቃሴ እየተሳተፉ ነው።

በአዲሰ አበባ ዛሬ ህብረት ችለናል በሚል መሪ ቃል የብዙሃን አካል ብቃት እንቅስቃሴ የህብረተሰብ ክፍሎች እየተሳተፉ ነው።

 የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር  "ህዳሴ ለማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል የማስ ስፖርት መርሀግብር መስቀል አደባባይ እያካሄዱ ይገኛሉ።
12/09/2025



የለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር "ህዳሴ ለማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል የማስ ስፖርት መርሀግብር መስቀል አደባባይ እያካሄዱ ይገኛሉ።

11/09/2025
"የወረዳው ኮሙኒኬሽን ፅህፈት ቤት የአዲስ አመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት"   በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር የወረዳው ኮሙኒኬሽን ፅህፈት ቤት መጪውን 2018 የዘመን መለ...
10/09/2025

"የወረዳው ኮሙኒኬሽን ፅህፈት ቤት የአዲስ አመት የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት"

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር የወረዳው ኮሙኒኬሽን ፅህፈት ቤት መጪውን 2018 የዘመን መለወጫ በዓል አስመልክቶ ጠቅላላ አመራሩ እና ለመላው ኢትዮጵያውያን የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፈ።

በወረዳው ኮሙኒኬሽን ፅህፈት ቤት አዘጋጅነት ለጠቅላላ አመራሩ የተበረከተው የአዲስ አመት የመልካም ምኞት መግለጫ ፓስት ካርድ የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አለሙ ጨመዳ እና የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ በአቶ ጌቴ ቢሰጠኝ በተገኙበት ስጦታው ተበርክቷል።

ኮሙኒኬሽን ፅህፈት ቤቱ በመልዕክቱም ኢዲሱ አመት ለሰው ልጆች ሁሉ ተስፋን የሚሰንቅበት በመሆኑ አዳዲስ ዕቅዶቻችን በስኬት የምንቋጭበት ብሎም ለመጪው ትውልድ እዳን ሳይሆን ምንዳን የምናወርስበት አመት እንዲሆን መልካም ምኞቱን ገልጿል።

ለሚ ኩራ ወረዳ 14 ኮሙኒኬሽን
ጷጉሜ 05-2017 ዓ.ም

"የደራው በዓል ተኮር ግብይት በአባዶ"   በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር መጪውን 2018 የዘመን መለወጫ በዓል በልዩ ድምቀት ለመቀበል ባለመው በዓል ተኮር የግብይት ማዕከላት ...
10/09/2025

"የደራው በዓል ተኮር ግብይት በአባዶ"

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር መጪውን 2018 የዘመን መለወጫ በዓል በልዩ ድምቀት ለመቀበል ባለመው በዓል ተኮር የግብይት ማዕከላት ሁሉን አቀፍ በሆነ መንገድ ፍላጎቶችን ሁሉ በሚያረጋግጥ መልኩ በዋዜማው ደማቅ የበዓል ድባብ ፈጥሮ ውሏል።

በበዓል ተኮር የግብይት ማዕከላቱም ሁሉም በአንድ ማዕከል በተሰናሰለበት የግብአት አማራጭፍላጎቶችን ሁሉ ማሟላት በሚያስችል መልኩ የደራ የግብይት ስርዓት መከናወን ውሏል አሁንም ግለቱን ጠብቆ በመካሄድም ላይ ይገኛል።

ለሚ ኩራ ወረዳ 14 ኮሙኒኬሽን
ጷጉሜ 05-2017 ዓ.ም

"በወረዳው አመራሮች መካከል ወንድማማችነትንና እህትማማችነትን ይበልጥ ለማጎልበት ያለመ የስጦታ ኘሮግራም ተካሄደ"በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር በዛሬው ዕለት የተከበረውን ጷጉሜ...
10/09/2025

"በወረዳው አመራሮች መካከል ወንድማማችነትንና እህትማማችነትን ይበልጥ ለማጎልበት ያለመ የስጦታ ኘሮግራም ተካሄደ"

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር በዛሬው ዕለት የተከበረውን ጷጉሜ 05 የነገውን ቀንን ምክንያት በማድረግ ወንድማችነትና እህትማማችነትን በሚያጎለብት መልኩ በወረዳው ጠቅላላ አመራሮች መካከል የርስ በርስ ስጦታ የማበርከት ስነ ስርዓቱ በልዩ ድምቀት አካሄዱ።

ወንድማማችነትንና እህትማማችነትን ከማጎልበት ባሻገር የተቀናጀ የአመራር ስምሪት ለመስጠት ያለመው የስጦታ ልውውጥ ስነ- ስርዓቱም በወረዳው አስተባባሪ ኮሚቴዎች ግንባር ቀደምትነት በልዩ ድምቀት የርስ በርስ ስጦታዎቹ ትዝታን በሚያጭር መልኩ ተካሂዷል።

በመጨረሻም በአመራር የስምሪት ሂደት ፍፁም የወንድማማችነት እና የእህትማማችነት መስተጋብርን ፈጥሮ ማለፍ በሁለንተናዊ መልኩ የተቀናጀ ስራ ብሎም ተደማሪ ውጤትን በዘላቂነት ለማረጋገጥ አስቻይ ሁኔታን ፈጥሮ ማለፍ የሚያስችል ስለመሆኑም በመድረኩ ተገልጿል።

ለሚ ኩራ ወረዳ 14 ኮሙኒኬሽን
ጷጉሜ 05-2017 ዓ.ም

በአዲስ አመት ለከተማችን ነዋሪዎች እነሆ  ገፀ በረከት “አዲስ-መሶብ”!የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓቱን የጠበቀ እና ቀልጣፋ እንዲሆን በቁርጠኝነት መስራታችንን ቀጥለናል::ዛሬ ክቡር ጠ...
10/09/2025

በአዲስ አመት ለከተማችን ነዋሪዎች እነሆ ገፀ በረከት “አዲስ-መሶብ”!

የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓቱን የጠበቀ እና ቀልጣፋ እንዲሆን በቁርጠኝነት መስራታችንን ቀጥለናል::

ዛሬ ክቡር ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ በተገኙበት "አዲስ መሶብ "የአንድ ማዕከል አገልግሎት ስራ አስጀምረን በአዲሱ አመት ዋዜማ እነሆ ገፀ በረከት ብለናል።

በአስራ ሶስት ተቋማት ፤ መቶ ሰባት አገልግሎቶችን የሚሰጠው አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል የነዋሪዎቻችን እንግልት የሚቀንስ ፣ ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት አዲስ ብስራት ይዘን መጥተናል።

በአዲሱ አመት በብዙ ብርታት እና ትጋት ልናገለግላችሁ ቆመናል ።
መልካም አዲስ አመት !

ፈጣሪ ኢትዮጵያ እና ህዝቦቿን ይባርክ!

"ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ማድረግ" በሚል መሪ ቃል በዛሬው ዕለት የሚከበረውን ጷጉሜ 05  የነገው ቀንን ምክንያት በማድረግ በለሚ ኩራ ክፍ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር  ቴክኖሎጂ ተኮር  አ...
10/09/2025

"ዲጂታል ኢትዮጵያን እውን ማድረግ" በሚል መሪ ቃል በዛሬው ዕለት የሚከበረውን ጷጉሜ 05 የነገው ቀንን ምክንያት በማድረግ በለሚ ኩራ ክፍ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር ቴክኖሎጂ ተኮር አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማትን የአገልግሎት አሰጣጥ አግባብ ለማረጋገጥ ያለመ ጉብኝት የወረዳው አስተባባሪ ኮሚቴዎች በተገኙበት ተካሂዷል።

ለሚ ኩራ ወረዳ 14 ኮሙኒኬሽን
ጳጉሜ 5-2017 ዓ.ም

"የነገውን ቀን"ምክንያት በማድረግ የአንድ ማዕከል የፅዳት ዘመቻ ተካሄደ።በዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር በወረዳው ፅዳትና ውበት አስተዳደር ጽህፈት ቤት አስተባባሪ...
10/09/2025

"የነገውን ቀን"ምክንያት በማድረግ የአንድ ማዕከል የፅዳት ዘመቻ ተካሄደ።

በዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር በወረዳው ፅዳትና ውበት አስተዳደር ጽህፈት ቤት አስተባባሪነት ጷጉሜ 05 "የነገውን ቀን"ን ምክንያት በማድረግ በከተማ ደረጃ የአንድ ማዕከል የፅዳት ንቅናቄ በሰፊ የህዝብ ተሳትፎ ታጅቦ በድምቀት ተካሂ
ዷል።

በዕለቱ በተካሄደው የአንድ ማዕከሉ የፅዳት ዘመቻውም ከፅዳት አስተዳደር ኤጀንሲ የመጡ ባለሙያዎችን ጨምሮ የወረዳው ፅዳትና ውበት አስተዳደር ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዋቢ ሰማ እና የወረዳው አመራሮች እንዲሁም በየደረጃው የሚገኙ የዘርፉ ደጋፊ ባለሙያዎች በተገኙበት የተካሄደ ሲሆን በንቅናቄውም የአካባቢው የህብረተሰብ በነቂስ ወጥቶ የዘመቻው አካል መሆን ችለዋል።

2018 አዲስ አመትን በጠራ አመለካከት ፅዱና ውብ አካባቢን በመፍጠር መቀበል ብሎም ፅዳት የስልጡን ማህበረሰብ መገለጫነቱን በሚያረጋግጥ መልኩ የዘወትር ተግባራችን አድርጎ መውሰድ እንሚገባም ተገልጿል።

ለሚ ኩራ ወረዳ 14 ኮሙኒኬሽን
ጷጉሜ 05-2017 ዓ.ም

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Lemi Kura Wereda 14 Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share