Lemi Kura Wereda 14 Communication

Lemi Kura Wereda 14 Communication ይህ የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት ገጽ ነው

On behalf of the City Administration and myself, I extend my warmest wishes for a peaceful and happy 2026 to all ambassa...
01/01/2026

On behalf of the City Administration and myself, I extend my warmest wishes for a peaceful and happy 2026 to all ambassadors, international organizations, and friends in Addis Ababa. We look forward to another year of strengthened friendship and cooperation. Happy New Year!

H.E Mayor Adanech Abiebie

"ተቋማዊ ውጤት በማይዝል ትጋት" በዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር"ተቋማዊ ውጤት በማይዝል ትጋት"በሚል 7/24 የተግባር ስምሪት የወረዳው ጠቅላላ አመራር በቀን የተ...
31/12/2025

"ተቋማዊ ውጤት በማይዝል ትጋት"

በዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር"ተቋማዊ ውጤት በማይዝል ትጋት"በሚል 7/24 የተግባር ስምሪት የወረዳው ጠቅላላ አመራር በቀን የተገበራቸውን ስራዎች በምሽቱ መርሃ ግብር መደበኛና ወቅታዊ ስራዎችን የተቀናጀ ውጤት ማምጣት በሚያስችል መልኩ እየገመገመ ይገኛል።

በሁሉም መስኮች በተቀናጀ የአመራር ስምሪት ውጤትን ለመቀናጀት ያለመው የጠቅላላ አመራር መድረኩም የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አለሙ ጨመዳ እና የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ይደንቃል አስማማው በተገኙበት ተካሂዷል።

ለሚ ኩራ ወረዳ 14 ኮሙኒኬሽን
ታህሳስ 22-2018 ዓ.ም

ለጉብኝት፣ ለቆይታና ለኮንፈረንስ ቱሪዝም ተመራጭ ውብ ከተማ፣ አዲስ አበባ፤አዲሲቷ የአፍሪካ የዕድገት መልክ! ከተማችን አዲሰ አበባ፣ በቱሪዝም ኮንፈረስ እያሰመዘገበች ያለውን ከፍተኛ መነቃቃት...
31/12/2025

ለጉብኝት፣ ለቆይታና ለኮንፈረንስ ቱሪዝም ተመራጭ ውብ ከተማ፣ አዲስ አበባ፤
አዲሲቷ የአፍሪካ የዕድገት መልክ!

ከተማችን አዲሰ አበባ፣ በቱሪዝም ኮንፈረስ እያሰመዘገበች ያለውን ከፍተኛ መነቃቃትና ዕድገት ይበልጥ ተመራጭ፣ የስሕበት ማከል እንድትሆን አድርጓታል፡፡ በተለይም፣ የቱሪዝም ኮንፍረስ መስሕብነት የሚያሳድጉ ደረጃቸውን የጠበቁ ኮንቬንሽ ማዕከላት፣ የወንዝ ዳርቻ መሠረተ-ልማቶች፣ ሁሉን-አቀፍ ፓርኮች ፣ ታሪካዊና ባህላዊ ሙዚየሞች ፣ ምቹ መንገዶች ፣ የህፃናት መጫወጫ ስፍራዎች እና ሞተር አልባ የትራንስፖርት አማራጭን ጨምሮ ዘመናዊ የመኪና ማቆሚያ ፓርኪንግ እና ደረጃቸውን የጠበቁ ፕላዛዎች ለጉብኝት እና ለኮንፈረንስ ቱሪዝም ተማራጭ ከተማ እንድትሆን አስችሏታል፡፡

በተጨማሪም ሀገር በቀል እጽዋት መገኛ የሆነው ጉለሌ እጽዋት ማዕከል ጨምሮ በከተማዋን ዙሪያ የከበቡ ታሪካዊ ዋሻዎችና ቅርሶች የጎብኚዎችን ቀልብ እንዲያርፍባት አድርጓል፡፡ በሌላ በኩል በመዲናዋ የተሰሩ ዘርፍ ብዙ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታቸው የጉላ ሰው ተኮር ልማቶች በአለም አቀፍ ጎብኚዎች ዘንድ በቀዳሚነት ስሟ እንዲጠቀስ አድርጓል፡፡

አዲስ አበባ በፍጥነት እያስመዘገበች በምትገኘው አስደማሚ ለውጦች፣ በርካታ አለም አቀፍና አህጉር አቀፍ ሁነቶችን እና ኮንፍረንሶችን በማዘጋጀት ተወዳዳሪ ከተማ ሆናለች፡፡

"የተሳለጠ አገልግሎት በጉዳይ ባለቤቶች ዕለት"    በዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር "የተሳለጠ አገልግሎት በጉዳይ ባለቤቶች ዕለት"በሚል መርህ የባለጉዳይ ቀናት ለ...
31/12/2025

"የተሳለጠ አገልግሎት በጉዳይ ባለቤቶች ዕለት"

በዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር "የተሳለጠ አገልግሎት በጉዳይ ባለቤቶች ዕለት"በሚል መርህ የባለጉዳይ ቀናት ለታለመላቸው አላማ መዋላቸውን ለማረጋገጥ ያለመ የአገልግሎት አሰጣጥ ውጤታማነት ቅኝት በወረዳው ኮሙኒኬሽን ፅህፈት ቤት ተካሂዷል።

የአገልግሎት አሰጣጥ ቅኝቱ በአንድ ማዕከል የሚከናወነውን የተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን ጨምሮ በሁሉም አገልግሎት ሰጭ ተቋማት አሚካኝነት ከሰላ የባለሙያ ሰምሪት ጀምሮ በተቀናጀ መልኩ ቀልጣፋና ዘመናዊ አገልግሎት ግልጋሎትን መስጠት በሚያስችል መልኩ እየተከናወነ ስለመሆኑም በዕለቱ ማረጋገጥ ተችሏል።

"የተሳለጠ አገልግሎት በጉዳይ ባለቤቶች ዕለት"በሚል መርህም የባለጉዳይ ቀናት እንግልትን በሚቀንስ ብሎም የውሳኔ ሰጭነት አቅምን በሚያዳብር ተግባራዊ በማድረግ የባለጉዳይ ቀናት ለታለመላቸው የህዝብ ግልጋሎት መስጫነት ብቻ እንዲውሉ ማድረግ እንደሚጠይቅም ተመላክቷል።

ለሚ ኩራ ወረዳ 14 ኮሙኒኬሽን
ታህሳስ 22- 2018 ዓ.ም

"ልዩ ትኩረት በሚሹ የፓርቲና የመንግስት ተግባራት ዙሪያ የጠቅላላ አመራር መድረክ ተካሄደ"   በዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር ልዩ ትኩረት በሚሹ የፓርቲና የመንግ...
30/12/2025

"ልዩ ትኩረት በሚሹ የፓርቲና የመንግስት ተግባራት ዙሪያ የጠቅላላ አመራር መድረክ ተካሄደ"

በዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር ልዩ ትኩረት በሚሹ የፓርቲና የመንግስት ተግባራት ዙሪያ የክፍለ ከተማ ደጋፊ አመራሮችና የወረዳ አስተባባሪዎች በተገኙበት የጠቅላላ አመራር መድረክ ተካሄደ።

የጠቅላላ አመራር መድረኩም የክፍለ ከተማ ደጋፊ አመራሮችን ጨምሮ የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አለሙ ጨመዳ እና የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ይደንቃል አስማማው በተገኙበት የተካሄደ ሲሆን የውይይት መድረኩም ልዩ ትኩረት በሚሹ የፓርቲና የመንግስት ተግባራት ዙሪያ ውጤት ማምጣት በሚያስችል መልኩ የሰላ ውይይት ተደርጓል።

ግምገማ አዘል የውይይት መድረኩም በዋናነት በዜጎች የስራ ዕድል ፈጠራ ስራዎች፣በሌማት ትሩፋት ተግባራት፣ በበጎ አድራጎት ተግባራት አፈፃፀም እንዲሁም በፓርቲና መንግስት ተግባራት በክላስተርና በተቋም ደረጃ የአፈፃፀም ሪፖርቶች ቀርበው ለቀጣይ የውጤት ስንቅ በሚሰንቅ መልኩ የትኩረት አቅጣጫ በማስቀመጥ መድረኩ ተቋጭቷል።

ለሚ ኩራ ወረዳ 14 ኮሙኒኬሽን
ታህሳስ 21-2018 ዓ.ም

"የመደመር መንግስት እይታ ለፓርቲ ተቋም ግንባታ"በሚል መሪ ቃል በወረዳ ደረጃ የአባላት ኮንፈረንስ የማጠቃለያ መድረክ ተካሄደበዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 ብልፅግና ፓርቲ ...
30/12/2025

"የመደመር መንግስት እይታ ለፓርቲ ተቋም ግንባታ"በሚል መሪ ቃል በወረዳ ደረጃ የአባላት ኮንፈረንስ የማጠቃለያ መድረክ ተካሄደ

በዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት አስተባባሪነት"የመደመር መንግስት እይታ ለፓርቲ ተቋም ግንባታ"በሚል መሪ ቃል በወረዳ ደረጃ የ2ኛ ሩብ አመት የብልፅግና ፓርቲ አባላት የማጠቃለያ ኮንፈረንስ በልዩ ድምቀት ተካሂዷል።

"የመደመር መንግስት እይታ ለፓርቲ ተቋም ግንባታ"በሚል መሪ ቃል በተካሄደው የአባላት የማጠቃለያ ኮንፈረንሱም የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አለሙ ጨመዳ፣የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ይደንቃል አስማማው እና የወረዳው ፓርቲ ኢንስፔክሽንና ስነ ምግባር ኮሚሽን ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሲሣይ ቤተማርያም እንዲሁም የወረዳው አስተባባሪ ኮሚቴ አባላት፣የህብረት አመራሮችና የቤተሰብ አመራሮችና ግንባር ቀደም አባላት በተገኙበት በልዩ ድምቀት ተካሂዷል።

በማጠቃለያ መድረኩም በወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት በ2018 በጀት አመት በ2ኛ ሩብ አመት የተከናወኑ የፓርቲ ተግባራት የአፈፃፀም ሪፖርት በወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ምክትልና የፓለቲካ ዘርፍ ኃላፊ በአቶ ታገስ ታምሩ አማካኝነት የቀረበ ሲሆን በተደማሪነትም በፓርቲ ኢንስፔክሽን ስራዎች የአፈፃፀም ሪፖርት በፓርቲው የኢንስፔክሽንና ስነ ምግባር ኮሚሽን ፅህፈት ቤት ኃላፊ በአቶ ሲሣይ ቤተማርያም አማካኝነት ሰነዶች ቀርበው ለውይይት በቅተዋል።

የመድረኩ ተሳታፊዎች በበኩላቸው ደረጃ በደረጃ ለሁለት ተከታታይ ቀናት የዘለቀው የአባላት ኮንፈረንስ ማጠቃለያ መድረኩ ተደማሪ አቅም ሊፈጥር በሚችል መልኩ የተከናወኑ ዝርዝር ተግባራት በክፍተትና በጥንካሬ ተመላክተው መቅረባቸው በቀጣይ ጊዜያት ትኩረት ተደርጎባቸው የሚከናወኑ ተግባራትን ጭምር ያመላከተ በመሆኑ በተቀናጀ የአመራር ስምሪት ውጤታማ ስራዎችን ማከናወን እንደሚገባ በመጠቆም ከመድረክ ማደማደሚያ ምላሽ ተሰጥቶባቸው ተግባቦት መድረኩ ተቋጭቷል።

ለሚ ኩራ ወረዳ 14 ኮሙኒኬሽን
ታህሳስ 21-2018 ዓ.ም

"የመደመር መንግስት እይታ ለፓርቲ ተቋም ግንባታ"በሚል መሪ ቃል በወረዳ ደረጃ የአባላት የማጠቃለያ ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው" በዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 ብልፅግና ፓር...
30/12/2025

"የመደመር መንግስት እይታ ለፓርቲ ተቋም ግንባታ"በሚል መሪ ቃል በወረዳ ደረጃ የአባላት የማጠቃለያ ኮንፈረንስ እየተካሄደ ነው"

በዛሬው ዕለት በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት አስተባባሪነት "የመደመር መንግስት እይታ ለፓርቲ ተቋም ግንባታ"በሚል መሪ ቃል በወረዳ ደረጃ የብልፅግና ፓርቲ አባላት የማጠቃለያ ኮንፈረንስ በልዩ ድምቀት በመካሄድ ላይ ይገኛል።

ለሚ ኩራ ወረዳ 14 ኮሙኒኬሽን
ታህሳስ 21-2018 ዓ.ም

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በሁሉም ክፍለ ከተሞች መርቀዉ ስራ ያስጀመሯቸዉ  32 አዳዲስ የፖሊስ እና የእሳትና አደጋ ሥጋት መከላከያ ተቋማት - በምስል
29/12/2025

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በሁሉም ክፍለ ከተሞች መርቀዉ ስራ ያስጀመሯቸዉ 32 አዳዲስ የፖሊስ እና የእሳትና አደጋ ሥጋት መከላከያ ተቋማት - በምስል

29/12/2025
ዛሬ ማምሻውን በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ፣ የመሪ ሎቄ አካባቢ ለህዝብ ሁለገብ አገልግሎት የተገነቡ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል።ይህ አዲስ አበባን ለነዋሪዎቿ ምቹ ከ...
28/12/2025

ዛሬ ማምሻውን በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ፣ የመሪ ሎቄ አካባቢ ለህዝብ ሁለገብ አገልግሎት የተገነቡ የመሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን ለአገልግሎት ክፍት አድርገናል።

ይህ አዲስ አበባን ለነዋሪዎቿ ምቹ ከተማ የማድረግ ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን የሚያሳይ ሲሆን፤ ማህበራዊ ትስስርን የሚያጠናክሩ፣ ለስፖርታዊ እንቅስቃሴ፣ ለውድድር፣ ለዕረፍትና ለህጻናት መጫወቻነት ምቹ ሆነው የተገነቡ ናቸው። ፕሮጀክቱ በአጠቃላይ በ10.5 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈ ሲሆን፣ ለከተማችን ጽዳትና ውበት ተጨማሪ አቅም የፈጠረ ድንቅ ስራ ነው።
በውስጡ ያካተታቸው፦

• ሁለት ዘመናዊ የአዋቂዎችና የህፃናት እግር ኳስ ሜዳዎች።
• የቅርጫት ኳስ፣ የቴኒስና የመረብ ኳስን አጣምሮ የያዙ ሁለገብ ሜዳዎች።
ለተፈጥሮ አድናቂዎች፦
• በተፈጥሮ ድንጋይ ያጌጠ አስደናቂ ፋውንቴንና ፕላዛ፣
• ⁠በማራኪ አበባዎች ያማረ አረንጓዴ ስፍራ፣
• ⁠ጸጥ ያሉ የማንበቢያ ቦታዎች እና ሰፋፊ የእግረኛ መንገዶች።
• ሙሉ የመጫወቻ ቁሳቁስ የተገጠመለት የህጻናት ማልሚያ (ECD)።
• ዘመናዊ ካፌቴሪዎች።
• ከ400 በላይ ተሽከርካሪዎችን የሚያስተናግድ የመኪና ማቆሚያ።
• ለኤሌክትሪክ መኪኖች የኃይል መሙያ (EV Charger)።
• የህዝብ መፀዳጃ ቤቶች
• አካባቢውን በስዕልና በቀለም ያስጌጡ የጥበብ ስራዎች ወዘተ ተካትተዉበታል ።

ይህ ፕሮጀክት ያረፈበት መሬት፣ በደላሎች እጅ የነበሩ 23 ህገ-ወጥ ካርታዎችን በማምከን መሬቱ መልሶ ለህዝብ ጥቅም እንዲውል የተደረገበት ነው። በተጨማሪም የአካባቢው ነዋሪዎችና ወጣቶች በስራ ዕድል ተደራጅተው የፕሮጀክቱ ዋነኛ ባለቤትና ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተደርጓል።
መዲናችንን በየዕለቱ እየለወጥን፣ ቃላችንን በተግባር እያረጋገጥን እንቀጥላለን።

ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ

ተፈጥሮአዊ ውበታቸውን በመጎናፀፍ ላይ ያሉ የአዲስ አበባ ወንዞች በከፊል:-
28/12/2025

ተፈጥሮአዊ ውበታቸውን በመጎናፀፍ ላይ ያሉ የአዲስ አበባ ወንዞች በከፊል:-

"በወረዳው የበጋ የበጎ አድራጎት መርሃ ግብር የቤት እድሳት የማስጀመሪያ ፕሮግራም ተካሄደ"   በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር በበጋው የበጎ አድራጎት መርሃ ግብር አስተዳደራዊ ...
27/12/2025

"በወረዳው የበጋ የበጎ አድራጎት መርሃ ግብር የቤት እድሳት የማስጀመሪያ ፕሮግራም ተካሄደ"

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር በበጋው የበጎ አድራጎት መርሃ ግብር አስተዳደራዊ ድጋፍ ለሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎች የሚከናወነው የቤት እድሳት ተግባር የማስጀመሪያ ፕሮግራም በዛሬው ዕለት ተካሂዷል፡፡

በቤት እድሳቱ የበጎ አድራጎት የማስጀመሪያ መርሃ ግብሩም የክፍለ ከተማ ደጋፊ አመራርን ጨምሮ የወረዳው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አለሙ ጨመዳ፣የወረዳው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ይደንቃል አስማማው እና የወረዳው ህብረተሰብ ተሳትፎና በጎ ፍቃድ ማስተባበሪያ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሚዛን ኪዳኔ እንዲሁም የአስተባባሪ ኮሚቴ አባላትና የክላስተር ደጋፊ አመራሮች በተገኙበት የተከናወነ ሲሆን በማስጀመሪያ መርሃ ግብሩም የበጎ ተግባሩ አስፈፃሚ አካላት ተገኝተዋል።

በሰው ተኮር የእሳቤ ማዕቀፍ በዕለቱ የተከናወነው የቤት እድሳት የበጎ አድራጎት መርሃ ግብሩም ልዩ ድጋፍ ለሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎች በጎ ፍቃደኛ ግለሰቦችን የተግባሩ ባለቤት እንዲሆኑ በማስቻል ተግባሩን ማስጀመር እንደተቻለ ተገልጿል።

ለሚ ኩራ ወረዳ 14 ኮሙኒኬሽን
ታህሳስ 18-2018 ዓ.ም

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Lemi Kura Wereda 14 Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share