08/08/2026
የቅዳሜና እሁድ የገበያ ማዕከላት የህብረተሰቡን የኑሮ እፎይታ መሆኑ ተረጋገጠ።
በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር መንግስት የህማህበረሰቡን የኑሮ ጫና ለማቅለልና የዋጋ ጭማሪዉን ለመቆጣጠር ብሎም የዋጋ ማረጋጋት ስራዎችን በዘላቂነት አጠናክሮ በመቀጠል በየቦታዉ የቅዳሜና እሁድ የገበያ ማዕከላትን በማቋቋምና አማራጮች በማቅረብ ለአካባቢው ማህበረሰብ እፎይታን ያረጋገጡ ሁነኛ መፍትሔዎች መሆናቸውን እያስመሰከሩ እንደሚገኙ የወረዳዉ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ባደረገዉ ምልከታ ማረጋገጥ ችሏል።
በቅዳሜና እሁድ የገበያ ማዕከላት የሸማች ማህበራትን ጨምሮ ለህብረተሰቡ በሰፊ የምርት አቅርቦት በታጀበ መልኩ በተመጣጣኝ የዋጋ ተመን የዕለት ተዕለት የፍጆታ ምርቶች የማቅረብ ሂደቱ ዛሬም እንደ ትላንቱ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
የቅዳሜና እሁድ የገበያ ማዕከላት የተለያዩ አማራጮችን በማቅረብ ረገድ ለህብረተሰቡ ትልቅ እፎይታን እየሰጡ ስለመሆናቸውም የወረዳዉ ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ባደረጉት ምልከታ ማረጋገጥ ችለዋል።
በተመሳሳይ በገበያ ማዕከላቶቹ አንዳንድ የፍጆታ ምርቶች ላይ የተወሰነ የአቅርቦት እጥረት እንዳለም ባለሙያዎቹ ባደረጉት ምልከታ መታዘብ ቸለዋል።
ለሚ ኩራ ወረዳ 14 ኮሙኒኬሽን
ነሐሴ 02-12-2018 ዓ.ም