Lemi Kura Wereda 14 Communication

Lemi Kura Wereda 14 Communication ይህ የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጽህፈት ቤት ገጽ ነው

የቅዳሜና እሁድ የገበያ ማዕከላት  የህብረተሰቡን የኑሮ እፎይታ  መሆኑ ተረጋገጠ።በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር መንግስት  የህማህበረሰቡን የኑሮ  ጫና ለማቅለልና  የዋጋ ጭማሪ...
08/08/2026

የቅዳሜና እሁድ የገበያ ማዕከላት የህብረተሰቡን የኑሮ እፎይታ መሆኑ ተረጋገጠ።
በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር መንግስት የህማህበረሰቡን የኑሮ ጫና ለማቅለልና የዋጋ ጭማሪዉን ለመቆጣጠር ብሎም የዋጋ ማረጋጋት ስራዎችን በዘላቂነት አጠናክሮ በመቀጠል በየቦታዉ የቅዳሜና እሁድ የገበያ ማዕከላትን በማቋቋምና አማራጮች በማቅረብ ለአካባቢው ማህበረሰብ እፎይታን ያረጋገጡ ሁነኛ መፍትሔዎች መሆናቸውን እያስመሰከሩ እንደሚገኙ የወረዳዉ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ባደረገዉ ምልከታ ማረጋገጥ ችሏል።

በቅዳሜና እሁድ የገበያ ማዕከላት የሸማች ማህበራትን ጨምሮ ለህብረተሰቡ በሰፊ የምርት አቅርቦት በታጀበ መልኩ በተመጣጣኝ የዋጋ ተመን የዕለት ተዕለት የፍጆታ ምርቶች የማቅረብ ሂደቱ ዛሬም እንደ ትላንቱ ተጠናክሮ ቀጥሏል።
የቅዳሜና እሁድ የገበያ ማዕከላት የተለያዩ አማራጮችን በማቅረብ ረገድ ለህብረተሰቡ ትልቅ እፎይታን እየሰጡ ስለመሆናቸውም የወረዳዉ ኮሙኒኬሽን ባለሙያዎች ባደረጉት ምልከታ ማረጋገጥ ችለዋል።
በተመሳሳይ በገበያ ማዕከላቶቹ አንዳንድ የፍጆታ ምርቶች ላይ የተወሰነ የአቅርቦት እጥረት እንዳለም ባለሙያዎቹ ባደረጉት ምልከታ መታዘብ ቸለዋል።

ለሚ ኩራ ወረዳ 14 ኮሙኒኬሽን
ነሐሴ 02-12-2018 ዓ.ም

07/08/2026

"የኦሮሞ ሕዝብ ኢትዮጵያን ኢትዮጵያ አድርጎ በመፍጠርና በመገንባት ረገድ ግንባር ቀደም ሚና አለው"

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

07/08/2026
►►►"የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደት መሻሻሉን ተገልጋዮች ገለጹ"◄◄◄በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር የአገልግሎት መስጫ ቀናት ለታለመላቸው ዓላማ መዋላቸውንና በአጠቃላይ የአገልግሎት...
07/08/2026

►►►"የአገልግሎት አሰጣጥ ሂደት መሻሻሉን ተገልጋዮች ገለጹ"◄◄◄

በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር የአገልግሎት መስጫ ቀናት ለታለመላቸው ዓላማ መዋላቸውንና በአጠቃላይ የአገልግሎት አሰጣጡ መሻሻል መታየቱን የወረዳው ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ባደረገው ምልከታ አረጋግጧል።

በምልከታው ወቅት በወረዳው የሚገኙ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት፣ የአንድ ማዕከልን ጨምሮ፣ ፈጣን፣ ቀልጣፋና የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድግ አገልግሎት እየሰጡ መሆኑ ታይቷል።

የወረዳው ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ያነጋገራቸው ተገልጋዮችም ከቀደመው ጊዜ አንጻር የአገልግሎት አሰጣጡ መሻሻሉን ገልጸዋል። በተለይም የሠራተኞች አቀባበል፣ የአገልግሎት ፍጥነትና ለጉዳያቸው የሚሰጠው ምላሽ አበረታች መሆኑን ጠቁመዋል።

በሌላ በኩል፣ አንዳንድ ተገልጋዮች በተወሰኑ ተቋማት የሚያጋጥመው የሲስተም መቆራረጥና የአገልግሎት ውስንነት በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ መስተጓጎል እንደሚፈጥር አስተያየት ሰጥተዋል። ችግሮቹ በቀጣይነት ከተፈቱ የተገልጋዮችን እንግልት የበለጠ ለመቀነስና የአገልግሎት ጥራቱን ለማሻሻል አዎንታዊ ሚና እንደሚኖረውም ገልጸዋል።

አስተዳደርም ለህብረተሰቡ ፈጣን፣ ቀልጣፋ፣ ግልጽና ተገልጋይን ያማከለ አገልግሎት ለመስጠት ያለውን ቁርጠኝነት በምልከታው የታየ ሲሆን የተለዩ ጉድለቶችን ለማስተካከል የአገልግሎት ጥራትና የተገልጋዮች እርካታ እንዲሻሻል ትኩረት አየሰጠ መሆኑን ተመልክተናል ።

ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14
ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት
ነሐሴ 01/2018 ዓ.ም.

►►►►" የአገልግሎት አሰጣጥ ከጊዜ ወደ ጊዜእየተሻሻለ እንደመጣ  ተገለፀ::በለሚኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር   የአገልግሎት መስጫ ቀናት ለታለመላቸዉ አላማ መዋላቸዉን የጉዳይ ባለ...
05/08/2026

►►►►" የአገልግሎት አሰጣጥ ከጊዜ ወደ ጊዜእየተሻሻለ እንደመጣ ተገለፀ::
በለሚኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 አስተዳደር የአገልግሎት መስጫ ቀናት ለታለመላቸዉ አላማ መዋላቸዉን የጉዳይ ባለቤቶች ገልፀዋል።
በአገልግሎት አሰጣጥ ሂደቱም በወረዳዉ የሚገኙ አገልግሎት ሰጭ ተቋማት የአንድ ማዕከልን ጨምሮ ፈጣን፣ቀልጣፋና የህዝብ አመኔታን ያተረፉ አገልግሎቶች እየተሰጡ እንደሆነ የወረዳዉ ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ባደረገዉ የአገልግሎት አሰጣጥ ምልከታ ማረጋገጥ ችሏል።
በሌላ በኩል ከአገልግሎት ተጠቃሚዎች ጋር በተደረገ ቃለ መጠይቅ፣ በወረዳው የአገልግሎት አሰጣጥ ከቀደመው ጊዜ ጋር ሲነፃፀር መሻሻሉንና የተሻለ አገልግሎት እየተሰጠ መሆኑን ያነጋገርናቸዉ የጉዳይ ባለቤቶች ገልጸዋል። በተለይም የሰራተኞች አቀባበል፣ የአገልግሎት ፍጥነት እና ለጉዳያቸው የሚሰጠው ምላሽ አበረታች መሆኑን ጠቅሰዋል።
በተመሳሳይም አንዳንድ ተጠቃሚዎች በተወሰኑ ጽ/ቤቶች የሚያጋጥም የሲስተም መቆራረጥ፣የአገልግሎት ዉስንነት በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ መስተጓጎል እንደሚፈጥር በመግለጽ፣ ችግሩ በቀጣይ በቋሚነት ከተፈታ የህዝቡን እንግልት የበለጠ ለመቀነስና የአገልግሎት ጥራትን ለማሻሻል ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው የጉዳዪ ባለቤቶች አስተያየታቸውን ለወረዳዉ ኮሙኒኬሽን ሰጥተዋል።
ወረዳ 14 አስተዳደርም ለህዝቡ ፈጣን፣ ቀልጣፋ፣ ግልጽና አመኔታን ያተረፈ አገልግሎት ለመስጠት ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር እያረጋገጠ እንደሚቀጥል ተገልጿል።

ለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14
ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት
ሐምሌ 29_11_ 2018 ዓ.ም

04/08/2026
04/08/2026

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Lemi Kura Wereda 14 Communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share