New art and event

New art and event Its smart page follow it for ethio beter life

27/09/2024

አንች አለም መልካም ነሽ
የደግነት ጠግ ከደጋግ ሰዎች
የክፍትን ጥግ ከክፉ ሰዎች አሳየሽኝ ።

10/09/2024

ውድ ኢትየጵያዊያን ።ይህ የዘመን አቆጣጠር የእኛና የእኛ ብቻ ነው ። እንኳን ለአዲሱ አመት በሰላም አደረሳችሁ ።
2016 ለኔ ፈታኝ ዘመን ነበር ።ሆኖም አልፏል ይህ አመት እንደተቋጨ 2016 የፈተናችን የችግራችን የሀዘናችን የአመማችን መቋጫ ሆኖ 2017 አዲሱ አመት የሰላም የፍቅር የደስታ የስኬት ይሁንላችሁ ።
እንቁለጣጣሽ
ዮሐንስ ነኝ ከዲቲ

አቡነ ጴጥሮስ በ1880 በሸዋ ክፍለ ሀገር፣ ፍቼ የተወለዱት አቡነ ጴጥሮስ፣ ከአርበኞች ጋር ለነጻነት ትግል ሲያካሂዱ ተይዘው፣ በስምንት የጣሊያን ወታደሮች በአዲስ አበባ ከተማ በአደባባይ በግ...
20/07/2024

አቡነ ጴጥሮስ

በ1880 በሸዋ ክፍለ ሀገር፣ ፍቼ የተወለዱት አቡነ ጴጥሮስ፣ ከአርበኞች ጋር ለነጻነት ትግል ሲያካሂዱ ተይዘው፣ በስምንት የጣሊያን ወታደሮች በአዲስ አበባ ከተማ በአደባባይ በግፍ የተረሸኑት፣ የዛሬ 86 ዓመት ነበር፡፡

በ1920 ከእስክንድሪያ ቤተ ክርስቲያን በይፋ ማዕረገ ጵጵስናን ከተቀበሉት የመጀመሪያዎቹ አራት ኢትዮጵያውያን አንዱ የኾኑት አቡነ ጴጥሮስ ከ1928 እስከ 1933 ለአምስት ዓመታት በዘለቀው የፋሺስት ኢጣሊያ ወረራ ወቅት ለጠላት አንበገርም በማለት ሕይወታቸውን ለሀገራቸው ክብር የሰጡ ሰማዕት ናቸው፡፡

ቀዳሚው የመጠሪያ ስማቸው ኃይለ ማርያም ሲኾን፣ ከገበሬ ቤተሰብ ነው የተወለዱት፡፡ ሀገራዊውን የቤተ ክህነት ትምህርት በደብረ ሊባኖስ ገዳም የተማሩት አቡነ ጴጥሮስ በ1908 ገደማ ነበር ሥርዓተ ምንኩስና የፈፀሙት፡፡

አቡነ ጴጥሮስ በጎጃም (ዋሸራ)፣ በጎንደር እና በቦሩ ሜዳ በሚገኙ ገዳማት ውስጥ ኖረዋል፡፡
የመምህርነት ሕይወታቸውን ወሎ፣ ሳይንት በሚገኘው ምስካበ ቅዱሳን ገዳም ቅኔ እና መጻሕፍት በማስተማር የጀመሩት አቡነ ጴጥሮስ፣ ኋላ በቤተ ክህነት የማስተማር ብቃታቸው ተመስክሮላቸው ወላይታ ወደሚገኘው የደብረ መንክራት ገዳም ተዛውረዋል፡፡

… በ1916 በዝዋይ ሐይቅ ደሴት ላይ ለሚገኘው የደብረ ማርያም ገዳም በዋና መምህርነት ተመደቡ፡፡ በ1919 ደግሞ በገነተ ልዑል ግቢ በሚገኘው የመንበረ ልዑል ማርቆስ ቤተ ክርስቲያን መምህር ኾነው የተመደቡ ሲኾን፣ በዚያም የደጃዝማች ተፈሪ (ኋላ ቀዳማዊ አጼ ኃይለሥላሤ) የነፍስ አባት ኾኑ፡፡

እውቀታቸው፣ ለሃይማኖታቸው ያላቸው ቀናዒነት እና ከንጉሣዊው ቤተሰብ ጋር የነበራቸው ቅርበት፣ በ1920 ለጵጵስና ከተመረጡት የመጀመሪያዎቹ ኢትዮጵያውያን አንዱ ሆነው ለመመረጥ አስችሏቸዋል፡፡ “ጳጳስ ዘምሥራቅ ኢትዮጵያ ተላዌ አሠሩ ለአቡነ ሞአ” በሚል ማዕረግ፣ በሀገረ ግብጽ፣ እስክንድሪያ በሚገኘው የቅዱስ ማርቆስ ገዳም ማዕረገ ጵጵስና ተቀበሉ፡፡ ከዚህ በኋላ፣ አቡነ ጴጥሮስ የሀገረ ስብከታቸውን ዋና ጽሕፈት ቤት ደሴ ላይ በማድረግ፣ የመንዝ አውራጃ እና የወሎ ክፍለ ሀገር ጳጳስ ኾነው ተሾሙ፡፡

በ1927 ፋሺስት ኢጣሊያ ኢትዮጵያን ስትወርር፣ በዘመኑ እንደነበሩት አብዛኞቹ የቤተ ክህነት ሰዎች፣ አቡነ ጴጥሮስም ከአጼ ኃይለሥላሤ ጋር ወራሪውን ለመመከት ወደ ማይጨው ዘመቱ፡፡ ሆኖም የወራሪው ጠላት ኃይል አይሎ፣ ንጉሡ ሀገር ጥለው ሲወጡ፣ አቡነ ጴጥሮስ ከአርበኞች ጋር ለመቆየት ወሰኑ፡፡

መቀመጫቸውን በደብረ ሊባኖስ ገዳም በማድረግ፣ አርበኞች ለሀገራቸው ነጻነት የሚያደርጉትን ተጋድሎ ያደፋፍሩ ነበር፡፡

ሐምሌ 20 ቀን 1928 አቡነ ጴጥሮስ በአዲስ አበባ የሚገኘውን የፋሺስት ጦር ከመዲናዋ በአራት አቅጣጫ ለማጥቃት ሲወጠን አቡነ ጴጥሮስ የዕቅዱ ተሳታፊ ነበሩ፡፡ በዕቅዱ ከመሳተፍ ባሻገር ራሳቸውም ጠብመንጃ ታጥቀው ከበስተ ሰሜን በኩል ጥቃት ከሚሰነዝረው የሰላሌው የአርበኞች ቡድን ጋር ተቀላቀሉ፡፡

በዕቅዱ መሠረት ጥቃቱ ሲፈፀም በተካሄደው ከባድ ውጊያ በጠላት ላይ ትልቅ ጉዳት ማድረስ ቢችሉም፣ በደጃዝማች አበራ ካሳ የሚመሩት የሰላሌ አርበኞች እና ሌሎችም ቡድኖች ማፈግፈግ ግድ ሆነባቸው፡፡ በማፈግፈግ ላይ ሳሉ ግን፣ አቡነ ጴጥሮስ በጣሊያኖቹ እጅ ላይ ወደቁ፡፡

ሐምሌ 22 ቀን 1928 በመሃል አዲስ አበባ፣ ዛሬ የስማቸው መጠሪያ በኾነው አካባቢ፣ በስምንት የኢጣሊያ ወታደሮች የእሩምታ ተኩስ በአደባባይ ተረሸኑ፡፡
ዮሐንስ አምባቸው
አዲስ አበባ

''ከምሁራን ማህደር''👉ህልምህ እንዳይሳካ የሚያደርግ አንድ መጥፎ ነገር አለ " አይሳካልኝም " የሚል ፍርሃት ።  👉ሰዎች እንዲረዱህ ከመጠን በላይ አትድከም ሰዎች እንደሆኑ የሚሰሙት መስማት...
16/06/2024

''ከምሁራን ማህደር''

👉ህልምህ እንዳይሳካ የሚያደርግ አንድ መጥፎ ነገር አለ " አይሳካልኝም " የሚል ፍርሃት ።

👉ሰዎች እንዲረዱህ ከመጠን በላይ አትድከም ሰዎች እንደሆኑ የሚሰሙት መስማት የሚፈልጉትን ብቻ ነውና ።

👉 አንድቀን ከእንቅልፍህ ስትነቃ ጊዜህ አልቆ ልታገኘው ትችላለህ ፤ ስለዚህ ልታደርገው የምትፈልገውን ነገር አሁኑኑ አድርገው ።

👉ስኬታማ ለመሆን ከፈለክ አንድ ሕግ አክብር ፈጽሞ ራስህን አትዋሽ ።

👉 የህይወት ምስጢሩ ሰባት ጊዜ ወድቆ ስምንት ጊዜ መነሳት ነው ።

👉 በዓለም ላይ ያለ ማንኛውም ሰው ሊገባው የሚችለው ቛንቛ አለ " ፍቅር " !

👉 ስትሸነፍ አይደለም የተሸነፍከው በቃኝ ብለህ ስታቆም እንጂ !

👉 አንድ ነገር አስታውስ ልብህ ያለበት ቦታ ሀብትህም ተቀምጧል ።

መልካም ቀን❤

+++ ከደብረ ምህረት ቆላድባ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ህንፃ አሰሪ ኮሚቴ የተላላፈ ጥብቅ አደራና መልዕክት  ++++++ ችላ ሊባል የማይገባዉ፤ ግዴታችንን የምንወጣበት ስለሆነ በትኩረት አ...
24/05/2024

+++ ከደብረ ምህረት ቆላድባ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ህንፃ አሰሪ ኮሚቴ የተላላፈ ጥብቅ አደራና መልዕክት +++

+++ ችላ ሊባል የማይገባዉ፤ ግዴታችንን የምንወጣበት ስለሆነ በትኩረት አንብበን እንተግብረዉ +++

+ የቤተክርስቲያናችን ግንባታ በእናንተ በልጆቹ ርብርብ ስላቭ/ሶሌታ መሙላት ጀምረናል። ይሁን እንጂ የገንዘብ እጥረት እየገጠመን በመሆኑ ማተሪያል ማቅረብ አለመቻል ብቻ ሳይሆን በብድር እና በትዉስት ያመጣነዉን ብረትም መመለስ አልቻልንም ሰራተኛም ልንበትን ነዉ።
+*+ በመሆኑም ከእርስዎ የሚጠበቅ ሃላፊነት ፦
1. እርስዎ የአቅምዎን ከበረከት እንዲሳተፉ
2. በዳታ/ኢንተርኔት መዘጋት እንዲሁም ከመረጃ እጦት የተነሳ ከብዙዎች መድረስ እንዲሁም መገናኘት አልቻልንም። በመሆኑም ቢያንስ ከ30 እስከ 50 ሰዉ ሃገር ዉስጥም ከሃገር ዉጭም ለሚኖሩ ቤተሰብዎ ፤ ጓደኛና ወዳጅዎ እርስዎ ለሚያዉቋቸዉ "" የቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን እየተሰራ ለመሆኑ መረጃዉ አለህ ወይ? እንግዲያዉ በገንዘብ እጥረት ስራዉ ሊቆም ስለሆነ የበኩልህን አድርግ"" በማለት መልዕክቱን እንዲያደርሱ
3. መልዕክቱን ካደረሱ በኋላ መልዕክቱ የደረሳቸውን ስምና ስልክ መልሰዉ ለእኛ ቢልኩልን ምክንያቱም እኛም እንድናስታዉሳቸዉ እንድንጠይቃቸዉ
ለበለጠ መረጃ
0918148149 ቀሲስ ያለምብርሃን - የህንፃ አሰሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ
0918037611 ቀሲስ ወልዱ አይቶ - ም/ሰብሳቢና ህዝብ ግንኙነት
ደዉለዉ መረጃ ማግኘት ይችላሉ
ከህንፃ አሰሪ ኮሚቴው

#& # በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ የምትኖሩ የቅዱስ ሚካኤል ወዳጆች ስለ ቅዱስ ሚካኤል እንላለን!
- ግንባታዉ ከበረከቱ ለመሳተፍ /ገቢ ለማድረግ/ አካዉንቱን እነሆ
* የአካዉንቱ ስም ➨ "ደብረ ምህረት ቆላድባ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ህንፃ አሰሪ" የሚል ሲሆን
* አካዉንት ቁጥር
# ንግድ ባንክ ➵ 1000401935472
# አቢሲኒያ ባንክ ➵ 77566678
# አባይ ባንክ ➵ 4041117567925017
# አማራ ባንክ ➵ 9900009052497
# አዋሽ ባንክ ➵ 013521097196700

የአለም መጨረሻ ምልክቱ ምንድን ነው?የአብይ ፆም አምስተኛ ሳምንት ደብረ ዘይትመድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ ሆኖ ስለ ዳግም ምፅአት ያስተማረበት.................
07/04/2024

የአለም መጨረሻ ምልክቱ ምንድን ነው?
የአብይ ፆም አምስተኛ ሳምንት ደብረ ዘይት
መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በደብረ ዘይት ተራራ ላይ ሆኖ ስለ ዳግም ምፅአት ያስተማረበት..............................
የአለም መጨረሻ ምልክቱ ምንድን ነው?
ይህን ሁሉ ታያላችሁን እውነት እላችኋለሁ፥ ድንጋይ በድንጋይ ላይ ሳይፈርስ በዚህ አይቀርም አላቸው።
እርሱም በደብረ ዘይት ተቀምጦ ሳለ፥ ደቀ መዛሙርቱ ለብቻቸው ወደ እርሱ ቀርበው። ንገረን፥ ይህ መቼ ይሆናል? የመምጣትህና የዓለም መጨረሻ ምልክቱስ ምንድር ነው? አሉት።
ኢየሱስም መልሶ እንዲህ አላቸው። ማንም እንዳያስታችሁ ተጠንቀቁ።
ብዙዎች። እኔ ክርስቶስ ነኝ እያሉ በስሜ ይመጣሉና፤ ብዙዎችንም ያስታሉ።
ጦርንም የጦርንም ወሬ ትሰሙ ዘንድ አላችሁ፤ ይህ ሊሆን ግድ ነውና ተጠበቁ፥ አትደንግጡ፤ ዳሩ ግን መጨረሻው ገና ነው።
ሕዝብ በሕዝብ ላይ መንግሥትም በመንግሥት ላይ ይነሣልና፥ ራብም ቸነፈርም የምድርም መናወጥ በልዩ ልዩ ስፍራ ይሆናል፤
እነዚህም ሁሉ የምጥ ጣር መጀመሪያ ናቸው።
፤ በዚያን ጊዜ ለመከራ አሳልፈው ይሰጡአችኋል ይገድሉአችሁማል፥ ስለ ስሜም በአሕዛብ ሁሉ የተጠላችሁ ትሆናላችሁ።
፤ በዚያን ጊዜም ብዙዎች ይሰናከላሉ እርስ በርሳቸውም አሳልፈው ይሰጣጣሉ እርስ በርሳቸውም ይጣላሉ፤
፤ ብዙ ሐሰተኞች ነቢያትም ይነሣሉ ብዙዎችንም ያስታሉ፤
፤ ከዓመፃም ብዛት የተነሣ የብዙ ሰዎች ፍቅር ትቀዘቅዛለች።
፤ እስከ መጨረሻ የሚጸና ግን እርሱ ይድናል።
፤ ለአሕዛብም ሁሉ ምስክር እንዲሆን ይህ የመንግሥት ወንጌል በዓለም ሁሉ ይሰበካል፥ በዚያን ጊዜም መጨረሻው ይመጣል።
የማቴዎስ ወንጌል ምዕ. 24 ቁ1-14

ምኩራብ_የዐቢይ_ጾም_ሦስተኛው ሳምንትሶስተኛው_ሰንበት ምኩራብ_ተብሎ የተሰየመበትምክንያት በዚሁ ዕለት የሚዘመረው ጾመ ድጓ ከዋዜማው ጀምሮ እስከ ሰላሙ ድረስ በዕለተ ሰንበት "ቦአ ኢየሱስ ምኩ...
24/03/2024

ምኩራብ_የዐቢይ_ጾም_ሦስተኛው ሳምንት
ሶስተኛው_ሰንበት ምኩራብ_ተብሎ የተሰየመበት
ምክንያት በዚሁ ዕለት የሚዘመረው ጾመ ድጓ ከዋዜማው ጀምሮ እስከ ሰላሙ ድረስ በዕለተ ሰንበት "ቦአ ኢየሱስ ምኩራበ አይሁድ'
ምኩራብ ማለትም ቀጥተኛ ፍችው፦ ኮረብታ፣ ተራራ የሚያኸል ታላቅ ሕንጻ ማለት ነው፡፡ ከዚህም የተነሣ የአይሁድ ቤተ ጸሎት ወይም ቤተመቅደስ ማለት ይሆናል፡፡ ዐቢይ ፍሬ ቃሉ ግን ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ድውያነ ሥጋን በትምህርቱ፣ ድውያነ ነፍስን በታምራቱ ሲፈውስ በምኩራብ እየተገኘ የፈጸመውን የማዳን ሥራ በኀሊና እያሳሰበ የሚያስተምር ሦስተኛ ሳምንት ነው፡፡ ዮሐንስ 2፥12
ኢየሱስ_በሰንበት ቀን ወደ አይሁድ ምኩራብ ገባ! " እያለ ኢየሱስ በአይሁድ ምኩራብ ማስተማሩን እየጠቃቀሰና እያነሣሣ ስለሚዘምር ይህን ሰንበት ለዚህ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምኩራብ እየገባ ለማስተማሩና በምኩራብ የሚሸጡ የሚለውጡ ነጋዴዎችን ለማስወጣቱ ቤተ መቅደሱን ለማስከበሩ መታሰቢያ ሆኖ ስለተሰጠ ነው፡፡ የዚህም በዓል ታሪክ ዝርዝር ሁኔታው በማቴዎስ 21፥12-13 ተጠቅሷል፡፡

ጨርሳችሁ አምብቡት "ቢልጌትስ በሐብት የሚበልጠኝ አንድ ጥቁር ብቻ ነው" አለየአለማችን ቀዳሚ ባለጠጋ በአንድ ኢንተርቪው እንዲህ ተጠየቀ ከአንተ የሚበልጥ ባለጠጋ ማን ነው ?ከአንተ ሚበልጥህ ...
21/03/2024

ጨርሳችሁ አምብቡት

"ቢልጌትስ በሐብት የሚበልጠኝ አንድ ጥቁር ብቻ ነው" አለ

የአለማችን ቀዳሚ ባለጠጋ በአንድ ኢንተርቪው እንዲህ ተጠየቀ ከአንተ የሚበልጥ ባለጠጋ ማን ነው ?
ከአንተ ሚበልጥህ ባለጠጋ አለ ?
‹‹አዎ የሚበልጠኝ ሰው አለ፡፡ የሚበልጠኝ አንድ ሰው ብቻ ነው፡፡ ከብዙ ዓመት በፊት ወደ ኒውዮርክ መሄድ ነበረብኝ፡፡ ወደ ኒውዮርክ ለመሄድ አየር መንገድ ላይ ሳለሁ የተለያዩ ጋዜጦችን የጋዜጣ አዟሪዎች እጅ ላይ አየሁ፡፡ ካየኋቸው ጋዜጦች መካከል አንዱን ወደድኩት ለመግዛት አስቤ ኪሴ ስገባ ዝርዝር ስላጣሁ ሳልገዛው መልሼ ተውኩት፡፡
በድንገትም አንድ ጥቁር ጋዜጣ አዟሪ ልጅ መጣና ጋዜጣውን ሰጠኝ፡፡ ዝርዝር የለኝም አልወስደውም አልኩት እርሱም ችግር የለውም በነጻ ውሰደው አለኝና በነጻ ሰጠኝ፡፡
ከሦስት ወር በኋላ ተመልሼ በዚያው አየር መንገድ ማለፍ ነበረብኝና በዚያ አየር መንገድ ሳልፍ አሁንም አጋጣሚ ሆነና ያንን ጋዜጣ አዟሪ ጥቁር ልጅ አገኘሁት፡፡ አሁንም በነፃ ጋዜጣ ሰጠኝ፡፡ እኔም በነፃ አልቀበልህም አልኩት እርሱም ግድየለም ከትርፌ ላይ እቀንሳለሁ ውሰድ አለኝና በነጻ ሰጠኝ፡፡
ከ19 አመትም በኋላ ባለጠጋ ከሆንኩ በኋላ ያንን ልጅ ፈልጌ ለማግኘት ወሰንኩና ፈለኩት ከአንድ ወር ተኩል ፍለጋም በኋላ አገኘሁት፡፡ ከዚያም አወቅከኝ ብዬ ጠየኩት ፡፡ አዎ አውቅሃለሁ ዝነኛው ቢልጌት አይደለህም አለኝ፡፡ ከብዙ አመት በፊት ሁለት ጊዜ ጋዜጣ በነጻ ሰጥተኸኛል፡፡ ያንን ውለታህን አካክሼ መመለስ እፈልጋለሁና የፈለከውን የትኛውንም ነገር እሰጥሃለሁ ጠይቀኝ አልኩት፡፡
ያም ጥቁር ሰው በምንም መካካሻ ልትሰጠኝ አትችልም አለኝ
እኔም ለምን አልኩት
እኔ የሰጠሁህ ደሃ በነበርኩ ጊዜ ከድህነቴ ነው፡፡ አንተ ግን ልትሰጠኝ የመጣኸው ባለጠጋ በሆንክ ጊዜ ነው፡፡ እነዚህን ሁለቱን እንዴት አካክሰህ ልትሰጠኝ ትችላለህ፡፡
ቢልጌትም ያጥቁር ወጣት በርግጥም ከእኔ የሚበልጥ ባለጠጋ ነው፡፡
ለመስጠት ባለጠጋ መሆንህን ወይም ባለጠጋ እስክትሆን ድረስ አትጠብቅ ፡፡ መስጠት የልብ ጉዳይ ነው እንጂ የአቅም ጉዳይ አይደለም፡፡

©ዋልተ_ንጉስ_ዘሸገር

ቅድስት አርሴማ ሆይ ሰማዕት እናቴ፡በፍቅር በረከት ግቢና ከቤቴ፡እኔንም አበርቺኝ ልቁም በሃይማኖቴ፡ሰማእቷ ቅድስት አርሴማ እኛንም ከተጋረጠብን ችግር ፈተና እምንወጣበትን ብርታት ታድለን አማላ...
15/03/2024

ቅድስት አርሴማ ሆይ ሰማዕት እናቴ፡
በፍቅር በረከት ግቢና ከቤቴ፡
እኔንም አበርቺኝ ልቁም በሃይማኖቴ፡
ሰማእቷ ቅድስት አርሴማ እኛንም ከተጋረጠብን ችግር ፈተና እምንወጣበትን ብርታት ታድለን አማላጅነቷ አይለየን

Memory
08/03/2024

Memory

Have  A nice day  😍😍😍😍💞💞💞💞💞💞💞💞 ETHIOPIAN
06/03/2024

Have A nice day 😍😍😍😍💞💞💞💞💞💞💞💞
ETHIOPIAN

ለጤዛ እድማያችን ለትንሿ ዘመን
28/02/2024

ለጤዛ እድማያችን ለትንሿ ዘመን

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when New art and event posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share