
10/02/2025
የእስራኤል ጦር በማዕከላዊ ጋዛ ከሚገኘው ኮሪደር ለቆ እየወጣ ነው ሲል ሀማስ አስታወቀ
የእስራኤል ጦር ናዛሪም እየተባለ ከሚጠራው በማዕከላዊ ጋዛ ከሚገኘው ኮሪደር ለቆ እየወጣ ነው ሲል ሀማስ በዛሬው እለት አስታውቋል።
የእስራኤል ጦር ከቀጣናው መውጣት ሀማስና እስራኤል በደረሱት የመጀመሪያ ምዕራፍ የተኩስ አቁም ስምምነት መሰረት የሚጠበቅ እርምጃ ነው ተብሏል።
ሮይተርስ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የእስራኤል ምንጭን ጠቅሶ እንደዘገበው የእስራኤል ጦር በማዕከላዊ ጋዛ ከነበረው ይዞታ እየወጣ ነው።በቦታው ያለው የእስራኤል ጦር ቁጥር ቀደም ሲል ነበር የቀነሰው።
ዝርዝሩን በተከታዩ ሊንክ ይመልከቱ፤ https://am.al-ain.com/article/israel-arms-withdraw-nazarim-corridor-central-gaza