MFM EGGCHAIN BUSSINES GROUP t.me/nnu1media

የሳውድ እና የፓኪስታን ስምምነት ወታደራዊ ዝግጅት ወይስ ሁለንተናዊ  ትብብር ?ሳውድ አረቢያ እና ፓኪስታን በታሪክ ወሳኝ የተባለውን ስምምነት ተፈራርመዋል።ይህ ስምምነት ወሳኝ የተባለ እስትራ...
18/09/2025

የሳውድ እና የፓኪስታን ስምምነት ወታደራዊ ዝግጅት ወይስ ሁለንተናዊ ትብብር ?

ሳውድ አረቢያ እና ፓኪስታን በታሪክ ወሳኝ የተባለውን ስምምነት ተፈራርመዋል።
ይህ ስምምነት ወሳኝ የተባለ እስትራቴጂካዊ ወታደራዊ ስምምነት ሲሆን በአንድኛቸው ላይ የሚደርስን ማንኛውም ወታደራዊ ጥቃት በሌላኛው ላይ እንደደረስ ይቆጠራል ይላል።

ሪያድ ተገኝተው ስምምነቱን የተፈራረሙት የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ሼህባዝ ሻሪፍ የሪያድ በመከላከያው ዘርፍ ለሙስሊሙ አለም ምሳሌ የሚሆን ስምምነት አድርገናል ብለዋል።
ስምምነቱ በመከላከያ እና በፀጥታ ዙሪያ ሰፊ ትብብርን የሚያካትት ሲሆን ሁለቱ ሀገራት ለውጭ ጥቃቶች በጋራ ምላሽ እንዲሰጡ የሚያስገድዳቸው የጋራ መከላከያ ህግ ያካተተ ነው።

ይህ የጋራ ስምምነት በተለይ እስራኤል በኳታር ላይ በቅርቡ ያደረሰችውን ጥቃት ተከትሎ ክልላዊ ምላሽ ለመስጠት ለሚወሰደው እርምጃ እንደጅማሮ የሚታይ ነው።

እንደ ሳዑዲ አረቢያ እና ፓኪስታን ያሉ ሀገራት ነፃ የጸጥታ ትብብር እንዲፈጥሩ ያነሳሳው በአለም መንግስት እና ሃይሎች በሚሰጠው የደህንነት ዋስትና ላይ የመካከለኛው ምስራቅ መሪዎች ተስፋ መቁረጣቸውን ያሳያል።
የፓኪስታን ጦር የሳዑዲ ጦርን በማሰልጠን ረገድ ትልቅ ሚና የተጫወተ ሲሆን በሳዑዲ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች በተለይም በየመን ውስጥ ንቁ ተሳትፎ አድርጓል።
በአንፃሩ ሳውዲ አረቢያ ፓኪስታንን በብድር እና በፋይናንሺያል ፍላጎቶች ከፍተኛ ድጋፍ ታደርጋለች።
ይህን ስምምነት የሚለየው የረዥም ጊዜ ግንኙነቱን ወደ ተደራጀ እና አስገዳጅ እና ቁርጠኛ ወደሆነ መደበኛ ትብብር የተሸጋገረ መሆኑ ነው።
ሁለቱንም ሀገራት ከህንድ፣ እስራኤል እና ኢራን ሊደርሱ ከሚችሉ ስጋቶች ጋር በስትራቴጂያዊ መንገድ በጋራ ለመከላከልን ያካትታል።
ስምምነቱ በይፋ ቢታወቅም ዝርዝር ድንጋጌዎቹ ግን ለጊዜው በሚስጥር ተይዘዋል።
ስምምነቱ የፓኪስታንን የኒውክሌር አቅምን ይጨምራልን የሚለው ጥያቄ ግልጽ ባይሆንም የኒውክሌር አቅምንም የሚያካትት ከሆነ ክልላዊ አንድምታው ጥልቅ ሊሆን ይችላል።
ይህም በመካከለኛው ምስራቅ እና በደቡብ እስያ ያለውን የሃይል ሚዛኑን ሊቀርጽ ይችላል።
በተለይም የእስራኤልን መስፋፋት ሊቀለብሰው ይችላል።
በአጠቃላይ ስምምነቱ እስራኤል በኳታር ላይ ጥቃት በሰነዘረችበት እና በጋዛ የጀመረችው የዘር ማጥፋት ዘመቻ ከፍተኛ ደረጃ ላይ በደረሰበት ወቅት መደረጉ የመካከለኛው ምስራቅ መሪዎች ትልቅ መልእክት ነው።
ምናልባትም እስራኤል ጥቃት ብታደርስ ተመጣጣኝ ምላሽ ለመስጠት ወይም ለጦርነት ዝግጅትም ሊሆን ይችላል ተብሏል።

በውብሸት ደርብ

ደቡብ አፍሪካ በእስራኤል ላይ አስችኳይ እርምጃ እንዲወሰድ ጠየቀችደቡብ አፍሪካ የተባበሩት መንግሥታት ድረጅት ገለልተኛ አጣሪ ኮሚሽን በጋዛ የዘር ማጥፋት እየተካሄደ መሆኑን እንደማረጋገጡ ሁሉ...
18/09/2025

ደቡብ አፍሪካ በእስራኤል ላይ አስችኳይ እርምጃ እንዲወሰድ ጠየቀች

ደቡብ አፍሪካ የተባበሩት መንግሥታት ድረጅት ገለልተኛ አጣሪ ኮሚሽን በጋዛ የዘር ማጥፋት እየተካሄደ መሆኑን እንደማረጋገጡ ሁሉ በእስራኤል ላይ ሊወሰድ የሚገባው አለም አቀፍ እርምጃ ሊዘገይ አይገባም ብላለች።

ደቡብ አፍሪካ ሁሉም መንግሥታት በዘር ማጥፋት ስምምነት ማዕቀፍ ላይ የተጣለባችውን ግዴታ በአስቸኳይ እንዲወጡ ጥሪ አቅርባለች።
የደቡብ አፍሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እስራኤል የዓለም አቀፉን የጦር ወንጀለኞች ፍርድ ቤት ትዕዛዝ እንድትፈፅም ማስገደድ ይገባል ብሏል።
በተጨማሪም ደቡብ አፍሪካ እስራኤል በጋዛ ላይ የምተፈፅመውን የዘር ማጥፋት ለማስቆም በጋራ መሥራት፣ የዘር ማጥፋት እንዲፈፀም የሚያስችሉ መሳሪያዎችን ማገድ፣ የጋዛ ጦርነት በፍፁም ሕጋዊ አድርጎ አለመቀበል እና የዓለም አቀፍ ሕግ ጥሰቶችን መመርመር እና መቅጣት እንዳለበት ጥሪ አቅርባለች፡፡

የደቡብ አፍሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስተር ዛሬ በሰጠው መግለጫ "የፍልስጤም ህዝብ የመጥፋት ስጋት እየገጠመው መሆኑ ግልጽ እየሆነ መጥቷል ፣ አጠቃላይ የዓለም አቀፍ ሕግ ሥርዓት ባለበት ሁኔታ አደጋ ላይ የወደቀው የፍልስጤም ህዝብ እጣ ፋንታ ብቻ ሳይሆን የፍትሕ መርህ ጭምር ነው" ብሏል።

ደቡብ አፍሪካ በእስራኤል ላይ ያቀረበችው የዘር ማጥፋት ወንጀል ክስ አቅርባ ለዓለም አቀፍ ፍትሕ ከፍተኛ ትግል እያደረገች ትገኛለች።

በመሃመድ ሚፍታህ

የፀጥታው ምክር ቤትን ለማሻሻል ተገደናል - አንቶኒዮ ጉቴረዝየመንግስታቱ ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ የተባበሩት መንግሥታት  ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት እንዲሻሻል አስገዳጅ ሁኔታዎች...
18/09/2025

የፀጥታው ምክር ቤትን ለማሻሻል ተገደናል - አንቶኒዮ ጉቴረዝ

የመንግስታቱ ድርጅት ዋና ጸሐፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት እንዲሻሻል አስገዳጅ ሁኔታዎች ገጥመውናል ብለዋል።

ዋና ፀሐፊው ምክር ቤቱ የመሻሻሉ ጉዳይ ለዘመኑ ትልቅ ትርጉም የሚሰጥ እና አሳማኝ ነው ብለዋል፡፡

የፀጥታው ምክር ቤት አወቃቀር የ1945ቱን እንጂ የዘመናዊውን ዓለም እውነታን የሚያንፀባርቅ አይደለም ያሉት ጉቴረዝ ምክር ቤቱ እስካልተሻሻለ ድረስ የድርጅቱ ቅቡልነት እና ውጤታማነት ጥያቄ ውስጥ ነው ብለዋል።

ሩሲያ ምክር ቤቱ ካልተሻሻለ በስተቀር ምክር ቤቱ አሁን ያለውን ዓለም አቀፍ እውነታ እንደማያንፀባርቅ እና በዛሬው ኢኮኖሚ እና ጂኦፖለቲካ ውስጥ ከፍተኛ ተፅዕኖ ያላቸውን ሀገራት እንደሚያገል ደጋግማ በመግለጽ እንዲሻሻል ጥሪ አቅርባለች።

በዚህም ምክንያት የጸጥታው ምክር ቤት እንዲሻሻል አስገዳጅ ሁኔታዎች ተፈጥረዋል ያሉት አንቶኒዮ ጉቴረዝ ከዘመኑ ጋር በሚሄድ እና አሁን የተፈጠሩት አለም አቀፋዊ እና ቀጣናዊ ችግሮችን መፍታት በሚያስችል ቁመና መደራጀት አለበት ብለዋል።
በመሃመድ ሚፍታህ

13/08/2025
የእስራኤል ጦር በማዕከላዊ ጋዛ ከሚገኘው ኮሪደር ለቆ እየወጣ ነው ሲል ሀማስ አስታወቀየእስራኤል ጦር ናዛሪም እየተባለ ከሚጠራው በማዕከላዊ ጋዛ ከሚገኘው ኮሪደር ለቆ እየወጣ ነው ሲል ሀማስ ...
10/02/2025

የእስራኤል ጦር በማዕከላዊ ጋዛ ከሚገኘው ኮሪደር ለቆ እየወጣ ነው ሲል ሀማስ አስታወቀ

የእስራኤል ጦር ናዛሪም እየተባለ ከሚጠራው በማዕከላዊ ጋዛ ከሚገኘው ኮሪደር ለቆ እየወጣ ነው ሲል ሀማስ በዛሬው እለት አስታውቋል።

የእስራኤል ጦር ከቀጣናው መውጣት ሀማስና እስራኤል በደረሱት የመጀመሪያ ምዕራፍ የተኩስ አቁም ስምምነት መሰረት የሚጠበቅ እርምጃ ነው ተብሏል።

ሮይተርስ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የእስራኤል ምንጭን ጠቅሶ እንደዘገበው የእስራኤል ጦር በማዕከላዊ ጋዛ ከነበረው ይዞታ እየወጣ ነው።በቦታው ያለው የእስራኤል ጦር ቁጥር ቀደም ሲል ነበር የቀነሰው።

ዝርዝሩን በተከታዩ ሊንክ ይመልከቱ፤ https://am.al-ain.com/article/israel-arms-withdraw-nazarim-corridor-central-gaza

06/02/2025

Address

Addis Ababa
KELIFFABUSSINESCENTER

Telephone

+19726936980

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when MFM posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to MFM:

Share

muslim world news-amharic

the true voice of muslim