Ethiopia 24

Ethiopia 24 Ethiopia 24 is a private media outlet and Public Relations Center established in 2011. Its major obj

በተለያዩ የትምህርት መስኮች የሰለጠኑና ወደ መምህርነት ሙያ መግባት ለሚፈልጉ ምሩቃን አዲስ የአሠራር ስርዓት ገቢራዊ ሊሆን ነው። እነዚህ ባለሙያዎች ተጨማሪ ስልጠና ወስደው መምህር መሆን የሚ...
07/06/2025

በተለያዩ የትምህርት መስኮች የሰለጠኑና ወደ መምህርነት ሙያ መግባት ለሚፈልጉ ምሩቃን አዲስ የአሠራር ስርዓት ገቢራዊ ሊሆን ነው።

እነዚህ ባለሙያዎች ተጨማሪ ስልጠና ወስደው መምህር መሆን የሚችሉበት የሰልጠና ማዕቀፍ ማዘጋጀቱን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።

ይህም በሀገሪቱ የሚታየውን የመምህራን እጥረት ለመቅረፍ እንደሚያስችል በሚኒስቴሩ የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማት መሪ ሥራ አስፈፃሚ ሙሉቀን ንጋቱ (ዶ/ር) ገልፀዋል።

በዚህም መምህር ሆነው መስራት ለሚፈልጉ ምሩቃን በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ገብተው ተጨማሪ የመምህርነት ሙያ፣ የማስተማር ዘዴ፣ የትምህርት ቴክኖሎጂ እና የጋራ ኮርሶችን ስልጠና እንዲወስዱ ይደረጋል ብለዋል።

በተለያዩ የትምህርት መስኮች የተመረቁ ባለሙያዎች፥ ተጨማሪ የማስተማር ሙያ ስልጠና ቢሰጣቸው ወደ ሙያው የመግባት ፍላጎት እንዳላቸው በተደረገ የዳሰሳ ጥናት ለማረጋገጥ መቻሉን በሚኒስቴሩ የመምህራንና የትምህርት አመራር ልማት ዴስክ ኃላፊ አሰገድ ምሬሳ ገልፀዋል።

አዲሱን የስልጠና ማዕቀፍ ወደ ሥራ ለማስገባት ከአሰልጣኝ የትምህርት ተቋማት፣ ከክልል ትምህርት ቢሮዎች እና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር የምክክር መድረክ እየተካሔደ ይገኛል።

አዲስ የተዘጋጀው አማራጭ የመምህራን ማሰልጠኛ ማዕቀፍ ከቀጣይ ዓመት ጀሞሮ ገቢራዊ ይሆናል ተብሏል።

ፌስቡክ፡- https://m.facebook.com/ethiopia24
ቴሌግራም፦ https://t.me/ethiopia_24

   ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አዲስ በሚከፍተው የቡታጅራ ካምፓስ ከ2018 የትምህርት ዘመን ጀምሮ ተማሪዎችን መቀበል ይጀምራል፡፡   የቡታጅራው ካምፓስ ከዓመታት በፊት እንዲሠራ ቃል የተገባና የወል...
18/05/2025

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አዲስ በሚከፍተው የቡታጅራ ካምፓስ ከ2018 የትምህርት ዘመን ጀምሮ ተማሪዎችን መቀበል ይጀምራል፡፡

የቡታጅራው ካምፓስ ከዓመታት በፊት እንዲሠራ ቃል የተገባና የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲን ተደራሽነት ለማስፋትና የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ ለማድረግ የተጀመረ መሆኑን የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ሀብቴ ዱላ (ዶ/ር) ለኢፕድ ተናግረዋል፡፡

ካምፓሱ ከ2018 የትምህርት ዘመን ጀምሮ ተማሪዎች መቀበል እንዲጀምር ለማስቻል የመምህራን መኖሪያ፣ የመማሪያ ክፍሎች፣ የተማሪዎች መመገቢያ፣ የተማሪዎች መኖሪያ እንዲሁም የቢሮዎች ግንባታ መጠናቀቁን ገልፀዋል።

ኮምፒውተሮች፣ ወንበሮች እና ሌሎች በግዢ የሚሟሉ ግብዓቶችን በቀሪው ጊዜ ለማሟላት እየተሠራ መሆኑን የጠቆሙት ኃላፊው፤ ዩኒቨርሲቲው ከሚሰጣቸው የትምህርት ፕሮግራሞች የተወሰኑት ወደ አዲሱ ቡታጅራ ካምፓስ ይሔዳሉ ብለዋል፡፡

የሦስተኛ ትውልድ ዩኒቨርሲቲ የሆነው ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ፤ ከ2004 ዓ.ም ጀምሮ ተማሪዎችን ተቀብሎ እያስተማረ ይገኛል፡፡ #ኢፕድ

ፌስቡክ፡- https://m.facebook.com/ethiopia24
ቴሌግራም፦ https://t.me/ethiopia_24

ጤና ሚኒስቴር ምን አለ ?   " የጤና ሞያ የሥራ ማቆም አድማ ከማይደረጉባቸው የሥራ ዘርፎች መካከል አንዱ መሆኑ በግልጽ ተደንግጓል " - ጤና ሚኒስቴርዛሬ ምሽት ጤና ሚኒስቴር በወቅታዊ የጤ...
15/05/2025

ጤና ሚኒስቴር ምን አለ ? " የጤና ሞያ የሥራ ማቆም አድማ ከማይደረጉባቸው የሥራ ዘርፎች መካከል አንዱ መሆኑ በግልጽ ተደንግጓል " - ጤና ሚኒስቴር

ዛሬ ምሽት ጤና ሚኒስቴር በወቅታዊ የጤና አገልግሎት ዙሪያ መግለጫ አውጥቷል።

ሚኒስቴሩ " መቼምና በምንም ሁኔታ መቋረጥ ከሌለባቸው ማኅበራዊ አገልግሎቶች አንዱ የጤና አገልግሎት ነው " ያለ ሲሆን " ዛሬን ጨምሮ ባለፉት ቀናት በመላ ሀገራችን በሚገኙ የጤና ተቋማት እንደ ወትሮው ሁሉ መደበኛ የጤና አገልግሎቶች ለማኅበረሰባችን ያለምንም መቆራረጥና መስተጓጎል እየተሰጡ ይገኛሉ " ብሏል።

" ይሄንን የተረዳው የጤና ባለሞያ በማኅበራዊ ሚዲያ በሚሠራጩ የተሳሳቱ መረጃዎች ጫና ሳይገፋ የገባውን የሞያ ቃል ኪዳን እና መሐላ ጠብቆ ማኅበረሰቡን እያገለገለ በመሆኑ ምስጋና ይገባዋል " ሲል ገልጿል።

ሚኒስቴሩ " በጥቂት የማስተማሪያ የጤና ኮሌጆች/ተቋማት በመደበኛ የሥራ ገበታቸው ላይ ያልተገኙ የተወሰኑ ባለሞያዎች እንዳሉ መረጃዎች ደርሰውናል " ያለ ሲሆን " ከእነዚህ የጤና ባለሞያዎች መካከል ብዙዎቹ በሐሰተኛ መረጃ የተወናበዱ ሲሆኑ ጥቂቶቹ ደግሞ ጥፋትን ዓላማቸው ያደረጉ ናቸው " ብሏል።

" ድርጊቱ የራስን ቤተሰብ፣ ዘመድ፣ ወገን እና መላውን ማኅበረሰብ ከመጉዳት ባለፈ ከሞያ ሥነ ምግባር፣ ከሰብአዊነት አኳያ ተቀባይነት የሌለው ተግባር ነው " ሲል ገልጿል።

" ከሕግ አኳያም የጤና ሞያ የሥራ ማቆም አድማ ከማይደረጉባቸው የሥራ ዘርፎች መካከል አንዱ መሆኑ በግልጽ ተደንግጓል። የጤና ባለሞያዎች ጥያቄ እንኳን ቢኖራቸው በሥራ ገበታቸው ተገኝተው መደበኛ ሥራቸውን እያከናወኑ ጉዳያቸውን ለሚመለከተው አካል ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል " ብሏል።

" እነዚህ የጤና ባለሞያዎች ወደ ሥራ ገበታቸው ተመልሰው ማኅበረሰባቸውን እንዲያገለግሉ በየተቋማቸው ጥሪ ተደርጓል " ያለው ጤና ሚኒስቴር " መንግሥት የጤና ባለሞያውን ዘላቂ ተጠቃሚነት ባረጋገጠ መልኩ በጥናት ላይ የተመሠረተ መፍትሔ ለመስጠት ቀደም ብሎ የጤና አገልግሎት አስተዳደርና ቁጥጥር አዋጅ 1362 /2017 አጸድቆ ደንብና መመሪያዎችን በማውጣት ትኩረት ሰጥቶ እየሠራ ይገኛል " ሲል ገልጿል።

" በጎ ኅሊና ያላቸው የጤና ባለሞያዎች ይህንን በመገንዘብ ሥራቸውን በአግባቡ እንዲያከናውኑ ጥሪ እናቀርባለን " ብሏል ሚኒስቴሩ።

" በሌላ በኩል ኅብረተሰቡ በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች በሚሠራጩ የሐሰት መረጃዎች ሳይረበሽ የሚፈልገውን የጤና አገልግሎት በተለመደው መልኩ በጤና ተቋማት ማግኘት እንደሚችል እናሳውቃለን " ብሏል።

" መንግሥት በሆደ ሰፊነት ችግሩን ለመፍታት ያሳየውን ትዕግሥት ወደጎን በመተው በሥራ ገበታቸው ላይ ባልተገኙ እንዲሁም በጤና ተቋሙም ሆነ ከጤና ተቋሙ ውጭ ሆነው ሁከትና ብጥብጥ በሚፈጥሩት ላይ አስፈላጊ የሆነ ሕጋዊ እርምጃ የሚወሰድ መሆኑን ቀድመን እናሳውቃለን " ሲል አስጠንቅቋል።

ከሰሞኑን በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች የጤና ባለሙያዎች " መኖር ከብዶናል የጤና ስርዓቱ መለወጥ አለበት ለዚህም ያቀረብናቸው ጥያቄዎች አሉ የጊዜ ገደብ ብናስቀምጥም ምላሽ አልተሰጣቸውም " በማለት ከፊል የስራ ማቆም አድማ እያደረጉ ይገኛሉ።

ከጤና ባለሙያዎቹ እንቅስቃሴ ጋር በተያያዘ ለእስር እየተዳረጉ በርካታ ባለሙያዎች እንዳሉ በርካቶችም ማስፈራሪያና ወከባ እየደረሰባቸው እንደሆነ የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ማኅበር አሳውቆ እንደነበር አይዘነጋም።

ፌስቡክ፡- https://m.facebook.com/ethiopia24
ቴሌግራም፦ https://t.me/ethiopia_24

   በሰኔ 2017 ዓ.ም የሚሰጠው የመውጫ ፈተና መመዝገቢያ ጊዜ እስከ ግንቦት 14/2017 ዓ.ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ብቻ መራዘሙን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡እስካሁን ያልተመዘገባችሁ የ...
14/05/2025

በሰኔ 2017 ዓ.ም የሚሰጠው የመውጫ ፈተና መመዝገቢያ ጊዜ እስከ ግንቦት 14/2017 ዓ.ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ብቻ መራዘሙን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡

እስካሁን ያልተመዘገባችሁ የድጋሚ ተፈታኞች (Re-sitters) ከዚህ በፊት ለምዝገባ በተከፈተው የመመዝገቢያ ፕላትፎርም (https://exam.ethernet.edu.et) ገብታችሁ ምዝገባችሁን እንድታጠናቅቁ ተብሏል።

ለመጀመሪያ ጊዜ ለመውጫ ፈተና የምትቀመጡ ተፈታኞች በተቋሞቻችሁ በኩል መመዝገባችሁን እንድታረጋግጡ ሚኒስቴሩ አሳስቧል።

የመውጫ ፈተናው ከሰኔ 2-10/2017 ዓ.ም የሚሰጥ መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር አረጋግጧል።

ለፈተናው የምታመለክቱ አመልካቾች ለመመዝገብ የብሔራዊ መታወቂያ ካርድ (ፋይዳ) ሊኖራችሁ ይገባል፡፡

ለግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማትና ለቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት መረጃ ከላይ በፎቶ ተያይዟል

ፌስቡክ፡- https://m.facebook.com/ethiopia24
ቴሌግራም፦ https://t.me/ethiopia_24

የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) አዳዲስ የዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢዎች ምደባ እየሰጡ ነው። የገቢዎች ሚኒስትር ዴኤታ የሆኑት አቶ አብዱርህማን ኢድጣሂር ከሚያዝያ 22...
13/05/2025

የትምህርት ሚኒስትር ብርሃኑ ነጋ (ፕሮፌሰር) አዳዲስ የዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢዎች ምደባ እየሰጡ ነው።

የገቢዎች ሚኒስትር ዴኤታ የሆኑት አቶ አብዱርህማን ኢድጣሂር ከሚያዝያ 22/2017 ዓ.ም ጀምሮ የወለጋ ዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ሆነው እንዲሠሩ ተመድበዋል።

ወለጋ ዩኒቨርሲቲ ከሚያዝያ 2014 ዓ.ም እስከ ሚያዝያ 2017 ዓ.ም ድረስ ለሦስት ተከታታይ ዓመታት የዩኒቨርሲቲው ሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ሆነው ላገለገሉት የማዕድን ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሚሊዮን ማቴዎስ አሸኛኘት አድርጓል።

በተመሳሳይ የፍትህ ሚኒስትር ዴኤታ የሆኑት አቶ በላይሁን ይርጋ ከሚያዝያ 22/2017 ዓ.ም ጀምሮ የደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ ሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ ሆነው እንዲሠሩ ተመድበዋል።

ፌስቡክ፡- https://m.facebook.com/ethiopia24
ቴሌግራም፦ https://t.me/ethiopia_24

የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ተደረገ።  የ2017 ትምህርት ዘመን ኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ / የ12ኛ ክፍል ፈተና የሚሰጥበት መርሃ ግብር ይፋ ተደርጓል...
09/05/2025

የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ተደረገ። የ2017 ትምህርት ዘመን ኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ / የ12ኛ ክፍል ፈተና የሚሰጥበት መርሃ ግብር ይፋ ተደርጓል።

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ይፋ ባደረገው መርሃ ግብር ፈተናው ከሰኔ 23/2017 ዓ/ም ጀምሮ እስከ ሐምሌ 8/2017 ዓ/ም የሚሰጥ ይሆናል።

በወረቀት የሚፈተኑ የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ሰኔ 21 እና 22/2017 ዓ/ም እንዲሁም የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ሰኔ 29 እና 30/2017 ዓ/ም ወደሚፈተኑበት ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ ይሆናል፡፡

በበይነ መረብ የሚፈተኑ ተፈታኞች ከመኖሪያ ቤታቸው በየቀኑ እየተመላለሱ በተመደቡበት መፈተኛ ማዕከል የሚፈተኑ ሲሆን ዝርዝር መርሃ ግብሩ ከላይ ተያይዟል።

የፈተናው ይዘት በተማሪው መጽሐፍ ላይ ያተኮረ በመሆኑ እያንዳንዱ ተፈታኝ በትምህርት ቤቱ የተማረበትን የተማሪ መጽሐፍ መሠረት አድርጎ ተገቢ የሆኑ አጋዥ መጽሐፍትን ለበለጠ እውቀትና መረዳት በመጠቀም እንዲዘጋጅ አገልግሎቱ ጥሪውን አስተላልፏል።

በፈተና ወቅት ለፈተና ስርቆትና ኩረጃ የሚውሉ ማንኛውንም ቁሳቁሶች መጠቀም የተከለከለ ነው ተብሏል።

መረጃው ከትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የተላከ ነው።

ፌስቡክ፡- https://m.facebook.com/ethiopia24
ቴሌግራም፦ https://t.me/ethiopia_24

የጤና ባለሙያዎች የብቃት ምዘና ፈተና ውጤት ይፋ ሆኗል። ተመዛኞች ከሚያዝያ 25/2017 ዓ.ም ጀምሮ http://hple.moh.gov.et/hple ላይ በመግባት ሙሉ ስም እና የፈተና መለያ ቁ...
06/05/2025

የጤና ባለሙያዎች የብቃት ምዘና ፈተና ውጤት ይፋ ሆኗል።

ተመዛኞች ከሚያዝያ 25/2017 ዓ.ም ጀምሮ http://hple.moh.gov.et/hple ላይ በመግባት ሙሉ ስም እና የፈተና መለያ ቁጥራችሁን በማስገባት የፈተና ውጤታችሁን መመልከት ትችላላችሁ ተብሏል።

በውጤታችሁ ላይ ቅሬታ ያላችሁ ተመዛኞች ውጤት ከዛሬ ጀምሮ ባሉት 10 (አስር) ተከታታይ የሥራ ቀናት በስልክ ቁጥር 0115186275 / 0115186276 ላይ በመደወል ቅሬታችሁን ማቅረብ የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል።

ፈተናውን ያለፋችሁ ተመዛኞች ከሚያዝያ 29/2017 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ክልል ተቆጣጣሪ አካላት በመሔድ የሚጠበቅባችሁን ቅድመ ሁኔታዎች በሟሟላት የሙያ ፈቃድ መውሰድ የምትችላላችሁ ተብሏል።

የስም ፊደል ግድፈት ያለባችሁ ተመዛኞች ሙሉ በሙሉ የስም ትርጉም ለውጥ ከሌለው በስተቀር ከዲግሪያችሁ ጋር በማመሳከር የምትስተናገዱ መሆኑ ተገልጿል።

ፌስቡክ፡- https://m.facebook.com/ethiopia24
ቴሌግራም፦ https://t.me/ethiopia_24

የፋይዳ መታወቂያ አውጥተዋል?   በሰኔ 2017 ዓ.ም የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና ለመውሰድ ተፈታኞች የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) ሊያወጡ እንደሚገባ ትምህርት ሚኒስቴር መግለፁ ይታወቃል።...
04/05/2025

የፋይዳ መታወቂያ አውጥተዋል? በሰኔ 2017 ዓ.ም የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና ለመውሰድ ተፈታኞች የብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) ሊያወጡ እንደሚገባ ትምህርት ሚኒስቴር መግለፁ ይታወቃል።

የመንግሥት እና የግል ዩኒቨርሲቲዎች የፋይዳ መታወቂያ ምዝገባ በማድረግ ላይ ይገኛሉ።

የመውጫ ፈተናውን ለመውሰድ ምዝገባውን በጊዜ በማድረግ የፋይዳ መታወቂያዎን ይያዙ።

ምዝገባዎን በአገልግሎት ማዕከሎቻችን በነጻ አካሄደው ቴሌብር ሱፐርአፕ
👉 http://bit.ly/42IOUGn
telebirr SuperApp ‘’NID (Fayda) Printing’’ መተግበሪያ የካርድ ኅትመትዎን በቀላሉ ይዘዙ፡፡

- እንደምርጫዎ በ6 የሥራ ሰዓታት፣ በ2 ቀናት ወይም በ7 ቀናት ውስጥ በመረጡት የመረከቢያ ቀንና ቦታ ካርድዎን ይውሰዱ!

በአቅራቢያዎ የሚገኙ የመረከቢያ ቦታዎችን ለመመልከት ቴሌብር ሱፐርአፕ ➡️ http://bit.ly/42IOUGn telebirr SuperApp መተግበሪያን ይጠቀሙ።

በተከታታይ ሦስት ጊዜ በተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ከ25 በመቶ በታች ውጤት በሚያስመዘግቡ ዩኒቨርሲቲዎች ላይ እርምጃ እንደሚመወሰድ ተገለፀ።ይህ የተገለጸው የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አ...
03/05/2025

በተከታታይ ሦስት ጊዜ በተመራቂ ተማሪዎች የመውጫ ፈተና ከ25 በመቶ በታች ውጤት በሚያስመዘግቡ ዩኒቨርሲቲዎች ላይ እርምጃ እንደሚመወሰድ ተገለፀ።

ይህ የተገለጸው የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች ከቡሌሆራ ዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ አባላት ጋር በተወያዩበት ወቅት ነው።

የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በተከታታይ ሦስት ጊዜ በተመራቂ ተማሪዎች መውጫ ፈተና ውጤት ከ25 በመቶ በታች የሚያስመዘግቡ ዩኒቨርሲቲዎች በትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን በኩል እርምጃ እንደሚወሰድ አመላክተዋል።

የዩኒቨርሲቲ አመራሮች በብቃትና በችሎታ እንዲመደቡ እየተደረገ መሆኑን አንስተው " አሰራራቸውን ለማዘመንም የዩኒቨርሲቲ አመራሮች ማሰልጠኛ ተቋም ለማቋቋሞ እየተሠራ ነው " ብለዋል።

ፌስቡክ፡- https://m.facebook.com/ethiopia24
ቴሌግራም፦ https://t.me/ethiopia_24

ትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት መውጫ ፈተና ያላለፉ ተማሪዎች የምስክር ወረቀት ቅፅ አዘጋጅቶ ለሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መላኩ ይታወቃል።የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪ...
29/04/2025

ትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት መውጫ ፈተና ያላለፉ ተማሪዎች የምስክር ወረቀት ቅፅ አዘጋጅቶ ለሁሉም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት መላኩ ይታወቃል።

የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ህብረት ኃላፊዎች ከትምህርት ሚኒስትር ዴኤታ ኮራ ጡሸኔ ጋር በመውጫ ፈተና እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ተወያይቷል።

በዚህም ልኩ ሰርተፊኬቱ የሚሰጠው የመውጫ ፈተና ወስደው የማለፍያ ነጥብ ላላመጡ ተማሪዎች ብቻ መሆኑን ገልፀዋል።

የመውጫ ፈተናውን ያለፉ ተማሪዎች አዲሱ ሰርተፊኬት የማይመለከታቸው ሲሆን፤ በፊት ይሰጥ በነበረው ፎርማት እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

ከዘንድሮ ጀምሮ ማለትም በሰኔ 2017 ዓ.ም ከሚሰጠው የመውጫ ፈተና አስቀድሞ ሁለም ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት #ሞዴል የመውጫ ፈተና በአስገዳጅነት ለተማሪዎቻቸው እንዲሰጡ ይደረጋል ብለዋል።

ፌስቡክ፡- https://m.facebook.com/ethiopia24
ቴሌግራም፦ https://t.me/ethiopia_24

ከ2018 ዓ.ም ጀምሮ ተማሪዎች ሞባይል ስልክ ይዘው ወደ ትምህርት ቤት እንዳይሔዱ የሚያደርግ ሕግ ሊተገብር መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር መግለፁ ይታወቃል፡፡ሕጉን ወደ መሬት ለማውረድ ትምህርት ...
28/04/2025

ከ2018 ዓ.ም ጀምሮ ተማሪዎች ሞባይል ስልክ ይዘው ወደ ትምህርት ቤት እንዳይሔዱ የሚያደርግ ሕግ ሊተገብር መሆኑን ትምህርት ሚኒስቴር መግለፁ ይታወቃል፡፡

ሕጉን ወደ መሬት ለማውረድ ትምህርት ሚኒስቴር ከክልል ትምህርት ቢሮ ኃላፊዎች እና ከዘርፉ አመራሮች ጋር ውይይት ለማድረግ ዕቅድ ይዟል፡፡

በሕጉ ዙሪያ ሸገር ኤፍኤም ያነጋገራቸው መምህራን ውሳኔው ጥሩ መሆኑን ገልፀው፤ ሊታዩ የሚገባቸው ሌሎች ነገሮች መኖራቸውን አንስተዋል፡፡

ተማሪዎች አሁን ላይ ክፍል ውስጥ ሞባይል ስልክ ይዘው ሲማሩ ‘’ትምህርታቸው ላይ ትኩረት ከማድረግ ይልቅ፣ ማኅበራዊ ትስስር ገጾችን መከታተል እንደሚያበዙ" ጠቅሰዋል፡፡

ስልክ መያዛቸው ከትምህርታቸው እንዲናጠቡ እያደረጋቸው መሆኑን ያነሱት መምህራኑ፤ መፅሐፍት እና ጥናት ላይ ከማተኮር ይልቅ ሌሎች ዘመን አመጣሽ ቴክኖሎጂዎች ላይ ጥገኛ እንዲሆኑ አድርጓል ብለዋል፡፡

ይሁን እንጂ ትምህርት ቤቶች ሊያሟሏቸው የሚገቡ ጉዳዮች እንዳሉ ገልፀዋል፡፡ በቂ የመፅሐፍት አቅርቦት፣ የICT ላብ፣ የኮምፒውተር ግብዓቶች እንዲሁም የተለያዩ አጋዥ መፅሐፍት ሊሟሉ እንደሚገባ አንስተዋል፡፡

ፌስቡክ፡- https://m.facebook.com/ethiopia24
ቴሌግራም፦ https://t.me/ethiopia_24

22/04/2025

Body || Name

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopia 24 posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share