Phroneo Biblical

Phroneo Biblical We Post Verses and biblical thought through different means. Help us spread thought of heavenly thin

እንኳንም ሞቶ አልቀረእርሱ በዚህ የለም፤ እንደ ተናገረው ተነሥቶአል፤ ኑና ተኝቶበት የነበረውን ቦታ እዩ። ማቴዎስ 28:6እኔን ሞተኝእኔ የተቀበልሁትንና ከሁሉ በላይ የሆነውን ለእናንተ አስተላ...
18/04/2025

እንኳንም ሞቶ አልቀረ

እርሱ በዚህ የለም፤ እንደ ተናገረው ተነሥቶአል፤ ኑና ተኝቶበት የነበረውን ቦታ እዩ።
ማቴዎስ 28:6

እኔን ሞተኝ

እኔ የተቀበልሁትንና ከሁሉ በላይ የሆነውን ለእናንተ አስተላልፌአለሁ፤ ቅዱሳት መጻሕፍት እንደሚሉት ክርስቶስ ስለ ኀጢአታችን ሞተ፤
1 ቆሮንቶስ 15:3

https://t.me/PhroneoBiblical

ምስጉን ክርስቲያንእንደ እግዚአብሔር ትጉህ ነውስድስት ቀን ሥራ የሚለውን ቃል ዘለን የሰባተኛው ቀን ምንነት ላይ እንመራመራለን እንጨቃጨቃለንዘጸአት 20⁹ ስድስት ቀን ሥራ ተግባርህንም ሁሉ አ...
03/02/2025

ምስጉን ክርስቲያን
እንደ እግዚአብሔር ትጉህ ነው
ስድስት ቀን ሥራ የሚለውን ቃል ዘለን የሰባተኛው ቀን ምንነት ላይ እንመራመራለን እንጨቃጨቃለን
ዘጸአት 20
⁹ ስድስት ቀን ሥራ ተግባርህንም ሁሉ አድርግ፤
¹⁰ ሰባተኛው ቀን ግን ለእግዚአብሔር ለአምላክህ ሰንበት ነው፤ .......
ሮሜ 12: 11
❝ለሥራ ከመትጋት አትለግሙ፤ በመንፈስ የምትቃጠሉ ሁኑ፤ ለጌታ ተገዙ፤❞
ካልተሻሩት ትዛዛት ቀዳሚዎ
❝ወደ ወጣህበት መሬት እስክትመለስ ድረስ በፊትህ ወዝ እንጀራን ትበላለህ፤...❞
ዘፍጥረት 3: 19
ብዙዎቻችን ለፍተን ከመስራት
በነፃ የተሠጠንን ፀጋ ወደ ገንዘብ ለመለወጥ እንሻለን።

19/01/2025

ራብከኝ የእኔ ጌታ

ኢየሱስ ቆሞ ከፍ ባለ ድምፅ እንዲህ አለ፤ “ማንም የተጠማ ቢኖር ወደ እኔ ይምጣና ይጠጣ፤”
ዮሐንስ 7:37

JESUS is BORNኢየሱስ ተወልዷል።እንኳን አደረሳችሁ!
06/01/2025

JESUS is BORN
ኢየሱስ ተወልዷል።

እንኳን አደረሳችሁ!

2ሳሙ 6...ላይ ዳዊት ልብሱን ያወለቀበት part ነው እና ይገርመኛል።ብዙዎቻችን ስናድግ ያካበትናቸው እና ያሉን ነገሮች መተማመኛ እና መደገፊያ አለመሆናቸውን check አናረግም።ዳዊት ግን ...
07/12/2024

2ሳሙ 6...ላይ ዳዊት ልብሱን ያወለቀበት part ነው እና ይገርመኛል።

ብዙዎቻችን ስናድግ ያካበትናቸው እና ያሉን ነገሮች መተማመኛ እና መደገፊያ አለመሆናቸውን check አናረግም።

ዳዊት ግን በእግዚያብሔር ታቦት ፊት ልብሱን ሲያወልቅ እና በሰው ፊት ሲያመልክ "አሁንም መደገፊያዬ አንተ ነህ ፤ንግስናም እንኳን ቢሆን በአንተ ፊት ከሆነ ይወልቃል፤የረዳኝን አልረሳሁም ፤still ሌላው ሁሉ ሸንበቆ ነው። " ያለ ይመስለኛል።

እና ባደግን ቁጥር የሆነን ነገር ባገኘን ቁጥር ሌላ መደገፊያ ሳይሆን እግዚያብሔርን ማመስገኛ ምክንያት መሆኑን እናረጋግጥ
...እርሱም ቢሆን ይወልቃል...

እግዚያብሔርን መታመን ሳስብ ብዙ ግዜ ማስበው
👉🏽"ደመና ባላይም ሸለቆ ይሞላልን" ነው ግን ሳስበው...

👉🏽ደመናን አይቼ ይዘንባል አልልም....ማለትንም ያጠቃልላል... ያነው በምንም ነገር አለመታመን...በእግዚያብሔር ብቻ መደገፍ
እና
...ምንም ቢሆን ይወልቃል....

10/11/2024
ጉዞ ከጌታ ጋርበማዕበል ውስጥ ሆነው ሲታወኩ ኢየሱስ በታንኳ ውስጥ ተኝቶ ነበር። ከጭንቀታቸው ብዛት "ስንጠፋ አይገድህምን" ብለው ቀሰቀሱት እርሱም እናንተ እምነት የጎደላችሁ አላቸው። እምነት...
03/11/2024

ጉዞ ከጌታ ጋር

በማዕበል ውስጥ ሆነው ሲታወኩ ኢየሱስ በታንኳ ውስጥ ተኝቶ ነበር። ከጭንቀታቸው ብዛት "ስንጠፋ አይገድህምን" ብለው ቀሰቀሱት እርሱም እናንተ እምነት የጎደላችሁ አላቸው። እምነት ያላቸው የትኛውን ይሆን? መቼም አምላክ ሆኖ ሳለ ፍጥረታት ሁሉ የሚታዘዙለት ጌታ እርሱ ማዕበሉን ፀጥ እንዳደረገ እነርሱም እንዲህ ማዕበሉን እንዲያዙ እምነት አነሳችሁ ማለቱ ነው ለማለት ይከብዳል። ገና መጠራታቸውንን እና ማንንታቸውንን ያላረጋገጡ በመንፈስ ቅዱስ በኩል የልጅነት ስልጣናቸውን ያልተቀበሉ በእውቀትም በልምምድም ገና የሆኑ ስለነበሩ።

ይልቁንስ የጠየቃቸው እምነት የአእምሮ እውቀትን የማይሻ ተግባራዊ ምሳሌ ላይ ያልተመረኮዘ በንጹህ ልብ እና ሞኝነት ላይ የተመሠረተ እንሻገር ብሎ ጉዞ ባስጀመረው መምህር ማንነቱን በእምነት መቀበል ነው። ያለውን የሚያደርግ መሆኑን በልብ እርጋታ እና ሰላም እርሱን ስለመደገፍ ይመስለኛል።

ከእኛ የሚጠበቀው ተግባር መፍትሔ ፍለጋ መውጫውን ለማግኘት በመፍጨርጨር ምነው ዝም አልክ ጌታ፤ በዚህ ጉዳይ ስንጠፋ፣ ስንበደል መከራን ስንቀበል ግድ አይልህምን እያልን መጮኽ ሳይሆኖ የሕይወታችን ጅማሬ እና ፍፃሜ የሆነውን መኖራችንም መሞታችንም ለእርሱ ለሆንለት አምላክ በእምነት በልብ እርጋታ እና ሰላም ፀንተን መቆም ነው።

በቅጡ ሳናምንህ መልስ ላሻንበት አንደበታችን ይቅር በለን።
የራሳችንን መፍትሄ ሞክረን የመጨረሻ አማራጭ ስላረግንህ ይቅር በለን።

ጻድቅ በእምነት በሕይወት ይኖራል።
እምነትም ከመስማት ነው፤ መስማትም ከእግዚአብሔር ቃል ነው።

ቃልም ደሞ እንዲህ ይላል።
ምሳሌ 11:1-31

#0151

How would we feel, Meeting Jesus in person.  What will it be like?  #0150
30/10/2024

How would we feel, Meeting Jesus in person.
What will it be like?

#0150

እኛ ክፉዎች ሳለንወንድማችንን ገለን እኔ ጠባቂው ነኝ ወይ የምንልሰው በቆፈረው የውሃ ጉድጓድ የኔ ነው የምንልተባብረን ወንድማችንን ጉድጓድ ውስጥ የምንከትበሃዘን የምታለቅሰዋን ሴት አንቺ ሰካ...
29/10/2024

እኛ ክፉዎች ሳለን
ወንድማችንን ገለን እኔ ጠባቂው ነኝ ወይ የምንል
ሰው በቆፈረው የውሃ ጉድጓድ የኔ ነው የምንል
ተባብረን ወንድማችንን ጉድጓድ ውስጥ የምንከት
በሃዘን የምታለቅሰዋን ሴት አንቺ ሰካራም የምንል
ሌላ ሰው እንዳይበልጠን በጦር ለመውጋት የምንሞክር
ለተበደረን ሰው ጭካኔን የምናሳይ
የተቸገሩት የምናገል እና በመበለቲቷ የምናሾፍ
አብሬህ ሆናለው ባልንበት አንደበት በገረድ ፊት የምንክድ
ጌታችንን ለገንዘብ አቅፈን የምንሸጥ
እኛ ክፉዎች ሆነን ሳለን ከክፉም ክፉ ሆነን ለልጆቻችን ግን መልካም ስጦታ መስጠት ካወቅን።

ከማንነቱ መልካም እና ሩህሩህ የሆነው የሰማይ አባታችን እግዚአብሔር ለእኛ ምንኛ መልካምን ነገር አብልጦ ይሰጥ ይሆን?

"ከእናንት መካከል ልጁ ዳቦ ቢለምነው፣ ድንጋይ የሚሰጥ አባት አለ? ወይንም ዓሣ ቢለምነው እባብ የሚሰጥ ይኖራልን?"

"ታዲያ እናንት ክፉዎች ሳላችሁ ለልጆቻችሁ መልካም ስጦታ መስጠት ካወቃችሁ፣ የሰማዩ አባታችሁማ ለሚለምኑት መልካም ስጦታን እንዴት አብልጦ አይሰጣቸውም?"
ማቴዎስ 7:9-11

አትጨነቁ በጌታ ታመኑ።

#0149
https://t.me/PhroneoBiblical

እግዚአብሔር እረኛዬ ነው፤አንዳች አይጐድልብኝም።በለመለመ መስክ ያሳርፈኛል፤በዕረፍት ውሃ ዘንድ ይመራኛል፤ነፍሴንም ይመልሳታል።ስለ ስሙም፣በጽድቅ መንገድ ይመራኛል።በሞት ጥላ ሸለቆ ውስጥ፤ብሄድ...
20/10/2024

እግዚአብሔር እረኛዬ ነው፤
አንዳች አይጐድልብኝም።
በለመለመ መስክ ያሳርፈኛል፤
በዕረፍት ውሃ ዘንድ ይመራኛል፤
ነፍሴንም ይመልሳታል።
ስለ ስሙም፣
በጽድቅ መንገድ ይመራኛል።
በሞት ጥላ ሸለቆ ውስጥ፤
ብሄድ እንኳ፣
አንተ ከእኔ ጋር ስለ ሆንህ፣
ክፉን አልፈራም፤
በትርህና ምርኵዝህ፣
እነርሱ ያጽናኑኛል።
ጠላቶቼ እያዩ፣
በፊቴ ማዕድ አዘጋጀህልኝ፤
ራሴን በዘይት ቀባህ፤
ጽዋዬም ሞልቶ ይፈስሳል።
በሕይወቴ ዘመን ሁሉ፣
በጎነትና ምሕረት በእርግጥ ይከተሉኛል፤
እኔም በእግዚአብሔር ቤት፣
ለዘላለም እኖራለሁ።
መዝሙር 23:1-6

#0148
https://t.me/PhroneoBiblical

በሚያስፈራው እና በሚያስጨንቅ ወቅት ጌታ በተአምሩ በማዕበሉ መሃል እየተራመደ ይምጣላችሁ።ኢየሱስም ወዲያውኑ፣ “አይዞአችሁ፤ እኔ ነኝ አትፍሩ” አላቸው። ማቴዎስ 14:27እንኳን ለ2017 ዓ/ም...
10/09/2024

በሚያስፈራው እና በሚያስጨንቅ ወቅት ጌታ በተአምሩ በማዕበሉ መሃል እየተራመደ ይምጣላችሁ።

ኢየሱስም ወዲያውኑ፣ “አይዞአችሁ፤ እኔ ነኝ አትፍሩ” አላቸው። ማቴዎስ 14:27

እንኳን ለ2017 ዓ/ም በሰላም አደረሳችሁ!

#0147
https://t.me/PhroneoBiblical

05/09/2024

Address

Addis Ababa

Telephone

+251965199365

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Phroneo Biblical posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Phroneo Biblical:

Share

Category