08/08/2021
"ወታደራዊ ጣልቃ ገብነቱ የሚታሰብ አይደለም!!
-------------------------------------
ሰማንታ ፓዋር በሀገራት ላይ ወታደራዊ ጣልቃ ገብነት እንዲተገበር ከሚያቀነቅኑ የአሜሪካ ፖለቲከኞች ውስጥ አንዷ ነበረች። አሁን ግን አሜሪካ በተለይም በአፍጋኒስታንና በኢራቅ ጣልቃ ገብነት የደረሰባትን ኪሳራ አስልታ ወታደራዊ ጣልቃ ገብነቱን ይቅርብኝ ብላለች።
ስለዚህም ቀጣዩ የአሜሪካ ሚና ዕርዳታን በመቀነስና ከነአካቴውም በማቆም አሊያም በውክልና ጦርነት ጣልቃ ገብነቱን መቀጠል አማራጭ የውጭ ሀገር ፖሊሲዋ ነው። የትናንትናው "Washington Post" ዘገባ "US rules out military action to end Tigray war; considers aid cuts" በሚለው ርዕስ ሥር ሰማንታ ፓዋርን በመጥቀስ ያረጋገጠልን ይህንኑ ነው። ሰማንታ ወታደራዊ ጣልቃ ገብነቱ ሲያምራት ቀርቷል፣ ለኢትዮጵያ ይደረግ የነበረውን ዕርዳታ ለማቋረጥ ግን እየፎከረች ነው።
"Power’s past advocacy for humanitarian intervention, including with U.S. military force, has fallen out of favor in recent years as public confidence in Washington’s ability to reshape distant lands wanes. U.S. forces will conclude a 20-year occupation in Afghanistan in September, and the military will formally end combat operations in Iraq by the end of the year, Biden said last week. The two missions have cost thousands of lives, trillions of dollars and fallen far short of U.S. ambitions to bring about stability, democracy or prosperity. The protracted chaos and bloodshed in Libya following the ouster of Moammar Gaddafi in a NATO-led military operation in 2011 also dampened the appeal of humanitarian interventions."
ያም ሆነ ይህ ሰማንታ ፓዋር ከጉብኝቷ በኋላ የፎከረችው የዕርዳታ ማቋረጥ ማስጠንቀቂያ ተግባራዊ ቢሆን ጉዳቱ ቀላል አይሆንም፣ ስለዚህም ኢትዮጵያዊያን በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገራት ያለን ተፅዕኖውን ለመቋቋም በሕብረት መቆም ያለብን ጊዜ አሁን ነው።
ከዚህ ባለፈ የአሜሪካ የወቅቱን የውጭ ፖሊሲን በቅጡ ባለመረዳት ኢትዮጵያ ውስጥ የአሜሪካ ጦር እንዲገባ በዲያስፖራ ጭምብል ፊታቸውን ሸፍነው እነ ኬረን ቤይስን ሲማፀኑ የነበሩ የሕወሓት ደጋፊዎች ቁርጣቸውን ማወቃቸውም አንድ ነገር ነው። ለነገሩ የአሜሪካ ወታደሮች የኢትዮጵያን አፈር ቢረግጡ በአፀፌታው ታሊባኖቹም ከሰነዘሩት ተቃውሞ የከፋው እንደሚገጥመው ሳይታለም የተፈታ ነው። ለዚህም ምክንያቱም የኢትዮጵያ ሕዝብ በሙሉ በሚባልበት ደረጃ በአሁኑ ወቅት ልዩነታቸውን ወደ ጎን ትተው በሀገሪቱ ሉዓላዊነት ርዕሰ ጉዳይ ላይ አንድ የሆኑበት ወቅት መሆኑ ነው!
Getahun Heramo