Yoseph Bedada Dida - Megersa

Yoseph Bedada Dida - Megersa Smile when it hurts more 🤣

📌 "ጎረቤቶቻችን አሁንም ራሳቸውን ለድርድር ዝግጁ ቢያረጉ መልካም ነው! ጠ /ሚ/ር ዐቢይ አሕመድ የባህር በርን በተመለከተ የዐቢቹ ቃል እየተፈፀመ ነው።ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር...
29/09/2025

📌 "ጎረቤቶቻችን አሁንም ራሳቸውን ለድርድር ዝግጁ ቢያረጉ መልካም ነው!
ጠ /ሚ/ር ዐቢይ አሕመድ

የባህር በርን በተመለከተ የዐቢቹ ቃል እየተፈፀመ ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በህዳሴ ግድቡ ምርቃት ላይ ሲናገሩ "ጎረቤቶቻችን በፈጠነ ጊዜ ራሳቸውን ለድርድር ዝግጁ ቢያረጉ መልካም ነው" ብለው ተናግረው ነበር፡፡ንግግሩ ይመለከተቸዋል የተባሉት ኤርትራ እና ሶማሊያም ፈጠን ያለ መልስ ሰጥተዋል፡፡የሶማሊያው ፕሬዚዳንት ሀገራቸው በወደብ ጉዳይ በጋራ ለመጠቀም ዝግጁ ናት ብለዋል፡፡የኤርትራው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኦስማን ሳለህም ሰሞኑን ከተመድ ስብሰባ ጎን ለጎን ከአሜሪካ ልዩ የአፍሪካ ቀንድ መልእክተኛ ጋር ባደረጉት ውይይት "ስለ ቀጠናዊ ጉዳዮች መክረዋል" ተብሏል፡፡ምናልባትም አሜሪካኖቹ ኤርትራውያኑን በወደብ ጉዳይ ከኢትዮጵያ ጋር ለምን አትነጋገሩም!?" ሳይሏቸው አይቀርም፡፡ለወትሮው ስለወደብ ጉዳይ ሲጠየቁ "በሉአላዊነት ላይ ድርድር የለም" የሚሉት የአስመራ ሰዎች እንዲህ አይነት "መደራደር እንችላለን" የሚል ትርጉም ያለው ለዘብ ያለ መልስ ለምን ሰጡ? ከተባለ አንድም ኢትዮጵያ ነገሩን አጠንክራ ስለያዘች እና ወደ ጦርነትም ልትገባበት እንደምትችል ስለገመቱ ይመስላል፡፡ጦርነት ከተገባ ደግሞ ነገሩ ዝቅ ሲል ለኢሳያስ አፈወርቂ የስልጣን ህልውና ከፍ ሲል ለኤርትራ ዘላቂ ህልውና ብዙ አደጋዎችን ያነገበ ጉዳይ ስለሆነ ነው፡፡

በሌላ መልኩ ኤርትራውያኑ "እንደራደራለን" አይነት መልስ የሰጡት አሜሪካውያኑን እና አውሮፓውያኑን ለማዘናጋት እና ጊዜ ለመግዛት ወደፊትም ነገሩ ወደ ጦርነት ከሄደ "እኛኮ ሲጀመር የሰላም አማራጮችን ሁሉ እሺ ብለን ነበር" ለማለት ነው እንጂ ከልባቸው እንዳልሆነ የታወቀ ነው፡፡ሶማሊያውያኑም ሆነ ኤርትራውያኑ አሁን "በጋራ መጠቀም" የሚሉት ሀሳብ ኢትዮጵያ ከጅቡቲ ጋር ካላት "የወደብ ኪራይ" አሰራር ብዙም አይለይም፡፡ኢትዮጵያ ደሞ የፈለገችው የኪራይ ወደብ ሳይሆን የራሷን የባህር በር ነው፡፡ይሄ በሰላማዊ መንገድ ሊገኝበት የሚችልበት እድል ጨርሶ የለም ባይባልም ግን አናሳ ነው፡፡
እና ምን ተሻለ? አገራችን በሰላም አማራጭ በሰጥቶ መቀበል መርህ የሚገኝ የባህር በር ካለ ጦርነት ምርጫዋ አይደለም፥ ግን አሁን በእርግጠኝነት መናገር የሚቻለው የባህር በር ጥያቄው ከጎረቤትም ሆነ ከሀያላኑ ዘንድ ትኩረት አግኝቷል፡፡

#ዐቢቹ

#ኢትዮጵያ

📌 በአንድነትና በመተባበር የህዳሴ ግድብን እውን እንዳደረግነው በቀይ ባህር ላይም እንደግመዋለን!ታላቁ ህዳሴ ግድብ ማለቁን በማስመልከት በተለያዩ ክልሎች የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄዱ ይገኛሉ። ይ...
18/09/2025

📌 በአንድነትና በመተባበር የህዳሴ ግድብን እውን እንዳደረግነው በቀይ ባህር ላይም እንደግመዋለን!

ታላቁ ህዳሴ ግድብ ማለቁን በማስመልከት በተለያዩ ክልሎች የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄዱ ይገኛሉ። ይህ ታላቁ ህዳሴ ግድብ በእኛ በኢትዮጵያውያን ደምና ላብ የተገነባ መሆኑን ህዝቡ የተካሄደው ሰልፍ ያረጋገጠበት ነው።

ሕዳሴ ግድቡ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን እንደ አህጉራችንም አፍሪካውያንን ሰርተን መጨረስ እንደምንችል ማሳያ ኩራታችን ነው። ታዲያ ይህንን እንዳሳካነው ሁሉ የወደብ እስረኛ ሆነን መቆየት ስለማንችል የቀይ ባሕር ባለቤትነትን ለማሳካት
በአንድነትና በመተባበር መቆም ይኖርብናል። በህብረት የማንችለው ነገር ስለሌለ የዘመናት ቁጭታችንን በሕዳሴ ድል እንደተቀናጀነው ሁሉ በቀይ ባህር ላይም በአንድነት ደስታችንን እናበስራለን:: ይቻላል! 💪🇪🇹🙏






ህልም ተፈፀመ! A once-in-a-lifetime leader!ዋዜማ በጉባ! በህዳሴ ግድብ ምርቃት!
08/09/2025

ህልም ተፈፀመ! A once-in-a-lifetime leader!
ዋዜማ በጉባ! በህዳሴ ግድብ ምርቃት!

Ashaaraan magariisaa ashaaraa dhalootni har'aa guddummaa biyyaa fi dhaloota boruuf kaa'uudha. Waamicha egeree dhalootaa ...
30/06/2025

Ashaaraan magariisaa ashaaraa dhalootni har'aa guddummaa biyyaa fi dhaloota boruuf kaa'uudha.

Waamicha egeree dhalootaa ifaa dhaabuu!

#በመትከልማንሰራራት

ሚኒስትሩ በመልካም ጤንነት ላይ ናቸው‼️"የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ሰኔ 15 ቀን 2017 ዓ.ም እንደ ወትሮ ከመደበኛ ስራቸው ወደ ቤታቸው በመመ...
30/06/2025

ሚኒስትሩ በመልካም ጤንነት ላይ ናቸው‼️

"የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ክቡር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) ሰኔ 15 ቀን 2017 ዓ.ም እንደ ወትሮ ከመደበኛ ስራቸው ወደ ቤታቸው በመመለስ ላይ እያሉ ከምሽቱ 1:00 አካባቢ መኖሪያ ቤታቸው የሚገኝበት ካርል አደባባይ ላይ ድንገተኛ የመኪና አደጋ ደርሶባቸው ነበር። በእለቱ ክቡር ሚኒስትሩ ወደ ሆስፒታል አምርተው በቂ የህክምና አገልግሎት አግኝተው አሁን ላይ በሙሉ ጤንነት ላይ ይገኛሉ። እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ እውነቱን ለርካሽ ፖለቲካዊ ግብ ለመጠቀም ከአውድ ውጪ ባልተረጋገጠ መረጃና በአሉባልታ የሚናፈሰው የማህበራዊ ሚዲያ ዘገባ የተሳሳተና መሰረተቢስ መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ሚስቴር አበክሮ ለመግለጽ ይወዳል፡፡ በቅርቡም ክቡር ሚኒስትሩ ከበቂ የጤና እርፍት ቆይታ በሃላ ወደ መደበኛ ስራ ገበታቸው የሚመለሱ መሆናቸውን በአክብሮት እንገልፃለን።"

የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር!
Ethiopian Ministry of Trade and Regional Integration

የነዳጅ ጉዳይ‼️Gatiin Boba'aa hin dabalu!👏~~~~~~የሐምሌ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት እንደሚቀጥል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገለጸ‼️ የሐም...
28/06/2025

የነዳጅ ጉዳይ‼️
Gatiin Boba'aa hin dabalu!👏
~~~~~~
የሐምሌ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት እንደሚቀጥል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገለጸ‼️
የሐምሌ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ከዛሬ ሰኔ 21 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በሰኔ ወር ሲሸጥ በነበረበት የመሽጫ ዋጋ እንዲቀጥል በመንግሥት መወሰኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገለጸ፡፡

የነዳጅ ማደያዎች እና ኩባንያዎች በነዳጅ ውጤቶች ግብይት አዋጁና በአሠራር መመሪያው መሠረት ውሳኔውን ተግባራዊ በማድረግ ህብረተሰቡን በቅንነትና በታማኝነት እንዲያገለግሉ የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር በጥብቅ ያሳስባል፡፡

የትም የማይሄደው መርከብበአላማ የመኖር ቁልፍ(“25 የስኬት ቁልፎች” ከተሰኘው የዶ/ር ኢዮብ ማሞ መጽሐፍ የተወሰደ)በአንድ ከተማ ውስጥ በየምሽቱ ሰዎችን እየጫነ ለሰዓታት በባህሩ ላይ ወዲህና...
18/06/2025

የትም የማይሄደው መርከብ
በአላማ የመኖር ቁልፍ

(“25 የስኬት ቁልፎች” ከተሰኘው የዶ/ር ኢዮብ ማሞ መጽሐፍ የተወሰደ)

በአንድ ከተማ ውስጥ በየምሽቱ ሰዎችን እየጫነ ለሰዓታት በባህሩ ላይ ወዲህና ወዲያ በመሄድ ካሳለፈ በኋላ በመጨረሻ ሰዎቹን የነበሩበት ስፍራ መልሶ የሚያራግፋቸው መርከብ እንዳለ ይነገራል፡፡

ይህ ግዙፍ መርከብ በውስጡ አለ የተባለ በማንኛውም ዘመናዊ ከተማ ውስጥ የሚገኙ ነገሮችን አካቷል፡፡ መዝናኛው፣ መዋኛው፣ መጫወቻው፣ የሚበላውና የሚጠጣው ሙሉ ነው! የዚህ መርከብ ስም፣ “የትም የማይሄደው መርከብ” በመባል ይታወቃል፡፡

ይህ መርከብ በየምሽቱ ሰዎችን በመጫን ወዲህና ወዲያ ይሄዳል፣ ነገር ግን የትም አይደርስም፡፡ በጉዞው ወቅት ተሳፋሪዎቹ ይጫወታሉ፣ ይበላሉ፣ ይጠጣሉ፣ ይደንሳሉ፣ ይተዋወቃሉ፣ ያወራሉ … በመጨረሻ ግን ራሳቸውን የተነሱበት ቦታ ላይ ያገኙታል፡፡ በእለቱ በተከናወነው ነገር “እጅግ ደስ ከተሰኙ” በኋላ ሌላ የደስታ ምንጭ ፍለጋ ወደየስፍራቸው ይሰማራሉ - ጉዞአቸው ግን የትም አልወሰዳቸውም!

“ታላላቅ አእምሮዎች ዓላማ አላቸው፣ ሌሎቹ ግን ምኞት ብቻ ይዘዋል” - Washington Irving

በዚህች ምድር ላይ ከ7 ቢልየን ሕዝብ በላይ ወዲህና ወዲያ ሲመላለስና ዓለም ሕይወት ባላቸው ፍጡራን መሞላቷን ማየት ደስ ያሰኛል፡፡ ሆኖም ይህንን ደስ የሚያሰኝ ነገር ጥቁር ነጥብ የሚጥልበት አንድ አሳዛኝ ነገር አለ፣ ቁጥራቸው ጥቂት ያልሆኑ ሰዎች የሚሄዱበትን አያውቁም፡፡

እነዚህ ሰዎች በቀን ውስጥ ብዙ እንቅስቃሴ ቢያስመዘግቡም፣ የእነዚህ እንቅስቃሴዎች ድምር ውጤቱ ዜሮ ወይም ባዶ ነው፡፡

የብዙ ቁጥሮች ድምር ዜሮ የሚሆነው እንዴት ነው? መልሱ ቀላል ነው፡፡ የብዙ ቁጥሮች ድምር ዜሮ የሚሆነው የተደመሩት ቁጥሮች በሙሉ ዜሮ ሲሆኑ ነው፡፡ የየእለት እንቅስቃሴአችን ዜሮ የሚሆንበት ብቸኛ ምክንያት ካለምንም ዘላቂ እይታ ስለምንተገብረው ነው፡፡

የእለቱ ተግዳሮት የሚያመጣብን ትግልና የጊዜው መልካም ገጠመኝ የሚሰጠን ጊዜአዊ ደስታ ልንገነባው ከሚገባን አጠቃላይ የሕይወት ዓላማ አይነ-ህሊናችንን ይጋርዱታል፡፡ ግንባታ-የለሽ ደስታ፣ ግንባታ-የለሽ ጨዋታ፣ ግንባታ-የለሽ ስራ፣ ግንባታ-የለሽ ወዳጅነት፣ ፍጻሜ የለሽ ሩጫ … ዝርዝሩ ብዙ ነው፡፡

አንድ ሰው ስኬታማነትን በብርቱ ከፈለገ፣ በሕይወቱ ያለው ዓላማ ጉዳይ ግድ ሊለው ይገባል፡፡
መልካም ምሽት ተመኘሁ 🙏

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Yoseph Bedada Dida - Megersa posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Yoseph Bedada Dida - Megersa:

Share