ETV News

ETV News ETV News page is part of EBC which is the national media stationed in Ethiopia.

የፌዴራል ተቋማት እና ማህበራት አጀንዳ ማሰባሰብ የቡድን ውይይት ተጀመረ*************ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በዛሬው ዕለት የጀመረው የፌዴራል ተቋማት እና ማኅበራት አጀንዳ ማሰባሰብ መ...
30/05/2025

የፌዴራል ተቋማት እና ማህበራት አጀንዳ ማሰባሰብ የቡድን ውይይት ተጀመረ
*************

ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በዛሬው ዕለት የጀመረው የፌዴራል ተቋማት እና ማኅበራት አጀንዳ ማሰባሰብ መድረክ የቡድን ውይይት ተጀምሯል፡፡

በቡድን ውይይቱ ተቋማትን እና የተለያዩ ሕብረተሰብ ከፍሎችን ወክለው በመድረኩ የተገኙ አካላት የወከሉትን ማኅበረሰብ እና ተቋምን አጀንዳ በጥልቀት ያነሳሉ፡፡

የቡድን ውይይቱ የተጀመረው በየቡድኖቹ ሰብሳቢ እና ፀሐፊ በመምረጥ ሲሆን፣ ተሳታፊዎቹ ከወከሉት ማኅበረሰብ እና ተቋም አንጻር ሊያዝ ይገባል የሚሉትን አጀንዳ በነጻነት የሚያነሱ ይሆናል፡፡

የቡድን ውይይቱ እስከ ነገ ከሰዓት የሚቆይ ሲሆን፣ እሁድ ሁሉም የተግባባቸው አጀንዳዎች ተደራጅተው ለኮሚሽኑ የሚቀርቡ መሆናቸውን የወጣው መርሐ ግብር ያሳያል፡፡

በለሚ ታደሰ

#ምክክር

21/04/2025

13/12/2024

17/10/2023

የቀን 6 ሰዓት አማርኛ ዜና … 06/02/2016 ዓ.ም

13/10/2023

ኢቲቪ አመሻሽ ምዕራፍ ሁለት…ጥቅምት 02/2016 ዓ.ም

ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ እና የአካባቢ ጥበቃ ላይ የመሪነት ሚናን እየተጫወተች ነው፡-የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን*****************ኢትዮጵያ  የአየር ንብረት ለውጥ እና የአካባቢ...
06/09/2023

ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ እና የአካባቢ ጥበቃ ላይ የመሪነት ሚናን እየተጫወተች ነው፡-የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን
*****************

ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥ እና የአካባቢ ጥበቃ በአለም አቀፍ መድረኮች ባሉ መዋቅሮች ውስጥ ከፍተኛ ተሳትፎ ከማድረግ ባለፈ፤ ነባራዊ ሁኔታን ያገናዘቡ ሀገራዊ ዕቅዶችን በማዘጋጀት ውጤት ማስመዝገብ መቻሏን የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን አስታወቀ።

በኬንያ ናይሮቢ እየተካሄደ ባለው የአየር ንብረት ጉባኤ እየተሳተፉ የሚገኙት የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ጌታሁን ጋረደው፤ ኢትዮጵያ ለፈረመቻቸው አለም አቀፍ ስምምነቶች ተግባራዊነት ከመስራት ባሻገር አዳዲስ የዶክመንት ዝግጅቶች ላይ በቀዳሚነት እየተሳተፈች መሆኑን ገልፀዋል።

ኢትዮጵያ ብሔራዊ የአየር ንብረት ለውጥ ማጣጣም ዕቅድን በመንደፍ እንዲሁም ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር አረንጓዴ ልማት ስልትን ተግባራዊ በማድረግ፤ ከአህጉረ አፍሪካ በቀዳሚነት ትጠቀሳለች ብለዋል።

የአየር ንብረት ለውጥ እና የአካባቢ ጥበቃ ጉዳይ የብዙ ዘርፎች ተግባርን የሚጠይቅ በመሆኑ፤ ሁሉም ሚኒስቴር መስሪያቤቶች የዕቅዶቻቸው አካል አድርገው መስራታቸው ለተገኘው ውጤት አንዱ ምክንያት መሆኑን አንስተዋል።

በተሳትፎ ብቻ ይገለፅ የነበረው የአካባቢ ጥበቃ እና የአየር ንብረት ጉዳይን ባለፉት ሁለት አመታት በልማት ዕቅዶች ውስጥ በማስገባት ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ተችሏል ብለዋል።
መቅደስ ጥላሁን (ናይሮቢ፤ ኬንያ)

የጉሙዝ ብሄረሰብ የዘመን መለወጫ (ጓንዷ) በዓል  በተለያዩ ዝግጅቶች  መከበር ጀምሯል********የጓንዷ በዓል የጉሙዝ ብሄረሰብ ተወላጆች በድምቀት የሚያከብሩት የዘመን መለወጫ በዓል ነው፡፡...
06/09/2023

የጉሙዝ ብሄረሰብ የዘመን መለወጫ (ጓንዷ) በዓል በተለያዩ ዝግጅቶች መከበር ጀምሯል
********

የጓንዷ በዓል የጉሙዝ ብሄረሰብ ተወላጆች በድምቀት የሚያከብሩት የዘመን መለወጫ በዓል ነው፡፡

በዓሉ የተጣሉ የሚታረቁበት፣ የተቸገሩ የሚጠየቁበት፣ መልካም ስራዎች የሚከወኑበት ባህላዊ ዕሴቱ የዳበረ የዘመን መለወጫ በዓል ነው፡፡

በዓሉ ከዛሬ ጀምሮ በክልሉ በጳጉሜ ቀናትና በመስከረም ወር እስከ መስቀል በዓል ድረስ ማህበራዊ ፋይዳ ባላቸው በተለያዩ ዝግጅቶች ይከበራል፡፡

የበዓሉ ዝግጅት ኮሚቴ ሰብሳቢ አወቀ አይሸሽም (ዶ/ር)፤ የጓንዷ በዓል ከጳጉሜ1 ጀምሮ በአካባቢ ጽዳት፣ በደም ልገሳ ፣ ለአቅመ ደካማ ለተማሪዎች የትምህርት ቁሳቁስ ድጋፍ በማድረግ፣ በችግኝ እንክብካቤና በተለያዩ መርሀ ግብሮች በዓሉ ባህላዊ ዕሴቶቹን በጠበቀ መልኩ ይከበራል ብለዋል ፡፡

በጀማል አህመድ

የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ለዘመን መለወጫ በዓል ከ5ሺህ በላይ የዕርድ እንሰሳት ማዘጋጀቱን አስታወቀ**********************የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ለመጪው ለመጪው የዘመን...
06/09/2023

የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ለዘመን መለወጫ በዓል ከ5ሺህ በላይ የዕርድ እንሰሳት ማዘጋጀቱን አስታወቀ
**********************

የአዲስ አበባ ቄራዎች ድርጅት ለመጪው ለመጪው የዘመን መለወጫ በዓል ከ5ሺህ በላይ የእርድ እንሰሳትን ማዘጋጀቱን የህዝብ ግንኙነት ኃላፊው አቶ አታክልቲ ገብረሚካኤል አስታውቀዋል።

ኃላፊው የዓል ዝግጅቱን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ ፤ ለዕርድ ከታጋጁት እንስሳት ውስጥም ሁለት ሺህ የሚሆኑት በግና ፍየል መሆናቸው ተናግረዋል።

ድርጅቱ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 211ሚልዮን ብር ትርፍ ማግኘቱንም መግለጻቸውን የዘገበው ኢፒድ ነው።

በ2015 በጀት ዓመት 391ሺህ እንስሳትን እርድ ሊፈፅም አቅዶ 381ሺህ በማረድ የእቅዱን 97 በመቶ ማሳካቱን የገለፁት አቶ አታክልቲ፤ ድርጅቱ 116 ሚሊዮን ብር ለማትረፍ አቅዶ 211 ሚሊዮን ብር አትርፏል ብለዋል።

የአለም አቀፍ ተቋማት መሪዎች ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም እያደረገች ያለችውን ለውጥ አደነቁ*************በኬንያ ናይሮቢ እየተካሄደ ባለው የአየር ንብረት ጉባኤ ንግግር ...
06/09/2023

የአለም አቀፍ ተቋማት መሪዎች ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም እያደረገች ያለችውን ለውጥ አደነቁ
*************

በኬንያ ናይሮቢ እየተካሄደ ባለው የአየር ንብረት ጉባኤ ንግግር ያደረጉ የአለም አቀፍ ተቋማት መሪዎች፤ ኢትዮጵያ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም እያደረገች ያለችውን ተጨባጭ ለውጦች አድንቀዋል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ዋና ፀሀፊ አንቶኒዮ ጉተሬዝ፤ አፍሪካ በአየር ንብረት ለውጥ ጉዳይ አንድ ድምፅ ለመሆን ወደ አንድ አይነት ተግባር መምጣት ይኖርባታል ብለዋል፡፡

አያይዘውም ለዚህ ደግሞ መልካም ተሞክሮዎችን ከሌሎች አህጉራት ከመጠበቅ ይልቅ፤ ከኢትዮጵያ ተግባራዊ እንቅስቃሴዎች መማር ይገባል ብለዋል።

በአረንጓዴ ኃይል ልማት ዘርፍ ተፈጥሯዊ ምላሾችን በመስጠት ኢትዮጵያ በተግባር ካሳየቻቸው የቢሊየኖች ችግኝ ተከላ እና መሰል በዕቅድ የተመሩ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል የተሰሩ ልምዶች ሊወሰዱ ይገባል ብለዋል ጉተሬዝ።

የአፍሪካ ልማት ባንክ ፕሬዚዳንት ዶክተር አክንውሚ አዴሲና፤ "የአፍሪካ ሀገራት በአየር ንብረት ለውጥ ላይ ድጋፍ ከጠየቃችሁ ፤እንደ ኢትዮጵያ በሚታይ ስራ ጉዳይ ላይ ጠይቁ" ሲሉ አንስተዋል።

የባንኩ ፕሬዘዳንት በምሳሌነትም ኢትዮጵያ አፍሪካ ውስጥ ያለን የተፈጥሮ ፀጋ በመጠቀም እንዴት ምርታማ መሆን እንደሚቻል በስንዴ ምርት ላይ የሰራችው ስራ ጠቅሰዋል።

የ28ኛው የአለም አየር ንብረት ጉባኤ አዘጋጇ ሀገር የተባበሩት አረብ ኤሜሬት የ COP 28 ፕሬዚዳንት ዶክተር ሱልጣን አልጀብር፤ ኢትዮጵያ በአረንጓዴ አሻራ ማሳካት የቻለቻቸው ስራዎች ተሞክሯቸው ለአፍሪካ ብቻ ሳይሆን እንደ አለም ሊወሰድ የሚገባው ነው ብለዋል።

በምግብ ራስን መቻልን ለማረጋገጥ ስርዓታዊ ምላሽ የተሰጠበት እና ተጨባጭ ውጤት የተመዘገበበት እንደሆነም አንስተዋል።

በመቅደስ ጥላሁን (ናይሮቢ፤ ኬንያ)

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ETV News posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share