03/12/2025
" ' የቁጥጥር ሰራተኞቹ ይደራደራሉ፣ አላግባብ ደረሰኝ ቆርጠንም እያለ ይቀጡናል ' የሚለውን የግብር ከፋዩን ቅሬታ ለመፍታት ነው ይህ ቴክኖሎጂ የመጣው " - ገቢዎች ቢሮ
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በ2018 በጀት ዓመት በከተማ ደረጃ ለመሰብሰብ ያቀደው 350 ቢሊዮን ብር ነው።
ቢሮው ይህንን ገቢ ለመሰብሰብ እንዲችል የሌብነትና ብልሹ አሰራሮች ለመከላከልና የአገልግሎት አሰጣጥ ቅልጥፍና ለማጎልበት ፣ ይረዳሉ ያላቸውን አዳዲስ ቴክኖሎጂዎች በማልማት ወደ ተግባር መሸጋገሩን በዛሬው ዕለት በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ገልጿል።
ገቢዎች ቢሮ ይፋ ያደረገው የቦዲ ዎርም የካሜራ ቴክኖሎጂ የቁጥጥር ባለሙያዎችን የቁጥጥር ስራዎቻቸውን በድምፅና በምስል በመቅረፅ ከዋና መስሪያ ቤትና ከቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች ለመከታተል የሚያስችል ነው፡፡
ቴክኖሎጂው እያንዳንዱ በቡድን የሚንቀሳቀሱ የቁጥጥር ባለሙያዎች በየትኛው አካባቢ ቁጥጥር እየካሄዱ እንደሚገኝ ፣ ከግብር ከፋዮች ጋር የሚያደርጓቸው ንግግሮች በድምፅና በምስል ከዋና መስሪያ ቤቱ ለመከታተል ያስችላል።
በካሜራ የተደገፈው የቁጥጥር ስራው በአሁኑ ሰአት መርካቶ አንድ እና ሁለት፣ በቦሌ እና ንፋስ ስልክ ክፍለ ከተሞች የተጀመረ ሲሆን በሚቀጥሉት ቀናት በሌሎች ክፍለ ከተሞችም የሚጀመር ይሆናል ተብሏል።
280 ካሜራዎች በሦስት በሦስት በተዋቀሩ የቁጥጥር ባለሞያዎች አማካኝነት የቁጥጥር ስራውን ያከናውናሉ የተባለ ሲሆን ባለሞያዎቹ ከተሰጣቸው ቦታ ውጪ መንቀሳቀስም ሆነ ከቡድናቸው መነጠል አይፈቀድላቸውም።
ስለ ቴክኖሎጂው ማብራሪያ የሰጡት የገቢዎች ቢሮ ሃላፊ አቶ ቢኒያም ምክሩ በቁጥጥር ስራው ወቅት የቢሮው ሰራተኞች በቡድን እንጂ በተናጠል አይንቀሳቀሱም ብለዋል።
አቶ ቢንያም " ሰራተኞቹ የቁጥጥር ስራውን የሚያከናውኑት በቡድን ሆነው ነው አንድ በከተማዋ ውስጥ የሚሰራ የቁጥጥር ሰራተኛ ለብቻው የሚያደርገው ቁጥጥር አይኖርም ሦስት ሰራተኞች በጋራ ሆነው ነው የሚያደርጉት " ነው ያሉት።
" ከሦስቱ በአንዱ ላይ ካሜራ ይገጠማል ፣ሦስቱ በጋራ ይንቀሳቀሳሉ ይቆጣጠራሉ፣ ለእያንዳንዱ ቡድን የተሰጠው አካባቢ አለ ከዛ አከባቢ ውጪ መንቀሳቀስ አይችሉም በሚወጡበት ጊዜ ካሜራው ወደ ዋናው መስሪያ ቤት ጥቆማ(Signal) ይልካል በቀላሉ ሰራተኞቻችን ላይ ቁጥጥር የምናደርግበት ስርዓት ነው ያለው " ሲሉም አክለዋል።
ሃላፊው በሦስት በሦስት ቡድን ተደራጅተው በተዘጋጁት ቡድኖች ላይ ከ 280 በላይ ካሜራዎች ሲገጠሙ ከ 800 በላይ የሚሆኑ የቁጥጥር ሰራተኞችን እንደሚሸፍን ገልጸው የሰራተኞችን ቁጥር በመጨመር በተመሳሳይ የካሜራውም ቁጥር እየተጨመረ እንዲሄድ መታቀዱን ገልጸዋል።
የገቢዎች ቢሮ ሃላፊ አቶ ቢኒያም ምክሩ በዝርዝር ምን አሉ ?
" በከተማችን የሚካሄደው የቁጥጥር እና የህግ ማስከበር ስራ ለሌብነት ለብልሹ አሰራር የተጋለጠ ነው የቁጥጥር ሰራተኞቹ ይደራደራሉ፣ አላግባብ ደረሰኝ ቆርጠንም እያለ ይቀጡናል የሚለውን የግብር ከፋዩን ቅሬታ ለመፍታት ነው ይህ ቴክኖሎጂ የመጣው።
ይህ ቴክኖሎጂ በእኛ ቁጥጥር ሰራተኞች እና በግብር ከፋዩ መካከል የሚደረጉ ግንኙነቶችን ግልጽነት እንዲኖረው ለማድረግ የመጣ ነው።
ከእዚህ በኋላ ማንኛውም ነጋዴ በእኛ ቁጥጥር ሰራተኞች ያለአግባብ ተቀጥቻለሁ፣ ኢ ፍትሃዊ በሆነ አግባብ ተቀጥቻለሁ ለሚል ቅሬታ ግልጽ የሆነ መልስ የምንሰጥበት ስርአት የሚዘረጋ ነው።
በቁጥጥር ሰራተኞቻችን ዩኒፎርሞቻቸው ላይ የሚገጠም ፣የሚሄዱበት ቦታ መገኛቸውን የምንከታተልበት፣ የቁጥጥር ሰራተኛው ከተፈቀደለት አካባቢ ውጪ በሚወጣ ጊዜ ምልክት የሚሰጠን፣ ለቁጥጥር በሚሰመ