Omo Islamic Media-OIM

Omo Islamic  Media-OIM Information platform (mainly islamic)

01/02/2023
26/07/2022

" ዳግማዊ የሰው ልጆች አባት ነብዩላህ ኑህ "

- የመጀመሪያው የሰው ልጆች አባት አደም ( ዐ.ሰ ) ከሞቱ ከ1000 አመት በኋላ በረሱልነት የተላኩት ኑህ ( ዐ.ሰ) ናቸው።

- ሽርክ የተጀመረው በኑህ ዘመን ሲሆን ወደ አላህ በመጣራት ( በተውሂድ) ከ900 አመት በላይ ያሳለፉ ሲሆን ግን የሰለመላቸው( ያመነላቸው) 80 ብቻ ነው

- ከዚያም የዘንባባ ዛፍ እንድተክል አላህ አዘዘው። ዛፎቹ ከተተከሉ ቡኋላ ለ 40 አመት ሴቶቻቸው አይፀንሱም ነበር። አላህ 50 አመት ሲሞላቸው ዛፎችን ቁረጥ የሚል ትዕዛዝ ሰጠው። ከዚያም መርከብ ስራ የሚል ትዕዛዝ በመላኢካው ጂብሪል አማካኝነት መልዕክት ለኑህ መጣለት።

* ኑህ (ዐ.ሰ) የሰራው መርከብ
የጎን ስፍት = 800 ክንድ
ዕርዝመት = 1200 ክንድ
ከፍታ = 80 ክንድ ነበር።

- ኑህ መርከቧን ሰርቶ ሲጨርስ 80 አማኞችን፣ከቤት እና ከዱር እንስሳ አንድ ወንድ ና ሴት ጥንድ ጥንድ አድርጎ መርከቡ ላይ እንድጭን ታዘዘ።

- ኑህ ሁለት ሚስት ነበሩት አንዷ ሙስሊም ስትሆን ሁለተኛዋ ካፊር ነበረች እሱ ግን ሙስሊሟን ብቻ መርከቡ ላይ ጫነ።

- እንድሁም ኑህ 4 (አራት) ልጆቹን እንድጭን ተዘዘ ማለትም

1. ሳም = የአረቦች ፣ ሮም እና ፐርሺያ ዘሮች
2. ሐም = የቂብጥ ፣ በርበር እና ሱዳን ዘሮች
3. ያፈስ = የቱርክ ፣ ሶቃሊባ እና የዕጁጅ እና
መዕጁጅ ዘሮች
4. ከነዐ

- ከዚያም ነብዩላህ ኑህ ( ዐ.ሰ) ልጆቹን መርከቧ ላይ እንድወጡ አዘዟቸው ነገር ግን ሶስቱ እሽ ብለው ሲወጡ ከነዐ እንቢ አልወጣም አለ። ሁሉም መርከቧ ላይ ቦታቸውን ሲይዙ ፀሀይ ብርሃኗን ተነጠቀች፤ ሰማይም ዶፍ ዝናቧን ማውረድ ጀመረች ፤ መሬትም የያዘችውን ውሀ ተፍች መሬትም በጎርፍ ተጥለቀለቀ።

- ኑህ መርከቧ ላይ ሁኖ ወደታች ሲመለከት ከነዐ ልጃቸው በጎርፍ ውስጥ ሲባክን አዩት ኑህም ልጄ ሆይ ና መርከቧ ላይ ውጣ ትድን ዘንድ አሉት ልጁም ከተራራ ላይ እወጣለሁ እንቢ አለ። ኑህም አላህ ካዘዘው ዛሬ የሚቀር የለም እሱ ያዘነለት ቢሆን እንጅ አሉት። ወዲያውኑ ከተራራ ላይ ማዕበል ጎርፍ ተነስቶ ከነዐን ልጃቸውን እና መሬት ላይ ያለ ሁሉ ጠፋ መርከቧ ላይ ያሉት ብቻ ሲቀሩ።

- በመጨረሻም ለ 40 ቀን መሬት በጎርፍ ከተጥለቀለቀች ቡሃላ መርከቧ " ጁዲይ " በተባለ ተራራ ላይ አረፈች። አማኞችም ከጎርፍ ማዕበል ድነው ህይወታቸውን በኢባዳ ማሳለፍ ቀጠሉ።

ማሳሰቢያ፦ ከነብዩላህ ኑህ ታሪክ የምንረዳው ለተውሂድ እና ለእያንዳንዱ የዕለት ተዕለት ህይወታችን ሶብርና በአላህ መመካት ወሳኝ እንደሆነ ያስተምረናል።

አላህ በ ነብዩላህ ኑህ ላይ ሰላም ያስፍን

ምንጭ፦ ከነብያት ታሪክ የተወሰዴ

19/07/2022

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ከብዙ ውጣ ውረድና መስዕዋትነት በኋላ በአላህ ፈቃድ ሙስሊሙ የሚወክሉትንና አስፈፃሚዎቹን በሰላም መርጧል አልሃምዱሊላህ።

ምናልባትም ብዙዎች ዋጋ የከፈሉበት ላይ ታች ያሉበትና ክብራቸውን ለዑማው ሲሉ የተዉበት ጉዳይ ነው።

በዚህም መሠረት ሀጂ ኢብራሂም ቱፋን ፕሬዚዳንት አድርጎ የመረጠ ሲሆን አሁንም ግን በርካታ የቤት ስራዎች የሚጠበቁብንና የዱአም የተግባር እገዛ ከሁሉም ኢትዮጵያዊ ሙስሊም የነፍስ ወከፍ ስራ እንደሚጠበቅብን መዘንጋት የሌለበት ጉዳይ ነው።

ዋናው ነገር ደግሞ ከብሽሽቅ ወጥተን ማንም በአመለካከቱ ምክንያት የማይገፋበትና ሁሉንም ሙስሊም በእኩል አይን አይቶ በአንኳር ጉዳዮቻችን ላይ ከፊት ተሰልፎ መብታችንን የሚያስከብርልን ፋና ወጊ ሰበብ እንዲሆንልን ጌታችንን አላህን ሱ.ወ እንጠይቀዋለን። ፈሊላሂል ሀምድ።

ስለወደፊቱ ደግሞ አላህ የበለጠ ያውቃል።

12/07/2022

በኡመር (ረ.ዐ) ዘመን ሦስት ወጣቶች አንድ ሰውዬን ጎትተው በማምጣት ያ! አሚረል ሙእሚኒን ይህ ሰው አባታችንን ገድሏል ተገቢ ቅጣት እንድትወስንበት እንሻለን በማለት ተናገሩ።

ለምን ገደልክ? ሲሉ ኡመር ጠየቁት
እኔ የግመል እረኛ ነኝ አንደኛው ግመሌ የአባታቸው መሬት ላይ ካለ ዛፍ ቅጠል ቀንጥሦ ሲበላ አባታቸው ድንጋይ ወርውሮ ሲመታው ግመሌ ሞተ እኔም እሱ የወረወረውን ድንጋይ አኖስቼ ስወረውር መታሁትና ሞተ ሲል ተናገረ።

እንደዛ ከሆነ ቅጣት እወስንብሀለሁ! አሉ ኡመር (ረ.ዐ)

እሺ ሦስት ቀናትን አቆየኝ አባቴ ሢሞት ለኔና ለወንድሞቼ የተወልን ከንዝ የተደበቀ ሀብት አለ እኔ አሁን እዚሁ ከሞትኩ ከንዙም ይጠፋል ወንድሞቼም ይጠፋሉ (ይቸገራሉ) ስለዚህ ፍቀድልኝና ሄጄ ልምጣ አለ።

ታዲያ እስክትመለስ ዋስ የሚሆንህ ማነው አሉት ኡመር (ረ.ዐ)

ሰውየው የተሰበሰቡትን ሠዎች ተመለከተ የሚያውቀው የለም የእያንዳንዱን ፊት ተመለከተና ያ! ሰውዬ ሲል ጠቆመ።

ያ! አቡዘር ለዚህ ሠውዬ ዋስ ትሆናለህ? በማለት ዑመር (ረ.ዐ) ጠየቁት።

አዎን! ያ አሚረል ሙኡሚኒን በማለት መለሰ።

ይህ ሠው ካመለጠ ቅጣቱ አንተ ላይ ተፈፃሚ እንደሚሆን አታውቅም እንዴ? ሲሉ ኡመር ተገርመው ጠየቁት።

ግድ የለም ያ አሚረል ሙዕሚኒን እኔ ዋስ እሆነዋለው ሲል አቡዘር መለሠ።

ሰውየው ሄደ!!
አንድ ቀን አለፈ። ሁለተኛው ቀን ተከተለ። በሦስተኛው ቀን ሰውየው ካልመጣ ቅጣቱ አቡዘር ላይ ሥለሚፈፀም ሰዎች ተጨናነቁ ሆኖም የዛን ቀን ከመግሪብ በፊት ያ ሠው እያለከለከ መጣ። በጣም እንደደከመው ገፅታው መስካሪ ነበር። ከኡመር (ረ.ዐ) ፊት ለፊት በመቆም ከንዙን ለወንድሞቼና ለእናቴ ወንድሞች አስረክቤ መጣሁ አሁን በቁጥጥርህ ሥር ነኝ ቅጣቱን ፈፅምብኝ በማለት ተናገረ።

ዑመር ተገረሙ በዚያው ማምለጥ የምትችል ሆነህ እንዴት ተመለስክ ሢሉ ጠየቁት።
«ሰዎች ዘንድ ቃል አክባሪነት ጠባቂነት ጠፋ እንዳይባል ፈርቼ ነው። በማለት መለሰ»

ኡመር ወደ አቡዘር ዞር በማለት.. ይህን ሠው እንዴት ዋስ ሆንከው? በማለት ጠየቁት።
«እኔማ ዋስ የሆንኩት በሰዎች ዘንድ ህይር ስራ/መልካም ሥራ ጠፋ እንዳይባል ፈርቼ ነው» ሲል አቡዘር መለሰ።

በሁኔታው የሟች ልጆች ልባቸው ተነካ….. በቃ! አፉ ብለነዋል
ቅጣቱ እንዳይፈፀምበት ሲሉ ተናገሩ።

ዑመር ረ.ዐ ለምን? ሲሉ ጠየቁዋቸው።
«እኛ ደግሞ በሰዎች መሃል ይቅር መባባልን ጠፋ እንዳይባል እንፈራለን" ሲሉ መለሱ።

✔ከይቅር ባዮች ያድርገን🤲

28/06/2022

"በውቅያኖስ ጥልቀት ውስጥ ያለው ጨለማ"

"የከሀዲዎች ሁኔታ በጥልቅ ባህር ውስጥ እንዳለ ጥቅጥቅ ያለ ጨለማ በማእበል ላይ ማእበል በላይ ላይ ደግሞ ደመና ጥቅጥቅ ያለ ጨለማ አንዱ ባንዱ ላይ የተደራረበ አንድ ሰው እጁን በባህር ውስጥ ቢሰነዝር እጁን አያየውም : አላህ ብርሀን ያልሰጠው ሰው ለርሱ ብርሀን የለውም(24:40)

-ማንኛውም ብርሀን ከሰባት ህብረ ቀለሞች የተሰራ ነው:እነዚህምቀለሞች_ሀምራዊ:ጥቁር ሠማያዊ:አረነጎዴ:ቢጫ:ብርቱካናማና :ቀይ ናቸው _ብርሀን የባህር አቅጣጫ ላይ ሲደርስ መጀመሪያ የነበረውን አቅጣጫ ይለዉጣል::

_ከላይ ያለው ከ10-15 ሜትር የሚደርሰው የባህሩ አካል ቀዩን ቀለም ይቀበላል: ይህ ማለት በዚህ ክልል ውስጥ ቀዩን ከለር ብቻ ነው ማየት የሚቻለው: አንድ ጠላቂ ከባህሩ 25 ሜትር ጥልቀት ውስጥ አደጋ ደርሶበት ቢደማ የደማውን ቀይ ቀለም ማየት አይችልም ::ምክንያቱም ቀይን ቀለም የሚያሳየው ቀይ የብርሃን አይነት በ25 ሜትር ላይ ስለማይደርስ ነው።

በተመሣሣይ ብርቱካንማ የብርሀን ጨረር ከ25-50ሜትር ጥልቀት ላይ ይንፀባረቃል
-ቢጫ ከ50-100 ሜትር ላይ ይነፀባረቃል
-አረንጎዴው ከ100-200 ሜትር ላይ ይንፀባረቃል
-ጥቁር:ሰማያዊ :ሀምራዊ:ከ200 ሜትር ርቀት በላይ ከውቅያኖስ ስር ይሆናል:ቀስ በቀስ ከባህር በላይ የተንፀባረቀው ብርሀን እየጠፋ ስለሚሄድ በጣም ጨለማ እየሆነ ይሄዳል :ይህ ማለት የጥቁር የሰማያዊ የሀምራዊ መብራት ተከትሎ በጨለማ ይዋጣል።
ከ1000 ሜትር ጥልቀት በላይ ሙሉ ለሙሉ ጨለማ ይሆናል።

2- የፀሀይ ጨረር በደመና ላይ ሲያርፍ ደመናው ጨረሩን ይወስድና ከደመናው በታች ወዳለው የከባቢ አየር ይበትነዋል :በዚህ ምክንያት ልክ ከላይ እንዳየነው እንደ ባህሩ ጨረሩ ሲበተን ከተወሰነ ርቀት በሆላ ጨለማ እንዲፈጠር ያደርገዋል። ይህ የመጀመሪያ የጨለማ ሁኔታ ሲሆን ከዚህ በሆላ ትንሹም ቢሆን ደመናው አልፎ የመጣው የብርሀን ጨረር በባህሩ አካል ላይ ሲደርስ በማእበል አማካኝነት ወደ ባህሩ የውጭ አካል ይንፀባረቃል ።ስለዚህ ይህ ማእበል የመጣውን የብርሀን ጨረር ወደ ውጭ (ከባህሩ በላይ) በማንፀባረቅ ብርሀን ወደ ውስጥ ሣይገባ ጨለማ እንዲፈጠር ያደርገዋል።የተወሰነው ደግሞ ወደ ውጭ ሳያንፀባርቅ ወደ ባህር ውስጥ የሚገባ የብርሀን ጨረር አለ።በሌላ ማእበል ለሁለት ይከፈላል።ውስጥ ለውስጥ የሚሄደው ማእበል ከሱ በታች ያለውን የባህሩን ወይም የውቅያኖሱን ጥልቀት የበለጠ ጨለማ እንዲሆን ያደርገዋል ሌላው ቀርቶ ጥልቀት ውስጥ ያሉት አሳዎች ማየት የመይችሉበት ደረጃ ይደርሳሉ የነሱ ብቸኛው የብርሃን ምንጭ ከአካላቸው የሚወጣው ብርሀን ይሆናል።

ምንጭ 👉 ቁርአንና ዘመናዊ ሳይንስ ይጣጣማሉ ወይስ ይጋጫሉ በዶ/ር ዛኪር ናይክ

28/06/2022

የወቅቱ የሙስሊሞች ፈተናና ውጣ ውረዶች👇

አሰላሙዐለይኩም ያ ጀመዓ- ምንም እንኳን እንደማንኛውም ኢትዮጵያውያን በሀገር ደረጃ የገጠመን ፈተና ትልቅ ቢሆንም እንደ ሙስሊም ደግሞ ሌሎች ሰፊ የቤት ስራዎች ከፊት ለፊታችን ተጋርጠው ይጠብቁናል።

-የተቋም እጦት(የመጅሊስ ፈተና)

-የእስልምና ጥላቻ(Islamophobia)

-የፖለቲካ ቁማር

-የሙስሊሞች የራሳችን የንቃት ማነስ(ተራው ህዝብ ላይ)
እና ሌሎች ጉዳዮች ከብዙ በጥቂቶቹ ናቸው። በቀጣይ ስለያንዳንዳቸው ጉዳዮች በዝርዝር እናያለን ኢንሻአላህ!!

27/05/2022

#ዱዐ

«መለመን ስትፈልግ አላህን ብቻለምን፣ እርዳታ ብትፈልግ በአላህ ብቻ ተረዳ» ቲርሚዚ ዘግበውታል

*ሁሉም ፍጡር ከአላህ ከጃይ ነው። አላህ ዘንድ ያለው ያስፈልገዋል። እርሱ(አላህ) ደግሞ ከፍጡራኑ የተብቃቃና ሀብታም ነው። አላህ የሚለምነውን ይወዳል። እሱን በመለመን ችክ ባዮቹንም ባሮች ይወዳል። ለዚህም ነው ሶሀቦች ለትንሽ ነገር ቢሆን እንኳን አላህን ከመለመን
የማይቦዝኑት።

*የዱዐዕ ደረጃ፡- ዱዐ አላህ ዘንድ ትልቅ ደረጃ አለው፤ የአላህን ቀደር ሊመልስ/ሊቋቋም/ ይችላል። ዱዐ ከእንቅፋቶች ከፀዳና ቅድመ ሁኔታው ከተሟላ ተቀባይነት አላው። አላህ(ሱ.ወ) እንዲህ ይላል «ጌታችሁም አለ ለምኑኝ እቀበላኋለው፤እነዛ እኔን ከመገዛት የሚኮሩት ተዋራጆች ሆነውጀሀነም ይገባሉ» 46፡60

*ነቢዩ(ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ይላሉ «ዱዐ እርሱ እራሱ
አምልኮ ነው» ቲርሚዚና ሌሎችም ዘግበውታል
በሌላ ቦታ ነቢዩ አህመድ በዘገቡት ሀዲስ «ዱዐ የኢባዳ መቅኒ ነው» ብለዋል። ዱዐ በኢስላም ቁርዐንን ከማንበብና ከዚክር በመቀጠል በላጭ የሆነ ኢባዳ ነው።

**ለዱዐ ተቀባይነት የሚረዱ መስፈርቶች፡-

የዱዐ ወቅቶች፡-
በለሊቱ የመጨረሻ ሲሶ ላይ፣ በአዛንና በኢቃማ መካከል፣ ከውዱዕ በኋላ፣ በሱጁድ ውስጥ፣ ከሶላት ማሰላመት በፊት፣ ከሶላቶች በኋላ፣ በቁርዐን ማኽተሚያ ወቅት፣ ዶሮ ሲጮህ፣ ሙሳፊር ሰው፣ የተቸገረ ሰው፣ የአባት ዱዐ
ለልጅ፣ ሙስሊም ወንድሙ በርቀት የሚያደርግለት፣ ከጠላት ጋር ሲገናኙ፣ በጁሙዐ ኩጥባ ሶላቱ እስኪያልቅና ከአሱር በኋላ፣ በረመዳን በፊጥርና በሱሁር ወቅት፣ ለይለተል ቀድር፣ የአረፋ ቀን ናቸው።

ሰደቃ፣ውዱዕ፣ ሶላት፣ ወደ ቂብላ መዞር እጅን ማንሳት፣ አላህን በተገቢው ሁኔታ ማወደስ፣በነቢዩ(ሰ.ዐ.ወ) ላይ ሶለዋት ማውረድ፣ ወንጀሉን ማመን፣ የአላህ ስሞችን እያነሱ መለመን… የመሳሰሉትን መጠቀም ናቸው።

***የዱዐ ቦታዎች፡-

በሁሉም መስጂዶች በተለይ ከካዕባ አጠገብ፣መቃሙ ኢብራሂም ዘንድ፣ ሶፋና መርዋ ላይ፣ በሐጅ ጊዜ(በዐረፋ፣በሙዝደሊፋና፣በሚና) ላይ፣
ዘምዘምን በሚጠጡበት ጊዜ ናቸው። ይሁን እንጅ አመቺ ሁኖ ባገኘነው ሁኔታ እና ቦታ ለይ አሏህን መለመን የተወደደ ተግባር ነው።

Aselamu aleykum werahmetullahi weberekatuh
24/05/2022

Aselamu aleykum werahmetullahi weberekatuh

Address

Omo Valley
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Omo Islamic Media-OIM posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share