Meri Konjoo

Meri Konjoo I'm Focusing on Facts and Unity:
I speak for the real facts and unwavering spirit of my Ethiopian people.
(2)

We reject the narratives of division and stand firm in our unity. 🇪🇹ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር። 🇪🇹
🙏

  በብርሃን ፍጥነት እየተቀየረች ነው! አዲስ አበባ የዛሬን ብቻ ሳይሆን የነገን ኢትዮጵያ እየገነባች ነው። በዘመናዊ መሠረተ ልማት፣ በአረንጓዴ ልማት፣ በተሻሻሉ መንገዶችና ኮሪደሮች፣ በቱሪዝ...
15/08/2026

በብርሃን ፍጥነት እየተቀየረች ነው! አዲስ አበባ የዛሬን ብቻ ሳይሆን የነገን ኢትዮጵያ እየገነባች ነው። በዘመናዊ መሠረተ ልማት፣ በአረንጓዴ ልማት፣ በተሻሻሉ መንገዶችና ኮሪደሮች፣ በቱሪዝም፣ በቴክኖሎጂ እና በኢንቨስትመንት ከተማዋ አዲስ መልክ እየያዘች ነው።

የትላንትናዋ አዲስ አበባ በታሪኳ ኩራት ነበረች፤ የዛሬዋ አዲስ አበባ ግን ታሪክን ከዘመናዊነት፣ ባህልን ከፈጠራ፣ እድገትን ከአረንጓዴ ከተማ ራዕይ ጋር እያጣመረች ወደፊት እየተራመደች ነው።

ይህ ለውጥ የአንድ ቀን ስራ አይደለም፤ የብዙ ሰዎች ጥረት፣ የልማት ራዕይ እና የጋራ ትብብር ውጤት ነው። ከተማችንን በንጽህና፣ በአረንጓዴነት፣ በፈጠራ እና በዘላቂ ልማት ይበልጥ ማስዋብ የሁላችንም ድርሻ ነው።

አዲስ አበባ — የአፍሪካ ዲፕሎማሲ ማዕከል፣ የኢትዮጵያ የእድገት ልብ፣ የነገ ራዕይ! 🇪🇹

#አዲስአበባ #ኢትዮጵያ #ልማት

አዲስ አበባን እንደ ደሴት ማሰብ ከንቱ ቁዠት ነው፤ የሀሰት ፕሮፖጋንዳው ይቁም!​በማህበራዊ ሚዲያ ላይ አዲስ አበባን እና ኦሮሚያን እርስ በርስ ለማጋጨት ሆን ተብለው የሚነዙ የተሳሳቱ ትርክቶ...
15/08/2026

አዲስ አበባን እንደ ደሴት ማሰብ ከንቱ ቁዠት ነው፤ የሀሰት ፕሮፖጋንዳው ይቁም!
​በማህበራዊ ሚዲያ ላይ አዲስ አበባን እና ኦሮሚያን እርስ በርስ ለማጋጨት ሆን ተብለው የሚነዙ የተሳሳቱ ትርክቶችን በስፋት እየተመለከትን ነው። ነገር ግን ሁላችንም በግልጽ ልንገነዘበው የሚገባው ትልቁ እውነታ፣ አዲስ አበባ ከኦሮሚያ ክልል ጋር ያላት ግንኙነት እጅግ ጥብቅ፣ የማይነጣጠል እና ተፈጥሯዊ መሆኑን ነው። አዲስ አበባን ከዙሪያዋ ካለው የተፈጥሮ ማህጸን ሙሉ በሙሉ ነጥሎ እንደ ደሴት ብቻዋን እንድትኖር ማድረግ ፈጽሞ የማይቻል እና ከተፈጥሮ ህግ ጋር የሚጋጭ ነው። ይህን ለማድረግ መሞከርም ሆነ እንደዚያ አድርጎ ማሰብ ከንቱ ቁዠት ነው።
​ከተማዋ የእለት ተዕለት የምግብ ፍጆታዋን፣ የውሃ አቅርቦቷን፣ የግንባታ ጥሬ እቃዋን እንዲሁም የኢንቨስትመንት ፍላጎቷን የምታሟላው ከዚሁ ተፈጥሯዊ ጎረቤቷ ጋር በጥብቅ በመቀናጀት ነው። ላለፉት 35 አመታት የኦሮሚያ ክልል መንግስት መቀመጫ በመሆን፣ ህዝቡም በሰላም፣ በፍቅር እና በመከባበር አብሮ ኖሯል። ይህ የ35 ዓመታት ጤናማ አብሮነት ዛሬም ወደፊትም የሚቀጥል እንጂ፣ ማንም ፖለቲከኛ በፈጠረው የሀሰት ትርክት የሚፈርስ አይደለም።
​ስለዚህ፣ ከተማዋን "ልትወረር ነው" ወይም "በሌላ ክልል ልትዋጥ ነው" በሚል የሚሰራጨው አፍራሽ እና የሀሰት ፕሮፖጋንዳ በአስቸኳይ መቆም አለበት። ህዝባችንም ኢትዮጵያን ለማፍረስ እና ወንድማማች ህዝቦችን ለማጋጨት ለሚሰሩ የጥፋት ሃይሎች የፈጠራ ወሬ በፍጹም ጆሮ መስጠት የለበትም። በእነዚህ ወገኖች የሚነዛው አሉባልታ ለሀገራችን ሰላም ምንም አይነት ፋይዳ የለውም። አዲስ አበባ የሁላችንም ማዕከል እና ፌደራላዊ ከተማ ሆና የሰላም ጉዞዋን አጠናክራ ትቀጥላለች። ከሀሰተኛ መረጃ ራሳችንን በማራቅ ለጋራ እድገታችን እና ለሰላማችን ዘብ እንቁም! ኢትዮጵያ በህዝቦቿ አንድነት ፀንታ ትኖራለች!

Happy 50th Birthday, Prime Minister Abiy Ahmed Ali ! May the years ahead bring health, happiness, and remarkable fulfill...
15/08/2026

Happy 50th Birthday, Prime Minister Abiy Ahmed Ali ! May the years ahead bring health, happiness, and remarkable fulfillment in every aspect of your life.

Addis Ababa stands at the heart of African diplomacy and is growing as a center for tourism, culture and investment. Wit...
14/08/2026

Addis Ababa stands at the heart of African diplomacy and is growing as a center for tourism, culture and investment. With Mayor Adanech Abiebie’s urban transformation agenda, the capital is creating new spaces and opportunities while celebrating its unique identity. 🇪🇹
Adanech Abiebie- አዳነች አቤቤ
የአዲስ አበባ ከተማ ኮሙኒኬሽን ቢሮ Addis Ababa City Communication

ኢትዮጵያ በዐቢቹ ዘመን ለአፍሪካ ሀገራት ዘመናዊ የልማት ተምሳሌት ለመሆን በቅታለች​የጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ አርቆ አሳቢ ራዕይና የመደመር ፍልስፍና የፈጠረው አዲስ የሐሳብ ልዕ...
14/08/2026

ኢትዮጵያ በዐቢቹ ዘመን ለአፍሪካ ሀገራት ዘመናዊ የልማት ተምሳሌት ለመሆን በቅታለች

​የጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ አርቆ አሳቢ ራዕይና የመደመር ፍልስፍና የፈጠረው አዲስ የሐሳብ ልዕልና፣ ዛሬ ላይ ኢትዮጵያን የውበት፣ የቱሪዝም እና የዘመናዊ ልማት ተምሳሌት አድርጓታል። ከቤተ መንግሥት ግቢ በመነሳት "ገበታ ለሸገር"፣ "ገበታ ለሀገር" እና "ገበታ ለትውልድ" በሚሉ ሀገራዊ ምዕራፎች አድማሱን ያስፋው ይህ የለውጥ ጉዞ፤ አንጦጦን፣ ወንጪን፣ ኮይሻን፣ ጎርጎራን እና መላው የኮሪደር ልማት ማዕከላትን በማስጌጥ የሀገራችንን ገጽታ ሙሉ በሙሉ ቀይሮታል። የሊቀ መመንገዱ ሌት ተቀን ያለማቋረጥ የመሥራት ባህልና ትናንት የተዘሩትን የልማት ነጠብጣቦች ዛሬ አቀናጅቶ ግዙፍ ሀገራዊ ምሥል የመፍጠር አቅም፣ እውነተኛ ሀገር ፍቅር በዕውን የሚታይ የልማት ሥራ እንጂ በባዶ ዲስኩር የሚለካ ባለመሆኑ ኢትዮጵያ የነገ ትውልድ ኩራት የሆነ አብዮታዊ የብልጽግና ከፍታ ላይ እንድትደርስ አስችሏታል። #አዲሲቷኢትዮጵያ #የዐቢይአሕመድራዕይ #የመደመርመንግሥት #የቱሪዝምአብዮት #ኮሪደርልማት #ገበታለሀገር #የኢትዮጵያብልጽግና #አፍሪካተምሳሌት
Ethio-Trends
Taye Bogale Arega
Hana Abiy Ahmed
የኢትዮጵያ ክንድ/Arm of Ethiopia

ምን አዲስ ነገር ተገኝቶ ነው? 35 ዓመት የክልሉ መቀመጫ አልነበረችም ወይ!በማህበራዊ ሚዲያ ላይ አዲስ አበባንና የኦሮሚያ ክልልን በተመለከተ አዳዲስና የሚያስፈሩ ትርክቶች ሆን ተብለው ሲፈበ...
14/08/2026

ምን አዲስ ነገር ተገኝቶ ነው? 35 ዓመት የክልሉ መቀመጫ አልነበረችም ወይ!
በማህበራዊ ሚዲያ ላይ አዲስ አበባንና የኦሮሚያ ክልልን በተመለከተ አዳዲስና የሚያስፈሩ ትርክቶች ሆን ተብለው ሲፈበረኩ እንሰማለን። ግን እስቲ ቆም ብለን በምክንያት እናስብ፤ ዛሬ የተለየ ምን አዲስ ነገር ተገኝቶ ነው? አዲስ አበባ ላለፉት 35 ዓመታት የኦሮሚያ ክልል መንግስት መቀመጫ ሆና አላገለገለችም ወይ?
በእነዚህ 35 ዓመታት ውስጥ ከተማዋ የፌዴራል መንግስቱ ርዕሰ መዲና፣ የብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በሰላም፣ በፍቅርና በአብሮነት የሚኖሩባት "ትንሿ ኢትዮጵያ" ሆና ዘልቃለች። በተጓዳኝ ደግሞ የኦሮሚያ ክልል ማዕከል በመሆኗ የተፈጠረ አንዳችም የጎላ ችግር አልነበረም። ይልቁንም ይህ ሁኔታ አብሮ ለማደግና ሰላምን ለማስፈን ትልቅ ዕድል የፈጠረ ነው።
ከተፈጥሯዊ ማህጸኗ ኦሮሚያ ጋር ያላት ጥብቅ ቁርኝት ትናንትም የነበረ፣ ዛሬም ያለ፣ ነገም የሚቀጥል ፀጋ እንጂ ስጋት ሊሆን አይችልም። "ልዩ ጥቅም" በሚለው የሕገ-መንግስት ቃል ፈንታ "የጋራ ተጠቃሚነት" የሚል ማዕቀፍ መዘጋጀቱ የ35 ዓመቱን ጤናማ አብሮነት ሕጋዊና ዘመናዊ ከማድረግ የዘለለ ምንም የተለየ አጀንዳ የለውም። ስለዚህ የፈጠራ ስጋቶችን ትተን የሁላችንም በሆነችው አዲስ አበባ የጋራ ብልጽግና ላይ ብቻ እናተኩር!

13/08/2026
  🇪🇹Under Mayor Adanech Abiebie, Addis Ababa continues to focus on development projects, job opportunities, urban transf...
12/08/2026

🇪🇹
Under Mayor Adanech Abiebie, Addis Ababa continues to focus on development projects, job opportunities, urban transformation and initiatives that improve citizens’ lives. A more beautiful, modern and attractive Finfinnee is being built through action and commitment. 🇪🇹🏙️
#አዲስአበባ #ኢትዮጵያ
Adanech Abiebie- አዳነች አቤቤ

ዶ/ር ዐቢይ፡ ኢትዮጵያን የቱሪዝም መዳረሻ አደረጓት።🇪🇹================//============ኢትዮጵያ ያላትን የተፈጥሮ ውበት፣ ታሪካዊ ቅርስና ልዩ ባህል ለዓለም በማስተዋወቅ የቱሪ...
12/08/2026

ዶ/ር ዐቢይ፡ ኢትዮጵያን የቱሪዝም መዳረሻ አደረጓት።🇪🇹
================//============
ኢትዮጵያ ያላትን የተፈጥሮ ውበት፣ ታሪካዊ ቅርስና ልዩ ባህል ለዓለም በማስተዋወቅ የቱሪዝም አቅሟን ወደ ኢኮኖሚያዊ ዕድል ለመቀየር እየሰራች ነው።

በዶ/ር ዐቢይ አህመድ የለውጥ አመራር ስር የቱሪዝም ልማት ላይ የተሰጠው ትኩረት፣ ተፈጥሮንና ቅርስን ከመጠበቅ ባለፈ የሥራ ዕድል፣ የገቢ ምንጭና የአገር ገጽታ ግንባታ እንዲሆኑ አዲስ አቅጣጫ እየፈጠረ ነው።

የኢትዮጵያ ውብ መልክዓ ምድሮች፣ ታሪካዊ ስፍራዎችና ባህላዊ ቅርሶች ለዓለም በበለጠ መልኩ እየተጋሩ ሲሄዱ፣ ኢትዮጵያ ከታሪኳ ብቻ ሳይሆን ከውበቷና ከተፈጥሮ ሀብቷም ተጠቃሚ የሆነች የቱሪዝም መዳረሻ እየሆነች ነው።

ኢትዮጵያን ማስተዋወቅ፣ ውበቷን ማሳየትና ሀብቷን ለብልጽግና መጠቀም—የነገ ተስፋን የሚገነባ ጉዞ ነው። 🇪🇹
Abiy Ahmed Ali

Address

Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Meri Konjoo posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share