Apple Tube

Apple Tube ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት ይቀላቀሉን

በኢትዮጵያ የህጻናት የልብ ህክምና ማዕከልን ስራዎች ለመደገፍ የሚያስችል የገቢ ማሰባሰቢያና የግንዛቤ ማስጨበጫ ዝግጅት በዋሽንግተን ተካሂዷል። የኢትዮጵያ የህጻናት የልብ ህክምና ማዕከል ዋና ...
31/10/2019

በኢትዮጵያ የህጻናት የልብ ህክምና ማዕከልን ስራዎች ለመደገፍ የሚያስችል የገቢ ማሰባሰቢያና የግንዛቤ ማስጨበጫ ዝግጅት በዋሽንግተን ተካሂዷል። የኢትዮጵያ የህጻናት የልብ ህክምና ማዕከል ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሄለን በፍቃዱ በዚሁ ወቅት እንደገለጹት ማዕከሉ በሙሉ አቅሙ እንዳይሰራ የአላቂ እቃዎች እጥረት ፈተና እንደሆነበት ገልፀዋል።

ማዕከሉ በሳምንት ሶስት የህጻናት ልብ ህክምና እንደሚያደርግ በመግለጽ፤ ቁሳቁሶች ቢሟሉለት ግን አምስት ህክምናዎችን ማድረግ እንደሚችል ዶክተር ሄለን ተናግረዋል። በአገር ውስጥም በውጭም ያሉ አጋር አካላት ድጋፋቸውን እንዲያጠናክሩ ጥሪ አቅርበዋል። በማዕከሉ የህጻናት ልብ ሃኪም ዶክተር ያዩ መኮንን በበኩላቸው ÷ በማዕከሉ ያላቸውን ተሞክሮና አጠቃላይ እንቅስቃሴዎች ገለጻ አድርገዋል።

አምባሳደር ፍጹም አረጋ የተካሄደው ዝግጅት አስቸኳይ የልብ ህክምና ለሚያስፈልጋቸው ህጻናት ለመድረስ ነው ያሉ ሲሆን የህጻናትን ልብ ለመታደግ ልባችሁ የሚነግራችሁን ስጡ ሲሉ ገልጸዋል። ኤምባሲው አጋር አካላትን በማስተባበር ለማዕከሉ ድጋፍ የሚያስገኙ ተግባራዊ ጥረቶችን እንደሚያደርግም አስታውቀዋል።

ቀይ መስሠር ተጥሷል!ክብርት ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ  የሰሞኑን ሀገራዊ ጉዳይ አስመልክቶ በቲውተር ገጻቸው እንዲህ ብለዋል፡-"ዘርና ሀይማኖት ለፖለቲካ ጥቅም እንዲውሉ ሲደረግ፤ ንጹሀን ዜ...
31/10/2019

ቀይ መስሠር ተጥሷል!

ክብርት ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ የሰሞኑን ሀገራዊ ጉዳይ አስመልክቶ በቲውተር ገጻቸው እንዲህ ብለዋል፡-

"ዘርና ሀይማኖት ለፖለቲካ ጥቅም እንዲውሉ ሲደረግ፤ ንጹሀን ዜጎቻችን በአሰቃቂ ሁኔታ ሲገደሉ፣ ሲፈናቀሉና ሲንከራተቱ ስናይ ስሜትን ለመግለጽ ቃላት ያጥራል፣ ለቅሶ፣ድንጋጤና ሥጋት የብዙዎችን በር አንኳኩቷል ሃዘናቸው ሃዘኔ/ሃዘናችን ነው። ለሀገርና ለህዝብ ጥቅም ሲባል ልናሰምረው እና ልናከብረው የሚገባን ቀይ መስመር ተጥሷል። አገራችንን ካንዣበበባት ክፉ አዳጋ ለማዳን ሁላችንም ሚና አለን፤ የሚመለከታቸው ሁሉ የበኩላቸውን መወጣት አለባቸው፡ቀይ መስመር መጣስ የለበትም እንበል።"

Address

Addiss Ababa
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Apple Tube posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category