Press Fact Check/የፕሬስ መረጃ ማጣሪያ

Press Fact Check/የፕሬስ መረጃ ማጣሪያ Contact information, map and directions, contact form, opening hours, services, ratings, photos, videos and announcements from Press Fact Check/የፕሬስ መረጃ ማጣሪያ, Media/News Company, �, Addis Ababa.

ከኢትዮጵያ መረብ ደህንነት አስተዳደር የተላለፈ የጥንቃቄ መልዕክት***************ከዉስጥ አዋቂዎች ጋር የተያያዙ ዋና ዋና የጥቃት ስጋቶችተቋማት ብዙውን ጊዜ ጠቃሚ ሀብቶችን ከጥቃት ለ...
24/04/2025

ከኢትዮጵያ መረብ ደህንነት አስተዳደር የተላለፈ የጥንቃቄ መልዕክት
***************

ከዉስጥ አዋቂዎች ጋር የተያያዙ ዋና ዋና የጥቃት ስጋቶች

ተቋማት ብዙውን ጊዜ ጠቃሚ ሀብቶችን ከጥቃት ለመጠበቅና በአግባቡ ለማስተዳደር ለተወሰኑ አካላት ሚስጥራዊ መረጃዎችን የማግኘት እድል ለዉስን ሰራተኞች ይሰጣሉ።

ይህን መብት ያገኘ አንድ ሰራተኛ ግልጽ ባልሆነ የሥራ ምክንያት ከተሰጠዉን መብት በላይ ለመጠቀም ከሞከረ፣ ይህ አይነቱ ሁኔታ ምናልባት የውስጥ አዋቂ ስጋት ምልክት ተደርጎ ይወሰዳል። ከዚህ በታችም የዉስጥ አዋቂዎች ጋር የተያያዙ የጥቃት ስጋቶች እንደሚከተለዉ ቀርበዋል፡

👉የመረጃ ምዝበራና ጥሰት

👉የአእምሮአዊ ንብረት ስርቆት

👉የተቋምን መረጃ መረጃና የመረጃ ስርአትን ማበላሸት

👉የገንዘብና ተያያዥ ጉዳዮች ማጭበርበር



#ጥንቃቄ

በበዓላት ወቅት በምን መልኩ ልንጭበረበር እንችላለን ሲል የኢትዮጵያ መረብ ደህንነት ኤጀንሲ የጥንቃቄ መልዕክት እንደሚከተለው አጋርቶናልበበዓላት ወቅት በዲጂታል ምህዳሩ ዉስጥ ከፍተኛ የሚባሉ ...
16/04/2025

በበዓላት ወቅት በምን መልኩ ልንጭበረበር እንችላለን ሲል የኢትዮጵያ መረብ ደህንነት ኤጀንሲ የጥንቃቄ መልዕክት እንደሚከተለው አጋርቶናል

በበዓላት ወቅት በዲጂታል ምህዳሩ ዉስጥ ከፍተኛ የሚባሉ የማጭበርበር እንቅስቃሴዎች ይስተዋላሉ። በተለይ ለወዳጅ ዘመዶቻችን ስጦታዎችን ለመግዛት በተለያዩ መንገዶች ከፍተኛ ግብይቶችን የምናከናዉንበት ወቅት መሆኑን ተከትሎ አጭበርባሪዎችም ይህንን እድል ለመጠቀም የተጠና እንቅስቃሴ የሚያደርጉበት ወቅት ነዉ። በዚህ ወቅት አጭበርባሪዎች የተለያዩ መንገዶችን የሚጠቀሙ ሲሆን ከእነዚህ መንገዶች መካከል፡-

👉በኢ-ሜይል/አጭር የጽሁፍ መልዕክቶችን በመላክ የሚፈጸም ማጨበርበር፡
አጭበርባሪዎች በዚህ መንገድ ጥቃት ለማድረስ የሚያግዛቸዉን አጥፊ ተልዕኮ ያላቸዉን ሊንኮች እንዲከፍቱና የክፍያ ዝርዝሮችን እንዲያስገቡ በመጠየቅ ጥቃቶችን ያደርሳሉ። በተለይ በተጠቂያቸዉ እምነትን ለማግኘት የታዋቂ ተቋማትን ስም ይጠቀማሉ፤

👉የበጎ አድራጎት ስራ በማስመሰል የሚፈጸሙ ማጭበርበሮች፡
በበዓላት ወቅት የበጎ አድራጎት ስራዎች ይጨምራሉ። አጭበርባሪዎችም የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን እንቅስቃሴ በመኮረጅ እና የድጋፍ ጥያቄዎችን በኢ-ሜይል ወይም በሌሎች አመራጮች በመላክ የሚፈጸሙ ማጭበርበሮች ስለጨመሩ ድጋፍ ከማድረግዎ በፊት፣ የድርጅቱን ህጋዊነት ያረጋግጡ።

👉ቅናሽ የጉዞና የማረፊያ ዋጋ ያቀረቡ በማስመሰል የሚፈጸሙ ማጭበርበሮች፡
በበዓላት ወቅት ቤተሰብ ዘመድ ለመጥየቅና አብሮ ለማሳለፍ የሚደረጉ የጉዞ እንቅስቃሴዎች ይጨምራሉ። ይህን ሁኔታም አጭበርባሪዎች በዝቅተኛ ዋጋ የማረፊያ እና የትራንስፖርት ዋጋ ያስተዋውቃሉ። ምንም እንኳ ይህ ሁኔታ አጓጊ ቢሆንም ስለትክክለኛነቱ መለስ ብሎ ማሰብና ማረጋገጥ ይገባል።

👉ከክፍያ ጋር የተያያዙ ማጭበርበሮች፤
አጭበርባሪዎች ሰዎች በበዓላት ወቅት ትኩረታቸው በበዓል ጉዳዮች ስለሚወሰድ ጥንቃቄ እንደሚቀንስ ያውቃሉ። ይህን ጊዜ አጭበርባሪዎች የከፈልናቸዉን ክፍያዎች እንዳልከፈልን ሳይከፍሉን ደግሞ ክፍለናል ብለዉ በዲጂታል የክፍያ አመራጭ ሊያጭበረብሩን ስለሚችሉ ክፍያዎችን ስንፈጽምና ስንቀበል በጥንቃቄ ልናድረግ ይገባል።



#ጥንቃቄ
#መረጃማጣሪያ

ወደ አውሮፓና አሜሪካ ዜጎችን ለሥራ ለማሰማራት ለየትኛውም አካል ውክልና አልተሰጠም **********************(ፕሬስ መረጃ ማጣሪያ) በውጭ ሀገር ስራ ስምሪት አገልግሎት ወደ አውሮፓ...
13/04/2025

ወደ አውሮፓና አሜሪካ ዜጎችን ለሥራ ለማሰማራት ለየትኛውም አካል ውክልና አልተሰጠም
**********************
(ፕሬስ መረጃ ማጣሪያ)

በውጭ ሀገር ስራ ስምሪት አገልግሎት ወደ አውሮፓ እና አሜሪካ ሀገራት ዜጎችን ለሥራ ለማሰማራት ለየትኛውም አካል ውክልና አለመስጠቱን የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር አስታወቀ።

ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ በጉዳዩ ላይ የሚከተለውን የጥንቃቄ መልዕክት በማህበራዊ ትስስር ገጹ አስተላልፏል።

ካናዳን ጨምሮ በተለያዩ የአውሮፓ ሀገራት ለሥራ ዜጎችን እንልካለን፡፡ ለዚህም ከሚመለከታቸው አካላት ፍቃድ አግኝተናል በሚል በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገጾች ህገ-ወጥ ማስታወቂያዎችን በማሰራጨት ህብረተሰቡን ለአላስፈላጊ ወጪና እንግልት እየዳረጉ በመሆኑ መሰል የማጭበርበር ተግባር እየፈፀሙ የሚገኙ አካላትን በህግ ተጠያቂ ለማድረግ ሚኒስቴር መስሪያ ቤታችን በትኩረት እየሰራ ይገኛል፡፡

በውጭ ሀገር ስራ ስምሪቱ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ወደ አውሮፓና አሜሪካ ዜጎችን ለሥራ ለማሰማራት ለየትኛውም አካል የሰጠው ውክልና የሌለ መሆኑን እየገለጽን ዜጎቻችን በስምሪቱ ተጠቃሚ ለመሆን ህጋዊ አማራጮችን ብቻ በመጠቀም ካላስፈላጊ ወጪ፣ እንግልትና ሌሎች አስከፊ አደጋዎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡

የሁለትዮሽ ስምምነት በተፈረመባቸው መዳረሻ ሀገራት የሥራ ዕድል ማግኘት ከፈለጉ የሚከተለውን ማስፈንጠሪያ (lmis.gov.et) በመጠቀም የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ላይ በመመዝገብ ደህንነቱ የተረጋገጠ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ተጠቃሚ ይሁኑ ሲልም መልዕክት አስተላልፏል፡፡

ሚያዝያ 5 ቀን 2017 ዓም



#ጥንቃቄ

በማህበራዊ ሚዲያዎችና በኢንተርኔት ሊደርሱብን የሚችሉ የሳይበር ጥቃቶችን ለመከላከል ሊወሰድ የሚገባ ጥንቃቄየማህበራዊ ሚዲያዎችና በኢንተርኔት የሚፈጸሙ የማጭበርበር እንቅስቃሴዎች እየበረከቱ ይ...
12/04/2025

በማህበራዊ ሚዲያዎችና በኢንተርኔት ሊደርሱብን የሚችሉ የሳይበር ጥቃቶችን ለመከላከል ሊወሰድ የሚገባ ጥንቃቄ

የማህበራዊ ሚዲያዎችና በኢንተርኔት የሚፈጸሙ የማጭበርበር እንቅስቃሴዎች እየበረከቱ ይገኛሉ። በመሆኑም ይህንን መሰል የዲጂታል ማጭበርበሮችና ለመከላከል ልንወስዳቸዉ የሚገቡ የጥንቃቄ ርምጃዎች ያሉ ሲሆን ከእነዚህ ዉስጥ የሚከተሉት ይገኙበታል ሲል የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር አስታውቋል።

👉ያልታወቁ አድራሻዎችን ወይም ሊንኮችን ከመክፈት በመቆጠብ፤
ከላይ ያሉትን ወይም ተመሳሳይ አድራሻዎች በመልዕክት፣ በማህበራዊ መገናኛ፣ ወይም በሌላ መንገድ ከደረስዎ ከመክፈት መቆጠብ በተለይ “እንኳን ደስ ያለህ! ገንዘብ አሸንፈሃል፣ ይህን አገናኝ ጫን” የሚል መልዕክት ከመጣ፣ ይህ ማጭበርበሪያ ሊሆን ስለሚችል መጠንቀቅ፤

👉የሞባይል እና የባንክ መረጃዎችን ደህንነቱ በተጠበቀ መልኩ በመጠቀም፤
የሞባይል ባንኪንግ መተግበሪያዎችን ከታመኑ ምንጮች (እንደ Google Play) ወይም አፕስቶር (app-store) ብቻ ያውርዱ።
👉የይለፍ-ቃልዎን ወይም የባንክ መለያዎችን ባልታወቁ ድረ-ገፆች ከማስገባት መቆጠብ፤

👉በዲጂታል ሚዲያዎች አጠራጣሪ ነገሮችን ሲመለከቱ ሪፖርት በማድረግ፤
እንደዚህ አይነት መልዕክቶች ወይም አድራሻዎች ካዩ፣ ወዲያውኑ ለEthio-CERT በኢ-ሜይል ([email protected]) ወይም በስልክ (933) ያሳውቁ፤

👉በነፃ Wi-Fi ስንጠቀም በጥንቃቄ በመጠቀም፤
በካፌዎች፣ በሆቴሎች፣ ወይም በሌሎች የህዝብ ቦታዎች ያለውን ነፃ Wi-Fi ሲጠቀሙ፣ የግል መረጃዎችን አያስገቡ።

11/04/2025

ትዕቢት ውድቀትን ታስከትላለች!!
ፓስተር ጻዲቁ አብዶ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ህብረት ፕሬዚዳንት

ከኢትዮጵያ ኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር  የተላለፈ የጥንቃቄ መልዕክት *********************(ፕሬስ መረጃ ማጣሪያ)የጥንቃቄ መልዕክት ለቴሌግራም ተጠቃሚዎች❗️የኢንተርኔት...
10/04/2025

ከኢትዮጵያ ኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር የተላለፈ የጥንቃቄ መልዕክት
*********************
(ፕሬስ መረጃ ማጣሪያ)

የጥንቃቄ መልዕክት ለቴሌግራም ተጠቃሚዎች❗️
የኢንተርኔት አጠቃቀም በየቀኑ እየጨመረ በሄደበት በዚህ ዘመን፣ ከዚህ ጋር ተያይዘው የሚመጡ ስጋቶችም እየተስፋፉ ነው። የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በቅርቡ በርካታ አደገኛ የኢንተርኔት አድራሻዎችን (URLs) መርምሮ፣ እነዚህ አድራሻዎች ለሀገራችን የኢንተርኔት ተጠቃሚዎች በይበልጥ የቴሌግራም ተጠቃሚዎች አካዉንቶችን በመንጠቅን ከፍተኛ ስጋት ሊያስከትሉ እንደሚችሉ አረጋግጧል። ከተለያዩ አካላት በቴሌግራም የሚደርሱን ሊንኮች በርካታ አደጋዎችን የሚይዙ ሲሆን የሚከተሉት አደጋዎች በዋናነት ይገኙበታል፡
👉የግል መረጃ መጠለፍ:- እንደ የባንክ መለያ ወይም የይለፍ ቃል ያሉ መረጃዎችን መሰረቅ፤
👉የማልዌር ስርጭት:- ስልኮችን ወይም ኮምፒውተሮችን የሚጎዱ ቫይረሶች፤
👉ማጭበርበሪያ:- ተጠቃሚዎችን በሀሰተኛ ተስፋዎች (እንደ ውርርድ ወይም ኢንቨስትመንት) መታለል፤
በመሆኑም ማኅበረሰቡ በቴሌግራም አማካኝነት የሚላኩለትን አጠራጣሪ ሊንኮች ከመክፈት እንዲቆጠብ እያሳሰብን፤ ሰሞኑን በቴሌግራም ከሚላኩና በፍጹም ልንከፍታቸዉ ከማይገቡ ሊንኮች መካከል የሚከተሉት ከታች በምስሉ ያሰፈርናቸዉ ይገኙበታል፡፡
ከዚሁ ጋር በተያያዘ በቴሌግራማችን አጠራጣሪ የሆኑ ሊንኮች ካጋጠመን ለኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር በሚከተሉት አድራሻዎች ማሳወቅ የሚችሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
• e-mail: [email protected]
• ነጻ የስልክ መስመር፡ 933



#ጥንቃቄ

ከአጭበርባሪዎች እንጠንቀቅ!!(ኢፕድ መረጃ ማጣሪያ)
08/04/2025

ከአጭበርባሪዎች እንጠንቀቅ!!
(ኢፕድ መረጃ ማጣሪያ)

የርእሰ መስተዳድሩ ቤተሰብ በመምሰል ገንዘብ ለመሰብሰብ ሙከራ ያደረገች ተጠርጣሪ በቁጥጥር ስር ዋለች
*************
(ኢ ፕ ድ)

የሀረሪ ክልል ርዕስ መስተዳድር አቶ ኦርዲን በድሪ ቤተሰብ በመምሰል ከተለያዩ ባለሃብቶች ገንዘብ በመሰብሰብ ወንጀል የተጠረጠረች ግለሰብ በፖሊስ በቁጥጥር ስር ዋለች።

የሀረሪ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን እንዳስታወቀው ወ/ሮ ነጀሃ ጠሃ ዩሱፍ የተባለችው ተጠርጣሪ የርዕሰ መስተዳድሩ ቤተሰብ ነኝ በማለት ወደተለያዩ ባለሃብቶች ስልክ በመደወል ገንዘብ ስታስልክ እንደነበረ ፖሊስ ባደረገው ክትትል ተረጋግጧል።

ከዚህ በተጨማሪም ተጠርጣሪዋ በሌሎች በመሰል ከፍተኛ የማጭበርበር ስራ ላይ ተሰማርታ መቆየቷን የሚያመላክቱ መረጃዎች እንዳሉ ተገልጿል።

አሁን ላይ ግለሰቧ በቁጥጥር ስር ውላ ምርመራ እየተጣራ መሆኑን ያስታወቀው ፖሊስ በቀጣይም ጉዳዩን በሚመለከት በዝርዝር ለህዝብ ይፋ እንደሚደረግ ተመላክቷል።

ህዝቡ ከዚህ አይነት የማጭበርበር ድርጊቶች ሰላባ እንዳይሆን ጥንቃቄ እንዲያደርግና አጠራጣሪ ክስተቶች ሲያጋጥሙ ለፖሊስ ጥቆማ እንዲሰጥ ኮሚሽኑ ማሳሰቡን የክልሉ ኮሙኒኬሽን ዘግቧል።

መጋቢት 30 ቀን 2017 ዓም

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ለአባላቱ የጥንቃቄ መልዕክት አስተላለፈ*****************(የፕሬስ መረጃ ማጣሪያ)የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያና...
07/04/2025

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ለአባላቱ የጥንቃቄ መልዕክት አስተላለፈ
*****************
(የፕሬስ መረጃ ማጣሪያ)

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል መዋጮ አስገቡ በማለት የግለሰብ አካውንት እየላኩ ማህበረሰቡን የማጭበርበር ተግባር እየፈጸሙ ያሉ ግለሰቦች በመኖራቸው አባላቱ እንዲጠነቀቁ መልዕክት አስተላለፈ፡፡

ካውንስሉ ባወጣው የጥንቃቄ መልዕክት በስሩ የመዘገባቸው ቤተ- እምነቶችን በካውንስሉ መተዳሪያ ደንብና መመሪያዎች መሰረት የማጥራት ስራውን እየሰራ መሆኑ አስታውቋል፡፡

ከዚሁ ጋር ተያይዞ በካውንስሉ የፌስ ቡክ ገጽ ላይ የተለጠፈውን የቤተ እምነቶችን አድራሻ በመጥቀስ በ0910106908 እና 0932676452 ስልክ ቁጥሮች በመደወል ከካውንስሉ ጽህፈት ቤት እንደሆነ በመጥቀስ አመታዊ መዋጮአችሁን አስገቡ በማለት የግለሰብ አካውንት እየላኩ ማህበረሰቡን የማጭበርበር ተግባር እየፈጸሙ ያሉ ግለሰቦች መኖራቸውን ገልጹዋል፡፡

ስለሆነ የካውንስሉ አባላት በሙሉ ጥንቃቄ እንድያደርጉ እና ማንኛውንም ጉዳይ ወደ ካውንስሉ ጽህፈት ቤት በአካል በመምጣት እንድያስፈጽሙ ያስታወቀ ሲሆን፤ የሚመለከታቸው የህግ አካላትም የስልክ ቁጥሮቹን በመጠቀም የሚሰራውን ወንጀል እንድያስቆሙ ጥሪ አቅርቧል፡፡የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ለአባላቱ የጥንቃቄ መልዕክት አስተላለፈ

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል መዋጮ አስገቡ በማለት የግለሰብ አካውንት እየላኩ ማህበረሰቡን የማጭበርበር ተግባር እየፈጸሙ ያሉ ግለሰቦች በመኖራቸው አባላቱ እንዲጠነቀቁ መልዕክት አስተላለፈ፡፡

ካውንስሉ ባወጣው የጥንቃቄ መልዕክት በስሩ የመዘገባቸው ቤተ- እምነቶችን በካውንስሉ መተዳሪያ ደንብና መመሪያዎች መሰረት የማጥራት ስራውን እየሰራ መሆኑን አስታውቋል፡፡

ከዚሁ ጋር ተያይዞ በካውንስሉ የፌስ ቡክ ገጽ ላይ የተለጠፈውን የቤተ እምነቶችን አድራሻ በመጥቀስ በ0910106908 እና 0932676452 ስልክ ቁጥሮች በመደወል ከካውንስሉ ጽህፈት ቤት እንደሆነ በመጥቀስ አመታዊ መዋጮአችሁን አስገቡ በማለት የግለሰብ አካውንት እየላኩ ማህበረሰቡን የማጭበርበር ተግባር እየፈጸሙ ያሉ ግለሰቦች መኖራቸውን ገልጹዋል፡፡

ስለሆነ የካውንስሉ አባላት በሙሉ ጥንቃቄ እንድያደርጉ እና ማንኛውንም ጉዳይ ወደ ካውንስሉ ጽህፈት ቤት በአካል በመምጣት እንድያስፈጽሙ ያስታወቀ ሲሆን፤ የሚመለከታቸው የህግ አካላትም የስልክ ቁጥሮቹን በመጠቀም የሚሰራውን ወንጀል እንድያስቆሙ ጥሪ አቅርቧል፡፡

#ጥንቃቄ

ከኢትዮጵያ  ንግድ ባንክ የተሰጠ መግለጫ ሙሉዉን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ!!
07/04/2025

ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተሰጠ መግለጫ
ሙሉዉን ለማንበብ ሊንኩን ይጫኑ!!

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለመንግሥት ያበደረው ብር አለመኖሩን አስታወቀ
***************
(ኢ ፕ ድ)

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለመንግሥት ያበደረው ብር አለመኖሩን በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ባወጣው መግለጫ አስታወቀ።

ለመንግሥት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ካቀረበው እውነታ ባፈነገጠና በተዛባ መልኩ የሪፖርተር ጋዜጣ በዜና አርዕስቱ “መንግስት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተበደረው አንድ ትሪሊየን ዕዳ እንዳለበት ተገለጸ” እንዲሁም በሌሎች ጥቂት ሚዲያዎች የመንግስት ዕዳ ብር 1 ነጥብ 3 ትሪሊየን እንደተሻገረና አሁናዊ የመንግስት የብድር ዕዳ ዕድገትን የሚያሳይ በሚመስል መልኩ የቀረበው ዘገባ ሐሰተኛ መሆኑን አስታውቋል፡፡

ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተሰጠ መግለጫ እንደሚከተለው ቀርቧል።

የኢትዮዽያ ንግድ ባንክ ለመንግስት አንድም ብር አበድሮ አያውቅም!

የኢትዮዽያ ንግድ ባንክ በዚህ በጀት ዓመትም ሆነ ከዚያ በፊት አንድም ብር ለመንግስት በቀጥታ አበድሮ አያውቅም። መንግስት ከሀገር ውስጥ የንግድ ባንኮች (በብሔራዊ ባንክ በኩል ለሽያጭ ከሚቀርበው የግምጃ ቤት ሰነድ ግዢ ውጪ) በቀጥታ የመበደር አሰራርም ሆነ ልምድ የለውም። ሀቁ ይህ ሆኖ ሳለ የኢትዮዽያ ንግድ ባንክ በዚህ በተገባደደው ሳምንት ለኢ.ፌ.ዲ.ሪ. የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመንግስት የልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የስምንት ወራት የስራ አፈጻጸም ማቅረባችንን ተንተርሶ በሪፓርተር ጋዜጣ የዕሁድ ዕትም ቅጽ 30 ቁጥር 2602 መጋቢት 28 ቀን 2017 ዓ.ም. ታትሞ የተሰራጨው ዜና ከርዕሱ ጀምሮ ለቋሚ ኮሚቴው ከቀረበው ሪፖርትም ሆነ ከእውነታው የተለየና የተዛባ መረጃ ሆኖ አግኝተነዋል። ለምሳሌ በጋዜጣው ዕትም ርዕስ ላይ የተገለጸውና “̋መንግስት ከኢትዮዽያ ንግድ ባንክ የተበደረው አንድ ትሪሊየን ዕዳ እንዳለበት ተገለጸ” የተባለው ዜና ከእውነት የራቀ ከመሆኑም በላይ በሪፖርቱም ፈጽሞ እንደዚህ አይነት ኃሳብ አልቀረበም።

“ባለፉት 15 ዓመታት 92 በመቶ ብድር የተሰጠው ለመንግስት ተቋማት ነው ተብሏል” የሚለው ኃሳብም ስህተት ነው። የቀረበው ሪፖርት በግልጽ እንደሚያሳየው ከለውጡ በፊት የባንካችን የብድር ትኩረት ለመንግስት ተቋማት እንደነበርና ይህ ብድር አድጎ በመጨረሻም ከአምስት ዓመት በፊት እስከ 92% እንደደረሰ እና ከአምስት ዓመት ወዲህ ግን ያ አሰራር የተቀየረና ቅድሚያ ለግል ተበዳሪዎች እየተሰጠ በመሆኑ ፤ ለምሳሌ ያህል በዚህ ስምንት ወራት ከተሰጠው ጠቅላላ ብር 264.65 ቢሊዮን ብድር ውስጥ ከ88% በላይ ብድር የተሰጠው ለግሉ ዘርፍ በመሆኑ አሁን ያለው የመንግስት ተቋማት የብድር ክምችት ድርሻ ወደ 72% ዝቅ ማለቱን ተመላክቷል።

በመሰረቱ ይህ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ዕዳ መንግስት በቀጥታ ራሱ የተበደረው የመንግስት ዕዳ ሳይሆን የተለያዩ እንደ ባንካችን ያሉ የመንግስት የልማት ድርጅቶች የተበደሩት ዕዳ ነው። መንግስት በእነኚህ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ውስጥ የባለቤትነት ድርሻ ቢኖረውም እነዚህ ተቋማት ከአስፈፃሚው መንግስት የተለዩና የራሳቸው ካፒታል ያላቸው፣ እንደ ማንኛውም ድርጅት ንግድ ፍቃድ አውጥተው የሚነግዱ፣ በድርጅታቸው ስም ገንዘብ የሚበደሩ፣ ሊያተርፉም ሆነ ሊከስሩ የሚችሉ፣ ለትርፍ የተቋቋሙ የልማት ድርጅቶች ሲሆኑ ብድሮቹንም የወሰዱት ለራሳቸው ፕሮጀክቶች በመሆኑ ለእነዚህ ተቋማት የተሰጠውን ብድር የመንግስት ብድር ተደርጎ መወሰዱ ስህተት ነው። በሀገሪቱ የማክሮ ኢኮኖሚ አስተዳደር መሰረት መንግስት ማንኛውም ዓይነት የአጭርም ሆነ የረጅም ግዜ የገንዘብ ፍላጎቱን በሕግ በተቀመጠው አሰራርና ምንጭ ያሟላል እንጂ ከሀገር ውስጥ የንግድ ባንኮች በቀጥታ ብድር የሚወስድበት አግባብ የለም።

ትክክለኛው እውነታ ይህ ሆኖ እያለ አንዳንድ የመገናኛ ብዙኃን ዕዳውን መንግስት በቀጥታ የተበደረው ዕዳ እንደሆነ አድርገው በሪፖርተር ጋዜጣም ሆነ ጋዜጣውን ተከትለው በወጡ አንዳንድ የሚዲያ አካላትም መረጃውን በተዛባና በተሳሳተ መልኩ መዘገባቸው ከባንካችን መግለጫ አውድ ውጭ የቀረበ ከመሆኑም በላይ የጋዜጣው ርዕስ በውስጡ ከተጻፉት ኃሳቦች ጋርም ያልተጣጣመ መሆኑ አንባቢያንን ግራ ሊያጋባ እንደሚችል ስለሰጋን እውነታውን ለማሳወቅ ተገደናል።

በጋዜጣው በጉልህ ከተገለጸው በተቃራኒ መንግስት የልማት ድርጅቶች ከባንካችን የተበደሩትንና ለበርካታ ዓመታት ሳይከፍሉ የቆዩትን ከፍተኛ የብድር ገንዘብ በባንካችን ላይ የደቀነውን አደጋ በመገንዘብ የሚከተሉትን እርምጃዎች በመውስድ ባንካችንን ከውድቀት ታድጎታል።

1ኛ. የልማት ድርጅቶቹ ከባንካችን ብድሩን የሚወስዱበት አሰራር አመላለሱን የሚያረጋግጥ ስላልነበረ ይህ አሰራር ሙሉ በሙሉ እንዲቀርና ባንካችን የውሳኔ ነጻነት እንዲኖረው ለመንግስት ተቋማትም ቢሆን አዋጭ የንግድ ኃሳብ ለሚያቀርቡና ባንካችን ስለአመላለሱ እርግጠኛ ለሆነባቸው ብቻ ብድር እንዲሰጥ አቅጣጫ የተቀመጠው ከ5 ዓመት በፊት ነው። ይህ ብቻ ሳይሆን ቅድሚያ ለግል ተበዳሪዎች እንዲሰጥ እና የመንግስት የልማት ድርጅቶችም ቀድመው የጀመሩትን ፕሮጀክቶች ሳይጨርሱ ሌላ እንዳይጀምሩ ስለተደረገ ከ5 ዓመት በፊት 92% ደርሶ የነበረው የመንግስት ተቋማት አጠቃላይ የብድር ድርሻ ወደ 72% በአጭር ጊዜ ውስጥ ዝቅ ማለቱ እና የግሉ ተበዳሪዎች ድርሻ ደግሞ ከ8% ወደ 28% በፍጥነት ማደጉ ከፍተኛ ስኬት ሆኖ የቀረበና አንባቢያን ሊያውቁት የሚገባው ጥሬ ሀቅ ነው።

2ኛ. የልማት ድርጅቶቹ በወቅቱ መመለስ ያልቻሉትን ዕዳ በተመለከተ

ሀ. መጀመሪያ የመንግስት ዕዳ እና ኃብት አስተዳዳሪ ድርጅት በማቋቋም እዳዎቹን እንዲከፍል ከፍተኛ ጥረት ተደርጓል። በዚህ ጥረትም ከብር 42.4 ቢሊዮን በላይ እንዲከፈል ተደርጓል።

ለ. ችግሩ በዕዳና ሀብት አስተዳደር ድርጅት ጥረትም ሊፈታ እንደማይችል በመረጋገጡ በዚህ የበጀት ዓመት መጀመሪያ ላይ አጠቃላይ የአከፋፈል ችግር የገጠመው የመንግስት የልማት ድርጅቶች የብር 845.3 ቢሊዮን ዕዳ ተሰባስቦ ወደ ገንዘብ ሚኒስቴር እንዲዞር እና በየዓመቱ በጀት ተይዞለት እና በአስተማማኝ ሁኔታ እንዲከፈል ለዚህም ተመጣጣኝ የመንግስት ቦንድ ለባንካችን እንዲሰጥ በፓርላማ ጭምር በማጸደቅ ኃላፊነት የሚሰማውና ቆራጥ መንግስት ብቻ የሚፈጽመው ታሪክ በመስራት ባንካችንን ከውድቀት ኢኮኖሚያችንንም ከትልቅ አደጋ ያዳነ እርምጃ በመውሰዱ መንግስታችንን እጅግ በጣም አመስግነናል፤ አሁንም እጅግ በጣም እናመሰግናለን። ከዚሁ ከተዛወረው ዕዳ ላይ ደግሞ በስምምነቱ መሰረት የመጀመሪያ የግማሽ ዓመት ወለድ በጥር ወር መጀመሪያ ላይ በገንዘብ ሚኒስቴር በኩል ብር 38 ቢሊዮን ለባንካችን ተከፍሏል። ስለዚህ መንግስት ባንካችንን ለማዳን ሲል ከልማት ድርጅቶች ተቀብሎ መክፈል ከጀመረው ዕዳ ውጪ የተበደረው ምንም ገንዘብ እንደሌለ ለሕዝባችን ማሳወቅ እንፈልጋለን።

3ኛ. መንግስት ከልማት ድርጅቶች ከተረከበው ከፍተኛ ዕዳ በተጨማሪ ባንካችንን ለማጠናከር የብር 54.7 ቢሊዮን የካፒታል ጭማሪ በማድረግ ከላይ ከተገለጸው የድርጅቶች ዕዳ ጋር ተደምሮ ብር 900 ቢሊዮን የመንግስት ቦንድ እንዲሰጠን በማድረጉም ባንካችንን ሊገጥሙት የሚችሉትን የፋይናንሻል ስጋቶችን መቋቋም ብቻ ሳይሆን ጠንካራ እና ተወዳዳሪ ባንክ እንዲሆን ረድቶታል።

4ኛ. መንግስት ባንካችንን የበለጠ ለማጠናከር ከዓለም ባንክ ጋር በመተባበር ላለፉት አምስት ዓመታት ጥልቅ ሪፎርም እንድናደርግ ከፍተኛ ድጋፍ እና አመራር የሰጠን ሲሆን የባንካችን ካፒታል የበለጠ እንዲጠናከርና የውጪ ምንዛሬ ፍላጎታችንን ለማሟላት ያለመ 650 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር የካፒታል ማሳደጊያ ድጋፍ እንድናገኝ በማድረጉ ባንካችንን የበለጠ የሚያገዝፈው እና የማይበገር ጠንካራ ተወዳዳሪ የሚያደርገው የመንግስታችን ልዩ ድጋፍ በመሆኑ ባንካችን አሁንም አብዝቶ ያመሰግናል።

እንግዲህ እውነታው ይህ ሆኖ ሳለ በስብሰባው ላይ የቀረቡትና ሕዝባችን ሊያውቃቸው የሚገቡ ብዙ መልካም ዜናዎች እያሉ ያለመታደል ሆኖ አሉታዊ ዜና የመናፈቅ ችግር ጎልቶ በታየበት አኳኋን ሪፖርተርም ሆነ ሌሎች ጥቂት ሚዲያዎች የባንካችንን እጅግ በጣም አንጸባራቂ የስምንት ወራት አፈጻጸም ላይ ጥላሸት ለመቀባት መሞከራቸው አሳዛኝ ተግባር ሆኖ አግኝተነዋል።

በመጨረሻም ባንካችን ለመንግስት ልማት ድርጅቶች ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴው በግልጽ ካቀረበው እውነታ ባፈነገጠና በተዛባ መልኩ የሪፖርተር ጋዜጣ በዜና አርዕስቱ “መንግስት ከኢትዮዽያ ንግድ ባንክ የተበደረው አንድ ትሪሊዮን ዕዳ እንዳለበት ተገለጸ” በሚል እንዲሁም በሌሎች ጥቂት ሚዲያዎችም የመንግስት ዕዳ ብር 1.3 ትሪሊዮን እንደተሻገረና አሁናዊ የመንግስት የብድር ዕዳ ዕድገትን የሚያሳይ በሚመስል መልኩ ተቀናብሮ የቀረበው ዘገባ ሀሰተኛ ከመሆኑም ባሻገር ከላይ በዝርዝር በተመላከቱት እውነተኛ መረጃዎች ላይ ተመስርቶ በባንካችን በኩል የቀረበውን ትክክለኛ ሪፖርት የማያንጸባርቅ እና እነዚህን ለመንግስት የልማት ድርጅቶች የተሰጡትን ብድር ለባንካችን ለመክፈል መንግስት እያደረገ ያለውን ቁርጠኝነት ታሳቢ ያላደረገ በመሆኑ ጉዳዩ በሚመለከታቸው ሚዲያዎች የተላለፈው የተዛባና የተሳሳተ ዘገባ እንዲታረም እናሳስባለን።

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ሹመትን አስመልክቶ እየተሰራጨ የሚገኘው ደብዳቤ ሀሰተኛ ነው*******************(የፕሬስ መረጃ ማጣሪያ)በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ፒኤችዲ)...
05/04/2025

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ሹመትን አስመልክቶ እየተሰራጨ የሚገኘው ደብዳቤ ሀሰተኛ ነው
*******************
(የፕሬስ መረጃ ማጣሪያ)

በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ (ፒኤችዲ) ለአቶ ጌታቸው ረዳ መጋቢት 27/2017 ዓ/ም እንደተፃፈ ተደርጎ እየተሰራጨ የሚገኝ ደብዳቤ እንዳለ ተስተውሏል።
"የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ርዕሰ መስተዳድር ሆነው እንዲቀጥሉ" በሚል ርዕስ ተቀናብሮ የቀረበው ደብዳቤው አቶ ጌታቸው ረዳ የክልሉ ግዜያዊ አስተዳደር ሆነው እንዲቀጥሉ በጠቅላይ ሚኒስትሩ መወሰኑን የሚገልጽ ነው።
የፕሬስ መረጃ ማጣሪያ በደብዳቤው ላይ ባደረገው ማጣራት በቅንብር የቀረበ ሀሰተኛ ደብዳቤ መሆኑን አረጋግጧል።
ሀሰተኛ ደብዳቤው መጋቢት 13/2017 ዓ/ም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ለረዳት ፕ/ር ነብዩ ባዬ የሰጡትን ትክክለኛ ደብዳቤ በመጠቀም እና እሱን ኤዲት በማድረግ የተቀናበረ መሆኑን ለማየት ተችሏል።
ከዚህም በተጨማሪ ጎግል ሌንስ በመጠቀም ባደረግነው ማጣራት 'መጋቢት 27' የሚለው ቀን እና ሙሉው የደብዳቤው የፅሁፍ አካል በቅንብር ተቆርጦ ለረዳት ፕ/ር ነብዩ የተፃፈው ደብዳቤ ላይ መቀጠሉን አይተናል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ቀጣዩን የክልሉን ጊዜያዊ አስተዳደር መሪ ለመምረጥ ህዝቡ በኢሜይል ጥቆማ እንዲሰጥ ከቀናት በፊት ሀሳብ ማቅረባቸው የሚታወስ ነው፡፡



#መረጃማጣሪያ
#ጥንቃቄ

በማህበራዊ ሚዲያ ከሚሰራጩ አሳሳች መረጃዎች ስለመጠንቅ!!*******************(የፕሬስ መረጃ ማጣሪያ)
29/03/2025

በማህበራዊ ሚዲያ ከሚሰራጩ አሳሳች መረጃዎች ስለመጠንቅ!!
*******************
(የፕሬስ መረጃ ማጣሪያ)

ህብረተሰቡ በማህበራዊ ሚዲያ ከሚሰራጩ አሳሳች መረጃዎች መጠንቀቅ እንዳለበት ተገለፀ
*******************
(ኢ ፕ ድ)

በኢቢኤስ ቴሌቭዥን ወጣት ብርቱካን ተመስገንን አስመልከቶ የተላለፈው ሀሰተኛ መረጃ በተመለከተ የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዚዳንት ዛዲግ አብርሃ ለመገናኛ ብዙሃን በሰጡት ማብራሪያ ሕብረተሰቡ በሚዲያዎች የሚሰራጩ መረጃዎች ትክክለኛነት ማረጋገጥ ይኖርበታል።

ሀገር የሚያፈርሱና ህዝብና ህዝብን የሚያጋጩ መረጃው እየፈበረኩ የሚያሰራጩበት ጊዜ በመሆኑ ሕብረተሰብ የሚጠቀማቸውን መረጃዎች ማጣራት ይኖርበታል ብለዋል።

ሚዲያ የራሱ ጥቅምና ጉዳት አለው ያሉት አቶ ዛዲግ፣ ከሰሞኑ በኢቢኤስ ቴሌቭዥን የተላለፈው ሀሰተኛ መረጃ መነሻው ማህበራዊ ሚዲያ መሆኑን ጠቅሰዋል።

በኢትዮጵያ ጉዳይ በርካታ ፍላጎት ያላቸው አካል እየመሩት በመሆን ጥንቃቄ ማድረግ ያስፈልጋል ሲሉ ጠቅሰዋል።

ሴቶችን አጀንዳ በማድረግ የፖለቲካ ፍላጎትን ለማሳካት የተሰራጨ መረጃ ነው ያሉት አቶ ዛዲግ አብርሃ፣ መንግስት ለሴቶች ብዙ ዕድል በሰጠበት በዚህ ጊዜ ለፖለቲካ ፉክክር መዋል ያልነበረበት ድርጊት መሆኑን ተናግረዋል።

ሐሰተኛ መረጃን በመከላከል ረገድ ጋዜጠኞችና ምሁራን ትልቅ ሚና እንዳለባቸው ጠቅሰዋል።

በሞገስ ፀጋዬ

መጋቢት 20 ቀን 2017 ዓም

ተመሳስለው በተዘጋጁ ሀሰተኛ ሰነዶች ህብረተሰቡ እንዳይጭበረበር የተሰጠ ማሳሰቢያ!!!***************(ኢፕድ መረጃ ማጣሪያ)የፌደራል ሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት አንዳንድ ...
21/03/2025

ተመሳስለው በተዘጋጁ ሀሰተኛ ሰነዶች ህብረተሰቡ እንዳይጭበረበር የተሰጠ ማሳሰቢያ!!!
***************
(ኢፕድ መረጃ ማጣሪያ)

የፌደራል ሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት አንዳንድ ህገወጦች ሀሰተኛ ሰነዶችን ከተቋሙ ተረጋግጦ የወጣ በማስመሰል ህብረተሰቡን በማጭበርበር የማይገባቸውን ጥቅም ለማግኘት እየሞከሩ መሆኑን ለተቋሙ በደረሰው ጥቆማ መረዳት መቻሉን ገልጿል፡፡

ተቋሙ እንዲህ አይነቱን የወንጀል ድርጊት የማይተገስና ተከታትሎ ለህግ የሚያቀርብ መሆኑን አስገንዝቧል፡፡

ህብረተሰቡም በእንደዚህ አይነት ሀሰተኛ ሰነድ እንዳይጭበረበር እና መሰል አጠራጣሪ ሁኔታ ሲኖር ለፖሊስ ጥቆማ በመስጠት ወንጀል ፈፃሚዎች በህግ ተጠያቂ ሊያደርግ እንደሚገባ አሳስቧል::

ከተቋሙ የሚመነጩ የውክልና ሰነዶች ባር ኮድ ያላቸው ሲሆኑ፣ ልዩ ውክልና ከሆነ ደግሞ የራሱ የሆነ የደህንነት መለያ እና ኤሌክትሮኒክስ/ደረቅ ማህተም የያዙ በመሆኑ በቀላሉ በሃሰተኛ መንገድ ሊዘጋጁ የማይችሉ መሆናቸውን ከአገልግሎቱ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡



Address


Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Press Fact Check/የፕሬስ መረጃ ማጣሪያ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Press Fact Check/የፕሬስ መረጃ ማጣሪያ:

Share