
24/04/2025
ከኢትዮጵያ መረብ ደህንነት አስተዳደር የተላለፈ የጥንቃቄ መልዕክት
***************
ከዉስጥ አዋቂዎች ጋር የተያያዙ ዋና ዋና የጥቃት ስጋቶች
ተቋማት ብዙውን ጊዜ ጠቃሚ ሀብቶችን ከጥቃት ለመጠበቅና በአግባቡ ለማስተዳደር ለተወሰኑ አካላት ሚስጥራዊ መረጃዎችን የማግኘት እድል ለዉስን ሰራተኞች ይሰጣሉ።
ይህን መብት ያገኘ አንድ ሰራተኛ ግልጽ ባልሆነ የሥራ ምክንያት ከተሰጠዉን መብት በላይ ለመጠቀም ከሞከረ፣ ይህ አይነቱ ሁኔታ ምናልባት የውስጥ አዋቂ ስጋት ምልክት ተደርጎ ይወሰዳል። ከዚህ በታችም የዉስጥ አዋቂዎች ጋር የተያያዙ የጥቃት ስጋቶች እንደሚከተለዉ ቀርበዋል፡
👉የመረጃ ምዝበራና ጥሰት
👉የአእምሮአዊ ንብረት ስርቆት
👉የተቋምን መረጃ መረጃና የመረጃ ስርአትን ማበላሸት
👉የገንዘብና ተያያዥ ጉዳዮች ማጭበርበር
#ጥንቃቄ