Prosperity ADDIS ብልፅግና አዲስ

Prosperity ADDIS ብልፅግና አዲስ UPRISING PEACE, DEMOCRACY ,UNITY & DEVELOPMENT

24/08/2025
24/08/2025

የአይበገሬነታችን ማሳያ፣ የሀገራችን ትንሳኤ ማብሰሪያ ግድብ!

ኢትዮጵያዊያን በጋራ ጉዳያቸው ላይ በህብር ደምቀው ከመሪዎቻቸው ጎን በመቆም የቁጭት ምንጭ ሆኖ በቆየው በዓባይ ወንዝ ላይ አኩሪ ታሪክ ፅፈዋል፡፡ በቅርቡ ለምርቃት የሚበቃው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የትብብራችን ውጤት ነው፡፡

ተጋርጠውበት የነበሩትን በርካታ ተግዳሮቶች እንዲሁም ጫናዎች በድል አድራጊነት በመሻገር ለፍፃሜ የበቃው ግድባችን አይበገሬነታችንን ለዓለም አሳይቷል፡፡

የሰንደቅ ዓላማችን ፕሮጀክት የሆነው የህዳሴ ግድባችን የተለያዩ ሴራዎችን በመበጣጠስ፣ ከተለያዩ አቅጣጫዎች የሚመጡ ጫናዎችን በመቋቋም በእልህ እና ወኔ በማለፍ ለፍሬ ያበቃነው አንደኛው የብሔራዊ ኩራታችን ምንጭ ነው፡፡

በአድዋ ጦርነት በወራሪዎች ላይ የተረባረበው የኢትዮጵያውያን ክንድ በዘመናችንም የጣና ሀይቅን ሁለት እጥፍ የሚያህል የውሀ መጠን የሚይዝ በአፍሪካ ተወዳዳሪ የማይገኝለት ግዙፍ ግድብ ገንብቷል፡፡

የሁሉም ኢትዮጵያዊ አሻራ ያረፈበት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በላብአችን የፃፍነው፣ በድካማችን ያሳካነው አኩሪ ታሪካችን ጭምር ነው።

በቅርቡ ሪቫን የምንቆርጥለት ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድባችን ትስስራችንን ይበልጥ በማጥበቅ የኢትዮጵያን ትንሳኤ ያበስራል።

በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት

23/06/2025

በሀገሪቱ አንዳንድ አካባቢዎች ተቋርጦ የነበረው ኤሌክትሪክ ሙሉ በሙሉ ተመልሷል

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 16፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) አዲስ አበባን ጨምሮ በሀገሪቱ አንዳንድ አካባቢዎች ተቋርጦ የነበረው የኤሌክትሪክ ኃይል ሙሉ በሙሉ ተመልሷል አለ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፡፡

የአገልግሎቱ የኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ አንዋር አብራር ለፋና ዲጂታል እንዳሉት ÷ ከዋናው ግሪድ ባጋጠመ የቴክኒክ ችግር ሳቢያ ተቋርጦ የነበረው የኤሌክትሪክ ኃይል ተመልሷል፡፡

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባደረገው ርብርብ ብልሽቱ ተቀርፎ አሁን ላይ አዲስ አበባ ጨምሮ በሁሉም አካባቢዎች አቅርቦቱ ሙሉ በሙሉ መመለሱን አረጋግጠዋል፡፡

ብልሽቱ ተስተካክሎ አገልግሎቱ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት ለጠበቁ ደንበኞችም ምስጋና አቅርበዋል፡፡

በመላኩ ገድፍ

ፈጣን እና ወቅታዊ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
YouTube www.youtube.com/
Facebook FBC (Fana Broadcasting Corporate S.C.)
Telegram t.me/fanatelevision
Website www.fanamc.com
TikTok www.tiktok.com/
WhatsApp www.whatsapp.com/channel/0029VbB0dRxG8l59MUkoWR29
Amharic Entertainment YouTube www.youtube.com/
Facebook WMCC
TikTok www.tiktok.com/
Amharic Documentary YouTube www.youtube.com/ በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስለሆኑ እናመሰግናለን!

23/06/2025
Ethiopia, the Land of Origins, will host the Second Africa Climate Summit (ACS2) from September 8–10, 2025, in partnersh...
16/06/2025

Ethiopia, the Land of Origins, will host the Second Africa Climate Summit (ACS2) from September 8–10, 2025, in partnership with the African Union. Centered on “Green Talks and Green Actions,” the summit will promote Nature-Based Solutions as key to Africa’s climate strategy, with a focus on re-greening the continent and fostering African solidarity. As Ethiopia launches its Green Legacy season, its preparations reflect a deep commitment to practical climate solutions. The call is clear: invest in nature, scale proven solutions, and embrace a model where ecology drives the economy. We look forward to welcoming you.

PMAbiyAhmedAli

የከንቲባ አዳነች አቤቤ መልዕክት  ...!!ብቃት ያለው እና ከሌብነት የፀዳ አገልግሎት ለኢትዮጵያ ብልፅግና!!"ብቃት ያለው ሲቪል ሰርቪስ ለኢትዮጵያ ብልጽግና " በሚል መሪ ሀሳብ በዛሬው እለ...
10/06/2025

የከንቲባ አዳነች አቤቤ መልዕክት ...!!
ብቃት ያለው እና ከሌብነት የፀዳ አገልግሎት ለኢትዮጵያ ብልፅግና!!
"ብቃት ያለው ሲቪል ሰርቪስ ለኢትዮጵያ ብልጽግና " በሚል መሪ ሀሳብ በዛሬው እለት ከወረዳ እስከ ከተማ ማዕከል ካሉ ተቋማት ከተውጣጡ የመንግሥት ሰራተኞች ተወካዮች ጋር በከተማዊና ሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ተመካክረናል።
አዲስ አበባ ለነዋሪዎቿ ምቹ፣ ለጎብኚዎቿ አስተማማኝ የቱሪስት መዳረሻ እንድትሆን በየደረጃው ካለው የመንግሥት ሰራተኛ ጋር በጋራ በመሆን ከከተማዋ ገቢ 71 በመቶውን ለዘላቂ ልማት ስራዎች በማዋል ውጤቶችን ማስመዝገብ ችለናል።
ለህዝባችን የምንሰጣቸው መንግሥታዊ አገልግሎቶች ፍትሃዊ እና ጥራት ያላቸው እንዲሆኑ ጽኑ አቋም ይዘው ተጨባጭ ውጤቶችን ያስመዘገቡ እና በተግባር ውጤታማ የሆኑ የመንግሥት ስራተኞቻችን ሚና ከፍተኛ ነው።
ሆኖም ተገልጋዩን ህዝብ የሚያማርሩ ሙሠኛ የሆኑ ሰራተኞችም እንዳሉ በየደረጃው በምናደርጋቸው ግምገማዎች ብሎም ህዝባችን በሚሰጠን ጥቆማዎችና ክትትሎች እየለየን የእርምት እርምጃዎችን ስንወስድ ቆይተናል።
አሁንም የመንግስት ሰራተኞቻችንን በጀምላ ከመዉቀስ ወጥተን ችግር ያለባቸዉን እያረምን፤ ጥፋተኞቹን እያጋለጥንና ተጠያቂ እያደረግን ህዝባችንን በላቀ ትጋትና ታማኝነት ማገልገላችንን አጠናረን እንቀጥላለን።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከመላው ኢትዮጵያ ከተወጣጡ የንግዱ ማኅበረሰብ ተወካዮች ጋር ያካሄዱትን ውይይት ዛሬ ምሽት ይጠብቁን
10/06/2025

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከመላው ኢትዮጵያ ከተወጣጡ የንግዱ ማኅበረሰብ ተወካዮች ጋር ያካሄዱትን ውይይት ዛሬ ምሽት ይጠብቁን

ታሪካዊ ጠላቶችም ሆኑ ተላላኪዎች በኢትዮጵያና ሕዝቦቿ ላይ የሚመኙት የጥፋት ድግስ አይሳካም - ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ታሪካዊ ጠላቶችም ሆኑ ተላላኪ ባንዳዎች በኢትዮጵያና ሕዝቦቿ ላይ የሚ...
07/06/2025

ታሪካዊ ጠላቶችም ሆኑ ተላላኪዎች በኢትዮጵያና ሕዝቦቿ ላይ የሚመኙት የጥፋት ድግስ አይሳካም - ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ

ታሪካዊ ጠላቶችም ሆኑ ተላላኪ ባንዳዎች በኢትዮጵያና ሕዝቦቿ ላይ የሚመኙት የጥፋት ድግስ አይሳካም አሉ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ።

የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ በብላቴ ማሰልጠኛ ማዕከል ያሰለጠናቸውን 43ኛ ዙር የመሰረታዊ ኮማንዶ ሰልጣኞችን በዛሬው ዕለት አስመርቋል።

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ በሥነ ሥርዓቱ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ፥ ኢትዮጵያ በብቃትም ሆነ በትጥቅ አስተማማኝ ሠራዊት የመገንባቷን ሒደት ይበልጥ አጠናክራ ትቀጥላለች ብለዋል፡፡

በኢትዮጵያ ቅጥረኛና ባንዳዎች የታጡበት ጊዜ ባይኖርም መሸነፍንና የበታችነትን በማይቀበሉ አይበገሬ ልጆቿ ሉዓላዊነቷና አንድነቷ ተጠብቆ እስከዛሬ ጸንታ መቆየቷን አውስተዋል።

ሠራዊቱ ባልተቋረጠ ሁኔታ ዝግጁነቱን እያጠናከረ እና አቅሙን በተሻለ ሁኔታ እያሳደገ እንደሚገኝም በንግግራቸው አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡

በሠራዊቱ መስዋዕትነት የኢትዮጵያ የብልጽግና ጉዞ ቀጥሏል ያሉት ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ጁላ ÷ ታሪካዊ ጠላቶቻችንም ሆኑ ተላላኪ ባንዳዎች በኢትዮጵያ የሚመኙት የእልቂት ድግስ ፈጽሞ አይሳካም ብለዋል፡፡

ፊልድ ማርሻል ብርሃኑ ተመራቂዎች የተሰጣቸውን ሀገራዊ ተልዕኮ በላቀ ዲሲፒሊን እና ግዳጅ ይወጣሉ ብለዋል

የክብርት ከንቲባችን መልዕክት!ዛሬ ለ6ኛ ዙር የሰለጠኑ 2074 ደንብ አስከባሪ ፓራሚሊተሪ ኦፊሰሮችን አስመርቀናል። አዲስ አበባ እጅግ በጣም ፈጣን ለውጥ እያስመዘገበች የምትገኝ ከተማ ስትሆን...
07/06/2025

የክብርት ከንቲባችን መልዕክት!

ዛሬ ለ6ኛ ዙር የሰለጠኑ 2074 ደንብ አስከባሪ ፓራሚሊተሪ ኦፊሰሮችን አስመርቀናል።
አዲስ አበባ እጅግ በጣም ፈጣን ለውጥ እያስመዘገበች የምትገኝ ከተማ ስትሆን ፤ ለነዋሪዎቿ እና ለዓለም አቀፍ ጎብኚዎች ተመራጭ ትሆን ዘንድ በልማቱ ብቻ ሳይሆን በሰላም፣ ደህንነት፣ ህግ እና ስርዓትን በማስከበር ረገድም ውጤታማ ስራዎች ተመዝግበዋል።
ዛሬ የተመረቃችሁ እና ስምሪት የወሰዳችሁ የደንብ ማስከበር ኦፊሰሮቻችን፣ ዋነኛው የሰላም ባለቤት ከሆነው የከተማችሁ ህዝብ ጋር በመሆን የተጣለባችሁን ታላቅ እምነት ይዛችሁ በንድፈ ሀሳብና በተግባር በቀሰማችሁት እውቀትና ክህሎት ህዝባችሁን በቅንነት፣ በታማኝነትና በአገልጋይነት መንፈስ ማገልገል ይጠበቅባችኋል።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ
Har'a marsaa 6ffaan kan leenji'an oofisarootaa Paaraamiiliitarii dambii kabachiisan 2074 eebbisiisneerra.
Finfinneen jijjiirama baay'ee saffisaa galmeessaa kan jirtu yemmuu ta'u, jiraattota ishee fi daaw'attoota idil-addunyaaf filatamtuu akka taatuuf misooma qofaan osoo hin taane gama nageenyaa fi heera fi seera kabachiisuutiinis hojiiwwaan milkaa'oon galmaa'aniiru.
Har'a kan eebbifamtan fi kabachiisa dambiif bobbaatan Ofisarootni keenya, abbaa nageenyaa olaanaa kan ta'e uummata magaalaa keenyaa waliin ta'uun imaanaa guddaa isinitti kenname fudhattanii beekumsaa fi ogummaa qabatamaa fi yaadaan argattaniin uummata keessan haqummaa, amanamummaa fi hafuura tajaajiltummaatiin tajaajiluutu isin irraa eegama.
Waaqni Itoophiyaa fi uummata ishee haa eebbisu

አገልግሎት አሰጣጡ ላይ ሆን ብለው እንቅፋት የሚፈጥሩ ግለሰቦች ከህሊና ፣ ከህግ እና ከፈጣሪ ፍርድና ተጠያቂነት ማምለጥ አይችሉም ! -አቶ አለማየሁ እጅጉየየካ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ...
02/06/2025

አገልግሎት አሰጣጡ ላይ ሆን ብለው እንቅፋት የሚፈጥሩ ግለሰቦች ከህሊና ፣ ከህግ እና ከፈጣሪ ፍርድና ተጠያቂነት ማምለጥ አይችሉም ! -አቶ አለማየሁ እጅጉ
የየካ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት አባላት ከብልፅግና ቤተሰብ ጀምሮ ሲያካሂዱት የቆዩት የጥያቄና መልስ ውድድር በሰው ሰራሽ አስተውሎት ( AI ) በታገዘ የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር ተጠቃልሏል።
በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት ም/ኃላፊና የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ አቶ አለማየሁ እጅጉ በፕሮግራሙ መክፈቻ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት የጠረ ሀሳብ እና የጠራ ራዕይ ያለውና የሚታይ ውጤት እያስመዘገበ የሚገኘው ብልፅግና ፓርቲ ድሎችን ለማስፋት በአመራሩና በአባላት ዘንድ የአስተሳሰብና የተግባር አንድነትን እያጠናከረ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
የተሟላ ግልፅነትን በመያዝ ፣ በአቋም በመፅናት ውጤታማነትን ማላቅ እንደሚገባ ያሳሰቡት አቶ አለማየሁ ተቀራራቢ አስተሳሰብ እና አመለካከት ለመያዝ በየጊዜው ከሚሰጡ ስልጠናዎችና ከሚደረጉ ውይይቶች ባሻገር መሰል የጥያቄና መልስ ውድድሮችም ፋይዳቸው የጎላ መሆኑን ገልፀዋል።
የአባላትን አቅም በማብቃት ፣ የተቋማትን ተወዳዳሪነት በማሳደግ የህዝባችንን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ እንደሚገባም አሳስበዋል ።
አገልግሎት አሰጣጡ ላይ ሆን ብለው እንቅፋት የሚፈጥሩት ግለሰቦች ከህሊና ፣ ከህግና ከፈጣሪ ፍርድና ተጠያቂነት ማምለጥ እንደማይችሉ የጠቆሙት አቶ አለማየሁ አባላት በአገልግሎት አሰጣጡ ግንባር ቀደም መሆንና የአሰራር ብልሽቶችን መተጋገል እንደሚጠበቅባቸውም መዕክታቸውን አስተላልፈዋል።
የየካ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ብርሃኑ ረታ በበኩላቸው እውቀትንና እውነትን መርሁ አድርጎ እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው ብልፅግና ፓርቲ የትናንት ዕዳዎች እንዳይሻገሩ ለዛሬ ብቻ ሳይሆን ለነገ ትውልድ የሚተርፉ ስራዎችን እያከናወነ እንደሚገኝ አስረድተዋል።
መጪው ጊዜም የተሻለ ስኬት የሚመዘገብበት ብሩህ ዘመን እንደሚሆን የጠቀሱት አቶ ብርሃኑ ህዝባችንን የበለጠ እያገለገልን ለትውልድ የሚተርፍ አሻራ ጥለን ልናልፍ ይገባል ብለዋል።
የየካ ክፍለ ከተማ ብልፅግና ፓርቲ ቅ/ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ መገርሳ ገላና የአባላትን ፖለቲካዊ አቅም ለመገንባትና ለላቁ ተልዕኮዎች ዝግጁ ለማድረግ የተለያዩ የአቅም ግንባታ ስራዎች እየተከናወኑ መሆናቸውን አመላክተዋል።
የጥያቄና መልስ ውድድሮች በብልፅግና ህብረት ደረጃ ሲካሄዱ ቆይተው ብርቱ ተወዳዳሪዎች ለዛሬው የአሸናፊዎች አሸናፊ ውድድር መብቃታቸውን ያስረዱት አቶ መገርሳ የሚሰጡ የማበረታቻና የእውቅና ሽልማቶችም በአባላት ዘንድ ተነሳሽነትን የሚጨምሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል።
በፕሮግራሙ ላይ አባ ገዳዎች እና የሀገር ሽማግሌዎች ለህዝባችንና ለሀገራችን ሰላምና ብልፅግና ምርቃታቸውን አቅርበዋል።
በጥያቄና መልስ ውድድሩ የተሳሳተፉና ያሸነፉ ብርቱ ተወዳዳሪዎች ደግሞ የማበረታቻ ሽልማቶቻቸውን ወስደዋል።
በብልፅግና ፓርቲ የአዲስ አበባ ቅ/ፅ/ቤት

Address

Addis Ababa

Telephone

+25111 667 3938

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Prosperity ADDIS ብልፅግና አዲስ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Prosperity ADDIS ብልፅግና አዲስ:

Share