Nida Tube ኒዳ ቲዩብ

Nida Tube ኒዳ ቲዩብ ኒዳ ቲዩብ አስተማሪና አዝናኝ ድህረ ገፅ
መጪው ግዜ የኢስላም ነው
Like ያድርጉን ኒዳ ቲዩብ አስተማሪና አዝናኝ ድረ ገፅ

በትግራይ ክልል አክሱም ከተማ አብርሃ እና አጽበሃ እና ክንደያ ትምህርት ቤቶች 20 ሙስሊም ተማሪዎች በሂጃብ ምክንያት የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና እንዳይፈተኑ ተደረጉ። mohammed hagos
11/06/2025

በትግራይ ክልል አክሱም ከተማ አብርሃ እና አጽበሃ እና ክንደያ ትምህርት ቤቶች 20 ሙስሊም ተማሪዎች በሂጃብ ምክንያት የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና እንዳይፈተኑ ተደረጉ።

mohammed hagos

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሃድያ ዞን አንሌሞ ወረዳ የሚኖሩ የሙስሊም ማህበረሰብ አባላት ሀይማኖትን መሠረት ያደረገ ጥቃት እየተፈጸመባቸው እንደሚገኝ ገለጹ ፡፡ የማህበረሰቡ አባላት “ በወረዳ...
10/06/2025

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሃድያ ዞን አንሌሞ ወረዳ የሚኖሩ የሙስሊም ማህበረሰብ አባላት ሀይማኖትን መሠረት ያደረገ ጥቃት እየተፈጸመባቸው እንደሚገኝ ገለጹ ፡፡ የማህበረሰቡ አባላት “ በወረዳው የሙስሊም ሃይማኖት ጥላቻ አለባቸው “ ያሏቸው ቡድኖች ባለፈው ሳምንት ሀሙስ ሱመያ የተባለ መስጅድ በውስጡ ከነበረ ቁራዓን እና ኪታብ ጋር ማቃጠላቸውን ለዶቼ ቬለ ተናግረዋል ፡፡

ፖለቲካዓለም አቀፍየሰኔ 3 ቀን 2017 ዓ.ም የዓለም ዜናTo play this audio please enable JavaScript, and consider upgrading to a web browser that supports HTML5 videoፖለቲካዓለም አቀፍYohannes Gebre Egiziabher Tareke3 ሰኔ 2017ማክሰኞ፣ ሰኔ 3 2017htt...

እዚህ ሀገር ህግ የሚሰራ ከሆን  ለሁሉም ነው ።ውዱን ነብያችንን ሰ.አ.ወ የተሳደበው ባለጌ እሰካሁን አልተያዝም። እዚህ ሀገር  ሙሰሊሙን መሳደብ እና ነብያቸውን ማንቆሸሽ የማያሰስር በተቃራኒ...
09/06/2025

እዚህ ሀገር ህግ የሚሰራ ከሆን ለሁሉም ነው ።

ውዱን ነብያችንን ሰ.አ.ወ የተሳደበው ባለጌ እሰካሁን አልተያዝም።
እዚህ ሀገር ሙሰሊሙን መሳደብ እና ነብያቸውን ማንቆሸሽ የማያሰስር በተቃራኒው ሌላውን ማሀበረሰብ ወይም እምነት ቲኒሽ መንካት ግን በሰኣታት ውስጥ ተየዞ ለፍርድ የሚቀርብበት ሀገር ነው።

ህግ ለሁሉም ሊተገበር ይገባል።

"..በሀድያ ዞን በሙስሊሙ ማህበረሰብ እና በመስጂዶች ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶች ተባብሰው ቀጥለዋል"- የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤትየማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስ...
09/06/2025

"..በሀድያ ዞን በሙስሊሙ ማህበረሰብ እና በመስጂዶች ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶች ተባብሰው ቀጥለዋል"

- የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት

የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ባወጣው መግለጫ በሀዲያ ዞን በተለያዩ ወረዳዎች በተለየም በሌሞ እና በአንሌሞ ወረዳዎች በሙስሊሙ ማህበረሰብ እና በመስጂዶቻችን የሚፈፀሙ ጥቃቶች በየጊዜው እየተባባሱ መቀጣላቸውን ገልጿል።

መጅሊሱ በሀድያ ዞን በሙስሊሙ ላይ የተፈፀሙ ጥቃቶችን በዝርዝር አቅርቧል።

1ኛ/ ከቅርብ ጊዜ ትዉስታችን ከዚህ በፊት በአንሌሞ ወረዳ በጪንጎ ቀበሌ በሙስሊሞች ላይ መስጂዳቸውና መኖሪያ ቤታቸው ድረሥ በመግባት ከ30 ሙሥሊም በላይ ተጠቅቷል አካለ ሥንኩል ሆኗል በወረዳው እና በዞኑ በኩል አንድም ሠው ተጠያቂ ሣይደረግ ተግበስብሶ ታልፏል።

2ኛ/ በሌሞ ወረዳ በአምቢቾ ጎዴ ቀበሌ በሼክ ያሲን መቶ ዓመት ባስቆጠረ መስጂድ አጠገብ ቤተ ክርስቲያን እንዲሠራ የወረዳው አሥተዳደር ለአንድ ወገን በመወገን ደብዳቤ በመፃፉ ይህንን ህገ ወጥ ተግባር ለመከላከል እና ለማዉገዝ በወጡ ሙስሊሞች ላይ ድብደባ እና ወከባ ተፈፅሞባቸዋል ንብረታቸውም ተዘርፏል በተጨማሪም ተጠቂዎቹ በሀሰት ክስ ተመስርቶባቸው ፍ/ቤት እየተመላለሱ ይገኛሉ።

3ኛ/ በሀዲያ ዞን በአንሌሞ ወረዳ በምሥራቅ አንሌሞ ቀበሌ ቀድሞ በተገናቡ የነሱን ህሊዉና ጥያቄ ዉስጥ በሚያስገባ መልኩ በሡመያ መስጅድ እና በአራዕልዶ መስጂድ በሁለቱም መስጅዶች መካከል ርቀቱን ባልጠበቀ መልኩ ቤተክርስቲያን መገንባት በመጀመሩ መብታቸውን ለመጠየቅ አቤቱታ ባቀረቡ በሁለቱም መስጂድ ኮሚቴዎች ላይ የውሸት ክስ በማቀነባበር በሰባት ሠዎች ላይ ከአንድ አመት በላይ ተፈርዶባቸው ሆሳዕና ማረሚያ ቤት በእስር ይገኛሉ ።

በተጨማሪም ሌሎችንም የሙስሉሙን መህብረሰብ የነቃሉ በተባሉ ሰዎች ላይ የነጣጠረ ክትትልና አካባቢዉን ለቀዉ እንዲጠፉ ኢየተደረገ በሀሰት በተቀነባበረ ክስ መጥሪያ ወጥቶባቸው በመታደን ላይ ይገኛሉ፡፡

4 እንደገናም በዚሁ ቀበሌ በነባር ሰላት በሚሠገድበትና ቂራዐት በሚቀራበት መስጂድ ላይ ደረሳዎቾ በተገኙበት በማታ መስጅድ ከነቁርዓኑና ኪታቡ ተቃጥሏል። ለዚህም ጥቃት ለአንሌማ ወረዳ ለሚመለከተው የመንግስት አካላት አቤቱታ ቢቀርብም አቤት ባዮችን እንደገና ወንጀለኛ ለማድረግ እየተሠራ ይገኛል ሲል በ መግለጫው አክሏል።

የክልሉ መጅሊስ ከላይ የተጠቀሱ ጉዳዮች በወረዳና በዞን ደረጃ እልባት እንዲያገኙ ታች ባሉ መዋቅሮች በኩል ጥረት ስያደርግ ቆይቷል ።ነገር ግን የተናበበ በሚመስል መልኩ ጥቃቱ እየተባባሰ አሁን ላለበት ደረጃ ደርሷል ብሏል።

የማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል መጅሊስ ከሀዲያ ዞን፣ ከሌሞና ከአንሌሞ ወረዳ የመንግስት አካላት በሙስሊሙ ማህበረሰብ የሚደርሰውን ሃይማኖታዊ ጥቃት ከመቀነሱ ይልቅ የተባባሰ ከመምጠቱ በላይ የመስጂዶችንና የማህበረሱቡን የእምነት ደህንነት አስጊ ሁኔታ የደረሰ በመሆኑ ይህንን መግለጫ መዉጣት አስፈላጊ ሆኖዋል ::

የኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት እና የሁሉም ክልሎችና የሁለቱም ከተማ አስተዳዳር መጅሊሶች በሀዲያ ዞን የሚፈፀመውን የሙስሊሞችን ጥቃት እንዲያወግዙ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መጅሊስ ጥሪ አቅርቧል።

የማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል የሚመለከተው የመንግስት አካላት በአጭር ጊዜ ለጉዳዩ መፍትሄ እንዲሰጥና ይህ በሀዲያ ዞን በሙስሊሙ ማህበረሰብ የሚፈፀመው ጥቃት በአጭር ጊዜ ህጋዊ እልባት እንዲሰጥ ጠይቋል።

የማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል መጅሊስ በሀዲያ ዞን በየጊዜው በሙስሊሙ ማህበረሰብና በተቋሙ ላይ የሚፈፀመውን ጥቃትና በደል በዘላቂነት የሚወገድበትንና የሚቆምበትን ህጋዊና ሰላማዊ አካሄድ ተከትለን የምንሄድበትን አቅጣጫ በቀጣይ ለሙስሊሙ ማህበረሰብ እንደሚያሳውቅና በትዕግስት እንድትጠብቁን አደራ ለማለት እንወዳለን ሲል በመግለጫው ላይ አንስቷል።

© ሀሩን ሚዲያ

ዐይናፋሩ አሕመድ አሽ-ሸርዕከአል-ቃዒዳ እስከ ተሕሪረ-ሻም እሰከ ቤተመንግሥት *********የዚህን ሰው ጉዞ ከሚከታተሉት ነኝ። አሕመድ አሽ-ሸርዕ ይባላል፡፡ አቡ ሙሐመድ አል-ጆላኒ ይሉት ነ...
09/06/2025

ዐይናፋሩ አሕመድ አሽ-ሸርዕ
ከአል-ቃዒዳ እስከ ተሕሪረ-ሻም እሰከ ቤተመንግሥት
*********

የዚህን ሰው ጉዞ ከሚከታተሉት ነኝ። አሕመድ አሽ-ሸርዕ ይባላል፡፡ አቡ ሙሐመድ አል-ጆላኒ ይሉት ነበር በፊት፡፡ ቀስ እያለ ዓላማውን ለማሳካት የሚተጋ "ልስልሱ እባብ" ይሉታል ይሁዶቹ። ከ8ዓመት ወፊት ነበር በሰሜን ሶርያ ከአይኤስ ጋር ግንኙነት አለው ተብሎ ከሚወራው ከሶርያውን አማፂ ቡድን ጀብሀተ ኑስራ ራሱን በመገንጠል ሀይአት ተሕሪር አሽ-ሻም የተሠኘውን ድርጅት ያቋቋመው፡፡ ከዚያ በፊት በተለያዩ ኢስላማዊ ድርጅቶች ውስጥ አልፏል፡፡ አዲሱን ድርጅት ያልወደደችው አሜሪካ እሱን ላገኘልኝ ሰው 10 ሚሊዮን ዶላር እሸልማለሁ አለች፡፡ ኋላ ላይ በድርድር ሀሳቡን ብታነሳም፡፡
ጊዜው ተቀየረና ይህ ሰው በመራው አብዮት ተሳዳጁ ሰውዬ ባልታሰበ ፍጥነትና ቅጽበት ባለፈው ዓመት ቤተመንግሥት ገባ፡፡ ዓለም በሶርያ በተፈጠረው ነገር ጉድ አለ፡፡ ምንም የማይሳነው አላህ ሁኔታዎችን ወዲያው ሳይታሰብ ይቀይራል፡፡

ዐይናፋሩ ሸርዕ በሄደበት ቦታ ሁሉ ትሁት ነው፡፡ በትህትና የተሞላ ንግግሩን ሰምቻለሁ፡፡ ሁሌም የአላህን ችሮታ ሲያወሳ አውስቶ የሚጠግብ ዓይነት አይደለም፡፡

አንድ ሰው መንግሥት ሲሆን ስለቤተሰቡ፣ ሚስትና ልጆቹ ይጠየቃል መቸስ፡፡ ሰውዬው በጠንካራ ኢስላማዊ መሠረት ላይ እንደመምጣቱ ሚስቱ ማን ትሆን? ትታያለች አትታይም? ኒቃቢስት ናት ሒጃቢስት… ብለው ሰዎች ያወራሉ፡፡ ጋዜጠኞችም ቀድሞ ለማሳየት ይጓጓሉ፡፡ የሸርዕ ሚስት ለሚዲያ ለመታየት ብዙ አልፈጀባትም፡፡

ከትናንት ወዲያ ከባለቤቱ ጋር ሆነው ሴት ልዑካንን ተቀብለው ሲያነጋግሩ ከባለቤቱ ጋር ስላሳለፈው ውጣውረድ ሲናገር መልዕክቱ ትምህርት የሚሠጥ ሆኖ አገኘሁት፡፡ ሸርዕ ስለባለቤቱ ሲናገር እንዲህ ይላል፡-
“ በ 2012 ባልተለመደ ሁኔታ ነበር የተጋባነው፡፡ አስቸጋሪ ሁኔታ ነበር፡፡ ከተጋባን በኋላ ስለሥራዬ ብዙ መረጃ አልሠጣትም ነበር፡፡ በሂደት ግን እጅግ አስቸጋሪ ራሷ ደረሰችበት፡፡ ግና ሁሉንም ሁኔታ ትቋቋም ነበር፡፡ የአየር እና የከባድ መሣርያ ድብደባውን፣ ስደትና መፈናቀሉን ሁሉ ችላ ነው አብራኝ የዘለቀችው፡፡ በዚህ ሂደት ወደ 49 ቤቶችን ቀይረናል፡፡ በየሦስት ወሩ አንድ ቤት እንደማለት ነው፡፡ ለሴት ልጅ ይህ ከባድ ነው፡፡ ኑሯችን እንደ ዘላን ነበር፡፡ በርግጥ እነርሱ ለሕይወት አስፈላጊያቸው የሆነን ነገር ይዘው ይንቀሳቀሱ ነበር፡፡ እኛ ግን ሁኔታው ያን ሁሉ ስለማይፈቅድልን እጅግ አስቸጋሪ በሆኑ ቦታዎች ውስጥ ኖረናል፡፡ በዋሻዎች፣ በምሽጎችና በሌሎችም፡፡ በርግጥ አልፎአልፎ እንደሥራው ሁኔታ ጥሩ ቦታዎች ላይም ኖረናል፡፡ ብዙ ጊዜ ለሷም ለልጆቻችንም ደኅንነት ስል ወደተሻለ ቦታ እንድትሄድ እመክራት ነበር፡፡ እሷ ግን ፈጽሞ አትቀበልም፡፡ በዓላማዋ ፀንታ ቆየች፡፡ ከጎንህ ሆኜ ፈገግታህን ማየት ነው የምፈልገው ትለኝ ነበር፡፡ በርግጥ ባለፉት 14 ዓመታት ከባድ ሁኔታዎች ውስጥ አልፈናል እውነት ነው፡፡ ውጤቱ ግን ይኸው እንደምታዩት ነው፡፡ ዛሬ እዚህ ተቀምጠናል፡፡ እዚህ ከመድረሳችን በፊት ግን አስቸጋሪ ሁኔታዎችን አሳልፈናል፡፡ በያንዳንዱ ሁኔታና ቅጽበት ጽኑ ሆና ከጎኔ ቆማ ዘልቃለች፡፡ አላህ በመልካም ሁሉ ይመንዳት፡፡ አሁንም ያጽናት፡፡ በቀጣይም አገራችንን በመገንባቱና በማሳደጉ ረገድ በሚኖረው ሁለተኛው የሕይወታችን ክፍል የሴት ልጅ ሚና ወሳኝ ነውና አብረን እንዘልቃለን፡፡”

ትዕግሥት መራራ ብትሆንም ፍሬዋ ጣፋጭ ነው፡፡

Via ... Muhammed Seid Abx

ኢድ ሰላት በጎንደር
06/06/2025

ኢድ ሰላት በጎንደር

የዒድ አልድሓ ሰላት በመቐለ ❤ #በመቐለ ጎዳና ሰማእታት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሙስሊሞች የ 1446ኛው የዒደል አድሓ ሰላታቸውን ሰግደዋል።ዒድ ሙባረክ 😍
06/06/2025

የዒድ አልድሓ ሰላት በመቐለ ❤

#በመቐለ ጎዳና ሰማእታት በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሙስሊሞች የ 1446ኛው የዒደል አድሓ ሰላታቸውን ሰግደዋል።

ዒድ ሙባረክ 😍

ኢድ በደሴ ከተማ 1446ኛው ዓ.ሒ(2017 ዓ.ል) የኢደል አድሀ አረፋ በዓል በደሴ ከተማ በሆጤ ስታዲየም በምስል፦
06/06/2025

ኢድ በደሴ ከተማ

1446ኛው ዓ.ሒ(2017 ዓ.ል) የኢደል አድሀ አረፋ በዓል በደሴ ከተማ በሆጤ ስታዲየም በምስል፦

ኢድ ሰላት በአዲስ አበባ ስታዲየም
06/06/2025

ኢድ ሰላት በአዲስ አበባ ስታዲየም

የ1446ኛ የኢድአል አደሃ አረፋ በዓል አከባበር በጅማ
06/06/2025

የ1446ኛ የኢድአል አደሃ አረፋ በዓል አከባበር በጅማ

ኢድ ሰላት ሱማሌ ክልል ጅግጅጋ
06/06/2025

ኢድ ሰላት ሱማሌ ክልል ጅግጅጋ

06/06/2025

ኢድ እንዴት እያለፈ ነው ? የት ሀገር ነው እያከበራቹህ ያላችሁት ?

Address

Addis Ababa

Telephone

+251911000000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Nida Tube ኒዳ ቲዩብ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share