Nida Tube ኒዳ ቲዩብ

Nida Tube ኒዳ ቲዩብ ኒዳ ቲዩብ አስተማሪና አዝናኝ ድህረ ገፅ
መጪው ግዜ የኢስላም ነው
Like ያድርጉን ኒዳ ቲዩብ አስተማሪና አዝናኝ ድረ ገፅ

30/11/2025

አልሀምዱሊላህ በል

ከሚኩራሩበት መልካም ስራ ይልቅ፤የሚፀፀቱበት ሀጥያት በአላህ ዘንድ ትልቅ ዋጋ አለው
30/11/2025

ከሚኩራሩበት መልካም ስራ ይልቅ፤
የሚፀፀቱበት ሀጥያት በአላህ ዘንድ ትልቅ ዋጋ አለው

30/11/2025

Mashallah❤😍

27/11/2025

ምላስህን ጠብቅ

26/11/2025

ሁሉ ነገር አላህ ባለው ቀን ይሆናል
አትጨነቅ ! ሰበቡን አደርስ !

22/11/2025

ምርጥ ምክር👌

22/11/2025

በጠራራ ፀሀይ ሌብነት

22/11/2025

ዚክር

19/11/2025

ኢስቲግፋር አድርጉ

18/11/2025

ሰነፍ ሰው ለስኬት አይበቃም

"ሙስሊሙ ማሕበረሰብ ከሸሪዓ ጋር የሚፃረሩ ህጎችን ለመተግበር አይገደድም።" ሼህ ሐጂ ኢብራሒም ቱፋየኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በትምህርት ሚኒስቴር በኩል የተላለፈውን መመሪ...
18/11/2025

"ሙስሊሙ ማሕበረሰብ ከሸሪዓ ጋር የሚፃረሩ ህጎችን ለመተግበር አይገደድም።" ሼህ ሐጂ ኢብራሒም ቱፋ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት በትምህርት ሚኒስቴር በኩል የተላለፈውን መመሪያ በተመለከተ ዛሬ ጋዜጣዊ መግለጫ ሰጥቷል።

ሚኒስቴሩ በህዳር 2/2018 በአዳማ ከተማ ቀጣይ የመማር ማስተማር ሂደትን በተመለከተ ባስተላለፈው መመሪያ ላይ ኢስላማዊ አለባበስን በትምህርት ተቋማት ውስጥ ተግባራዊ እንዳይሆን ለማድረግ የከለከለበት መንገድ ተቀባይነት የሌለው መመሪያ መሆኑን ተገለጿል።

የትምህርት ሚኒስቴር መግለጫን በተመለከተ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሼህ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል::

ኢስላማዊ እሴታችን ትኩረት የሰጠውን እውቀት የመፈለግ ጥረት በምናደርግበት ሰአት በተለያዩ ግዜያት የተጠና ትንኮሳ እና በሴራ ሙስሊሙን ከትምህርት የማግለል ዘመቻ እየተደረገ እንደሚገኝ አሳውቀዋል::

በህገ መንግስት የተረጋገጠውን የመማር መብት በትምህርት ሚኒስቴር በኩል ተደጋጋሚ ችግር እየገጠመው መሆኑ ተቀባይነት የሌለው ስራ ነው ብለዋል::

የትምህርት ፖሊሲን አክብረን መቀበል እንዳለብን ብንረዳም ከሸሪዓ ጋር የሚፃረሩ ህጎችን ለመተግበር የማንገደድ መሆኑን ማሳወቅ እንፈልጋለን ሲሉ ገልፀዋል::

በተለያየ ግዜ የሚደረጉ ትንኮሳዎችን መንግስት ላይ ጫና ላለማሳደር በሚል በሆደ ሰፊነት ብናልፈውም አሁን ግን ከምንቀበለው በላይ ሆኗል በማለት ተናግረዋል::

ከሙስሊሙ ህዝብ በተገኘ ግብር በተሰራ ትምህርት ቤት ውስጥ አንዲትም የመብት ጥሰት እንዲፈጠር የማንፈቅድ ሲሆን ይህንንም ለማረጋገጥ ሁሉንም አይነት ጥረት እናደርጋለን ብለዋል::

ይህንን የመብት ጥሰት ተከታትሎ የእርምት እርምጃ ለመውሰድ እንዲያመች 17 አባላት ያሉት ግለሰቦች የተቋቋመ ሲሆን ጉዳዩን ከግብ እንዲያደርሱ ሀላፊነት እንደተሰጣቸውም አብራርተዋል።

በነዳጅ ምርቶች ላይ የተጣለዉ አጠቃላይ የ30% ግብር በቀጣይ ወር ተግባራዊ እንደሚሆን ተገለፀ የኢትዮጵያ መንግሥት ለረጅም ጊዜ የዘለቀውን የነዳጅ ድጎማ ቀስ በቀስ ለማስወገድ ከሚወስዳቸው ሰ...
17/11/2025

በነዳጅ ምርቶች ላይ የተጣለዉ አጠቃላይ የ30% ግብር በቀጣይ ወር ተግባራዊ እንደሚሆን ተገለፀ

የኢትዮጵያ መንግሥት ለረጅም ጊዜ የዘለቀውን የነዳጅ ድጎማ ቀስ በቀስ ለማስወገድ ከሚወስዳቸው ሰፋፊ የኢኮኖሚ ማሻሻያዎች አንዱ የሆነው አዲስ የግብር አወቃቀር ከሚቀጥለው ወር ጀምሮ ተግባራዊ ሊሆን ነው።

ይህ አዲስ እርምጃ በነዳጅ ምርቶች ላይ 15% ተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) እና 15% ኤክሳይዝ ቀረጥን ያካተተ አጠቃላይ 30% ታክስ መጣል ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ከአንድ ወር በኋላ ታክሱን መሰብሰብ ይጀምራል።

በአዲሱ መመሪያ መሠረት፣ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅቱ የተሰበሰበውን ግብር በሙሉ ለገቢዎች ሚኒስቴር ማስገባት ግዴታው ሲሆን፣ መንግሥት በዚህም እስከ ታኅሣሥ 2018 ዓ.ም. ድረስ ለቤንዚንና ናፍጣ መሸጫ ዋጋዎች ሁሉንም ህጋዊ የግብር መጠን ጨምሮ ሙሉ ወጪን የመሸፈን ግብ ላይ ለመድረስ አቅዷል።

​የገንዘብ ሚኒስቴር ከአዲሱ በጀት ዓመት ጀምሮ በነዳጅ ምርቶች ላይ አጠቃላይ 30 በመቶ ግብር ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ሊያደርግ ማቀዱን ካፒታል ጋዜጣ ከሁለት ወራት በፊት መዘገቡ ይታወሳል።

ሚኒስትሩ መስከረም 2018 ዓ.ም. አጋማሽ ላይ ባቀረቡት አጠቃላይ የዜጎች በጀት ዉስጥ፣ በተያዘው በጀት ዓመት ተግባራዊ የሚደረጉ የግብር አይነቶችን በዝርዝር አስቀምጠው ነበር።

capital

Address

Addis Ababa

Telephone

+251911000000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Nida Tube ኒዳ ቲዩብ posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share