
30/07/2023
ፈጠራ ለለውጥ እና ለውጤት❗️❗️
ቴክኒክና ሙያ ማስልጠኛ ኮሌጆች ክሎት መር ስልጠናዎች ላይ በማተኮር ከራሱ አልፎ ለሌሎችም የስራ ዕድል የሚፈጥር ብቁ እና ተወዳዳሪ የሰው ሀይል በማፍራት ለከተማችን እና ለአገራችን የኢንዱስትሪ ዕድገት የማይተካ አበርክቶ አላቸው።
አዳዲስ የፈጠራ ሀሳቦችን ወደ ተግባር ለመቀየር ምቹ ሁኔታን የሚፈጥሩት እነዚህ ተቋማት ቴክኖሎጂዎችን ከመፍጠር በተጨማር ቴክኖሎጂ በመኮረጅ እና እሴት ጨምሮ በማስፋፋት ምርታማነትንና ውጤታማነትን ያሳድጋሉ።
በኮሌጆች የሚሰጡ ተግባር ላይ የሚያተኩሩ እውቀት እና ክህሎቶች የመፍጠር አቅም በማሳደግ እራሳቸውን፣ ቤተሰባቸውን እና አገራቸውን መለወጥ የሚችሉ ዜጎችን እያፈሩ ነው።
ውድ የዕለቱ ምሩቃን በኮሌጅ ያገኛችሁትን እውቀት እና ክህሎት ኢንዱስትሪያችንን ተወዳዳሪ ለማድረግ እንድታውሉት እጠይቃለሁ!
:-ከንቲባ አዳነች አቤቤ