Momentum Media Production

Momentum Media Production Ethiopia

10/11/2025

ዕውቁ የታሪክ ምሑር ፕሮፌሰር ላጲሶ ጌታሁን ድሌቦ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

ዕውቁ የታሪክ ምሑር ፕሮፌሰር ላጲሶ ጌታሁን ድሌቦ በ87 ዓመት ዕድሜ ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት ዛሬ እሑድ ጥቅምት 30/2018 ነው።

በኢትዮጵያ ታሪክ ጥናት ጉልሕ አሻራ ማሳረፍ የቻሉት ፕሮፌሰሩ በርካታ መጻሕፍትን ለአንባቢያን አቅርበዋል። ከሥራዎቻቸው መካከል የኢትዮጵያ ረጅም የሕዝብና የመንግሥት ታሪክ እና የኢትዮጵያዊነት ታሪካዊ መሠረቶችና መሣሪያዎች ተጠቃሽ ናቸው።

ላጲሶ ጌታሁን ድሌቦ የተወለዱት በቀድሞው ከንባታና ሐዲያ አውራጃ በኩፋላ ቀበሌ ግንቦት 12/1930 ነው። የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርታቸውን በቢቾ ሆሣዕና ሚሽን፣ በመንግሥት ትምህርት ቤት እንዲሁም ኋላ ላይ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አዳማ በሚገኘው በዐፄ ገላውዴዎስ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተምረዋል።

ከዚያም መዳረሻቸውን አሜሪካ በማድረግ በኮሙኒቲ ኮሌጅ የከፍተኛ ትምህርታቸውን ተከታትለው በኀብረተሰብ ታሪክ የመጀመሪያ ዲግሪ አጠናቀዋል። ከሐዋርድ ዩኒቨርሲቲ በአፍሪካ ታሪክ ጥናት ሁለተኛ ዲግሪ፣ በኢትዮጵያ፣ በአፍሪካና በአውሮፖ ታሪክና በፍልስፍና ደግሞ የዶክትሬት ዲግሪ ወስደዋል።

ዶክትሬታቸውን ካጠናቀቁ በኋላ የፕሮፌሰርነት ማዕረግ ተሰጥቷቸው ለሁለት ዓመታት በቨርጂኒያ ዩንየን ዩኒቨርሲቲ ውስጥ አስተምረዋል። ፕሮፌሰር ላጲሶ ድሌቦ የኢትዮጵያ ታሪክ የእስልምናው፣ የክርስትናው እና የሌሎች ሃይማኖቶች እንዲሁም የበርካታ ቋንቋዎች እና ሕዝቦች መስተጋብር ነው በሚለው ሙግታቸው ይታወሳሉ። (ሚንበር ቲቪ)

★ ★ ★
Ethio Sat | 11545 | H | 45000
!

ከጥቂት አመታት በፊት የፊልም ፖሊሲው ከመውጣቱ በፊት የኢትዮጵያ ፊልም ፕሮውዲሰር አሶሶሽን መሪዎች ቢኒ  ይድኔ  አርማ  ኤርሚ  እና እኔ በመሆን በመኖሪያ በቤታቸው በመገኘት ብዙ መልክም እ...
17/08/2025

ከጥቂት አመታት በፊት የፊልም ፖሊሲው ከመውጣቱ በፊት የኢትዮጵያ ፊልም ፕሮውዲሰር አሶሶሽን መሪዎች ቢኒ ይድኔ አርማ ኤርሚ እና እኔ በመሆን በመኖሪያ በቤታቸው በመገኘት ብዙ መልክም እና ቁብ ነገሮችን ተጨዋውተን እንደነበር የቅርብ ትዝታዮ ነው::

በጊዜውም ብዙ ጠቃሚ ምክሮችን ስለዘርፉ እና ለኛ እንዳካፈሉን ሁላችንም አንዘነጋም::ጋሽ ደቤ በጥበቡ በርካታ ሥራዎችን የሠራ በዘርፍ እንቱታን ካተረፉ ስመ ጥር እንጋፋ የኢትዮጵያ ባለሙያዎች ውስጥ ከግንባር ቀደሞቹ ውስጥ የሚጠቀስ ነው :: ለሀገርህ ልህዝብህ ላደረከው እስትዋፆ ውለታ ትልቅ ምስጋናና አክብሮት አለኝ በሰራሃቸው ሥራዎች ባበርከትከው አስተዋፆ ሁሌም ስታወስ ትኖራለህ ትውልድ ያልፋል ህዝብ ይቀጥላል:: " አሸብርቆ ደምቆ እንደ ፀሐይ......" RIP ............ደበበ እሸቱ::

አንጋፋው አርቲስት ደበበ እሸቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 11፣ 2017 (ኤፍ ኤም ሲ) አንጋፋው አርቲስት ደበበ እሸቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል፡፡

አርቲስት ደበበ እሸቱ ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴዔታ ነብዩ ባዬ (ረ/ፕ) ለፋና ዲጂታል ተናግረዋል፡፡

አርቲስት ደበበ እሸቱ በኢትዮጵያ ኪነ ጥበብ ዘርፍ የላቀ አስተዋጽኦ ያበረከተ ሲሆን÷ በሬዲዮ፣ በቴሌቪዥን፣ በፊልም እና በጋዜጠኝነት ሙያ በርካታ ሥራዎችን ለአድማጭ ተመልካች አቅርቧል፡፡

ተዋናይ፣ ኮሜዲያን እና አዘጋጅ ሆኖ ለረጅም ዓመታት ያገለገለው አርቲስቱ ÷ በቴአትር መድረኮች በሕዝብ ዘንድ ተወዳጅ የሆኑ ሥራዎችን በማቅረብ ይታወቃል፡፡

አርቲስት ደበበ በሀገር ፍቅርና በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ (በአሁኑ ብሔራዊ ቴአትር) መድረክ ላይ ለበርካታ ዓመታት በተዋናይነትና በአዘጋጅነት አገልግሏል።

አርቲስት ደበበ መጀመሪያ በቴአትር መድረክ የታየው በመንግስቱ ለማ ያላቻ ጋብቻ ሲሆን÷ በመቀጠልም በሬዲዮ እና ቴሌቪዥን የተለያዩ ሥራዎችን አቅርቧል፡፡

አርቲስቱ ከተሳተፈባቸው ሥራዎች መካከል ያላቻ ጋብቻ፣ ሮሚዮና ዡልየት፣ ጠልፎ በኪሴ፣ ዳንዴው ጨቡዴ ፣ዘ ጌም ኦፍ ቼዝ፣ ኦቴሎ፣ አንድ ዓመት ከአንድ ቀን፣ እናት ዓለም ጠኑ፣ በቀይካባ ስውር ደባ፣ የአዛውንቶች ክበብ፣ የወፍ ጎጆ ፣ የቬኒሱ ነጋዴ ፣ ማዕበል እና ሌሎች ይገኙበታል፡፡

በተለያዩ ታሪካዊና አዝናኝ ፊልሞች እንዲሁም የቴአትር ሥራዎች አድናቆት የተቸረው አንጋፋው አርቲስት ደበበ እሸቱ÷ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲም የክብር ዶክትሬት ተሰጥቶታል፡፡

አርቲስቱ ሀገር ችግር ውስጥ በምትሆንበት ጊዜ ከፊት በመቆም በርካታ አስተዋጽኦ ያበረከተ ሲሆን ÷ በበጎ ፈቃድ ሥራዎችም ግንባር ቀደም ነበር፡፡

በሌላ በኩል አርቲስት ደበበ እሸቱ በ1995 ዓ.ም በሃገራዊ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ውስጥ በመሳተፍ የምክር ቤት አባል እስከመሆን ደርሷል፡፡

ፋና ሚዲያ ኮርፖሬሽን ለቤተሰቦቹ፣ ወዳጅ ዘመዶቹ እና ለመላው አድናቂዎቹ መጽናናትን ይመኛል።

17/09/2024

በየነ ጴጥሮስ (ፕ/ር) ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 7፣ 2017 (ኤፍ ቢ ሲ) በየነ ጴጥሮስ (ፕ/ር) በአደረባቸው ህመም ምክንያት በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ፡፡

የፕሮፌሰር በየነን ሕልፈተ-ሕወት ተከትሎ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የተሰማቸውን ሐዘን ገልጸዋል፡፡

በአስተላለፉት የሐዘን መግለጫ መልዕክትም÷ በየነ ጴጥሮስ (ፕ/ር) በኢትዮዽያ ገንቢ የፖለቲካ ባህል ለመፍጠር ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረከቱ የሰላማዊ የፖለቲካ ትግል ምልክት ነበሩ ብለዋል።

ረዘም ላለ ጊዜ በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን ስሰማ ከልብ አዝኛለሁ ሲሉም በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ገልጸዋል፡፡

ያቆዩት ውርስ እና ቅርስ ፀንቶ እንዲቀጥል ነፍሳቸውም በሰላም እንድታርፍ እመኛለሁ ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር)።

https://www.facebook.com/share/p/613UdgD4Uwa7qL1n/?mibextid=WC7FNe
03/09/2024

https://www.facebook.com/share/p/613UdgD4Uwa7qL1n/?mibextid=WC7FNe

ደራሲ እና ኢንጂነር ታደለ ብጡል ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
*********

ደራሲ እና ኢንጂነር ታደለ ብጡል ክብረት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።

ኢንጂነር ታደለ ብጡል የባንክ ባለሙያ፣ ሲቪል መሀንዲስ እና ደራሲ ናቸው።

ማራዥት እና ሦስትዮሽ የተሰኙ የግጥም መድብሎች እንዲሁም የክቡር ዶ/ር ከበደ ሚካኤል፣ የሀኪም ወርቅነህ እሸቴ፣ የአፄ ቴዎድሮስ እና የልዑል አለማሁ ቴዎድሮስን ግለ ታሪኮች ፅፈዋል። የአማርኛ የምልክት ቋንቋ መዝገበ ቃላትንም አዘጋጅተዋል።

ደራሲ እና ኢንጂነር ታደለ ብጡል በተለያዩ የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ተግባራት ላይ በመሳተፍም ይታወቃሉ። በቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ዘመነ መንግሥት የማታ ትምህርት ያስጀመሩ ናቸው። በታዋቂው አርበኛ የተሰየመውን ወንዲራድ ት/ቤትን ከሌሎች ጋር በመሆን አቋቁመዋል። የአክሱም ሀውልት ብሄራዊ አስመላሽ ኮሚቴ አባልም ነበሩ።

የተለያዩ ባህላዊ እና ትውፊታዊ ቅርሶችን ከተለያዩ ክፍላተ ዓለማት በራሳቸው ወጪ ገዝተው በመሰብሰብ በኢትዮጵያ ለሚገኙ የተለያዩ ሙዚየሞች በመለገስ ታሪካዊ አስተዋጽኦ አድርገዋል።

የበጎ ሰው ተሸላሚው ኢንጂነር ታደለ ብጡል ክብረት በ97 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።

https://www.facebook.com/share/p/zP9M562zX8Hqm1XW/?mibextid=WC7FNe
29/08/2024

https://www.facebook.com/share/p/zP9M562zX8Hqm1XW/?mibextid=WC7FNe

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ፕሬዚዳንት አንድርያስ እሸቴ (ፕ/ር) ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 23፣ 2016 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ፕሬዚዳንት አንድርያስ እሸቴ (ፕ/ር) ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።

አንድርያስ እሸቴ (ፕ/ር) ባደረባቸው ህመም በህክምና ሲረዱ ቆይተው ነው ዛሬ ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት እንደአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መረጃ፡፡

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ፕሬዚዳንት የነበሩት አንድርያስ እሸቴ (ፕ/ር) ÷ በፍልስፍና መምህርነት፣ በተመራማሪነትና በአማካሪነት አገልግለዋል፡፡

የተባረከ ነው ሁለቴ ተወልዶ አንዴ የሚሞተውአንዴ ተወልዶማ አንዴ የሚሞተው ሁሉም ሰው እኮ ነው:: ወደ አባቱ ሄደ  ወደ ዘላለሙቢወሳ  ቢረሳ  በምድር በሙሉ ምንድ ነው ጥቅሙ?ጭራሽ ምን ይጠቅ...
11/04/2024

የተባረከ ነው ሁለቴ ተወልዶ አንዴ የሚሞተው
አንዴ ተወልዶማ አንዴ የሚሞተው ሁሉም ሰው እኮ ነው::

ወደ አባቱ ሄደ ወደ ዘላለሙ
ቢወሳ ቢረሳ በምድር በሙሉ ምንድ ነው ጥቅሙ?
ጭራሽ ምን ይጠቅማል እዛ እስካለ ስሙ

ቀድሞም ዘምሮታል
ሰዎችም ሰምተዋል

ዓለም ተስፋ ቁረጭ እልተገናኘንም
አምላክ ከኔ ጋር ነው አታሸንፊኝም

ይህን ብቻ እይደልም እያለ ተቀኝቷል የእየሱስ ወታደር
ዝናው ከበሬታው ከርሱ ፍቅር ጋራ እንደማይወዳደር

ዛሬ ወደ እሚወደው ወደዘመረለት ወዳቧቱ ሄዷል::
ቢሞት መጠቀሙን ቢኖርም ላምላኩ መሆኑን ተረድቷል
የዘሪው ምሳሌ ለፍጥረታዊው ሰው በእውቀቱ ለሚጥር
አውቃለው እያለ ልቡን አደንድኖ ለሚጥር ለሚግር
በጣም ያሳዝናል የእግዚ/ር መንግስት ሆኖበታል ሚስጥር

A determination song by one of the legendary Ethiopian gospel singers, Muluken Melelse. The message is all about his denial of this carnal world and acceptan...

23/02/2024

" ጠቢብ በጥበቡ አይመካ
ኃያልም በኃይሉ አይመካ
አዋቂም በዕውቀቱ አይመካ
ብርቱ በብርታቱ አይመካ የሚመመካ የሚመካ በእግዚአብሔር ይመካ የሚደገፍ የሚደገፍ በእግዚአብሔር ይደገፍ"

https://www.facebook.com/share/p/BTFiVSZvKKdcdPqP/?mibextid=WC7FNe
23/02/2024

https://www.facebook.com/share/p/BTFiVSZvKKdcdPqP/?mibextid=WC7FNe

በተወዳጁና በኢትዮጵያ ሙዚቃ ውስጥ ጉልህ ሥፍራ በነበረው አንጋፋውና ዝነኛው ድምፃዊ ጌታቸው ካሣ ኅልፈተ ሕይወት የተሰማኝን ልባዊ ኅዘን ለመግለፅ እወዳለሁ።
ድምፃዊ ጌታቸው ካሣ ላለፉት ዐርባ ዓመታት በላይ በቆየበት የሙዚቃ ሕይወት በተጫወታቸው በርካታ እና በሕዝብ ዘንድ ተወዳጅ በሆኑ ሥራዎቹ የሚታወቅ ሲሆን፤ ከነዚህ ቆየት ካሉ የሙዚቃ ሥራዎቹ ውስጥም "የብዙኃን እናት፣ "ሳይሽ እሳሳለሁ" ፣ "ቀና ብዬ ሳየው " ከብዙ በጥቂቱ ይጠቀሳሉ።
አንጋፋው ድምፃዊ ጌታቸው ካሣ በስፋት ከሚታወቅበት የድምፃዊነት ሙያው ባሻገር የዜማና የግጥም ደራሲ እንዲሁም የሙዚቃ መሳሪያዎች ተጫዋች ነበር።
በዛሬው ዕለት በተሰማው ዜና ዕረፍቱም በደረሰው ኅዘን ለቤተሰቦቹ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹ፣ ለሙያ አጋሮቹ እና ለመላው አድናቂዎቹ በሙሉ መፅናናትን እየተመኘሁ ፤ ፈጣሪ ነፍሱን በአጸደ ገነት እንዲያኖርልን ከልብ እመኛለሁ።

01/01/2024

Happy New Year
መልካም የደስታ
አዲስ ዓመት 01/01/2024

Address

Addis Ababa
70028

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Momentum Media Production posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Momentum Media Production:

Share