Woreda 6 communication

Woreda 6 communication ለህብረተሰባችን ለውጥ ተግተን እንሰራለን

የ5ቱ ዓመታት ገፆች፡ በመደመር ትውልድ ያበበችውና ነዋሪዎቿን ያከበረችው አዲሲቱ ከተማየከተሜነት እውነተኛ ትርጉም በሰማይ ጠቀስ ህንፃዎች መደርደር ወይም በኮንክሪት ክምችት ብቻ ሳይሆን፣ ነዋ...
10/06/2026

የ5ቱ ዓመታት ገፆች፡ በመደመር ትውልድ ያበበችውና ነዋሪዎቿን ያከበረችው አዲሲቱ ከተማ

የከተሜነት እውነተኛ ትርጉም በሰማይ ጠቀስ ህንፃዎች መደርደር ወይም በኮንክሪት ክምችት ብቻ ሳይሆን፣ ነዋሪዎች በክብር፣ በምቾትና በደህንነት በሚኖሩበት ዘመናዊ ሥርዓት ይለካል።

ካለፈው 6ኛው ሀገራዊ ምርጫ እስከ 7ኛው ምርጫ ዋዜማ በተዘረጉት አምስት ዓመታት፣ የመደመር ትውልድ የከተሞቻችንን የትላንት ገፅታ በመቀየር፣ ከተሞችን ከድህነትና ከጥግግት አውጥቶ ለነዋሪዎቻቸው የተመቹ የብልፅግና ማዕከላት እንዲሆኑ አስደናቂ ስራዎችን በመንግሥት መሪነት አከናውኗል።

በእነዚህ የ5ቱ ዓመታት ገፆች ጎልቶ ከሚታየው ስኬት አንዱ የቤት ልማት አብዮት ነው። ቀደም ሲል ዘላቂና ውጤታማ ያልነበረውን የቤት ልማት ፕሮግራም በአዲስ መልክ በመቃኘት ታላቅ የቤት አቅርቦት ንቅናቄ ተደርጓል።

መንግሥት በዋነኝነት ሲያከናውነው የነበረውን ልማት ከግል ዘርፉ እንዲሁም ከመንግሥትና የግል አጋርነት (PPP) ጋር በማስተሳሰር የቤቶች ልማት በከፍተኛ ፍጥነት እንዲከናወን ተደርጓል። በዚህም ከ2013 እስከ 2017 በጀት ዓመት ባሉት ጊዜያት ብቻ ከመንግሥት፣ ከሪል ስቴት አልሚዎችና ከግል ቤት ሠሪዎች አቅም ጋር ተደምሮ ከ1.1 ሚሊዮን በላይ ቤቶች ተገንብተዋል። ከዚህ ጎን ለጎንም፣ ዐቅማቸው ዝቅተኛ ለሆኑ ቤት ፈላጊዎች በመንግሥት በኩል የሚከናወኑ የቤት ልማት ፕሮግራሞች ሳይቋረጡ ቀጥለዋል።

የመደመር ከተሜነት ሰውን ማዕከል ያደረገ በመሆኑ፣ ማኅበረሰብን በማስተባበር ዐቅመ ደካማ ለሆኑ ወገኖች 166,207 ደረጃቸውን የጠበቁ ቤቶች ተገንብተው ተላልፈዋል። ከተሞችን ከእርጅናና ከድህነት ገፅታ ለማላቀቅ፣ በዝቅተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ ቤቶችን ደረጃ የማሳደግ ሥራ በስፋት ተከናውኗል። በ2013 ዓ.ም ከ75 በመቶ በላይ የነበረውን ከደረጃ በታች የሆኑ (substandard) ቤቶች ድርሻ፣ በ2017 ዓ.ም ወደ 52 በመቶ ዝቅ ማድረግ ተችሏል። ይህ ዜጎችን ከማይመችና ኋላቀር አኗኗር ወደ ዘመናዊ የኑሮ ሁኔታ በፈቃደኝነት ያሸጋገረ የክብር ጉዞ ነው።

ይህ ታላቅ የከተማ ትራንስፎርሜሽን የሲቪል ሰርቪሱንና የከተሞችን አገልግሎት ከማዘመን ጋር ተጣምሮ የተጓዘ ነው። ከተሞች ዘመኑን የዋጀ አደረጃጀትና የአስተዳደር ሥርዓት እንዲኖራቸው በማድረግ፣ የማዘጋጃ ቤት አገልግሎቶች ለዜጎች በተሻለ ቅልጥፍና እንዲቀርቡ ተደርጓል።

ይሁን እንጂ፣ መንግሥት ከተሞችን በተቀናጀ አግባብ ሲያለማ፣ አንዳንድ ኃይሎች ይህንን የልማት አቅጣጫ ባለመረዳት የተዛባ አመለካከት ሲያራምዱ ቆይተዋል። ዜጎችን ወደ ተሻለ የኑሮ ሁኔታ ለማሸጋገር የሚሰሩትን የመልሶ ማልማት ስራዎች "ማፈናቀልና ማህበራዊ ኢንጂነሪንግ" ብለው ሲስሉ፣ የከተማን ይዞታ ስርዓት ለማስያዝና አረንጓዴ ቦታዎችን ለመጠበቅ የሚወሰዱ ህጋዊ እርምጃዎችን በሌላ ስም ለማጠልሸት ሞክረዋል። አልፎ ተርፎም ከተሞቻችን ባህላችንንና ታሪካችንን እንዲያንፀባርቁ ለማድረግ የተሰሩትን የውበት ሥራዎች "ታሪክን እንደ ማውደም" አድርገው አቅርበዋል።

ሆኖም እውነታው በተግባር ሊደበቅ አይችልም። ዜጎቻችን የስራዎቹን ፋይዳ አውቀው ምስክርነታቸውን ሲሰጡ፣ የውጭ ሀገራት ሚዲያዎችና ዜጎች ሳይቀሩ በከተሞቻችን ላይ የተመዘገቡትን አስደናቂ ለውጦች እያደነቁ ይገኛሉ። የአገልግሎት አሰጣጥን ለማዘመንና የሲቪል ሰርቪሱን ውጤታማ ለማድረግ የሚከናወኑ ሪፎርሞችንም አሉታዊ ስም በመስጠት ለውጡን ለማደናቀፍ የተሞከሩ ሙከራዎች ከሽፈዋል። በአጠቃላይ እነዚህ የ5ቱ ዓመታት ገፆች፣ መንግሥት ከተሞችን የነገው ዘመን የሥልጣኔ ማዕከላት ለማድረግ ያለውን ግልጽ አቋምና የማድረግ አቅም በተግባር ያረጋገጡ፣ እንዲሁም ለነዋሪዎቻቸው ምቹና ዘመናዊ ከተሞችን የፈጠሩ ደማቅ ታሪካዊ ምዕራፎች ናቸው።

በወረዳ 6 አስተዳደር እየተሰጠ ያለው አገልግሎት የዜጎችን እርካታ እያረጋገጠ መሆኑ ተገለጸበአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት፣ፕብሊክ ሰርቪስ እና ምክር ቤት ፅ...
10/06/2026

በወረዳ 6 አስተዳደር እየተሰጠ ያለው አገልግሎት የዜጎችን እርካታ እያረጋገጠ መሆኑ ተገለጸ

በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 አስተዳደር ኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት፣ፕብሊክ ሰርቪስ እና ምክር ቤት ፅ/ቤት በተቀናጀ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተገኝተው ባደረጉት ምልከታ የሚሰጡ አገልግሎቶች ተደራሽ፣ ቀልጣፋ እና ውጤታማ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

ተገልጋዮቹ እንደተናገሩት ጥያቄዎቻችን በአጭር ጊዜ ምላሽ እያገኙ ነው ብለው ፣ አገልግሎት ፈላጊውን ማዕከል ያደረገ አሠራር መዘርጋቱ የዜጎችን እምነትና እርካታ እንዲጨምር ማድረጉንም ገልጸዋል።
"ከዚህ በፊት ለአንድ ጉዳይ ብቻ ብዙ ቦታዎችን መዞር ይጠበቅብን ነበር፤ አሁን ግን በአንድ ማዕከል ፈጣን እና ቀላል አገልግሎት እያገኘን ነው" ሲሉ ተገልጋዮች ገልጸዋል።

በተጨማሪም የአገልግሎት አሰጣጡ በዘመናዊ አሠራር የተደገፈ መሆኑ፣ የመረጃ ፍሰቱ የተሻሻለ መሆኑ እና ለዜጎች የሚሰጡ ምላሾች ግልጽና ፈጣን መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

ሰኔ 03/2018 ዓ.ም
ወረዳ 6 ኮሚኒኬሽን ፅ/ቤት

አዲስ አበባ የዓለም አቀፍ ኮንፈረንሶች የስህበት ማዕከልነቷን እያረጋገጠች ትገኛለች!ዛሬ ከጤና ሚንስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ እና ከአፍሪካ በሽታዎች ቁጥጥርና መከላከል ማዕከል (Africa CD...
09/06/2026

አዲስ አበባ የዓለም አቀፍ ኮንፈረንሶች የስህበት ማዕከልነቷን እያረጋገጠች ትገኛለች!

ዛሬ ከጤና ሚንስትር ዶ/ር መቅደስ ዳባ እና ከአፍሪካ በሽታዎች ቁጥጥርና መከላከል ማዕከል (Africa CDC) ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ዦን ካሴያ ጋር በቀጣይ ኖቬምበር ወር ላይ ከተማችን አዲስ አበባ 5ኛውን አለምአቀፍ የህብረተሰብ ጤና ኮንፈረንስ ለማካሄድ መመረጥዋንና ኮንፈረንሱን በጋራ ለማዘጋጀት በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ እጅግ ፍሬአማ ውይይት አድርገናል።

አዲስ አበባ በቅርብ ዓመታት ውስጥ በመሰረተ ልማት በሰራናቸው ስራዎች ፣ በነዋሪዎቻችን እንግዳ ተቀባይነት፣ሰላሟ የተረጋገጠ ከተማ በመሆኗ እና የተለያዩ ዓለም አቀፍ ስብሰባዎች ለማካሄድ ምቹ ከተማ መሆን በመቻሏ “የአፍሪካ የጤና ሉዓላዊነት እና ደህንነትን ማላቅ/...to advance Africa’s health soverignity and security agenda./ በሚል 5ኛውን ዓለምዓቀፍ የህብረተሰብ ጤና ኮንፈረንስ ለማዘጋጀት የሚያስችሉ ዝግጅቶች በስፋት በጋራ በመከናወን ላይ ነው፡፡

5ኛውን ዓለምዓቀፍ የህብረተሰብ ጤና ኮንፈረንስ የሃገራት መሪዎች፥ ሚኒስትሮች ፥የህብረተሰብ ጤና መሪዎች፥ፖሊሲ አውጭዎች ፥ተመራማሪዎች እና ባለድርሻ አካላትን የሚሳተፉበት ትልቅ ዓለም አቀፍ ኮንፈረንስ ነው ።

ፊጣሪ ኢትዮጵያና ህዝቦቿን ይባርክ!

Today, I held a highly productive discussion with Minister of Health Dr. Mekdes Daba and the Director General of the Africa CDC, Dr. Jean Kaseya, regarding the selection of our city, Addis Ababa, to host the 5th International Conference on Public Health in Africa (CPHIA), which will take place next November. We also discussed key areas of collaboration to jointly organize the conference.

In recent years, Addis Ababa has become an increasingly attractive destination for major international gatherings, thanks to the significant infrastructure developments undertaken across the city ,the hospitality of our residents, being secured city and its growing capacity to successfully host global events. In this context, extensive preparations are being carried out in collaboration with partners to organize the 5th International Conference on Public Health, under the theme:
“Advancing Africa’s Health Sovereignty and Security Agenda.”
The conference will bring together Heads of State, ministers, public health leaders, policymakers, researchers, and other stakeholders and partners.
May God bless Ethiopia and its people.

ዛሬ ማለዳ በሶስተኛው ዙር የጀመርናቸውን 13.4 ኪሜ የሚሸፍነውን የኮሪደር ልማት ስራዎችን አፈፃፀም ገምግመናል።   የኮሪደሮቹ ልማት በአምስት መስመሮች ተከፋፍለዉ እየተሰሩ ሲሆን እነርሱም፦...
09/06/2026

ዛሬ ማለዳ በሶስተኛው ዙር የጀመርናቸውን 13.4 ኪሜ የሚሸፍነውን የኮሪደር ልማት ስራዎችን አፈፃፀም ገምግመናል።

የኮሪደሮቹ ልማት በአምስት መስመሮች ተከፋፍለዉ እየተሰሩ ሲሆን እነርሱም፦

1- ከቦሌ መድሃኔዓለም እስከ ጎላጎል ( የቦሌ አትላስን መንገድ ከመስቀል አደባባ መገናኛ መንገድ ጋር የሚገናኝ)፣
2- ከጎላጎል እስከ እንግሊዝ ኤምባሲ (የቀበና መገናኛ መንገድን ከመስቀል አደባባ መገናኛ መንገድ ጋር የሚገናኝ) ፣

3- ከቦሌ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በሞኤኮ እስከ ቦሌ መገናኛ መንገድ ( የቦሌ አትላስን መንገድ ከቦሌ መገናኛ መንገድ ጋር የሚገናኝ)፣
4- ከኢምፔሪያል በአደይአበባ ስቴድዮም እስከ ሻላ መናፈሻ ፣
5-ከውሃ ልማት በአትላስ ያለውን እና ከአትላስ እስከ ቦሌ ሩዋንዳ ( የቦሌ አትላስ መንገድን ከመስቀል አደባባ መገናኛ መንገድ እና ከቦሌ አየርመንገድ ጋር የሚገናኝ) በከፍተኛ ደረጃ የመንገድ ትስስርን የሚያሰፋ፣ የንግድ ተቋማት ፣ ሰፋፊ የእግረኛ መንገድ፣ የሳይክል መንገድ እና ለትራንስፖርት አገልግሎት ምቹ እንዲሆኑ ተደርገው እየተገነቡም ናቸው።

በተጨማሪም በርካታ የህዝብ አገልግሎት መስጫ ግንባታዎችን የያዘ ሲሆን የግንባታውም ሂደትም በጥሩ ሁኔታ ላይ ይገኛል።
በአደይአበባ ስታዲየም ዙሪያ አስቀድመው የተጀመሩ የኮሪደርና ሌሎች መሠረተ ልማት ግንባታዎች በፍጥነትና በጥራት እንዲከናወኑ የማድረግ ስራ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

ከኮሪደሩ በተጨማሪም ለብዙ ዘመናት ተረስቶ የኖረ፣ ከሕዝብ ተወስዶ በግለሰቦች ያለአግባብ ተወሮ ለብዙ ብልሽት ተዳርጎ የኖረውን ቦታ ለህዝብ አገልግሎት እንዲውል ተደርጎ በመሰራት ላይ ይገኛል።
ፕሮጀክቶቹን እስከ ሰኔ ወር መጨረሻ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ለአገልግሎት ለማዋል በትኩረት እየተሰራ ይገኛል።

ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!

ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ምአዲስ አበባ   56ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብስባ ውሳኔዎች የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 56ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተ...
09/06/2026

ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም
አዲስ አበባ

56ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብስባ ውሳኔዎች
የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 56ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡

1. ምክር ቤቱ በቅድሚያ የተወያየው የመካከለኛ ዘመን (2019-2023) የማክሮ ኢኮኖሚና ፊስካል ማዕቀፍ ላይ ነው፡፡ የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ ተግባራዊ ከተደረገ ወዲህ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ካሉበት ተግዳሮቶች እየተላቀቀና የኢኮኖሚው መሰረቶችም እየተጠናከሩ መጥተዋል፡፡ ማዕቀፉ በኢኮኖሚ ሪፎርሙ የተገኙ አበረታች ውጤቶችን ይበልጥ አጠናክሮ ማስቀጠል እንዲያስችልና በዋና ዋና የማክሮ ኢኮኖሚ እና ፊስካል ታሳቢዎች ላይ በመመስረት የ2019 በጀት ዓመት የፌዴራል መንግስት በጀት ዝግጅት መነሻ ሆኖ እንዲያገለግል ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በማዕቀፉ ላይ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ በስራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

2. በመጨረሻም ምክር ቤቱ ውይይቱን ያደረገው የ2019 በጀት ዓመት የፌዴራል መንግስት የበጀት ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ የ2019 የፌዴራል መንግስት በጀት የአስር አመቱ መሪ የልማት ዕቅድ አካል የሆነው የ2019-2021 የልማትና ኢንቨስትመንት ዕቅድ ላይ የተቀመጡ ግቦችንና የመካከለኛ ዘመን (2019-2023) የማክሮ ኢኮኖሚና የፊሲካል ማዕቀፍን መሰረት በማድረግ፣ የ2018 በጀት ዓመት የፕሮግራም በጀት አፈጻጸም መነሻ በማድረግ፣ በቀጣይ ሊኖር የሚችለውን የማህበራዊና የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን አቅጣጫዎችና አላማዎች እንዲሁም በመንግስት የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት የመንግስትን የፋይናንስ አቅም እና አስፈጻሚ መስሪያ ቤቶች ከተሰጣቸው ተልዕኮና ሃላፊነት አንጻር የሚያስፈልገውን ወጪ በመገምገም ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡

በዚሁ መሰረትም ለመደበኛ ወጪዎች፣ ለካፒታል ወጪዎች፣ ለክልል መንግስታት ድጋፍ፣ ለዘላቂ የልማት ግቦች ማስፈጸሚያ ድጋፍ የሚውል 2,339,268,126,738 (ሁለት ትሪሊዮን፣ ሶስት መቶ ሰላሳ ዘጠኝ ቢሊዮን፣ ሁለት መቶ ስድሳ ስምንት ሚሊዮን፣ አንድ መቶ ሀያ ስድስት ሺ፣ ሰባት መቶ ሰላሳ ስምንት ብር) በጀት ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በቀረበው የፌዴራል መንግስት የ2019 ረቂቅ በጀት አዋጅ ላይ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡

የፖሊሲ ጉዳይ ቅኝት - ሰኔ 2፣ 2018 ዓ.ም
09/06/2026

የፖሊሲ ጉዳይ ቅኝት - ሰኔ 2፣ 2018 ዓ.ም

በተያዘው ሰኔ ወር ለሚካሄደው የ12ኛ ክፍል ሐገር አቀፍ ፈተና ሙሉ ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸውን ተፈታኝ ተማሪዎችና መምህራን ተናገሩ::******************ሰኔ 2-2018ዓ.ምበአዲስ ...
09/06/2026

በተያዘው ሰኔ ወር ለሚካሄደው የ12ኛ ክፍል ሐገር አቀፍ ፈተና ሙሉ ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸውን ተፈታኝ ተማሪዎችና መምህራን ተናገሩ::
******************
ሰኔ 2-2018ዓ.ም

በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ የሚገኙ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎችና መምህራን በተያዘው ሰኔ ወር ለሚካሄደው የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና አስፈላጊውን ዝግጅት እያደረጉ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

የአስኮ አጠቃላይ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት እና የአዲስ ከተማ 2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ዘንድሮ በሚሰጠው ብሔራዊ ፈተና ብቁና የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ሙሉ ጊዜያቸውን ለጥናት ሰጥተው እያጠኑ መሆናቸውን ተናግረዋል::

የሁለቱም ት/ቤቶች መምህራን በበኩላቸው ፈተናውን ያማከለ የትምህርት ዓይነት ተማሪዎች የተሻለ ውጤት እንዲያመጡ የሚያስችል የመማር ማስተማር ሥርዓት መዘርጋቱንና ከመደበኛ ክፍለ ጊዜ በተጨማሪ የማጠናከሪያ ትምህርቶች እየሰጠን ተማሪዎችን ብቁ እያደረግን ነው ሲሉ ገልፀዋል::

የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ብሩክ ተ/ማርያም በበኩላቸው ፈተናውን ለማስፈፀም በከተማ አስተዳደሩ ከተዋቀረው የኮማንድ ፖስት አባላት ጋር በመቀናጀት ብሄራዊ ፈተናው ስኬታማ ሆኖ እንዲጠናቀቅ የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በመሰራት ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።

አቶ ብሩክ ተ/ማርያም አክለውም በ16 የመንግስትና የግል ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችን በ10 የፈተና ጣቢያዎች 5043 ተማሪዎች በፈተናው ላይ እንደሚቀመጡ ጠቅሰው፣ ፈተናው በበይነ መረብ ለመስጠት ልምምድ በማድረግ የተሻለ ውጤት ለማምጣት የሚያስችል ቅድመ ዝግጅት ማድረጋቸዉን ለኮሙኒኬሽን ዝግጅት ክፍላችን ተናገረዋል።

“ከተማ አስተዳደሩ ለነዋሪዎች አካታች፣ ተደራሽና ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት በትኩረት አየሰራ ነው!” በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ...
08/06/2026

“ከተማ አስተዳደሩ ለነዋሪዎች አካታች፣ ተደራሽና ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት በትኩረት አየሰራ ነው!”

በምክትል ከንቲባ ማዕረግ የአዲስ አበባ ከተማ ፐብሊክ ሰርቪስና የሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ጀማሉ ጀምበር (ዶ/ር)

ከተማ አስተዳደሩ ለነዋሪዎች አካታች፣ ተደራሽና ጥራት ያለው አገልግሎት ለመስጠት በትኩረት አየተሰራ ነው ሲሉ ዶር ጀማሉ ጀንበር ገለፁ።

አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አላስፈላጊ የቢሮክራሲ አሰራርን ያስቀረና ተጠያቂነትን ያሰፈነ ነውም ብለዋል።

በዛሬው ዕለት ለአገልግሎት የበቃው የአዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል ዲጅታል የመንግስት አገልግሎት የየካ ማዕከል 96 ተገልጋዮችን በአንድ ጊዜ ማስተናገድ የሚያስችል መስኮትና ሌሎች መሰረተ ልማቶች የተሟሉለት መሆኑን አስረድተዋል።

ማዕከሉ የ22 ተቋማትን 114 አገልግሎት መስጠት ያስችላል። በቀጣይ ተጨማሪ አገልግሎቶች እንደሚጀምሩ አስታውቀዋል።

የቀድሞው የአርሰናል ተጫዋች ኢማኑኤል ኢቦኤ በአዲስ አበባ ውበት መደነቁን ገለፀ።አዲስ አበባ ውብ ናት ያለው ኢማኑኤል ኢቦኤ፣ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጀምሮ ደማቅ አቀባበል እንደተደረገለት ...
07/06/2026

የቀድሞው የአርሰናል ተጫዋች ኢማኑኤል ኢቦኤ በአዲስ አበባ ውበት መደነቁን ገለፀ።

አዲስ አበባ ውብ ናት ያለው ኢማኑኤል ኢቦኤ፣ ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ጀምሮ ደማቅ አቀባበል እንደተደረገለት ተናግሯል።

አርሰናል የ2026 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮን መሆኑን ተከትሎ በአዲስ አበባ የደስታ መግለጫ ዝግጅት መካሄዱ ይታወቃል።

በዝግጅቱ ተካፋይ ለመሆን ወደ ኢትዮጵያ የመጣው ኢማኑኤል ኢቦኤ እና የኤኤፍ ቲቪ (የአርሰናል ደጋፊዎች ቴሌቪዥን) አባላት በአዲስ አበባ የሚገኙ የልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።

እንግዶቹ አዲስ ስፖርት ፓርክን ጨምሮ የተለያዩ የልማት ሥራዎችን የጎበኙ ሲሆን በዚህም መደነቃቸውን ገልጸዋል።

ኢማኑኤል ኢቦኤ በአዲስ አበባ በተመለከተው ዘመናዊነት ስለመደነቁ መናገሩን ኤኤምኤን ዘግቧል።

ጎብኚዎቹ፣ የከተማዋ አረንጓዴነት፣ ጽዳት እና አጠቃላይ ውበት እጅጉን ማራኪ ሆኖ እንዳገኙት ገልጸዋል።

በአዲስ አበባ ምቹ የአየር ንብረት፣ በነዋሪዎቿ እንግዳ ተቀባይነት እንዲሁም በከተማዋ ዘመናዊነትና ፈጣን ዕድገት እንደተደነቁ ተናግረዋል።

ይህም ከተማዋ በውጭ ቱሪስቶች ያላትን ተመራጭነት ይበልጥ እንደሚያሳድገው ያላቸውን እምነት ገልጸዋል።

አዲስ አበባ፥ የስፖርት ቱሪዝም ማዕከል! የአርሰናል  ክለብ ደጋፊዎች እና የቀድሞው የክለቡ ተጫዋች አዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻዎችና የተለያዩ ታሪካዊ መስህቦችን ጎበኙ።መንግስ...
06/06/2026

አዲስ አበባ፥ የስፖርት ቱሪዝም ማዕከል!

የአርሰናል ክለብ ደጋፊዎች እና የቀድሞው የክለቡ ተጫዋች አዲስ አበባ ከተማ የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻዎችና የተለያዩ ታሪካዊ መስህቦችን ጎበኙ።

መንግስት የስፖርት ቱሪዝም ለማሳደግ፣ የተለያዩ የስፖርት ማዕከላትን ከመገንባት ባሻገር፥ ሀገራዊ፣ ዓለማቀፉዊና አህጉራዊ ስፖርታዊ ፌስቲቫሎችን እንዲዘጋጁ በማድረግ ህብረተሰቡ እየተዝናና ጤናውን እንዲጠብቅ ምቹ ሁኔታን ተፈጥሯል።

የቀድሞው የአርሰናል ተጫዋች ኢማኑኤል ኢቦዬን ጨምሮ የክለቡ ደጋፊዎች እና የAFTV ሚድያ በከተማችን የሚገኙ የቱሪዝም መዳረሻዎችና የስፖርት ማዕከላትን በዛሬው ዕለት ጎብኝተዋል።

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Woreda 6 communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share