13/08/2026
📰 "ፅዳትን ባህሉ ያደረገ ወጣት" በሚል መሪ ቃል በአዲስ ከተማ ወረዳ 6 የፅዳት ዘመቻ ተካሄደ
ወረዳ 6 ኮሙኒኬሽን
(ነሐሴ 7/2018 ዓ.ም)
በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ወጣቶችና ስፖርት ጽሕፈት ቤት፣ከወረዳው ወጣት ማህበር እንዲሁም የወጣቶች ሰብዕና መገንቢያ ማዕከል (ቁጥር 1 እና 2) በጋራ በመሆን ያዘጋጁት "ፅዳትን ባህሉ ያደረገ ወጣት" የተሰኘ የፅዳት ፕሮግራም በዛሬው ዕለት በተሳካ ሁኔታ ተካሂዷል።
የፅዳት ዘመቻው የተካሄደው በወረዳ 6 አስተዳደርምድረ ግቢ ውስጥ ሲሆን፣ የአካባቢው ወጣቶችና ጥሪ የተደረገላቸው ተሳትፎ ቅጥር ግቢውንና አካባቢውን አፅድተዋል።