Woreda 6 communication

Woreda 6 communication ለህብረተሰባችን ለውጥ ተግተን እንሰራለን

📰 "ፅዳትን ባህሉ ያደረገ ወጣት" በሚል መሪ ቃል በአዲስ ከተማ ወረዳ 6 የፅዳት ዘመቻ ተካሄደወረዳ 6  ኮሙኒኬሽን(ነሐሴ 7/2018 ዓ.ም)በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ወጣቶችና ስፖ...
13/08/2026

📰 "ፅዳትን ባህሉ ያደረገ ወጣት" በሚል መሪ ቃል በአዲስ ከተማ ወረዳ 6 የፅዳት ዘመቻ ተካሄደ

ወረዳ 6 ኮሙኒኬሽን
(ነሐሴ 7/2018 ዓ.ም)

በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 ወጣቶችና ስፖርት ጽሕፈት ቤት፣ከወረዳው ወጣት ማህበር እንዲሁም የወጣቶች ሰብዕና መገንቢያ ማዕከል (ቁጥር 1 እና 2) በጋራ በመሆን ያዘጋጁት "ፅዳትን ባህሉ ያደረገ ወጣት" የተሰኘ የፅዳት ፕሮግራም በዛሬው ዕለት በተሳካ ሁኔታ ተካሂዷል።

የፅዳት ዘመቻው የተካሄደው በወረዳ 6 አስተዳደርምድረ ግቢ ውስጥ ሲሆን፣ የአካባቢው ወጣቶችና ጥሪ የተደረገላቸው ተሳትፎ ቅጥር ግቢውንና አካባቢውን አፅድተዋል።

በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ወረዳ 6 ጨው በረንዳ አካባቢ የሚገኙ አምስት መኖሪያ ቤቶች እድሳት ተጀመረ::*******************ነሐሴ 6-2018ዓምየአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ሰላምና ፀጥታ ጽ...
12/08/2026

በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ወረዳ 6 ጨው በረንዳ አካባቢ የሚገኙ አምስት መኖሪያ ቤቶች እድሳት ተጀመረ::
*******************
ነሐሴ 6-2018ዓም

የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ከክፍለ ከተማው የእስልምና ሀይማኖት ምክር ቤት ጋር በመተባበር በወረዳ 6 የሚገኙ አምስት ቤቶችን በአዲስ መልክ ለመገንባት ማስጀመሪያ መርሀግብር ተካሂዷል ።

በማስጀመሪያ ፕሮግራሙ የተገኙት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰላምና ፀጥታ ምክትል ቢሮ ሀላፊ አቶ ብርሐኑ ረታ በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን ማገዝ በሰማይም በምድርም ትልቅ በረከት ነው ሲሉ የቤት ግንባታው በእስታንዳርዱ መሠረት ተሠርቶ ለምርቃት እንደሚበቃም ተስፋቸው እንደሆነም ገልፀዋል።

የክፍለ ከተማው ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ኃላፊ ዶ/ር ጥበቡ ደጀኔ በበኩላቸው እስልምና ምክር ቤቱ በበርካታ የልማት ስራዎች ላይ በቅርበት እየሰሩ መሆናቸውን ገልፀዋል::


የወረዳ 6 ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ግዛቸው ይበልጣል በበኩላቸው የአቅመ ደካማ የሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎች የቤት ግንባታ ሲያስጀምሩ በዚህ ክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ለሁለተኛ ጊዜ መሆኑን ገልፀው ይህም ተግባር በዋናነት በእምነት ተቋማት መካከል ያለውን የመቻቻልና የመደጋገፍ ብሎም የአብሮነት የሚያሳይ ድንቅ ተግባር ነው ሲሉ ተናግረዋል።

# # # # # # # # # # # # # # #
መረጃን ከምንጭ በተለያየ አማራጭ
https://linktr.ee/Addis_Ketema_Communication

በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ ሴቶችን ያከበረች ከተማ አዲስ አበባ!በአዲስ አበባ ከተገነቡ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ሁሉ የተለየና የላቀ ትርጉም ያለው ለነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማ...
12/08/2026

በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ ሴቶችን ያከበረች ከተማ አዲስ አበባ!

በአዲስ አበባ ከተገነቡ ግዙፍ ፕሮጀክቶች ሁሉ የተለየና የላቀ ትርጉም ያለው ለነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል በአስቸጋሪና በምስቅልቅል ሁኔታ ውስጥ የነበሩ ሴችን ህይወት የቀየረ ለብዙዎች የመንፈስ እርካታን ያጎናፀፈ ዘመን ተሻጋሪ ስራ ነው፡፡

ማዕከሉ ከዚህ ቀደም ትኩረት የተነፈጋቸው እና በጎዳና ላይ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ይኖሩ የነበሩ በተለይም በወሲብ ንግድ ላይ የተሰማሩና ለጾታዊ ጥቃት ተጋላጭ የነበሩ ሴቶችን ከነበሩበት አሰቃቂ ህይወት በማላቀቅ በመንከባከብና መጠለያ በመሆን ህይወታቸው እንዲቀየርና ገቢ እንዲያገኙ ብሎም እራሳቸውን እንዲችሉ በማድረግ ከፍተኛ አስተዋጾ እያበረከተ ይገኛል፡፡

በመዲናችን አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ የሚገኘውና በከተማ አስተዳደሩ መልካም እሳቤ የተገነባው የነገዋ የሴቶች ተሀድሶ እና ክህሎት ማበልጸጊያ ማዕከል በአንድ ጊዜ እስከ 2 ሺህ በዓመት ደግሞ እስከ 10 ሺህ የሚደርሱ ሴቶችን የመቀበል አቅም አለው ፡፡

ይህ ግዙፍና ለብዙዎች የመንፈስ እርካታን ያጎናፀፈ ፕሮጀክት በአስቸጋሪ ህይወት ይኖሩ የነበሩ ሴቶችን ከነበረባቸው ሁለንተናዊ ችግር በማላቀቅ ኑሯቸውን በማሻሻል የሥነ ልቦና ድጋፍ እና የጤና እንክብካቤ እንዲያገኙ በማድረግ በስነ-ውበት፣ በፋሽንና ጨርቃ ጨርቅ፣ በምግብ ዝግጅት እንዲሁም በሌሎች 18 የሙያ ዘርፎች የተሟላ ዕውቀት እንዲያገኙ በማድረግ በቀጥታ ወደ ስራ እንዲገቡ እያደረገ ይገኛል፡፡

በአጠቃላይ ከተመሠረተ ጀምሮ በድምሩ 3258 ሰልጣኞችን በማብቃት ወደ ስራው ዓለም እንዲቀላቀሉ በማድረግ ህይወታቸውን በተሻለ መንገድ እንዲመሩና ለሌሎችም አርዓያ እንዲሆኑ በማድረግ ላይ ይገኛል ።

ለነገዋ የሴቶች ተሃድሶና ክህሎት ማበልፀጊያ ማዕከል በከተማ አስተዳደሩ የሚተገበሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶች የሰው ህይወት ላይ መሰረት ያደረጉ የብዙዎችን እንባ ያበሱ እንዲሁም ታሪክን በደማቁ የፃፉ ስለመሆናቸው ይህ ታላቅ ስራ ህያው ምስክር ነው፡፡

የባለጉዳይ ቀን አገልግሎት አሰጣጥ ምልከታ ተደረገ። በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 አስተዳደር የባለጉዳይ ቀን አገልግሎት አሰጣጥ ምልከታ ተደርጓል። በምልከታው በወረዳ አስተዳደሩ ያሉ ሴ...
12/08/2026

የባለጉዳይ ቀን አገልግሎት አሰጣጥ ምልከታ ተደረገ።

በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 አስተዳደር የባለጉዳይ ቀን አገልግሎት አሰጣጥ ምልከታ ተደርጓል።

በምልከታው በወረዳ አስተዳደሩ ያሉ ሴክተር ተቋማት ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ባለጉዳይን የሚያስተናግዱበት አግባብ በምልከታው ታይቷል ።

ነሀሴ 6/2018ዓ.ም
ወረዳ 6 ኮሙኒኬሽን

በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ለ8ኛ ዙር አዲስ ምልምል የሰላም ሰራዊት አባላት የንድፈሃሳብ ስልጠና መስጠት ተጀመረ::******ነሐሴ 4-2018ዓምበእለቱ የተገኙት የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ምክትል ስ...
11/08/2026

በአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ለ8ኛ ዙር አዲስ ምልምል የሰላም ሰራዊት አባላት የንድፈሃሳብ ስልጠና መስጠት ተጀመረ::
******
ነሐሴ 4-2018ዓም

በእለቱ የተገኙት የአዲስ ከተማ ክ/ከተማ ምክትል ስራ አስፈፃሚና የስራ ክህሎት ጽ/ቤት ሃላፊ ወ/ሮ እቴማር ጌታቸው የሰላም ሰራዊት አባላት የአካባቢን ሰላም ከማረጋገጥ አንፃር እያደረጉት ያለውን የተቀናጀ ስራ አጠናክረው ማስቀጠል ይኖርባቸዋል ሲሉ ገልፀዋል::

የከተማችንን ሰላምና ደህንነት ከሰላም ሰራዊትና ከፀጥታ አካላት ጋር አቀናጅተን እየሰራን እንገኛለን ያሉት የክፍለ ከተማው ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ሃላፊ ዶ/ር ጥበቡ ደጀኔ ዛሬ በንድፈሃሳብ የተጀመረው ስልጠና በቀጣይ ደግሞ በተግባር የታገዘ ወታደራዊ ስልጠና የሚሰጥ ይሆናል ብለዋል::

ቀጣይ የሚሰጠውን ስምሪት በተገቢው መንገድ ለመወጣት ስልጠናውን በአግባቡ በመጨረስ እንደሚገባ ገልፀው ስልጠናው በቀጣይ በተግባርም እየተካሄደ እንደሚገኝ ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን አስታውቀዋል::

በመድረኩ ስለ ሰላም አስፈላጊነት እና መሰል ጉዳዮች ዙሪያ መወያያ ሰነድ ቀርቧል::



# # # # # # # # # # # # # #
መረጃን ከምንጭ በተለያየ አማራጭ
https://linktr.ee/Addis_Ketema_Communication

በጤናው ዘርፍ በ5 ዓመታት ውስጥ  ባለፉት 100 ዓመታት ከተመዘገበው  በእጥፍ የሚበልጥ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል ።አዲስ አበባን የጤና ቱሪዝም ማዕከል የማድረግ ጉዞ ተጨባጭ ለውጦችን አስመ...
11/08/2026

በጤናው ዘርፍ በ5 ዓመታት ውስጥ ባለፉት 100 ዓመታት ከተመዘገበው በእጥፍ የሚበልጥ እድገት ማስመዝገብ ተችሏል ።

አዲስ አበባን የጤና ቱሪዝም ማዕከል የማድረግ ጉዞ ተጨባጭ ለውጦችን አስመዝግቧል።

ከተማችን በሁለንተናዊ መልኩ እንድትለወጥ ከተሰሩ ስራዎች አንዱ በጤናው ዘርፍ የታየው የጤና መሰረተ ልማት የማስፋፋት ስራ ዋነኛው ነው፡፡

ባለፉት 5 ዓመታት ውስጥ የጤና መሰረተ ልማትን ለማስፋፋት ከተሰሩ ስራዎች ውስጥ በዳግማዊ ሚኒሊክ ሆስፒታል ውስጥ የተገነቡት ዘመናዊ የአይን ሕክምና፣ የኩላሊት እጥበት እንዲሁም የፎረንሲክ እና ስነምረዛ ምርምር አገልግሎት መስጫ ማዕከላት ይጠቀሳሉ፡፡

በዘውዲቱ ሆስፒታል እጅግ ዘመናዊ ተደርጎ የተገነባው የህክምና ልህቀት ማዕከል እና በራስ ደስታ ዳምጠው ሆስፒታል ውስጥ ለታካሚዎች ዘመኑን የዋጀ የህክምና አገልግሎት የሚሰጥ “አዲስ የላቀ የህክምና ማዕከል” ተገንብተው አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ፡፡ በማዕከላቱ በነባሮቹ ሆስፒታሎች በኋላቀር የህክምና መሳሪዎች እና ለታካሚዎች በማይመችና በተጨናነቀ ሁኔታ ይሰጡ የነበሩ አገልግሎቶችን በመቀየር የዘመኑ ቴክኖሎጂ ተሟልተውላቸው አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ፡፡

በተጨማሪም የአበበች ጎበና እናቶችና ህጻናት ሆስፒታል፣ ላፍቶ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል፣ ኮልፌ እስፔሻላይዝድ ሆስፒታል እና የገላን ድንገተኛ ህክምና ሆስፒታል በጥቂት ዓመታት ውስጥ በአዲስ አበባ የተገነቡ የህክምና ማዕከላቶች ናቸው።

ለ4ዐ ጤና ጣቢያዎች መሰረታዊ ማስፋፊያ እና 9 አዳዲስ የጤና ጣቢያዎች ተገንብተው ወደ አገልግሎት ገብተዋል፡፡

አዲሰ አበባን የጤና ቱሪዝም ማዕከል ማድረግ እና በጤናው ዘርፍ ያለው ፍላጎት በመንግስት ብቻ የማይሟላ በመሆኑ የግሉን ዘርፍ በመደገፍም እጅግ ዘመናዊ የህክምና አገልግሎት የሚሰጡ ሆስፒታሎች እንዲገነቡ ተደጓል።

በአጠቃላይ በጤናው ዘርፍ በተከናወኑ ስራዎች ከ 5 ዓመት በፊት የነበሩትን አልጋዎች ቁጥር ከ 2 እጥፍ በላይ ማሳደግ ተችሏ፡፡ በዚህም በ 5 ዓመታት ውስጥ የታየው እድገት ባለፉት 100 ዓመታት ከተመዘገበው እድገት በእጥፍ እንዲበልጥ አድርጎታል፡፡

ጤናችንን የምንጠብቀው በሕክምና ብቻ ሳይሆን በመከላከል ጭምር በመሆኑ አዲስ አበባን ከብክለት በመከላከል፣ ፅዱ አረንጓዴ እና ለኑሮ ተስማሚ ከተማ በማድረግ ጤናማ አካባቢን የመፍጠር የጤና ፖሊሲያችን በከተማችን በተሟላ ሁኔታ እየተተገበረ ይገኛል፡፡

የፖሊሲ ጉዳይ ቅኝት - ነሐሴ 5፣ 2018 ዓ.ም
11/08/2026

የፖሊሲ ጉዳይ ቅኝት - ነሐሴ 5፣ 2018 ዓ.ም

09/08/2026

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Woreda 6 communication posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Shortcuts

Share