ዐዋዲ - Awadi

ዐዋዲ - Awadi ነገርን ከምንጩ
Straight from the horse's mouth

28/05/2025

“ለብዙ ጓደኞቼ ለመኖር እድል አግኝቼ 84 ዓመት ቀላል ጊዜ አይደለም፡፡ ይህንን ማክበር ብቻ ሳይሆን አገር አቋርጣችሁ ከአገር ወጥታችሁ ይህን በማድረጋችሁ አመስግ/ናችኋለሁ” ሲሉ የቀድሞው ረእሰ ብሄር መንግስቱ ሃይለማሪያም Ethiopian Society Partnership Advocacy የተባለው ድርጅት እና አባላቱ ስለሰጧቸው እውቅና ምስጋና አቅርበዋል፡፡
Video: Guenet Ayele



በሃገር ባህል መስተንግዶ ፍላጎትዎን የሚያሟላልዎ ሰሜን ሸዋ ሆቴል ሁሉንም አሟልቶ ይጠብቆታል። አድራሻ ላምበረት 02 መገንጠያ
17/05/2025

በሃገር ባህል መስተንግዶ ፍላጎትዎን የሚያሟላልዎ ሰሜን ሸዋ ሆቴል ሁሉንም አሟልቶ ይጠብቆታል። አድራሻ ላምበረት 02 መገንጠያ

በኒው ዚላንድ የበጎች ቁጥር ከአገሪቱ ዜጎች ቁጥር እጅጉን እንደሚልቅ የዓለም መገናኛ ብዙሃን በመዘገብ ላይ ይገኛሉ፡፡ ኒው ዚላንድ ዜጎች የበርካታ በጎች መኖሪያ ተብለው ከተመደቡ ጥቂት አገራ...
14/05/2025

በኒው ዚላንድ የበጎች ቁጥር ከአገሪቱ ዜጎች ቁጥር እጅጉን እንደሚልቅ የዓለም መገናኛ ብዙሃን በመዘገብ ላይ ይገኛሉ፡፡ ኒው ዚላንድ ዜጎች የበርካታ በጎች መኖሪያ ተብለው ከተመደቡ ጥቂት አገራት ተርታ ተቀምጣለች፡፡

የአገሪቱ መንግስት የስታቲስቲክስ ኤጀንሲ መረጃዎች እንደሚያሳዩት በኒው ዚላንድ 23.6 ሚሊዮን በጎች የሚገኙ ሲሆን የነዋሪዎች ቁጥር ደግሞ ከ5.3 ሚሊዮን አይበልጥም፡፡ ለአንዱ ነዋሪ በአማካይ 4.5 በግ ይደርሰዋል ማለት ነው፡፡

በጎችን ለስጋ እና ለሱፍ በግ ማርባት የኒውዚላንድ ነዋሪዎች ትልቁ የገቢ ምንጭ ሆኖ መቆየቱን የዘገበው አሶሼትድ ፕሬስ ነው፡፡

ፈረንሳይ ጉራራ ተብሎ በሚጠራው ሰፈር ሹፌርና ረዳቱን ብቻ የጫነ አውቶቡስ ከቀኝ መስመር ወጥቶ በግራ መስመር ላይ ወድቋል። ሁለቱም ተርፈዋል። አውቶቡሱ በርካታ ሰዎችን አሳፍሮ ቢሆን ኖሮ በር...
06/05/2025

ፈረንሳይ ጉራራ ተብሎ በሚጠራው ሰፈር ሹፌርና ረዳቱን ብቻ የጫነ አውቶቡስ ከቀኝ መስመር ወጥቶ በግራ መስመር ላይ ወድቋል። ሁለቱም ተርፈዋል። አውቶቡሱ በርካታ ሰዎችን አሳፍሮ ቢሆን ኖሮ በርካቶችን ለሞት የሚዳርግ አደጋ ይከሰት እንደነበር በስፍራው የነበሩ የፖሊስ ባልደረቦች ተናግረዋል።
ሚያዝያ 28 ቀን 2017 ዓ.ም

ወመዘክር አዳራሹን  በብላታ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ ስም ሰየመየብሄራዊ ቤተ መዛግብትና መጽሀፍት( ወመዘክር )ዋና ዳይሬክተር ይኩኑአምላክ መዝገቡ እንደገለጹት፤ ብላታ መርስዔ ኀዘን ወልደ...
03/04/2025

ወመዘክር አዳራሹን በብላታ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ ስም ሰየመ

የብሄራዊ ቤተ መዛግብትና መጽሀፍት( ወመዘክር )ዋና ዳይሬክተር ይኩኑአምላክ መዝገቡ እንደገለጹት፤ ብላታ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ ብዙ ሰአታቸዉን ለጽሁፍ በመስጠት ግዙፍ ስራዎችን አበርክተዋል።
ወመዘክር መታሰቢያ ሆኖ ከመቋቋሙ በፊት እርሳቸዉ ነገ ትዉልድ የሚፈልጉ ነገሮች ሲዘክሩ የኖሩ የሀገር ባለዉለታ መሆናቸዉን ገልጸዋል።
የወመዘክር አንዱ ስራ ባለዉለታዎቻችንን መዘከር ነዉ ያሉት ዳይሬክተሩ እንደነዚህ ያሉ ስራዎች እንደሚቀጥሉ አስታዉቀዋል።
የብላታ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ ልጅ የሆኑት አምሀ መርስዔ ኀዘን በበኩላቸዉ አባታቸዉ ብዙዉን ጊዜያቸዉ በመጽሀፍ ያሳለፉ መሆናቸዉ በመግለጽ ለስራቸዉ እዉቅና በመሰጠቱ መደሰታቸዉን ገልጸዋል።
የብላታ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ የእጅ ጽሁፍ ስራዎች ሳይቀር ለቤተመጽሀፉ ማስረከባቸዉን የገለጹ ሲሆን እንደነዚህ ያሉ ተግባሮች ሊለመዱ እንደሚገባ ጠቁመዋል።
‘የ20ኛው መቶ ክፍል ዘመን መባቻ’ የተሰኘ አይተኬ መዝገበ ታሪክ እና በርካታ ሃይማኖታዊ፣ ስርዓተ መንግስታዊ እና ማህበራዊ ይዘት ያላቸውን መጻህፍት ለትውልዱ ያበረከቱት ብላታ መርስዔ ኀዘን ወልደ ቂርቆስ በዘመናዊት ኢትዮጵያ ታሪክ ላይ ጉልህ አሻራቸውን ካሳረፉ የሃያኛው መቶ ክፍለ ዘመን ድንቅ ምሁራን መካከል ዋነኛው ናቸው፡፡
Ethiopian Press Agency /የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት/


31/03/2025

አስጨናቂ ትዕይንት

ዛሬ ከሰዓት በሩሲያ ሴንትፒተርስበርግ ከተማ በአንድ አፓርታማ ላይ የተከሰተ የእሳት አደጋን ተከትሎ አንድ ታናሽ ብላቴና ከሶስተኛ ፎቅ ላይ ሲዘል ይታያል። ሆኖም ጎረቤቶቹ ብርድልብስ በመዘርጋት ከመከስከስ አትርፈውታል።

በአሁን ሰዓት በሆስፒታል ውስጥ ህክምና በመከታተል ላይ መሆኑን የአር ቲ ሪፖርት ያመለክታል።

"ትህነግ/ህወሓት ወልቃይትን የሚፈልገው መሬቱን ነው። ሰው አይታየውም" ጌታቸው ረዳ!የድሮ የትህነግ ምክትል ሊቀመንበር፣ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝደንት፣ በፕሪቶሪያ ስምምነት ዋናው ተደራዳሪ፣...
31/03/2025

"ትህነግ/ህወሓት ወልቃይትን የሚፈልገው መሬቱን ነው። ሰው አይታየውም" ጌታቸው ረዳ!
የድሮ የትህነግ ምክትል ሊቀመንበር፣ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝደንት፣ በፕሪቶሪያ ስምምነት ዋናው ተደራዳሪ፣ በጦርነቱ ወቅት ዋናው ቃል አቀባይ፣ ትህነግ ህገወጥ ጉባኤ ካደረገ በኋላ የፍንካቹ ትህነግ ሊቀመንበርና ወዘተ አቶ ጌታቸው ረዳ አማራ ሲታገልበት የኖረውን፣ የአማራውን እውነት "ትክክል ናችሁ" ብሏል። አማራ ህዝቤ ላይ ጥቃት ደርሶበታል ሲል ትህነግ ለመሬት ብሎ ህዝብ ላይ ያደረሰውን መከራ ሲገልፅ፣ ሲታገልበት ኖሯል።
ትህነግ ወልቃይት ጠገዴ፣ ራያ፣ አበርገሌና ጠለምት ላይ ንፁሃንን ሲገድልና ሲያፈናቅል አማራ " ትህነግ የሚፈልገው መሬቱን ብቻ ነው" ሲል ኖሯል። ዛሬ ጌታቸው ረዳ "ትክክል ናችሁ" ብሎ ስለ ድርጅቱ አስተሳሰብና አላማ መስክሯል። ራሱ ጌታቸው ስለነበረበት አስተሳሰብ፣ ስለሚያውቀው የድርጅቱና የአመራሮቹ ክፉ አመለካከትና ተስፋፊነት ነው የፃፈው።
ጌታቸው ረዳ ዛሬ በትግርኛ በፃፈው ፅሁፍ ትህነግ ወልቃይት ሲባል መሬት ብቻ እንጂ ህዝብ አይታየውም ብሏል። ለአመታት የተፈፀመው በደልም ከዚህ ከምናውቀው ዛሬ ጌታቸው ረዳ ከመሰከረው ሀቅ የመጣ ነው። እውነቱ የሚታወቅ ቢሆንም የጌታቸው ረዳ ምስክርነት ቀላል አይደለም። የራሱ የትህነግ ቃል ነው። እውነታው ይህ ነው! ትህነግ ወልቃይት ላይ ሰው ከታየው ይገድለዋል። ሰው ሲታየውም ሲገድለውና ሲያፈናቅለው ነው የኖረው። ወልቃይት ጠገዴ፣ ራያ፣ ጠለምትና አበርገሌ ላይ ከእነ ቋንቋና ማንነቱ መቀጠል የፈለገ ፍጡር ቀርቶ አማራ ያሳደጋቸው ዛፎችን አጥፍቷል። የሚፈልገው መሬቱን ስለሆነ። አማራ "ወገኔ ላይ የዘር ፍጅት ተፈፅሟል" ሲል የሚታየው የሚጎዳው ህዝቡ ነው። አማራ ወገኖቼ በቋንቋቸው እንዳይማሩ፤ በቀያቸው እንዳይኖሩ ተደርገዋል ሲል የሚታየው ህዝብና ማንነቱ ነው። ትህነግ ግን ጌታቸው ረዳ ዛሬ የተናገረው ነው አመለካከቱ። አማራም ሲታገል የኖረው፣ ወደፊትም የሚታገለው ይህን ፀረ ሰው አስተሳሰብ ነው። ይህ ከቅኝ ከዥዎቹ ያልተለየን አመለካከት ተሸከመው ነው አሁንም በተለያየ ስልት መቀጠል የፈለጉት። አማራ ደግሞ ወገኔ በዚህ ክፉ አስተሳሰብ እንዲያልቅ አልፈልግም ብሎ ከተነሳ ውሎ አድሯል።
ጌታቸው ረዳ ይህን የመሰከረው ለአማራ ተቆርቁሮ አይደለም። ከትህነግ ፍንካች ጋር ባለው ጊዜያዊ ጠብ የዛ ቡድን አባላት ጋር ይዞት የነበረውን፣ ሲመክርበትና ሲያወሩ የኖሩትን ፀረ ሰው አመለካከት፣ አርሶ አደር ቁጥቋጦ መንጥሮ መሬት እንደሚያርሰው ሰው ፈጅተ***ው መሬት የሚፈልጉበትን አመለካከታቸውን ገልፆ ነው ክፉነታቸውን ሊያሳይ የጣረው።
Shiferaw.Offical

Address

Addis Ababa
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ዐዋዲ - Awadi posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share