ሔኖክ ሚዲያ - Henok Media

ሔኖክ ሚዲያ - Henok Media #ኢትዮጵያ

በዓለም ላይ የሂራቁን ሳዳም ሁሴን እና የሊቢያውን መሐመድ ጋዳፊን ጨምሮ ፣ ብዙ ነገሥታት ሹግጥ እጃቸው ላይ እያለ ተማርከው ፣ እጅ ሰጥተው ፣ ተሰቃይተው ተዋርደው አገራቸውንም አዋርደው ፣ ...
04/06/2025

በዓለም ላይ የሂራቁን ሳዳም ሁሴን እና የሊቢያውን መሐመድ ጋዳፊን ጨምሮ ፣ ብዙ ነገሥታት ሹግጥ እጃቸው ላይ እያለ ተማርከው ፣ እጅ ሰጥተው ፣ ተሰቃይተው ተዋርደው አገራቸውንም አዋርደው ፣ ክብራቸውን ሁሉ የጠላት መሳለቂያ አድርገው ፥ ላይቀርላቸው ነገር በጠላታቸው እጅ መገደላቸውን እናውቃለን፦ ለምሳሌ ያህልም ከታላላቅ ነገሥታቶች ውስጥ ጦርነት ላይ እጅ ስጡ ሲባሉ እጅ ሰጥተው ተማርከው ከተገደሉት ውስጥ ጥቂቶችን ለምስክርነት እንጠራለን፦

1. King Darius III of Persia
2. King Atahualpa of the Inca Empire
3. King Richard III of England
4. King Charles I of England
5. King Louis XVI of France
6. Jugurtha King of Numidia (North Afric)
7. Vercingetorix King of the Arverni (Gaul)
8. Bayinnaung's son (Nanda Bayin) King of Burma
9. Montezuma II Aztec Emperor

እንግዲህ ነገር ሳላበዛ እነዚህ ሁሉም ጦርነት ሲሸነፉ እጃቸው ሰጥተው ወይም ሊያመልጡ ሲሮጡ ተይዘው የተገደሉ ናቸው።

ምን ለማለት ፈልጌ ነው፦

ለክብሩ ሟች፣ የአገሩን ሥም በልዕልና ከፍ አድርጎ ይኽው እስከ ዛሬ ድረስ ለሁላችንም የመንፈስ ኩራት ሆኖ በኢትዮጵያውያን ልብ ውስጥ ተቀምጦ ለዘለአለም በሕይወት የሚኖረው ቴዎድሮስ ነው።
.....የሴቱን አናውቅም ወንድ አንድ ሰው ሞተ.....

#ኢትዮጵያ #ኢትዮጵያ2017 #መቅደላ #ቴዎድሮስ
#መስቀል #ተዋህዶ #ኦርቶዶክሳዊ
#አፍሪካ #ላሊበላ

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት ባደረገው ስብሰባ የሚከተለውን ውሳኔ አስተላልፏል ፦1. ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆርስን የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፤2. ብፁዕ አቡነ  ሳዊሮስን የመንበረ ...
23/05/2025

የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በዛሬው ዕለት ባደረገው ስብሰባ የሚከተለውን ውሳኔ አስተላልፏል ፦

1. ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆርስን የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ፤
2. ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስን የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽሕፈት ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ፤
3. ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስን የሐዲያ ሀ/ስብከትን እንደያዙ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤
4. ብፁዕ አቡነ ናትናኤል ዘኮሎራዶን የቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ገዳማት ሊቀ ጳጳስ፤
5. ብፁዕ አቡነ ናትናኤልን ሚኒሶታን እንደያዙ የኮሎራዶ ሀ/ስብከትን እንዲመሩ፤
6. ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የደቡብ አፍሪካ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳ ጳስ፤
7. ብፁዕ አቡነ ዕንባቆምን የገዳማት መምሪያ ሊቀ ጳጳስ ሆነው እንዲመሩ፤
8. ብፁዕ አቡነ ሙሴ አውስትራልያን እንደያዙ የግቢ ቅዱስ ገብርኤልና የበዐታ ለማርያም ገዳም ሊቀ ጳጳስ ሆነው እንዲመሩ ወስኗል።

መረጃው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ የተገኘ ነው።

እንኳን ለአርበኞች ቀን አደረሳችሁ።በአምስት ዓመት ነፃነት ትግሉ ውስጥ የሴቶች ሚና እጅግ ትልቅ ነው። ዘወትር መዘከርና ለትውልድ መነገር ያለበት ሥራ ነው። ይህንን ምክንያት በማድረግ የሴት ...
05/05/2025

እንኳን ለአርበኞች ቀን አደረሳችሁ።

በአምስት ዓመት ነፃነት ትግሉ ውስጥ የሴቶች ሚና እጅግ ትልቅ ነው። ዘወትር መዘከርና ለትውልድ መነገር ያለበት ሥራ ነው። ይህንን ምክንያት በማድረግ የሴት አርበኞችን ተጋድሎ የሚያሳይ ዝግጀት የቀረበ በመሆኑ በማስፈንጠሪያው በመግባት እንድትመለከቱ እጋብዛለሁ።

https://youtu.be/8TX2dFw1b_Y?si=HEUZdnvepCpi1hOT

Like, Subscribe; comment ያድርጉ።

share በማድረግ ለሌሎች ያድርሱልን።

 Like, Subscribe; comment ያድርጉ።
26/04/2025



Like, Subscribe; comment ያድርጉ።

S

እንኳን ለአድዋ ድል በዓል አደረሳችሁ።ነጥብ ሚዲያን ይወዳጁ።~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~You tube፦ https://youtube.com/@-netib_mediaTikt...
01/03/2025

እንኳን ለአድዋ ድል በዓል አደረሳችሁ።

ነጥብ ሚዲያን ይወዳጁ።
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
You tube፦ https://youtube.com/@-netib_media
Tiktok፦ tiktok.com/
Telegram፦ https://t.me/netib_media0
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~

27/02/2025




አድዋ የአባቶቻችን ተጋድሎ የአዲሱ ትውልድ ኩራት

ነጥብ ሚዲያ የአድዋ ድል በማስመልከት " " የተሰኘ ፕሮግራም አዘጋጅቷል። ዛሬ ለእናተ ይደርሳል።      ይልድርጉእናመሰግናለን።
27/02/2025

ነጥብ ሚዲያ የአድዋ ድል በማስመልከት " " የተሰኘ ፕሮግራም አዘጋጅቷል። ዛሬ ለእናተ ይደርሳል።

ይልድርጉ

እናመሰግናለን።

የካቲት 3 ቀን 2017 ዓ.ምለመገናኛ ብዙሀን.በየአሉበትጉዳዩ፦ ወደ አገሬ እንዳልጓዝ መከልከልን ይመለከታልወደ ኢትዮዽያ ለመሄድ በኢትዮዽያ አየር መንገድ ትኬት የቆረጥኩት ለዛሬ ስለሆነ ከጧቱ...
10/02/2025

የካቲት 3 ቀን 2017 ዓ.ም

ለመገናኛ ብዙሀን.

በየአሉበት

ጉዳዩ፦ ወደ አገሬ እንዳልጓዝ መከልከልን ይመለከታል

ወደ ኢትዮዽያ ለመሄድ በኢትዮዽያ አየር መንገድ ትኬት የቆረጥኩት ለዛሬ ስለሆነ ከጧቱ 12 ሰዓት በአትላንታ ዓለም-አቀፍ አየር ማረፊያ ተገኝቸ ነበር። የአገልግሎት ጊዜው ያላለፈ የኢትዮዽያ ፓስፖርትና የተረጋገጠ የጉዞ ትኬት ይዥ የተገኘሁ ቢሆንም የኢትዮዽያ አየር መንገድ ግን በአሜሪካ የኢትዮዽያ ኤምባሲን አነጋግሬ የተለየ ፈቃድ ካልተሰጠኝ በስተቀር ወደ ኢትዮዽያ መጓዝ እንደማልችል በአትላንታ የኢትዮዽያ አየር መንገድ ሀላፊ በሆኑት በአቶ
ተሾመ ገ/ስላሴ ተነግሮኝ ተመልሻለሁ።

በአሸባሪነት ወንጀል ሊከሰኝ እንደሚፈልግና በቁጥጥር ስር እንድውል ከኢንተር-ፖል ጋር ጭምር እየተነጋገረ እንደሆነ ሲገልፅ የነበረው የኢትዮዽያ መንግስት ዛሬ በራሴ ፈቃድ ወደ አገሬ ለመመለስ ስሞክር በእኔ ላይ ህገ-ወጥ ክልከላ ማድረጉ አስገርሞኛል። ምን አልባት እንዲህ አይነቱ ድርጊት በአለም ለመጀመሪያ ጊዜ የተፈፀመ ሊሆን ይችላል። መንግስት እኔን በወንጀለኛነት ከጠረጠረኝ ሊከሰኝና ሊያስረኝ ይችላል እንጅ ወደ አገሬ እንዳልገባ ሊከለክለኝ አይችልም።

አንድን ኢትዮዽያዊ የሆነና የኢትዮዽያ ፓስፖርት የያዘን ዜጋ ወደ አገሩ እንዳይገባ ለመከልከል የሚያስችል ምንም ዓይነት የህግ ማዕቀፍ የለም። ስለሆነም በሌላ አገር አየር መንገድ ትኬት ቆርጨ ሰሞኑን ወደ አገሬ ተመልሸ እንደምሄድ በዚህ አጋጣሚ አሳውቃለሁ።
ከአክብሮት ጋር
ልደቱ አያሌው

ግብፅና ሶማሊያ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ስትራቴጂካዊ አጋርነት መመስረታቸውን አስታወቁትናንት ወደ ግብፅ ያቀኑት ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀመድ ሶማሊያ እና ግብፅ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ስት...
25/01/2025

ግብፅና ሶማሊያ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ስትራቴጂካዊ አጋርነት መመስረታቸውን አስታወቁ

ትናንት ወደ ግብፅ ያቀኑት ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ ሞሀመድ ሶማሊያ እና ግብፅ ግንኙነታቸውን ለማጠናከር ስትራቴጂካዊ አጋርነት መመስረታቸውን አስታውቀዋል።

ስምምነቱ ፀጥታን ለማጠናከር፣ ዘላቂ የኢኮኖሚ ልማት ለማምጣት እና በአፍሪካ ቀንድ እና በቀይ ባህር አካባቢዎች ያሉ የጋራ ተግዳሮቶችን ለመቅረፍ ያለመ ነው ተብሏል።

ሁለቱ አገራት የጋራ ስትራቴጂዎችን አፈፃፀም ለመቆጣጠር እና ለትብብር የሚሆኑ አዳዲስ መንገዶችን ለመዳሰስ በፕሬዝዳንት እና ሚኒስትሮች ደረጃ መደበኛ ምክክር ለማድረግ የሚያስችሉ አሰራሮችን ለማቋቋም ማቀዳቸው ተጠቁሟል።

ግብፅ በጎርጎሮሳውያኑ 2024ቱ ወታደራዊ ትብብር ፕሮቶኮል መሠረት ለሶማሊያ የምታደርገውን ወታደራዊ ድጋፍ ለመቀጠል ቃል የገባች ሲሆን፣ ይህም በዋነኛነት በፀረ-ሽብርተኝነት ትግል ፣ በስልጠና እና በድንበር ደህንነት ላይ እንደሚያተኩር ተመላክቷል።

በተጨማሪም ሶማሊያ የፍትህ ስርዓቷን በማሻሻል፣ አዲስ ህገ መንግስት በማዘጋጀት እና ከሀገራዊ ግቦች ጋር ተስማሚ በሆነ መልኩ ምርጫ እንድታዘጋጅ ድጋፍ ታደርጋለች ተብሏል።



~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
You tube፦ https://youtube.com/@-netib_media
Tiktok፦ tiktok.com/
Telegram፦ https://t.me/netib_media0
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~

" ህዝቡ በመረጣችሁት መንገድ ይታገላችኋል " - በእነ አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓትበምክትል ሊቀ-መንበር አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራ ህወሓት ፤ ትናንት ጥር 15/2017 ዓ.ም  " የበላይ...
25/01/2025

" ህዝቡ በመረጣችሁት መንገድ ይታገላችኋል " - በእነ አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት

በምክትል ሊቀ-መንበር አቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራ ህወሓት ፤ ትናንት ጥር 15/2017 ዓ.ም " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል የተሰጠውን መግለጫ የሚቃወም መግለጫ አውጥቷል።

በዚህም መግለጫው ፥ በሊቀ-መንበር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመራውን ህወሓት" የነሃሴው " ብሎ ሲጠራው ራሱን ደግሞ " ነባር " በማለት ገልጿል።

" የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል ያወጡት መግለጫ የ " ነሃሴው ህወሓት ህዝቡን እና ሰራዊቱ ለመበታተነ የሰራው ክፋት ውጤት ነው " በማለት ገልፆታል።

" የነሃሴው ህወሓት ህዝብን እና የኢትዮጵያ ብሄራዊ የምርጫ ቦርድ ያልተቀበለው ጉባኤ በማካሄድ ነባሩን ህወሓት እንዲዳከም ሰርቷል " ሲል በአቶ ጌታቸው የሚመራው ህወሓት ፤ " ወታደራዊ አምባገንነት ታግሎ ዴሞክራሲያዊ እና ህዝባዊ መንግስት የጨበጠ ህዝብ ወደ ኋላ አይመለስም " ብሏል።

" የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል ስም የወጣውን መግለጫ " የጦርነት አዋጅ ነው ፤ በህዝብ ላይ አፋኝ አስተዳደር የሚጭን ተቀባይነት የሌለውና የውድቀት ጥሪ " ሲል ገልጾታል።

" ህዝቡ በመረጣችሁት መንገድ ይታገላቹሃል " ያለው በአቶ ጌታቸው ረዳ የሚመራው ህወሓት " የጦርነት አዋጃችሁ የፕሪቶሪያ ስምምነት አፍርሶ ፤ ትግራይ ለአህጉራዊ ዓለምአቀፋዊ ተነጥሎ እና ውግዘት የሚዳርግ ህዝቡን ለአደጋ የሚያጋልጥ ነው " ሲል አክሏል።

የአነ አቶ ጌታቸው ቡድን መግለጫውን መላ የትግራይ ኃይል አባላት እንዲያወግዙት ጠይቆ " ህዝብን እና መንግስታችሁ በሚስጡዋችሁ አቅጣጫ ብቻ እንድትንቀሳቀሱ ጥሪያችን እናቀርባለን " ሲል አሳስቧል።

ህዝቡ እና ወጣቱ በአደገኛ ሁኔታ ላይ እንደሚገኙም ገልጾ ይህንኑ በመገንዘብ ከመቼውም ጊዜ በላይ ትግሉ በማጠናከር ለመብቱ ለአንድነቱ እና ለህልውናው በመታገል የተደቀነበት አደጋ እንዲመከት ጥሪ አቅርቧል።

ለህዝቡ ፣ ለዳያስፓራ ፣ ለተፎካካሪ ፓርቲዎች እና ሲቪክ ማህበራት " የበላይ ወታደራዊ ኃይል አመራሮች ነን " በሚል ስም የወጣው መግለጫ እንዲያወግዙት ጠይቀዋል።

መግለጫውን ያወጡት አመራሮች ያለፈ ታሪካቸው ከሚያጎድፍ ተግባር በመውጣት አሁን የፈፀሙት ስህተት በአስቸኳይ እንዲያርሙ እና ታሪካቸው እንዲያድሱ ጥሪ አቅርቧል



~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
You tube፦ https://youtube.com/@-netib_media
Tiktok፦ tiktok.com/
Telegram፦ https://t.me/netib_media0
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~

በአማራ ክልል በሶስት ወራት ውስጥ 120 ንጹሀን ተገደሉ፡፡የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአማራ፣ ኦሮሚያ፣ ጋምቤላ ክልሎች ያደረጋቸውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሪፖርት ይፋ አድ...
24/01/2025

በአማራ ክልል በሶስት ወራት ውስጥ 120 ንጹሀን ተገደሉ፡፡

የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) በአማራ፣ ኦሮሚያ፣ ጋምቤላ ክልሎች ያደረጋቸውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሪፖርት ይፋ አድርጓል፡፡

ኮሚሽኑ እንደለጸው ሪፖርቱ ከመስከረም ወር አጋማሽ 2017 ዓ.ም እስከ ታኅሣሥ 2017 ዓ.ም አጋማሽ ባለው ጊዜ ውስጥ ያለውን ጊዜ የሚመለከት ነው ብሏል፡፡

ሪፖርቱ በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ በግጭት ዐውድ ውስጥ ባሉ አካባቢዎች የተፈጸሙ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችን በሙሉ የሚሸፍን አይደለም ያለው ኮሚሽኑ፤ በእነዚህ አካባቢዎች በነጻነት ተንቀሳቅሶ የተሟላ ክትትልና ምርመራ ለማካሄድ ምቹ ሁኔታ ባለመኖሩ፣ ውጤታማ ክትትልና ምርመራ የተከናወነባቸውን ጉዳዮች ብቻ በማሳያነት እንዳቀረበም ገልጿል፡፡

ኢሰመኮ በሪፖርቱ ላይ እንደጠቀሰው በግጭት በተጎዱ አካባቢዎች ከደረሱ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች አሳሳቢ ሆነው ከቀጠሉ ጉዳዮች መካከልም ከፍርድ ውጭ ግድያ መፈጸም፣ በግጭት ዐውድና አካባቢ የሚደርስ የሲቪል ሰዎች ሞት፣ የአካል ጉዳት፣ የንብረት ውድመትና ዘረፋ ዋነኞቹ ናቸው ተብሏል፡፡

እንዲሁም የዘፈቀደ፣ የጅምላና የተራዘመ እስራትና የተፋጠነ ፍትሕ እጦት፣ አስገድዶ መሰወር፣ እገታ፣ በመዘዋወር መብትና በመጓጓዣ መንገዶች ላይ የሚፈጸም ሕገ-ወጥ ገደብ፣ የሀገር ውስጥ መፈናቀል እና የዳኝነት ነጻነት መሸርሸሮች እንዳሉም ኢሰመኮ በሪፖርቱ ላይ ጠቅሷል፡፡

በአማራ ክልል በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ከ120 በላይ ንጹሃን ዜጎች እንደተገደሉ የገለጸው ኢሰመኮ ግድያው በአብዛኛው በመንግስት የጸጥታ ሀይሎች የተፈጸመ ሲሆን የፋኖ ታጣቂዎች ደግሞ የመንግስት አመራሮችን ጨምሮ ንጹሃን ዜጎች ላይ ግድያ እንደፈጸሙ በሪፖርቱ ላይ ተጠቅሷል፡፡



~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
You tube፦ https://youtube.com/@-netib_media
Tiktok፦ tiktok.com/
Telegram፦ https://t.me/netib_media0
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~

የሰው ስጋን የከተፈው ተከሳሽ በሞት እንዲቀጣ ተወሰነበትፀሃዬ ቦጋለ በየነ የተባለ ተከሳሽ ከነሐሴ 27 ቀን 2014 ዓ.ም በግምት ከቀኑ 5፡00 እስከ ነሐሴ 28 ቀን 2014 ዓ.ም ከምሽቱ 1...
24/01/2025

የሰው ስጋን የከተፈው ተከሳሽ በሞት እንዲቀጣ ተወሰነበት

ፀሃዬ ቦጋለ በየነ የተባለ ተከሳሽ ከነሐሴ 27 ቀን 2014 ዓ.ም በግምት ከቀኑ 5፡00 እስከ ነሐሴ 28 ቀን 2014 ዓ.ም ከምሽቱ 12፡30 ድረስ ባለው ጊዜ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 04 አርሴማ ፀበል አከባቢ ባለቤቱ የነበረችውን ሟች ወንበር ላይ ተቀምጣ እያለ ሳታየው ከኋላዋ በመምጣት በሊጥ ማዳመጫ ዱላ ማጅራትዋን በመምታት እራሷን እንድትስት ካደረገ በኋላ እዛው ትቷት ከቤት ወጥቶ በመሄድና ከተወሰነ ሰዓታት በኋላ ተመልሶ በመምጣት ሟች እራሷን ስታ ከወደቀችበት መሬት ለመሬት በመጎተት እቤት ውስጥ ወደሚገኘው መታጠቢያ ቤት በማስገባት አንድ እግሯን ከዳሌዋ ጀምሮ በመቁረጥና ሙሉ የእግሯን ስጋ አጥንቷ ባዶ እስኪሆን ድረስ መልምሎ በማውጣት ስጋዋን አድቅቆ በመክተፍና በመቆራረጥ ሽንት ቤት ውስጥ በመጨመር የቆረጠውን እግሯ ለሁለት በመስበርና በፌስታል በመቋጠር ፀጉሯን በመቀስ በመቁረጥ ቀሪ አስከሬንዋ ላይ ጨርቅና የተለያየ መዘፍዘፊያ በመጫን እዛው መታጠቢያ ቤት ውስጥ በማስቀመጥ እስከ 30/12/2014 ዓ.ም ድረስ ምንም እንዳልተፈጠረ እቤት ውስጥ እያደረ ከቆየ በኋላ ከ1/13/2014 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 16/1/2015 ዓ.ም ድረስ ቤቱን ዘግቶ በመሰወሩ ምክንያት በአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ምርመራ ተጣርቶ በፍትህ ሚኒስቴር የጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ ዘርፍ በሴቶችና ህጻናት ላይ ሚፈፀሙ ወንጀሎች ዐቃቤ ሕግ ዳይሬክቶሬት በወ/ሕ/አ539/1/ሀ/ መሰረት በፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 2ኛ የሰው ግድያና ከባድ ውንብድና ወንጀል ችሎት ክስ ቀርቦበት ክርክር ሲደረግ ቆይቷል፡፡

በክርክሩ ሒደትም የዐቃቤ ሕግ ማስረጃ ከተሰማ በኋላ ተከሳሽ እንዲከላከል ብይን ቢሰጥም የመከላከያ ማስረጃ አቅርቦ የቀረበበትን ክስ ሊከላከል ባለመቻሉ ፍ/ቤቱ በተከሳሽ ላይ የጥፋተኛነት ፍርድ በመስጠት በዕድሜ ልክ ፅኑ እስራት እንዲቀጣ የወሰነ የነበረ ቢሆንም ዐቃቤ ሕግ ባቀረበው ይግባኝ መሰረት የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት የወሰነውን የእድሜ ልክ ጽኑ እስራት ውሳኔ በመሻር ተከሳሹ በሞት እንዲቀጣ ወስኖበታል፡፡

(የፍትህ ሚኒስቴር)

~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~
You tube፦ https://youtube.com/@-netib_media
Tiktok፦ tiktok.com/
Telegram፦ https://t.me/netib_media0
~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~

Address

Addis Ababa

Telephone

+251966700540

Website

https://t.me/netib_media0

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ሔኖክ ሚዲያ - Henok Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to ሔኖክ ሚዲያ - Henok Media:

Share