Ethiopian News Agency

Ethiopian News Agency ENA is the sole national wire service of Ethiopia.
(327)

The 82 years old ENA gathers and disseminates text news, audio and video stories about local and international events to media enterprises and the public. The Ethiopian News Agency (ENA) is the sole national wire service of Ethiopia.

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ከ1934 ዓ.ም ጀምሮ ላለፉት 82 ዓመታት በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ውስጥ የዜና አገልግሎት ተግባር በማከናወን ላይ የሚገኝ ብቸኛው ተቋም ነው፡፡

     #ኢትዮጵያ  #ኢዜአ
24/07/2025

#ኢትዮጵያ #ኢዜአ

#...

     #ኢትዮጵያ  #ኢዜአ
24/07/2025

#ኢትዮጵያ #ኢዜአ

#...

24/07/2025

7 ቀን ቀረው!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሰባት ዓመት በፊት 2011 ዓ.ም ላይ ያስተላለፉት መልዕክት።

#አረንጓዴዐሻራ

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የእንስሳት ሃብት ልማት ትኩረት ተደርጎበታል ዲላ፤ ሐምሌ 17/2017(ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የእንስሳት ጤናን በመጠበቅ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታቸውን ለማሳደግ በትኩ...
24/07/2025

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የእንስሳት ሃብት ልማት ትኩረት ተደርጎበታል

ዲላ፤ ሐምሌ 17/2017(ኢዜአ)፦በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የእንስሳት ጤናን በመጠበቅ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታቸውን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ግብርና ቢሮ ገለጸ።

በክልሉ በጌዴኦ ዞን ገደብ ወረዳ "የእንስሳትን ጤናና የማኅበረሰብ ጤናን መጠበቅ የሀገር ኢኮኖሚን መታደግ ነው" በሚል መሪ ሃሳብ ክልል አቀፍ የእንስሳት በሽታ መከላከያ ክትባት ዘመቻ ተጀምሯል።

የክረምት ወራት መግባትን ተከትሎ ሊከሰቱ የሚችሉ የእንስሳት በሽታዎችን ለመከላከልና ለመቆጣጠር ታልሞ በሚካሄደው የክትባት ዘመቻ ከ6 ሚሊዮን በላይ እንስሳትን ተደራሽ ለማድረግ መታቀዱን ገልጸዋል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የዲላ ክላስተር አስተባባሪና የግብርና ቢሮ ኃላፊ መሪሁን ፍቅሩ (ዶ/ር) በወቅቱ እንዳሉት በክልሉ ያለውን ሰፊ የእንስሳት ሀብት በአግባቡ ለማልማትና ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው።

ለዚህም የእንስሳት ጤናን መጠበቅና ዝርያቸውን ማሻሻል ቀዳሚው ተግባር መሆኑን ጠቅሰው፣ በዚህም የኢኮኖሚ ጠቀሜታቸውን ለማሳደግ በትኩረት እየተሰራ መሆኑንና የክትባት ዘመቻውም የዚሁ አካል መሆኑን ተናግረዋል።

በክልሉ ሁሉም አካባቢዎች ዛሬ ክትባቱ መሰጠት መጀመሩን አንስተው በመጀመሪያው ቀን ውሎውም ከ1 ሚሊዮን ለሚበልጡ እንስሳት ክትባት መሰጠቱን አስረድተዋል።

የእንሰሳትን ጤና መጠበቅ ምርታማነትን ከማሳደግ ባለፈ የሌማት ትሩፋትን ለማሳካት ወሳኝ በመሆኑ ህብረተሰቡ እንስሳቱን በማስከተብ ኃላፊነቱን እንዲወጣም አሳስበዋል።

በዞኑ የእንስሳት ሃብት ትልቅ የኢኮኖሚ ምንጭ ከመሆኑ በተጓዳኝ ለምግብ ዋስትና መሰረት ነው ያሉት ደግሞ የጌዴኦ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ዝናቡ ወልዴ (ዶ/ር) ናቸው።

በተለይ የሌማት ትሩፋት ለእንስሳት ሃብት ልማት የተሰጠው ልዩ ትኩረት በዞኑ የእንስሳት ተዋጽኦ ውጤቶች እንዲጨምር ምክንያት ሆኗል ብለዋል።

ለዚህም የእንስሳቱን ጤና በመጠቀም የአርሶ አደሩን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የክትባቱ ድርሻ የጎላ በመሆኑ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።

በወረዳው አርሶ አደሮች እንስሳትን ከልቅ ግጦሽ ይልቅ በጋጣ በማርባት ተጠቃሚነታቸው እያደገ ነው ያሉት ደግሞ የገደብ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ሳሙኤል ምትኩ ናቸው።

"ወረዳው በሰብል ራሱን በመቻል ተረጂነትን የሚጸየፍ አርሶ አደር ያለበት ነው" ያሉት አስተዳዳሪው ይህንን በእንስሳት ሃብት ልማት ለመድገም የወተት መንደር በመመስረት በትኩረት እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል።

በገደብ ወረዳ የሃርሙፎ ቀበሌ ነዋሪ አርሶ አደር ናትናኤል ዶሪ ከእርሻ ስራ ጎን ለጎን የወተት ላሞችና በጎች እርባታ የኑሮ መሰረታቸው መሆኑን አንስተዋል።

ክትባቱ እስከ ጳጉሜን 1 ቀን 2017 ዓ.ም የሚሰጥ ሲሆን በመጀመሪያው ዙር ብቻ ከ6 ሚሊዮን በላይ እንስሳትን ተደራሽ እንደሚያደርግ ተገልጿል።



#ኢዜአ

የምክር ቤቱ መደበኛ ጉባኤ የተለያዩ አዋጆችና የዳኞችን ሹመት በማጽደቅ ተጠናቀቀ ወልቂጤ፤ሐምሌ 17/2017 (ኢዜአ)፦የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት 4ኛ መደበኛ ጉባኤ የተለያዩ አዋጆች...
24/07/2025

የምክር ቤቱ መደበኛ ጉባኤ የተለያዩ አዋጆችና የዳኞችን ሹመት በማጽደቅ ተጠናቀቀ

ወልቂጤ፤ሐምሌ 17/2017 (ኢዜአ)፦የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት 4ኛ መደበኛ ጉባኤ የተለያዩ አዋጆች እና የዳኞችን ሹመት በማጽደቅ ተጠናቀቀ።

ምክር ቤቱ ካፀደቃቸው አዋጆች መካከል የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት የቀበሌ ማህበራዊ ፍርድ ቤቶች ስልጣን እና ተግባርን ለመደንገግ የወጣ አዋጅ ይገኝበታል።

የአዋጁን ረቂቅ ያቀረቡት በምክር ቤቱ የህግና አስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ወይዘሮ መሰረት ወልደሰን፥ ማህበራዊ ፍርድ ቤቶቹ በእለት ተዕለት እንቅስቃሴ ለሚነሱ አለመግባባቶች አፋጣኝ እልባት ለመስጠት ያስችላሉ ብለዋል።

እንዲሁም ፍትህ ለማግኘት በሚደረግ ሂደት ይባክን የነበረን የ‎ጊዜ፣ ጉልበትና ገንዘብ ለመቆጠብ እንደሚያስችሉም አንስተዋል።

በፍትሀብሔር እና ቀላል የወንጀል ጉዳዮች ሙግት ውስጥ የገቡ ወገኖችን በማግባባት ብሎም ጉዳያቸውን በእርቅ በመጨረስ ለዘላቂ ሰላም ግንባታ የላቀ ሚና እንዳለው ተናግረዋል።

ሌላው በምክር ቤቱ የጸደቀው የክልሉ ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት የሠራተኞች መተዳደሪያ ደንብ ሲሆን የክልሉ ምክር ቤት የፋይናንስና በጀት ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ ታመነ ገብሬ፤ ደንቡ የኦዲት ግኝትን ለማጠናከርና ገቢን በአግባቡ ለመሰብሰብ እንደሚያስችል ለምክር ቤቱ አባላት አብራርተዋል።

በክልሉ በተለያዩ ደረጃዎች የሚያገለግሉ የ37 ዕጩ ዳኞች ሹመትም በክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ኤርሲኖ አቡሬ በኩል የቀረበ ሲሆን ዳኞቹ ያላቸው የትምህርት ዝግጅት፣ የሥራ ልምድ፣ ስነምግባርና ሌሎች ጉዳዮች ከግምት ውስጥ ገብተው ለሹመት መታጨታቸው ተገልጿል።

ምክር ቤቱም በቀረቡ ረቂቅ አዋጆችና በዳኞች ሹመት ላይ የተለያዩ ሀሳብና አስተያየቶችን ከሰጠ በኋላ ተቀብሎ አጽድቋል።

በዚህም ለከፍተኛ ፍርድ ቤት 11 እንዲሁም ለወረዳና ለከተማ አስተዳደር የመጀመሪያ ፍርድ ቤቶች 26 ዳኞች ሹመት ጸድቋል።

ተሿሚ ዳኞችም በምክር ቤቱ ቀርበው ቃለመሀላ ፈጽመዋል፡፡

የክልሉ ምክር ቤት ላለፉት ሁለት ቀናት ሲያካሂድ የቆየውን 6ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 4ኛ መደበኛ ጉባኤ አዋጆችና ሹመቶችን ካጸደቀ በኋላ ማምሻውን ተጠናቋል።

#ኢዜአ

ምርታማነታችንን ይበልጥ ለማሳደግ  በግብርና ባለሙያዎች ታግዘን በትጋት እየሰራን ነውደሴ፤ሐምሌ 17/2017(ኢዜአ)፦የሰብል ምርታማነታቸውን ይበልጥ ለማሳደግ በግብርና ባለሙያዎች ታግዘውና  ግ...
24/07/2025

ምርታማነታችንን ይበልጥ ለማሳደግ በግብርና ባለሙያዎች ታግዘን በትጋት እየሰራን ነው

ደሴ፤ሐምሌ 17/2017(ኢዜአ)፦የሰብል ምርታማነታቸውን ይበልጥ ለማሳደግ በግብርና ባለሙያዎች ታግዘውና ግብአት ተጠቅመው በትጋት እየሰሩ መሆኑን በደቡብ ወሎ ዞን ጃማ ወረዳ አስተያየታቸውን የሰጡ አርሶ አደሮች ገለጹ።

የደቡብ ወሎ ዞን አመራሮች በጃማ ወረዳ የስንዴ ዘር ልማትን በይፋ አስጀምረዋል።

በማስጀመሪያ ሥነ-ሥርዓት ላይ ከተሳተፉት የወረዳው አርሶ አደሮች መካከል ሸህ ሰይድ እንድሪስ እንዳሉት፤ በግብርና ባለሙያዎች ድጋፍ ታግዘው በተሻሻለ አሰራር ምርታማነታቸውን ለማሳደግ ጠንክረው እየሰሩ ነው።

የሚያስፈልጋቸውን ግብዓት ቀድመው በማግኘታቸው ዛሬ በዘመቻ አንድ ሄክታር መሬታቸውን በዘር መሸፈናቸውን ገልጸዋል።

ሰብሉን ከአረም በማጽዳትና ከተባይ በመከላከል የተሻለ ምርት እንደሚጠብቁ ተናግረዋል።

ሌላው አርሶ አደር እሸቱ ነጋ በበኩላቸው፥የመኸሩ ዝናብ ለሰብል ልማት ምቹ በመሆኑ የተሻለ ምርት ለማግኘት በዘርፉ ባለሙያዎች ታግዘው ተግተው እየሰሩ እንደሚገኙ ገልጸዋል።

ተገቢውን ግብዓት ተጠቅመው አንድ ሄክታር ተኩል መሬታቸውን የስንዴ ዘር ልማት ዛሬ መጀመራቸውን አንስተዋል።

የተጀመረው የዘር ስራ ከ40 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በማልማት ከአንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ የሚያስችል ነው ያሉት ደግሞ የጃማ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ለወጠኝ ጠጋው ናቸው።

አርሶ አደሩ በተሻሻለ አሰራር ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ዋስትናቸውን ለማረጋገጥ ተገቢው ድጋፍ እየተደረገ ነው ሲሉ ተናግረዋል።

የደቡብ ወሎ ዞን አስተዳደር የህዝብ ተሳትፎና አደረጃጀት ዘርፍ አማካሪ ወይዘሮ ሀና አለባቸው በበኩላቸው፥በዞኑ ምርታማነትን በማሳደግ አርሶ አደሩ ለገበያ የሚተርፍ ምርት ለማምረት እየተሰራ ነው ብለዋል።

የታቀደውን የምርት እድገት ለማሳካት የምርት ማሳደጊያ ግብዓት በማቅረብ የባለሙያ ድጋፍ እየተደረገ መሆኑን አስረድተዋል።

በ2017/2018 የምርት ዘመን በዞኑ በአጠቃላይ 432 ሺህ ሄክታር መሬት በማልማት 15 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለማምረት ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን የደቡብ ወሎ ዞን ግብርና መምሪያ ኃላፊ አቶ አህመድ ጋሎ ገልጸዋል።

በዞኑ በስንዴ ልማት 222 ሺህ ሄክታር መሬት ለመሸፈን ታቅዶ ዛሬ በተጀመረው ዘርም ከአንድ ሺህ 700 ሄክታር የሚበልጥ መሬት መሸፈኑን ጠቅሰዋል።

ወደ ዞኑ ከገባው 530 ሺህ ኩንታል ውስጥ የአፈር ማዳበሪያ 475 ሺህ ኩንታል የሚሆነውን ማሰራጨት መቻሉን ጠቁመው፥ ይህም የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።

በማስጀመሪያ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የዞንና የወረዳ አመራሮች እንዲሁም የአካባቢው አርሶ አደሮች ተገኝተዋል።

#ኢዜአ

በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ቅንጅታዊ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉወላይታ ሶዶ፤ ሐምሌ 17/2017 (ኢዜአ)፡-በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ...
24/07/2025

በክልሉ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ቅንጅታዊ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ወላይታ ሶዶ፤ ሐምሌ 17/2017 (ኢዜአ)፡-በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ የተጀመሩ ቅንጅታዊ ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።

የክልሉ መምህራን ማህበር 1ኛ ጠቅላላ ጉባኤ በወላይታ ሶዶ ከተማ ተካሂዷል።

በመድረኩ ላይ የተገኙት የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ፀሐይ ወራሳ እንዳሉት በትምህርት ዘርፍ ብቃት ያለው የሰው ሀይል ለማፍራት የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ወሳኝ ነው።

በክልሉ በየደረጃው ለትምህርት ጥራት ማረጋገጥ የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ወሳኝ መሆኑን ገልጸው፣ ለእዚህም ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጀት የተጀመሩ ሥራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።

ቢሮው የትምህርት ጥራት መጓደል ችግርን ለመፍታት ከመምህራን ማህበር ጋር እያከናወናቸው ያሉ ተግባራት በቀጣይም ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ወይዘሮ ፀሐይ አመልክተዋል።

መምህራን ከጥቅማጥቅም ጋር በተያያዘ ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች ተገቢ ምላሽ ለመስጠትም ከክልሉ መንግስት ጋር በመተባበር እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው፣ የመምህራንን አቅም ለማጎልበት የአጭርና የረዥም ጊዜ ስልጠና እየተሰጠ መሆኑን ተናግረዋል።

እንደ ሀገር የተጀመሩ የትምህርት ሪፎርም ሥራዎችን በውጤታማነት ለማጠናከር የመምህራን ማህበራት ድርሻ ከፍተኛ በመሆኑ ቅንጅታዊ ሥራው ይጠናከራል ብለዋል።

መምህራንና የትምህርት ባለሙያዎች የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ሚናቸው የጎላ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የወላይታ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ረዳት ፕሮፌሰር ሳሙኤል ተሰማ ናቸው።

የመምህራን ማህበር የመምህራን ድምጽ ሆኖ በዘርፉ የሚስተዋሉ ችግሮች እንዲፈቱና ለውጥ እንዲመጣ እያከናወነ ያለው ተግባር የሚበረታታና መጠናከር ያለበት መሆኑን ተናግረዋል።

"የትምህርት ጥራት ስብራትን በመጠገን ትውልዱን በሚገባ አንጾ ለማውጣት በቁርጠኝነት መስራት ይገባል" ያሉት ፕሮፌሰር ሳሙኤል፣ የትምህርት ዘርፍ የሪፎርም ሥራን ለማሳካት የሚደረገው ትጋት ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

የክልሉ መምህራን ማህበር ሰብሳቢ አቶ አማኑኤል ጳውሎስ በበኩላቸው፥ መምህራን የነገ ሀገር ተረካቢ ትውልድ የማፍራት ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ማህበሩ የበኩሉን እየተወጣ ይገኛል ብለዋል።

በትምህርት ዘርፍ ለሚስተዋሉ ችግሮች መፍትሄ ለመስጠትም ማህበሩ ዕቅድ ይዞ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

ማህበሩ ከተቋቋመ አጭር ጊዜ ቢሆንም የመምህራንን ችግር ለመፍታት ከክልሉ መንግስት እና ከትምህርት ቢሮው ጋር በቅንጅት የጀመራቸው ሥራዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።

የክልሉ መንግስት የመምህራን ጥያቄ እንዲፈታ በቅንጅት ለመስራት እያደረገ ያለው እንቅስቃሴ ይበረታታል ያሉት አቶ አማኑኤል፣ ማህበሩም የበኩሉን ለመወጣት የሚያደርገውን ጥረት ያጠናክራል ብለዋል።

መምህራንም የትምህርት ጥራት ችግርን ለመፍታት የገቡትን ቃል አክብረው መስራት እንዳለባቸው አስገንዝብዋል።

በመድረኩ የክልሉ ትምህርት ቢሮና የመምህራን ማህበራት አመራሮች እንዲሁም የመምህራንና ጤና ሳይንስ ኮሌጆች ዲኖችና ሌሎች ባለድርሻዎች ተገኝተዋል።

#ኢዜአ

በክልሉ የቤተሰብ ብልፅግናን ለማረጋገጥ የሚያግዙ ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋልሀዋሳ፤ሐምሌ 17/2017 (ኢዜአ) :-በሲዳማ ክልል ጠንካራ አደረጃጀት በመፍጠር የቤተሰብ ብልፅግናን ለማረጋገጥ ...
24/07/2025

በክልሉ የቤተሰብ ብልፅግናን ለማረጋገጥ የሚያግዙ ውጤታማ ተግባራት ተከናውነዋል

ሀዋሳ፤ሐምሌ 17/2017 (ኢዜአ) :-በሲዳማ ክልል ጠንካራ አደረጃጀት በመፍጠር የቤተሰብ ብልፅግናን ለማረጋገጥ የሚያግዙ ውጤታማ ተግባራት መከናወናቸው ተገለጸ።

በብልጽግና ፓርቲ የሲዳማ ክልል ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የ2017 በጀት ዓመት አፈጻጸምና ቀጣይ ዕቅድ ዙሪያ ከአባላቱ ጋር በሀዋሳ የውይይት መድረክ አካሂዷል።

በመድረኩ ላይ የቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቱ ሀላፊ አቶ አብርሀም ማርሻሎ እንዳሉት፤ፓርቲው በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት እስከታችኛው መዋቅር ጠንካራ አደረጃጀትን በመፍጠር ውጤታማ ተግባራትን ማከናወን ችሏል።

ይህም መላው አባልና አመራሩ የተያዙ ዕቅዶችን ለማሳካት በላቀ ብቃት ሲሰሩ መቆየታቸውን ተናግረዋል።

እንደ ሀገር የተያዙትን ኢንሼቲቮች ለማሳካት ከክልሉ ነባራዊ ሁኔታ ጋር በማቀናጀት የቤተሰብ ብልጽግናን ለማረጋገጥ የሚያግዙ የተሻሉ ተግባራት መከናወናቸወን ገልጸዋል።

የተግባርና አስተሳብ አንድነት ያለው፣ ራሱን አሳልፎ የሰጠና መልካም ስነምግባር ያለው አባል በጥራትና በብቃት በማፍራት የተገኘው ውጤት አመርቂ መሆኑን አብራርተዋል።

በቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቱ የአደረጃጀት ዘርፍ ሀላፊ አቶ አሸናፊ ኤልያስ በበኩላቸው፤ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት የብልጽግና ፓርቲን ተልዕኮ በብቃት የሚፈጽም ጥራት ያለው አባል ለማፍራት በትኩረት መሰራቱን ተናግረዋል።

በዚህም በየደረጃው የተለያዩ ግምገማዎችን በማድረግ ግንባር ቀደም ሆኖ የሚፈጽም የሚያስፈጽምና የሚመራ ከ47 ሺህ በላይ ጠንካራ የብልጽግና ሀይል ማፍራትእንደተቻለ ጠቁመዋል።

በመድረኩ ከክልል እስከ ቀበሌ ባለው መዋቅር የሚገኙ ከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች ተሳትፈዋል።

#ኢዜአ

ኢትዮ ቴሌኮም በዕድገት ስትራቴጂው ለዲጅታል ኢኮኖሚ ግንባታ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል-ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይዎት ታምሩአዲስ አበባ፤ሐምሌ 17/ 2017 (ኢዜአ)፦ኢትዮ ቴሌኮም  ለሦስት...
24/07/2025

ኢትዮ ቴሌኮም በዕድገት ስትራቴጂው ለዲጅታል ኢኮኖሚ ግንባታ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል-ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይዎት ታምሩ

አዲስ አበባ፤ሐምሌ 17/ 2017 (ኢዜአ)፦ኢትዮ ቴሌኮም ለሦስት ዓመታት የተገበረው መሪ የዕድገት ስትራቴጂ ለዲጅታል ኢኮኖሚ ግንባታ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱን የኩባንያው ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይዎት ታምሩ ገለጹ።

ዋና ስራ አስፈጻሚዋ፥ የኩባንያውን የ2017 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም እና የዕድገት ስትራቴጂውን ማጠቃለያ ሪፖርት ለመገናኛ ብዙሃን ይፋ አድርገዋል።

ኢትዮ ቴሌኮም ከሦስት ዓመታት በፊት ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነቱን የሚያሳደግ፣ ገቢውን ከፍ የሚያደርግ እና የደንበኞችን አገልግሎት አሰጣጥ የሚያሻሽል ስትራቴጂ ነድፎ ወደ ስራ መግባቱን አስታውሰዋል።

በዚህም ከቴሌኮም ግንኙነት ባሻገር የፋይናንስ ስርዓቱ ዘመናዊ እና አካታች እንዲሆን በማድረግ ረገድ ውጤታማ ስራ ማከናወኑን ተናግረዋል፡፡

በ2017 በጀት ዓመት ብቻ ከድምጽ ጥሪ፣ ከኢንተርኔት አገልግሎት፣ ከቫስ፣ ከመሠረተ ልማት ማጋራት፣ ከቴሌኮም ቁሳቁስ ሽያጭና ከሌሎች ምንጮች 162 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን አስታውቀዋል።

እንደ ቴሌ ብር፣ ቴሌ ገበያ እና የመሳሰሉት የዲጅታል የግብይት መተግበሪያዎችን በማስፋፋት የፋይናንስ ስርዓቱ ዘመናዊ እንዲሆንና የመንግስት ተቋማት አገልግሎት እንዲዘምን ማድረጉንም ጠቅሰዋል።

መሪ የሦስት ዓመት የእድገት ስትራቴጂው ለዲጅታል ኢኮኖሚ ግንባታ ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከቱንም ነው ያነሱት፡፡

ዋና ስራ አስፈጻሚዋ በ2017 በጀት ዓመት የቴሌኮም አገልግሎት ማስፋፊያዎች መከናወናቸውን ጠቅሰው፥ 16 ከተሞችን በ5 ጂ እና 512 ከተሞችን በ4ጂ ኔት ወርክ ተደራሽ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል፡፡

በርካታ የሞባይል ጣቢያዎች መገንባታቸውን በማንሳት፥ በአሁኑ ወቅት በሀገር አቀፍ ደረጃ ከ10 ሺህ በላይ የሞባይል ጣቢያዎች አገልግሎት እየሰጡ እንደሚገኙ አመላክተዋል።

በዚህም በመላ ሀገሪቱ በርካታ የህብረተሰብ ክፍሎችን የፈጣን ኢንተርኔት አገልግሎት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ምቹ ምህዳር መፈጠሩን ነው የተናገሩት።

ኩባንያው የቴሌኮም መሰረተ ልማት ማስፋፊያና የማሻሻያ ስራዎችን በማከናወን የአገልግሎት ተጠቃሚዎቹን ቁጥር 83 ነጥብ 2 ሚሊዮን ማድረሱን ገልጸዋል።

የቴሌ ብር፣የዘመን ገበያ እና መሰል አገልግሎት ተጠቃሚዎች ቁጥር በከፍተኛ መጠን እያደገ መሆኑንም ጠቁመዋል።

#ኢዜአ

ሰራዊቱ መደበኛ ተልዕኮን በላቀ ብቃት እየፈፀመ በአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ የነቃ ተሳትፎውን አጠናክሮ ቀጥሏልባሕርዳር፤ሐምሌ 17/2017(ኢዜአ)፡-መከላከያ ሰራዊት  መበደኛ ተልዕኮውን በላ...
24/07/2025

ሰራዊቱ መደበኛ ተልዕኮን በላቀ ብቃት እየፈፀመ በአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ የነቃ ተሳትፎውን አጠናክሮ ቀጥሏል

ባሕርዳር፤ሐምሌ 17/2017(ኢዜአ)፡-መከላከያ ሰራዊት መበደኛ ተልዕኮውን በላቀ ብቃት ከመፈፀሙ በተጓዳኝ በአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላና ልማት ላይም የነቃ ተሳትፎውን አጠናክሮ መቀጠሉን የምስራቅ ዕዝ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል መሃመድ ተሰማ ገለጹ።

"ችግኞችን እንተክላለን፤ ህግ እናስከብራለን፣ የሃገራችን ሰላም እኛ ተሰውተን እናረጋግጣለን" በሚል መሪ ሃሳብ የምስራቅ ዕዝ ሰራዊት አመራሮችና አባላት በባሕር ዳር ከተማ ችግኝ በመትከል ዐሻራቸውን አኑረዋል።

በዚህ ወቅት የዕዙ ዋና አዛዥ ሌተናል ጄኔራል መሃመድ ተሰማ እንደተናገሩት፥ መንግስት ለተከታታይ ሰባት ዓመታት በርካታ ችግኝ በመትከል ኢትዮጵያን የአረንጓዴ ዐሻራ እውን እንዲሆን በተግባር እያሳየ ነው።

ሰራዊቱ መደበኛ ተልዕኮን በላቀ ብቃት እየፈጸመ የአረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላና ልማት ላይ የነቃ ተሳትፎውን አጠናክሮ መቀጠሉን ገልጸዋል።

በዚህ ዓመትም እንደ ሃገር በመከላከያ ሰራዊት 18 ሚሊዮን ችግኝ ለመትከል አቅዶ እየተተገበረ እንደሚገኝም አንስተዋል።

ከዚህ ውስጥም የምስራቅ ዕዝ አንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ችግኝ በዕዙ የግዳጅ ቀጠናዎች ለመትከል አቅዶ እየተሰራ መሆኑን ጠቅሰው፤ ዛሬ በባሕርዳር ያከናወኑትም የዚሁ አካል እንደሆነ ተናግረዋል።

ይህም "ችግኞችን እንተክላለን፤ ህግ እናስከብራለን፤ የሃገራችን ሰላም እኛ ተሰውተን እናረጋግጣለን" በሚል መሪ ሃሳብ መሆኑን አብራርተዋል።

ሰራዊቱ በመንግስት የተጀመሩ የልማት ስራዎች ያለምንም የፀጥታ ችግር እንዲከናወኑ ከምን ጊዜውም በላይ በፅናት እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

የሕዝብንና የሃገርን ሰላም ከማስጠበቅ ባሻገርም ሰራዊቱ በጋራ ችግኞችን እንተክላለን ብሎም ለፅድቀት እንዲበቁ እንንከባከባለን ሲሉም አረጋግጠዋል።

በአማራ ክልል ለክረምቱ ወቅት በርካታ ችግኝ ተዘጋጅቶ የመትከል ስራ እየተከናወነ መሆኑን የገለጹት በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የገጠር ዘርፍ አስተባባሪና የክልሉ ግብርና ቢሮ ሃላፊ ድረስ ሳህሉ (ዶ/ር) ናቸው።

ለዚህም ከሐምሌ 1/2017ዓ.ም ጀምሮ መላ የክልሉን ሕዝብ በማሳተፍ በጥሩ ተነሳሽነት የተከላ ስራው ተጠናክሮ መቀጠሉን ተናግረዋል።

መከላከያ ሰራዊቱ ባለበት ቦታ ሁሉ ከሕዝባችን ጎን ሆኖ ሰላማችን ከማስጠበቅ ባሻገር የልማቱ ፈር ቀዳጅ በመሆን አሻራውን እያሳረፈ ነው ብለዋል።

በዛሬው ዕለትም የምስራቅ ዕዝ አመራሮችና አባላት በባሕር ዳር ከተማ ችግኝ በመትከል አረንጓዴ ዐሻራቸውን ማኖራቸውን አንስተዋል።

የባሕርዳር ከተማ አስተዳደር ተቀዳሚ ምክትል ከንቲባ አቶ ጎሹ እንዳላማው በበኩላቸው፤መከላከያ ሰራዊት በሰላም ማስከበርም ሆነ በልማቱ ከጎናችን ተለይቶ አያውቅም ብለዋል።

በተለይም ምስራቅ ዕዝ የሰላምም ሆነ የልማቱ ዋልታና ማገር ሆኖ እያገለገለ እንደሚገኝና ለዚህም ምስጋና አቅረበዋል።

በቀጣይም ከሰራዊቱ ጎን በመሆን በሰላም ማስከበሩም ሆነ በልማትም በጋራ መስራታቸውን እንደሚያጠናክሩ አረጋግጠዋል።

በችግኝ ተከላ መረሃ ግብር የዕዙ አመራሮችና አባላት እንዲሁም የከተማ አስተዳደሩ አመራሮች ተሳታፊ ሆነዋል።

#ኢዜአ

   #ኢዜአ  #አረንጓዴዐሻራ
24/07/2025

#ኢዜአ #አረንጓዴዐሻራ

ሰላማዊ የፖለቲካ ትግልን በማጠናከር ለችግሮች ዘላቂ መፍትሔ ማምጣት ያስፈልጋል-የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት  አዲስ አበባ፤ሐምሌ 17/ 2017 (ኢዜአ)፦ሰላማዊ የፖለቲካ ትግ...
24/07/2025

ሰላማዊ የፖለቲካ ትግልን በማጠናከር ለችግሮች ዘላቂ መፍትሔ ማምጣት ያስፈልጋል-የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት

አዲስ አበባ፤ሐምሌ 17/ 2017 (ኢዜአ)፦ሰላማዊ የፖለቲካ ትግልን በማጠናከርና ዴሞክራሲያዊ ባህልን በማዳበር ለችግሮች ዘላቂ መፍትሔ ለማምጣት የፖለቲካ ልሂቃን ሚናቸውን እንዲወጡ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ጥሪ አቀረበ።

የምክር ቤቱ ሰብሳቢ ሰለሞን አየለ ለኢዜአ እንዳሉት፤ ኢትዮጵያ በረጅም ዘመን ታሪኳ ያስተናገደቻቸው በርካታ የእርስ በእርስ ግጭቶች የዜጎቿን ህይወት ነጥቅዋል፤ በርካታ ንብረትን አውድመዋል።

ከዚህም ባለፈ ለፖለቲካዊ አለመረጋጋት በማጋለጥ የልማት ግቦቿን እንዳታሳካ እንቅፋት ሆነው መቆየታቸውን ነው ያነሱት።

በአገሪቷ ሰፊ ሀብት እና በርካታ የአብሮነት እሴቶች እንዳሉ ጠቁመው፤ ሆኖም ፖለቲካዊ ግብን በኃይል ለማሳካት የሚደረጉ ሙከራዎች ወደኋላ አስቀርተውናል ነው ያሉት።

አለመግባባት የሚፈጥር የጥሎ ማለፍ ፖለቲካ እንዲሁም የእኔ አውቅልሃለሁ አስተሳሰብ ግጭትን ከመውለድ ያለፈ ሚና እንደሌለውም አስረድተዋል።

የመጣንበት መንገድ አያዋጣም ያሉት ሰብሳቢው፤ ከዚህ በኋላ ኢትዮጵያ ውስጥ ፍላጎትን በኃይል ለማስፈጸም የሚደረግ ጥረት የሚያሳካው ግብ እንደሌለም ተናግረዋል።

በመሆኑም ካለፉት ግጭቶች በመማር ለችግሮች ዘላቂ መፍትሔ ማምጣት አስፈላጊ መሆኑን ጠቁመው፤ ሀገርን በጋራ ለመገንባት ሰላማዊ የፖለቲካ ትግልን እና የውይይት ባህልን ማዳበር እንደሚያስፈልግ አንስተዋል።

የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች፣ አባላትና ደጋፊዎቻቸው በሰላም ጉዳይ ላይ እንደሀገር አብሮ መስራት፣ በሀሳብ ልዕልና የሚገዛ የፖለቲካ አውድን መፍጠርና ዴሞክራሲያዊ ባህልን ማዳበር እንዳለባቸው ገልፀዋል።

ፍላጎታቸውን በኃይል ለማሟላት ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ አካላት የያዙት መንገድ እነርሱን ብቻ ሳይሆን ሀገርና ህዝብን የሚጎዳ መሆኑን በመገንዘብ የሀሳብ ልዩነቶቻቸውን በውይይት እንዲፈቱ ጥሪ አቅርበዋል።

ግጭት ሰላማዊ የሆነውን ማህበራዊ፣ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ምህዳር እንደሚያናጋ ገልጸው፤ለዚህ ደግሞ ከእኛ ከኢትዮጵያውያን በላይ ምስክር የለም ነው ያሉት።

በሀሳብ መወያየትና ችግሮችን መፍታት ለሀገር ግንባታ ትልቅ ሚና ያለው መሆኑን ያነሱት ሰብሳቢው፤ ነፍጥ አውርዶ ወደ ጠረጴዛ ውይይት መምጣት ለነገ የማይባል ጉዳይ መሆኑን ጠቅሰዋል።

የፖለቲካ ልሂቃንም የታጠቁ ኃይሎች ወደ ሰላማዊ ውይይት እንዲመጡ ግፊት ማድረግ እንዳለባቸው ጠቅሰው፤ ለሁሉም ነገር መሰረት ለሆነው ሰላም የትኛውንም ዋጋ መክፈል የግድ ነው ብለዋል።

#ኢዜአ

Address

Addis Abeba

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian News Agency posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethiopian News Agency:

Share

Category

Ethiopian News Agency

Ethiopian News Agency is the sole national wire service of Ethiopia which gathers information through its 36 branch offices across the country and disseminates news and related stories as well other productions to public and commercial media across Ethiopia.

Ethiopian News Agency was established in 1942, which makes it the oldest national news agency in Africa.