Ethiopian News Agency

Ethiopian News Agency ENA is the sole national wire service of Ethiopia.
(348)

The 82 years old ENA gathers and disseminates text news, audio and video stories about local and international events to media enterprises and the public. The Ethiopian News Agency (ENA) is the sole national wire service of Ethiopia.

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ከ1934 ዓ.ም ጀምሮ ላለፉት 82 ዓመታት በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ውስጥ የዜና አገልግሎት ተግባር በማከናወን ላይ የሚገኝ ብቸኛው ተቋም ነው፡፡

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለምረቃ መብቃቱን በማስመልከት በህብረት ችለናል በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ(በፎቶ) #ኢዜአ
14/09/2025

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለምረቃ መብቃቱን በማስመልከት በህብረት ችለናል በሚል መሪ ሀሳብ በአዲስ አበባ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ(በፎቶ)

#ኢዜአ


ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለምረቃ መብቃቱን በማስመልከት በአዲስ አበባ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ(በፎቶ) #ኢዜአ
14/09/2025

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለምረቃ መብቃቱን በማስመልከት በአዲስ አበባ ከተማ እየተካሄደ የሚገኘው ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ(በፎቶ)

#ኢዜአ


በአዲስ አበባ ከተማ ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ነውአዲስ አበባ፤ መስከረም 4/2018 (ኢዜአ)፦ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለምረቃ መብቃቱን ተከትሎ በአዲስ አበባ ከተማ ህዝባዊ የድ...
14/09/2025

በአዲስ አበባ ከተማ ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፤ መስከረም 4/2018 (ኢዜአ)፦ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለምረቃ መብቃቱን ተከትሎ በአዲስ አበባ ከተማ ህዝባዊ የድጋፍ ሰልፍ እየተካሄደ ነው፡፡

በህዝባዊ የድጋፍ ሰልፉ "በሕብረት ችለናል" የሚልና ሌሎች መልዕክቶች እየተላለፉ ይገኛሉ፡፡

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ባሳለፍነው ማክሰኞ ጳጉሜን 4/2017 በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) መመረቁ ይታወሳል፡፡

#ኢዜአ

ኢትዮጵያ በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮናው በአትሌት ትዕግስት አሰፋ የብር ሜዳሊያ አገኘችአዲስ አበባ፤ መስከረም 3/2018 (ኢዜአ)፦ በ20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ በሴቶች ማራ...
14/09/2025

ኢትዮጵያ በዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮናው በአትሌት ትዕግስት አሰፋ የብር ሜዳሊያ አገኘች

አዲስ አበባ፤ መስከረም 3/2018 (ኢዜአ)፦ በ20ኛው የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኢትዮጵያ በሴቶች ማራቶን በአትሌት ትዕግስት አሰፋ የብር ሜዳሊያ አግኝታለች።

ትዕግስት ውድድሩን ለማጠናቀቅ 2 ሰዓት ከ24 ደቂቃ ከ45 ሴኮንድ ፈጅቶባታል።

ኬንያዊቷ አትሌት ፔሬዝ ቺፕቺርቺር 2 ሰዓት ከ24 ደቂቃ ከ43 ሴኮንድ አንደኛ ወጥታለች:: አትሌቷ በመጨረሻዎቹ 200 ሜትሮች ፍጥነቷን በመጨመር አሸንፋለች።

የኡራጓይ አትሌት ጁሊያ ፓተርኒያን 2 ሰዓት ከ27 ደቂቃ ከ23 ሴኮንድ ሶስተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቃለች።

አትሌት ጉዳፍ ለኢትዮጵያ የመጀመሪያውን ሜዳሊያ በ10000 ሜትር ሴቶች ፍጻሜ ሶስተኛ በመውጣት ማስገኘቷ ይታወቃል።

#ኢዜአ

ህብረተሰቡ የቴሊግራምና የዋትሳፕ አካውንቶች ላይ ካነጣጠሩ አጭበርባሪዎች መጠንቀቅ አለበት አዲስ አበባ፤ መስከረም 3/2018(ኢዜአ)፦ ህብረተሰቡ የቴሊግራምና የዋትሳፕ አካውንት ተጠቃሚዎች ላ...
13/09/2025

ህብረተሰቡ የቴሊግራምና የዋትሳፕ አካውንቶች ላይ ካነጣጠሩ አጭበርባሪዎች መጠንቀቅ አለበት

አዲስ አበባ፤ መስከረም 3/2018(ኢዜአ)፦ ህብረተሰቡ የቴሊግራምና የዋትሳፕ አካውንት ተጠቃሚዎች ላይ ካነጣጠሩ አጭበርባሪዎች ሊጠነቀቅ እንደሚገባ የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር አሳሰበ።

የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ባስተላለፈው የጥንቃቄ መልዕክት እንደገለጸው ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሀገራችን የቴሌግራምና ዋትሳፕ ተጠቃሚዎች ላይ ያነጣጠረ የማጭበርበርና የአካውንት ነጠቃ እንቅስቃሴዎች እየጨመሩ መጥተዋል።

ከሰሞኑም ከዚህ ቀደም ከነበረው በተለየ ሁኔታ የግለሰቦች የቴሊግራምና ዋትሳፕ አካውንቶች በመረጃ መንታፊዎች በከፍተኛ ደረጃ እየተነጠቁና ማጭበርበሮች እየተፈጸሙ ስለመሆኑ በኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር የሳይበር አደጋ ዝግጁነትና ምላሽ መስጫ ማዕከል/Ethio-CERRT/ ማረጋገጥ ችሏል።

እነዚህ የአካውንት ነጠቃዎች የሚፈጸሙት ለጥቃት ኢላማ ላደረጉት አካል አጥፊ ተልዕኮ ያላቸውን ሊንኮች በመላክና ሊንኩን እንዲከፍቱ የሚያደርጉ ቴክኒኮችን በመጠቀም መሆኑንም አስታውቋል።

ከነዚህ ቴክኒኮች መካከል በጣም ወሳኝ በሆነ ጉዳይ አስቸኳይ በዙም ወይም በሌሎች የኦንላይን ፕላትፎርሞች ስብሰባ ስለሚኖር በተላከው ሊንክ አማካኝነት እንዲሳተፉ በመደወልና በማግባባት ሲሆን ሊንኩን ከፍተው በሚገቡበት ወቅት አካውንታቸውን ይነጥቃሉ ብሏል።

ከዚህ የአካውንት ነጠቃ በኋላ የተነጠቀውን የቴሊግራም ወይም ዋትሳፕ አካውንት በመጠቀም ወደ ግለሰቡ ወዳጆች ለወሳኝ ጉዳይ ገንዘብ እንደሚያስፈልጋቸዉና እንዲያስገቡላቸዉ በጽሁፍ መልዕክት በመጠየቅ እያጭበረበሩ እንደሚገኙም የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት አስተዳደር ገልጿል።

በመሆኑም የቴሌግራምና ዋትሳፕ ተጠቃሚዎች ከማታውቁት አካል አጓጊ የሆኑና አስቸኳይነት ያላቸው ሊንኮች ሲላክልዎት እንዲሁም ሊንኩን እንዲከፍቱ ጥሪ ሲደርስዎት አካውንትዎን ለመጥለፍ ሊሆን ስለሚችል ሊንኮችን ከመክፈት በመቆጠብ ከፍተኛ ጥንቃቄ ልታደርጉ ይገባል ብሏል።

ከዚህ ባሻገር የቴሌግራምና የዋትሳፕ ተጠቃሚዎች ከወዳጅ ዘመድ ወይም የስራ ባልደረባ በእነዚህ አካውንቶች ለሚቀርብ የብድርና የድጋፍ ጥያቄ ምላሽ ከመስጠት በፊት ወደ ጠያቂው ስልክ ደውሎ ማረጋገጥ እንደሚያስፈልግ የኢንፎርሜሽን መረብ ደኅንነት አስተዳደር አሳስቧል።

#ኢዜአ #ኢትዮጵያ

የሕዳሴ ግድብ አፍሪካውያን የኢነርጂ ሉዓላዊነትን  እንዲያረጋግጡ ተነሳሽነትን ፈጥሯል - ዓለም አቀፍ የንግድ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን  አዲስ አበባ፤ መስከረም 3/2018 (ኢዜአ)፦  የታላቁ የ...
13/09/2025

የሕዳሴ ግድብ አፍሪካውያን የኢነርጂ ሉዓላዊነትን እንዲያረጋግጡ ተነሳሽነትን ፈጥሯል - ዓለም አቀፍ የንግድ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን

አዲስ አበባ፤ መስከረም 3/2018 (ኢዜአ)፦ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ምረቃት ከብሄራዊ ድል ባለፈ ለመላው አፍሪካውያን የኢነርጂ ሉዓላዊነትን እንዲያረጋግጡ መነሳሳትን የፈጠረ ታሪካዊ ስኬት መሆኑን የዓለም አቀፍ የንግድ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን የአፍሪካ ቀጣና ድርጅት አስታወቀ።

የሕዳሴ ግድብ ለኢነርጂ ሉዓላዊነትና የአየር ንብረት ለውጥ ፍትህን መረጋገጥ ትልቅ እርምጃ መሆኑንም አመልክቷል።

የኮንፌዴሬሽኑ የአፍሪካ ቀጣና ድርጅት የታላቁ ሕዳሴ ግድብ መመረቅን አስመልክቶ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፏል።

ድርጅቱ ለኢዜአ በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው የሕዳሴ ግድብ መጠናቀቅ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ድል ባለፈ በመላው አፍሪካ ተነሳሽነትን መፍጠሩን አመልክቷል።

የኢትዮጵያ ስኬት አፍሪካ ያሏትን እምቅ የተፈጥሮ ሃብቶች በህዝባዊ ተሳትፎ እና በራስ አቅም መገንባትና ማልማት እንደምትችል ያሳየ መሆኑን ገልጿል።

ግድቡ የኢነርጂ ሀብት ጥቂቶች ለትርፋቸው የሚጠቀሙበት ሳይሆን የጋራ ሀብት መሆኑን ያመላከተ እንደሆነም ነው በመግለጫው ያመላከተው።

የሕዳሴ ግድብ የሚያመነጨው ንጹህ ኢነርጂ የኢትዮጵያን የኢንዱስትሪ ዘርፍ ከማሳደግ ተሻግሮ አፍሪካ በአየር ንብረት ለውጥ ፍትህ እና ሁሉን አሳታፊ ሽግግር እውን ለማድረግ የገባችውን ቃል ኪዳን እንዲሳካ የበኩሉን አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ድርጅቱ ገልጿል።

ግድቡ ኢትዮጵያ ከበካይ የሃይል ምንጮች በጸዳ መልኩ ዘላቂ የኢነርጂ አቅርቦትን ለማረጋገጥ እያከናወነች ያለውን ስራ እንደሚያግዝም አመልክቷል።

ኢትዮጵያ ልማትን እና የካርቦን ልቀት ቅነሳን በማቀናጀት እየሰራች መሆኑን በተግባር ማሳየቷን ኮንፌዴሬሽኑ በመግለጫው አመልክቷል።

ይህ የኢትዮጵያ ጉዞ ለሰራተኞች፣ ማህበረሰቦች እና ለከባቢ አየር ንብረት የቅድሚያ ትኩረት የሰጠ አይበገሬ የኢኮኖሚ አቅም ለመገንባት እንደሚያስችል አስታውቋል።

ኮንፌዴሬሽኑ የኢትዮጵያውያንን ጠንካራ ጽናት እና ድፍረት የተሞለበት ቆራጥነት ያደነቀ ሲሆን፤ ሕዳሴ ግድብ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት የኢነርጂ ሉዓላዊነትን እንዲያረጋግጡ ጥልቅ ተነሳሽነትን የፈጠረ መሆኑንም ገልጿል።

የአፍሪካ ሀገራት የታዳሽ ኢነርጂ ስርዓታቸው ህዝብ መር፣ ፍትሃዊነት የሰፈነበት፣ በዴሞክራሲያዊ መንገድ የሚመራ እና ማህበራዊ ፍትህ የሰፈነበት እንዲሆን አበክረው እንዲሰሩም ጥሪ አቅርቧል።

የዓለም አቀፍ የንግድ ማህበራት ኮንፌዴሬሽን የአፍሪካ ቀጣና ድርጅት (ITUC-Africa) እ.አ.አ በ2007 የተቋቋመ የፓን አፍሪካ የንግድ ማህበራት ድርጅት ነው።

#ኢዜአ #ኢትዮጵያ

ከጎንደር ከተማ የተወጣጡ እንግዶች የአምቦ እና ወንጪ የልማት ስራዎች ጉብኝት    #ኢዜአ    #ኢትዮጵያ
13/09/2025

ከጎንደር ከተማ የተወጣጡ እንግዶች የአምቦ እና ወንጪ የልማት ስራዎች ጉብኝት

#ኢዜአ #ኢትዮጵያ

የጎንደር ከተማ የኦርቶዶክስ፣ የእስልምና እና የወንጌላውያን እምነት መሪዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎችና የኅብረሰተብ ክፍል ተወካዮችም የአምቦ ከተማ የኮሪደር ልማት፣ ታሪካዊቷን የደብረ...

Address

Belay Zeleke
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian News Agency posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethiopian News Agency:

Share

Category

Ethiopian News Agency

Ethiopian News Agency is the sole national wire service of Ethiopia which gathers information through its 36 branch offices across the country and disseminates news and related stories as well other productions to public and commercial media across Ethiopia.

Ethiopian News Agency was established in 1942, which makes it the oldest national news agency in Africa.