Ethiopian News Agency

Ethiopian News Agency ENA is the sole national wire service of Ethiopia.
(360)

The 82 years old ENA gathers and disseminates text news, audio and video stories about local and international events to media enterprises and the public. The Ethiopian News Agency (ENA) is the sole national wire service of Ethiopia.

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ከ1934 ዓ.ም ጀምሮ ላለፉት 82 ዓመታት በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ውስጥ የዜና አገልግሎት ተግባር በማከናወን ላይ የሚገኝ ብቸኛው ተቋም ነው፡፡

የሀዋሳ ከተማ ምክር ቤት የከንቲባ ተክሌ ጆንባን ሹመት አፀደቀ ‎ሀዋሳ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፦ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት የከተማዋን ከንቲባ ተክሌ ጆንባን ሹመት አጽድቋል።‎የ...
11/10/2025

የሀዋሳ ከተማ ምክር ቤት የከንቲባ ተክሌ ጆንባን ሹመት አፀደቀ

‎ሀዋሳ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፦ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት የከተማዋን ከንቲባ ተክሌ ጆንባን ሹመት አጽድቋል።

‎የሀዋሳ ከተማ ምክር ቤት 2ኛ ዙር 10ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 1ኛ አስቸኳይ ጉባኤውን እያካሄደ ይገኛል።

‎ምክር ቤቱ በጉባኤው የቀረበለትን የከተማዋን ከንቲባ ተክሌ ጆንባን ሹመት ተቀብሎ በሙሉ ድምፅ አፅድቋል።

‎አቶ ተክሌ ጆንባ ከወረዳ እስከ ክልል በተለያዩ የሥራ ዘርፎች በኃላፊነት ሲመሩ መቆየታቸውም በወቅቱ ተጠቅሷል።

‎አዲሱ ከንቲባ ተክሌ ጆንባ በጉባኤው ፊት የተሰጣቸውን የህዝብና የመንግስት ኃላፊነት በታማኝነትና በቅንነት ለመወጣት ቃለ መሀላ የፈፀሙ ሲሆን ከቀድሞው ከንቲባ መኩሪያ ማርሻዬ የኃላፊነት ርክክብ አድርገዋል።


#ኢዜአ

የሳይበር ደህንነትን ማስጠበቅ የሀገር ሉዓላዊነት ጉዳይ መሆኑን መገንዘብ ይገባልአዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፦ የሳይበር ደህንነት ጉዳይ ከሀገር ሉዓላዊነት ጋር የሚተሳሰር መሆኑን ...
11/10/2025

የሳይበር ደህንነትን ማስጠበቅ የሀገር ሉዓላዊነት ጉዳይ መሆኑን መገንዘብ ይገባል

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፦ የሳይበር ደህንነት ጉዳይ ከሀገር ሉዓላዊነት ጋር የሚተሳሰር መሆኑን በመገንዘብ በዘርፉ የሚከናወኑ ቅንጅታዊ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ኃላፊና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዓለም ፀሐይ ጳውሎስ ገለፁ።

6ተኛው ሀገር አቀፍ የሳይበር ደህንነት ወር ማስጀመሪያ ስነ ሥርዓት እየተካሄደ ይገኛል።

የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ሃላፊና የካቢኔ ጉዳዮች ሚኒስትር ዓለምፀሐይ ጳውሎስ ባስተላለፉት መልእክት ባለፉት የለውጥ ዓመታት በሁሉም ዘርፎች ስኬታማ የልማት ስራዎች ተከናውነዋል።

የኢትዮጵያ የማንሰራራት ጅማሮ ማሳያ የሆኑ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጨምሮ የተመረቁና የተጀመሩ ግዙፍ ፕሮጀክቶች መንግስት ለዘላቂ ልማትና እድገት ያለውን ቁርጠኝነት በተግባር ያሳዩ ናቸው ብለዋል።

የዜጎችን የዕለት ተዕለት የህይወት እንቅስቃሴና የመንግሥትን አገልግሎት የሚያሳልጡ የዲጂታል አሠራሮችን በመተግበር ተጨባጭ ለውጦች መምጣታቸውን አንስተዋል።

በአሁኑ ወቅት ከ900 በላይ የሚሆኑና በተቋማት የሚሰጡ አገልግሎቶች በቴክኖሎጂ አማካይነት ለተገልጋዮች ተደራሽ እየተደረጉ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ቴክኖሎጂና ልማት ተሰናስለው የሚሔዱ ናቸው ያሉት ሚኒስትሯ፥ የልማት ስራዎቹ ደህንነታቸው ተጠብቆ እንዲቆይ ማድረግ ላይ ትኩረት ሰጥቶ መስራት ወሳኝ መሆኑን ገልፀዋል።

የሳይበር ደህንነት ጉዳይ ከሀገር ሉአላዊነት ጋር የሚተሳሰር በመሆኑ በዘርፉ የሚከናወኑ ተግባራት ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

ለዚህም በተለያዩ አማራጮች ተደራሽ የሚደረጉ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራዎች ጉልህ ሚና እንዳላቸው ነው የጠቆሙት።

የሳይበር ደህንነት ወር እንደ ሀገር በሳይበር ደህንነት ላይ የሚከናወኑ ተግባራትን በስፋት ለማስገንዘብ እድል የሚፈጥርና የተቋማትን ቅንጅታዊ አሰራር ለማጠናከር የሚያግዝ ነው ብለዋል።

በመሆኑም በመላ ሀገሪቱ በሳይበር ደህንነት ዙሪያ የሚከናወኑ ተግባራት ውጤታማ በሆነ መልኩ ተግባራዊ ለማድረግ ሁሉም የድርሻውን ሊወጣ እንሚገባ አስገንዝበዋል።


#ኢዜአ

የኢትዮጵያ የባሕር በር መሻት ፍትሐዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን ከማስጠበቅ የሚመነጭ የብሔራዊ ጥቅም አጀንዳ ነውአዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የባሕር በር መሻት ፍትሐዊ የ...
11/10/2025

የኢትዮጵያ የባሕር በር መሻት ፍትሐዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን ከማስጠበቅ የሚመነጭ የብሔራዊ ጥቅም አጀንዳ ነው

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የባሕር በር መሻት ፍትሐዊ የኢኮኖሚ ተጠቃሚነትን ከማስጠበቅ የሚመነጭ የብሔራዊ ጥቅም አጀንዳ መሆኑን በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ ፈትሂ ማህዲ (ዶ/ር) ገለጹ።

ምክትል ሰብሳቢው ለኢዜአ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በተፈፀመባት ታሪካዊ ስህተትና ኢ-ፍትሐዊ ሁኔታ የባሕር በር አልባ ከሆኑ ሀገሮች መካከል አንዷ ለመሆን ተዳርጋለች።

ኢትዮጵያ ከቀይ ባሕር በቅርብ ርቀት የምትገኝና የብዙ ሕዝብ ባለቤት ሀገር መሆኗ የባህር በር ከሌላቸው ሀገራት የተለየ እንደሚያደርጋት ገልጸዋል።

በዓለም የንግድ ሥርዓት በሸቀጦች እንቅስቃሴ ግዙፍ ስፍራ በሚሰጠው የቀይ ባሕር ላይ የባህር በር ማጣት በሀገር የኢኮኖሚ ዕድገት ላይ ኪሳራው ብዙ መሆኑን አስረድተዋል።

የባሕር በር ባለመኖሩ ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ የገቢና ወጪ የንግድ ሥርዓት ለከፍተኛ ወጪ እንድትጋለጥ ማድረጉን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ የባሕር በር ባለቤት አለመሆን የኢኮኖሚ ዕድገትን ለማስቀጠል በሚደረገው ጥረት በገቢና ወጪ ንግድ ተወዳዳሪነትና በዜጎች ኑሮ ላይ ጫና እያሳደረ እንደሚገኝ አንስተዋል።

በዓለም አቀፍ የኢኮኖሚ ተወዳዳሪነት ሥርዓት ውስጥ ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የባሕር በርና የወደብ አገልግሎት ወሳኝ ሚና እንደሚጫወት አብራርተዋል።

ኢትዮጵያ የግዙፍ ኢኮኖሚና ከፍተኛ የሕዝብ ቁጥር ባለቤት እንዲሁም ለቀይ ባህር በቅርብ ርቀት የምትገኝ መሆኗ የባሕር በር ፍትሐዊ ጥያቄዋ የብሔራዊ ጥቅም አጀንዳና የህልውና ጉዳይ መሆኑን አጽንኦት ሰጥተዋል።

የባሕር በር መሻቷም ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገትና ተጠቃሚነትን ከማሳለጥ የሚመነጭ፣ ቀጣናዊ የጋራ ተጠቃሚነትና ዓለም አቀፍ መርህን የተከተለ የብሔራዊ ጥቅም ጉዳይ መሆኑን አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ የባሕር በር መሻት የምስራቅ አፍሪካ የኢኮኖሚ ትስስርን በማሳለጥ ቀጣናዊ ሰላምና ደኅንነትን ከማስጠበቅ ጋር የተቆራኘ ጭምር መሆኑንም አስገንዝበዋል።

የምስራቅ አፍሪካ ትስስርም የንግድ ልውውጥና የቱሪስት ፍሰትን በማጠናከር የቀጣናውን ዜጎች የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት በማሳደግ የጋራ ብልጽግናን ለማረጋገጥ ጉልህ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ተናግረዋል።

የኢትዮጵያን በመርህ ላይ የተመሰረተ የባሕር በር ጥያቄም ለጋራ የኢኮኖሚ ዕድገት፣ ሰላምና ደህንነት የሚኖረውን ገንቢ ሚና በመገንዘብ የቀጣናው ሀገራት ተገቢውን ምላሽ ሊሰጡ እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያን የባሕር በር ፍላጎት እውን ለማድረግ የውስጥና የውጭ ዲፕሎማሲያዊ ጥረቶች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው አብራርተዋል።

ዜጎችም የኢትዮጵያን የባሕር በር ጥያቄ አዎንታዊ ምላሽ ለማስገኘት በሚደረገው ጥረት ሁሉ የድርሻቸውን ገንቢ ሚና ሊወጡ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡


#ኢዜአ

በግብርናው ዘርፍ የኢትዮጵያን ማንሰራራት ዕውን የሚያደርጉ ውጤታማ  የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ ነው - ሚኒስትር አዲሱ አረጋአዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፦ በግብርናው ዘርፍ የኢት...
11/10/2025

በግብርናው ዘርፍ የኢትዮጵያን ማንሰራራት ዕውን የሚያደርጉ ውጤታማ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ ነው - ሚኒስትር አዲሱ አረጋ

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018(ኢዜአ)፦ በግብርናው ዘርፍ የኢትዮጵያን ማንሰራራት ዕውን የሚያደርጉ ውጤታማ የልማት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ ገለጹ።

የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋን ጨምሮ የዘርፉ ከፍተኛ አመራሮች በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ቀቤና ልዩ ወረዳ በክላስተር የለማ የበቆሎ እርሻን ተመልክተዋል።

በምልከታው የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ መለሰ መኮንን(ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ ግብርና ትራንስፎርሜሽን ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ማንደፍሮ ንጉሴ(ዶ/ር)፣ በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የግብርና ቢሮ ኃላፊ ኡስማን ሱሩር እና ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።

የግብርና ሚኒስትር አዲሱ አረጋ በዚሁ ወቅት፤ ኢትዮጵያ የምግብ ሉዓላዊነቷን ለማረጋገጥ የጀመረቻቸው ስራዎች ውጤት እያስገኙ ነው ብለዋል።

በምርት ዘመኑ በተለያዩ ሰብሎች ከለማው ማሳ ውስጥ ከ12 ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በክላስተር መልማቱን ጠቁመዋል።

በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ ያሉ ውጤታማ ተግባራት የኢትዮጵያን ማንሰራራት ዕውን የሚያደርጉ መሆናቸውንም ሚኒስትሩ ገልጸዋል።

በቀቤና ልዩ ወረዳ በምርት ዘመኑ 12ሺህ 500 ሄክታር መሬት በበቆሎ የለማ ሲሆን በልዩ ወረዳው በዓመት አራት ጊዜ የግብርና ልማት እንደሚከናወን ተገልጿል።


#ኢዜአ

በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018 (ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵ...
11/10/2025

በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ ይገባሉ

አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 1/2018 (ኢዜአ)፡- በየዓመቱ በሚሊየን የሚቆጠሩ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል።

የዓለም የስደተኛ ወፎች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ20ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ15ኛ ጊዜ "ምቹ የመኖሪያ ቦታ፤ ለአዕዋፋት አኗኗር ምቹ የሆኑ ከተምች እና ማኅበረሰብ" በሚል መሪ ሐሳብ ዛሬ በመላው ዓለም እየተከበረ ነው።

በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ጥበቃ ባለሥልጣን የጥበቃ ቦታዎችና የብሔራዊ ፓርኮች ዋርደን ፋንታዬ ነጋሽ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የዓለም የፍልሰተኛ ወፎች ቀን የሚከበረው ስለ ፍልሰተኛ ወፎች ያለ የማኅበረሰብ ግንዛቤን ለማሳደግ እና በእንቅስቃሴያቸው ወቅት ተገቢ ጥበቃ እንዲደረግላቸው ዓለም አቀፍ ትብብርን ለማጎልበት ነው።

ለምግብና ለመራባት በይበልጥ ምቹ ሁኔታ በመፈለግ ብሎም ከወቅታዊ ተፈጥሯዊ ሁኔታዎች (ቅዝቃዜና ሙቀት ) ለማምለጥ ወፎች ምቹ ወደሚሉት አካባቢ እንደሚፈልሱ አንስተዋል።

በዚህም መሠረት ከአውሮፓ፣ እስያ፣ ከተለያዩ የአፍሪካ እና ባልካን ሀገራት በየዓመቱ በተለያዩ ወቅቶች በሚሊየን የሚቆጠሩ ወፎች በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ ጠቁመዋል።

አንዳንድ ፍልሰቶች አጭር መሆናቸውን ገልጸው፤ አኅጉራትን፣ በረሃዎችን እና ውቅያኖሶችን ማቋረጥ የግድ የሚሆንባቸው ረጅም ርቀት የሚሸፍኑ ፍልሰቶች እንዳሉም አስገንዝበዋል።

ትክክለኛ ዓመታዊ ቆጠራ ላይ የተመሠረተ አሀዛዊ መረጃ ማግኘት ቢያዳግትም፤ በተለይም በምሥራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ መስመር አማካኝነት በየዓመቱ በርካታ ፍልሰተኛ ወፎች ወደ ኢትዮጵያን ይመጣሉ ብለዋል።

በዚህም መሠረት ከ1 ነጥብ 5 ሚሊየን የሚልቁ ፍልሰተኛ ወፎች በኢትዮጵያ በኩል የሚያልፈውን የስምጥ ሸለቆ መስመር ይጠቀማሉ ነው ያሉት።

በተጨማሪም 199 ገደማ ዝርያዎች ከአውሮፓና እስያ እንዲሁም 47 ዓይነት ዝርያዎች ከአፍሪካ የተለያዩ ሀገራት በፍልሰት ወደ ኢትዮጵያ እንደሚገቡ እና ከወራት ቆይታ በኋላ ወደተለያዩ አቅጣጫዎች ተመልሰው እንደሚሄዱም አንስተዋል።

እንደዝርያቸው ቢወሰንም ከቅዝቃዜ እስከ ሞቃታማ የአየር ንብረት ያላቸውን አካባቢዎች በማካለል የሚኖሩት እነዚህ ፍልሰተኛ ወፎች ቋሚ የመኖሪያ ሥፍራ እና ወጥ የአየር ንብረት የላቸውም ብለዋል።

ነገር ግን አብዛኞቹ የወፍ ዝርያዎች ለአስተማማኝ የምግብ አቅርቦትና ልጆቻቸውን ለመንከባከብ ተስማሚ የአየር ንብረት ወዳላቸው አካባቢዎች ርቀው በመሄድ አስቸጋሪ ወቅቶች እስከሚያልፉ ይጠብቃሉ ነው ያሉት።

#ኢዜአ

ታሪኳንና ቅርሶቿን ገልጦ ለተመለከተ፣ መልክአ ምድሯን ለቃኘ፣ በማኅጸኗ ያቀፈቻቸውን እንስሳት፣ አዕዋፍና ዕጽዋት ዓይኑን ገልጦ ላሰሰ፣ የሕዝቦቿን ባህል፣ ትውፊት፣ ፍልስፍና፣ በማስተዋል ለመረ...
11/10/2025

ታሪኳንና ቅርሶቿን ገልጦ ለተመለከተ፣ መልክአ ምድሯን ለቃኘ፣ በማኅጸኗ ያቀፈቻቸውን እንስሳት፣ አዕዋፍና ዕጽዋት ዓይኑን ገልጦ ላሰሰ፣ የሕዝቦቿን ባህል፣ ትውፊት፣ ፍልስፍና፣ በማስተዋል ለመረመረ፤ ኢትዮጵያ የመስሕቦች ማንጸሪያ፣ የልዩነት አጽናፍ ማስረጃ ናት።

የመደመር መንግሥት መጽሐፍ ገጽ 260


#ኢዜአ

ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ትራንስፖርት ያሏትን ተሞክሮዎች የምታቀርብበት አህጉራዊ ሁነትአዲስ አበባ፤መስከረም 30/2018 (ኢዜአ)፦“ አፍሪካ ኢ-ሞቢሊቲ ዊክ 2025” የተሰኘ የአፍሪካ የአረንጓዴ ...
11/10/2025

ኢትዮጵያ በአረንጓዴ ትራንስፖርት ያሏትን ተሞክሮዎች የምታቀርብበት አህጉራዊ ሁነት

አዲስ አበባ፤መስከረም 30/2018 (ኢዜአ)፦“ አፍሪካ ኢ-ሞቢሊቲ ዊክ 2025” የተሰኘ የአፍሪካ የአረንጓዴ ትራንስፖርት ሳምንት ከጥቅምት 4 እስከ 6 ቀን 2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ይደረጋል።

ሳምንቱ “ በአፍሪካ ሁሉን አቀፍ እና ዘላቂ የትራንስፖርት ስርዓትን ማረጋገጥ” በሚል መሪ ሀሳብ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት አፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን (ኢሲኤ) ይካሄዳል።

ተቀማጭነቱን ኬንያ ናይሮቢ ያደረገው ”አፍሪካ ኢ-ሞቢሊቲ አሊያንስ” የተሰኘ ድርጅት፣ የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስቴር፣ የተባበሩት መንግስታት የአካባቢ ጥበቃ ፕሮግራም እና ሌሎች አጋሮች ሁነቱን በጋራ አዘጋጅተዋል።

በሁነቱ ላይ የተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት ኢኖቬተሮች፣ ፖሊሲ አውጪዎች፣ ባለሀብቶች፣ ዓለም አቀፍ ተቋማት እና የትራንስፖርት ዘርፍ መሪ ተዋናያን ይሳተፋበታል።

ሳምንቱ አፍሪካ ወደ ኤሌክትሪክ ተሽርካሪዎች የምታደርገውን ሽግግር ማፋጠን ዋንኛ ትኩረቱ አድርጓል።

የትራንስፖርት እና ሎጅስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ በርኦ ሀሰን በአረንጓዴ ትራንስፖርት ሳምንቱ ላይ ከ500 በላይ ሰዎች በአካል እና ከ2000 በላይ ሰዎች በበይነ መረብ አማራጭ እንደሚሳተፉ ለኢዜአ ገልጸዋል።

በሳምንቱ ላይ ከ30 በላይ የውይይት መድረኮች እና አውደ ርዕዮች እንደሚካሄዱ ጠቅሰው ከነዚህም አንዱ የአፍሪካ ሀገራት ከፍተኛ ባለስልጣናት የሚገኙበት መድረክ እንደሆነ ተናግረዋል።

አረንጓዴ ትራንስፖርትን የተመለከቱ የጥናት ውጤቶች እና ግኝቶች ይፋ እንደሚደረጉም ነው የገለጹት።

ከሁነቶቹ ጎን ለጎን የኢንዱስትሪ ጉብኝት መርሃ ግብር እንደሚኖር ጠቅሰው ከ200 በላይ ተሳታፊዎች የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ገጣጣሚዎችን፣ የኤሌክትሪክ ባሶች እንቅስቃሴ፣ የተሰሩ የኃይል መሙያ ማዕከላት፣ ዴፖዎች እንዲሁም በሽያጭ፣ አቅርቦት እና ጥገና የተሰማሩ አካላትን እንቅስቃሴ እንደሚጎበኙ አመልክተዋል።

ለተጨማሪ ንባብ 👉 https://www.ena.et/web/amh/w/amh_7495873

#ኢዜአ

የኢትዮጵያ የባህላዊ ምግቦች ፌስቲቫል ለመጀመሪያ ጊዜ ሊካሄድ ነውአዲስ አበባ፤ መስከረም 30/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የባህላዊ ምግቦች ፌስቲቫል  ነገ በሸገር ከተማ ይደረጋል።የባህላዊ ...
10/10/2025

የኢትዮጵያ የባህላዊ ምግቦች ፌስቲቫል ለመጀመሪያ ጊዜ ሊካሄድ ነው

አዲስ አበባ፤ መስከረም 30/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ የባህላዊ ምግቦች ፌስቲቫል ነገ በሸገር ከተማ ይደረጋል።

የባህላዊ ምግብ ፌስቲቫሉ የቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢኒስቲትዩት ከኩሪፍቱ አፍሪካ ቪሌጅ፣ ከሸገር ከተማ አስተዳደር እና ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ያዘጋጀው ነው።

የቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢኒስቲትዩት የህዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈጻሚ ወይዘሮ አስቴር ተክሌ፥ የኢንስቲትዩቱ ባለሙያዎች በክልሎች በሚገኙ የተለያዩ ብሄር፣ ብሄረሰቦች እና ህዝቦች የሚገኙ ባህላዊ ምግቦች ላይ ጥናት ማድረጉን ለኢዜአ ገልጸዋል።

የባህላዊ ምግቦቹ አዘገጃጀት፣ የምግቡ መጠን፣ የሚይዟቸው ንጥረ ነገሮች እና አጠቃላይ ሂደቱን ከሚያሳዩ እናቶች አንደበት በመስማት እና የተግባር ስራ በመመልከት ሰነድ መዘጋጀቱን አመልክተዋል።

ኢኒስቲትዩቱ 205 ገደማ የሚሆኑ ባህላዊ የምግብ አይነቶችን በመሰነድ በመጽሐፍ መልክ እያዘጋጀ መሆኑን ጠቁመዋል።

ጥናት ከተደረገባቸው መካከል ለማሳያነት የተመረጡ የ31 ብሄር ብሄረሰቦች ባህላዊ ምግቦች በምግብ ፌስቲቫሉ ላይ ይቀርባሉ ብለዋል።

ማሰልጠኛ ተቋሙ የባህላዊ ምግቦቹን ምንነት የሚገልጸውን ሰነድ ለየብሄረሰቦቹ ተወካዮች እንደሚያስረክብም ጠቁመዋል።

ፌስቲቫሉ የባህላዊ ምግቦቹን ማስተዋወቅ፣ ወደ ገበታ እንዲመጡ እና ለተጠቃሚ እንዲደርሱ ማድረግ፣ ባህሎችን የማስተዋወቅ፣ የእርስ በእርስ ትውውቅን መፍጠር፣ የሀገር ገጽታ መገንባት እና የምግብ ቱሪዝምን የማሳደግ ፋይዳዎች እንዳሉት ነው ወይዘሮ ተክሌ ያብራሩት።

የእናቶችን ሀገር በቀል እውቀት ወደ ቀጣዩ ትውልድ የማሻገር አላማ እንዳለውም ገልጸዋል።

ኢንስቲትዩቱ በመስኩ ሰፊ ጥናት አድርጎ ባህላዊ ምግቦች በትላልቅ ሆቴሎች የምግብ ዝርዝር (ሜኑ) ውስጥ እንዲካተቱ እያከናወነ ያለውን ስራ የሚያግዝ እንደሆነም ተናግረዋል።

በቀጣይ የባህላዊ ምግብ እና መጠጦች አውደ ርዕይ፣ የጥናትና ምርምር ግኝቶች ይፋ የሚደረጉባቸው መድረኮች እንዲሁም ሌሎች ተጓዳኝ መርሃ ግብሮች እንደሚከናወኑ ጠቁመዋል።

ፌስቲቫሉ የቱሪዝም ማሰልጠኛ ኢኒስቲትዩት ከሰጡት ተልዕኮዎች አንዱ የሆነው የጥናት እና ምርምር ውጤቶችን ለህዝብ ተደራሽ የማድረግ ስራ አካል እንደሆነም ነው የጠቀሱት።

በቀጣይ ተቋሙ በትላልቅ ሆቴሎች ባህላዊ ምግቦችን የምግብ ዝርዝር (ሜኑ) ውስጥ የማከተት ስራ ማስፋት እና የማስተዋወቅ እንዲሁም ሰነዶችን የማዘጋጀት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ገልጸዋል።

በባህላዊ ምግብ ፌስቲቫሉ ላይ ምግቡን ያዘጋጁ እናቶች፣ የየብሄረሰቦቹ ተወካዮች፣ ሆቴሎች፣ የመንግስት የስራ ኃላፊዎች፣ አምባሳደሮች እና የተለያዩ ተቋማት ይሳተፋሉ።
#ኢዜአ

የኢትዮጵያን ብልጽግና ስናረጋግጥ ፍትህ እና የአኗኗር ዘዴ ትኩረት የምናደርግባቸው ጉዳዮች ናቸው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)አዲስ አበባ፤ መስከረም 30/2018(ኢዜአ)፦ የኢት...
10/10/2025

የኢትዮጵያን ብልጽግና ስናረጋግጥ ፍትህ እና የአኗኗር ዘዴ ትኩረት የምናደርግባቸው ጉዳዮች ናቸው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

አዲስ አበባ፤ መስከረም 30/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያን ብልጽግና ስናረጋግጥ ፍትህ እና የአኗኗር ዘዴ ትኩረት የምናደርግባቸው ጉዳዮች ናቸው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተጀመረውን የፍትህ አሰጣጥ ቴክኖሎጂ ዛሬ ጎብኝተዋል::

ከጉብኝቱ በኋል በሰጡት ማብራሪያ፤ የኢትዮጵያን ብልጽግና ስናረጋግጥ ፍትህ እና የአኗኗር ዘዴ ትኩረት የምናደርግባቸው ጉዳዮች ናቸው ብለዋል።

የዲጂታል ኢትዮጵያ ስትራተጂ የተቀረጸው የፋይናንስ፣ የንግድ፣ የጸጥታ ተቋማትን ጨምሮ በርካታ ተቋማት የማሽን ግብዓት በመጠቀም አገልግሎትን እንዲያጠናክሩ ለማስቻል መሆኑንም ገልጸዋል።

ፍትሕ በተለያየ መንገድ የሚገዛ በመሆኑ ፍትሕ እና ርትዕን ለማረጋገጥ አንዱ መፍትሄ የኦቶሜሽን አሰራር ስርዓት መዘርጋት እንደሆነም አንስተዋል።

ችሎትን የተለያዩ አካባቢዎች ላይ ሆኖ በመከታተል ፍትሕን ማግኘት ትልቅ ዕድል መሆኑን ጠቁመው፤ ባለጉዳዮች ካሉበት ቦታ ሆነው ፍትሕ ማግኘታቸው በጊዜና በገንዘብ የማይለካ ጥቅም ያለው መሆኑንም ገልጸዋል።

ከዚህ አንጻር የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የሰራው ስራ አስደማሚ መሆኑንና ይህንን ስርዓት በቅርንጫፎች ማዳረስ ተችሏል ብለዋል።

ከዚህም አልፎ ክልሎች ይህንን መንገድ እንዲከተሉ እያደረጉ ነው ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማብራሪያቸው።

የኢትዮጵያን ብልጽግና ስናረጋግጥ ፍትህ እና የአኗኗር ዘዴ ትኩረት የምናደርግባቸው ጉዳዮች ናቸው ሲሉም ነው የገለጹት።

በፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የተጀመረው የፍትህ አሰጣጥ ቴክኖሎጂ በሁሉም አካባቢ ተዳርሶ ፍትህን ማጣጣም ያስፈልጋል ሲሉም ጠቅላይ ሚኒስትሩ አስገንዝበዋል።

በሀገሪቱ ያሉ የተለያዩ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት እየዘመኑ መሆናቸውን ጠቁመው፤ ለአብነትም መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ተጠቃሽ መሆኑን ገልጸዋል።

በሀገሪቱ እየተከናወነ ያለው የዲጂታላይዜሽን አሰራር ጠቀሜታው በስፋት እየታየ ይገኛል ሲሉም አክለዋል፡፡

#ኢዜአ

10/10/2025

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ጉብኝት

#ኢዜአ

Address

Belay Zeleke
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian News Agency posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethiopian News Agency:

Share

Category

Ethiopian News Agency

Ethiopian News Agency is the sole national wire service of Ethiopia which gathers information through its 36 branch offices across the country and disseminates news and related stories as well other productions to public and commercial media across Ethiopia.

Ethiopian News Agency was established in 1942, which makes it the oldest national news agency in Africa.