Ethiopian News Agency

Ethiopian News Agency ENA is the sole national wire service of Ethiopia.
(379)

The 82 years old ENA gathers and disseminates text news, audio and video stories about local and international events to media enterprises and the public. The Ethiopian News Agency (ENA) is the sole national wire service of Ethiopia.

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ከ1934 ዓ.ም ጀምሮ ላለፉት 82 ዓመታት በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ውስጥ የዜና አገልግሎት ተግባር በማከናወን ላይ የሚገኝ ብቸኛው ተቋም ነው፡፡

ኢትዮጵያ በየትኛውም መመዘኛ የባህር በር የባለቤትነት መብት ልትነፈግ አትችልምሰመራ፤ ህዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በየትኛውም መመዘኛ የባህር በር የባለቤትነት መብት ልትነፈግ እንደማ...
02/12/2025

ኢትዮጵያ በየትኛውም መመዘኛ የባህር በር የባለቤትነት መብት ልትነፈግ አትችልም

ሰመራ፤ ህዳር 22/2018(ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ በየትኛውም መመዘኛ የባህር በር የባለቤትነት መብት ልትነፈግ እንደማትችል ተመላከተ።

ኢትዮጵያ በህጋዊ፣ በመልክአ ምድራም ይሁን በታሪክ ከቀይ ባህር ልትነጠል የማትችል በመሆኑ የባህር በር ባለቤት መሆኗ የህልውና ጉዳይ ነው።

በመሆኑም የባህር በር ባለቤትነት ጉዳይ የትውልድ ጥያቄ በመሆኑ ምላሽ ማግኘት አለበት።

የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄን በማስመልከት በአፋር ክልላዊ ፓርቲ ሆኖ የሚንቀሳቀሰው የአፋር ነፃ አውጭ ግንባር(አነግፓ) ፓርቲ ሊቀ መንበር ሃንፈሬ አሊሚራህን ኢዜአ አነጋግሯል።

የኢትዮጵያ ህዝብ ቀይ ባህርን በአቅራቢያው እያየ መውጫ መግቢያ እንዳይኖረው መታጠሩ ፍፁም ተገቢነት የሌለውና ፍትሃዊነት የጎደለው መሆኑን ሊቀመንበሩ ገልጸዋል።

በመሆኑም ኢትዮጵያ በየትኛውም መመዘኛ የቀይ ባህር የባለቤትነት መብትን ልትነፈግ የማትችል መሆኑን አንስተው የባህር በር ባለቤት ልትሆን ግድ ይላል ብለዋል።

ኢትዮጵያ የባህር በር ያጣችበት መንገድ የተዳፈነ እና ግልጸኝነት የሌለው ሆኖ ከ30 ዓመታት በላይ መዝለቁን አስታውሰውአሁን ታሪክንና ሃቅን በመያዝ የትውልድ ጥያቄ ሆኖ መነሳቱ ተገቢና ምላሽ ሊሰጠው የሚገባ ጥያቄ መሆኑን ተናግረዋል።

በኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅምና በሉአላዊነቷ ማንም ኢትዮጵያዊ ሊደራደር እንደማይገባ አንስተዋው ጥያቄው ተገቢው ምላሽ እንዲያገኝ በጋራ እንደሚሰሩም አረጋግጠዋል።

የኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነት ጥያቄ ታሪካዊ እና ህጋዊ መሰረት ያለው፤ የኢኮኖሚ ህልውና እና የብሔራዊ ደህንነት ጉዳይ ጭምር በመሆኑ በሰላማዊ፣ በጋራ ተጠቃሚነትና በህጋዊ መንገድ ለማሳካት እየተሰራ መሆኑ ይታወቃል።


#ኢዜአ

ዲጂታል ግብርና፤ የአፍሪካ ግብርና አዲስ ምዕራፍ ዲጂታል ግብርና በጥቅሉ ሲተረጎም የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን ለግብርና ስራዎች መጠቀም ማለት ነው። ቴክኖሎጂዎቹ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ፣ ...
01/12/2025

ዲጂታል ግብርና፤ የአፍሪካ ግብርና አዲስ ምዕራፍ

ዲጂታል ግብርና በጥቅሉ ሲተረጎም የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችን ለግብርና ስራዎች መጠቀም ማለት ነው። ቴክኖሎጂዎቹ የግብርና ምርታማነትን በማሳደግ፣ የገበያ ተደራሽነትን በማስፋት፣ በአቅርቦት የእሴት ሰንሰለት ላይ መጠናከር፣ በቅድመ ማስጠንቀቂያ ስርዓት፣ የተፈጥሮ ሀብት አጠቃቀምና የአየር ንብረት ለውጥ አይገበገሬነት ስራዎችን ጨምሮ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ አላቸው።

የዓለም የዲጂታል ግብርና ገበያ እ.አ.አ በ2022 ከ10 እስከ 12 ቢሊዮን መድረሱን የተለያዩ መረጃዎች ያመለክታሉ። እ.አ.አ በ2028 የገበያ መጠኑ ከ23 እስከ 25 ቢሊየን ዶላር እንደሚደርስ ትንበያ ተቀምጧል።

የዲጂታል ግብርና በአውሮፓ፣ በሰሜን አሜሪካ እና እስያ ፓሲፊክ በፍጥነት እያደገ ሲሆን በአፍሪካና ላቲን አሜሪካ ጅምር ላይ ነው ማለት ይቻላል። ሰሜን አሜሪካ 40 በመቶ እና አውሮፓ 25 በመቶ የዓለም የዲጂታል ግብርና ገበያ ድርሻን ይይዛሉ።

አርሶ አደሮች ለዲጂታል ግብርና የሚያስፈልጋቸውን ቴክኖሎጂዎችን አለማግኘት፣ የዳታ ደህንነት እና የግል መረጃ ጥበቃ፣ የአየር ንብረት ለውጥ፣ የኢንተርኔት ተደራሽነትና ባህላዊ ልማዶችን ከዘመናዊ ቴክኖሎጂዎች ጋር ማስተሳሰር ዓለም አቀፍ የዘርፉ ፈተናዎች ናቸው።
አፍሪካ ከአምስት እስከ ሰባት በመቶ(ከ500 እስከ 800 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር) የሚገመት ነው።

በአፍሪካ የግብርና ቴክኖሎጂ ያለው ኢንቨስትመንት በፍጥነት እያደገ ይገኛል። ዘርፉ ከ400 ሚሊየን ዶላር መዋዕለ ንዋይ ፈሶበታል። በሞባይል የማማከር አገልግሎት፣ የገበያ ትስስር ማዕቀፎችና ለአርሶ አደሮች የፋይናንስ ቴክኖሎጂዎች ተደራሽ የማድረግ ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።

የቴክኖሎጂዎቹ የተደራሽነትና አላምዶ የመጠቀም ውስንነት፣ የመሰረተ ልማት ግንባታ፣ የፖሊሲ እና የህግ ማዕቀፍ እክሎች እንዲሁ አካታችነት የአፍሪካ ፈተናዎች ናቸው። በአፍሪካ አብዛኛው ግብርና በአነስተኛ ይዞታ ባላቸው አርሶ አደሮች ላይ የተመሰረተ ሲሆን ግብርና ለአፍሪካውያን ኑሮ እና የምግብ ዋስትና ወሳኝ የሚባል ነው።

በዚህ ረገድም የዲጂታል ግብርና ለግብርና ምርታማነት ማደግ፣ የአቅርቦት እጥረትን በመቅረፍና የልማት ግቦች በማሳካት ረገድ የበኩሉን ሚና ይጫወታል። ኢትዮጵያ ለጉዳዩ ትኩረት በመስጠት በጥር ወር 2017 ዓ.ም የዲጂታል ግብርና ፍኖተ ካርታ ይፋ አድርጋለች።

ለሙሉ ጽሁፉ 👉 https://www.ena.et/web/amh/w/amh_7825986

01/12/2025

የጉባ ብስራት ግዙፍ ብሔራዊ ፕሮጀክቶች የኢትዮጵያን የብልጽግና ዕድል የሚወስኑ ናቸው - ሚኒስትር መላኩ አለበል


#ኢዜአ

01/12/2025

ቱሪዝምን ከቅርስነት ወደ ቁርስነት እንቀይረው - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)


#ኢዜአ

01/12/2025

ዛሬ ከቀዳማዊት እመቤት ጽ/ቤት በጎንደር ከተማ እና በዞኖቹ ለሚገኙ ትምህርት ቤቶች፣ የስፖርት ማዘውተሪያ ቦታዎች እና ድጋፍ ለሚሹ አካል ጉዳተኞች የተደረገ ድጋፍ

#ኢዜአ

ብሔራዊ ባንክ ተግዳሮቶችን ለመፍታት እና የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞች ለማስጠበቅ ከግል ዘርፉ ጋር ለመስራት ቁርጠኛ ነው አዲስ አበባ፣ሕዳር 22 /2018 ( ኢዜአ) ፦ብሔራዊ ባንክ ተግዳሮ...
01/12/2025

ብሔራዊ ባንክ ተግዳሮቶችን ለመፍታት እና የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞች ለማስጠበቅ ከግል ዘርፉ ጋር ለመስራት ቁርጠኛ ነው

አዲስ አበባ፣ሕዳር 22 /2018 ( ኢዜአ) ፦ብሔራዊ ባንክ ተግዳሮቶችን ለመፍታት፣ ተገዢነትን ለማሻሻል እና የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞች ለማስጠበቅ ከግል ዘርፉ ጋር ለመስራት ቁርጠኛ መሆኑ ተገለጸ፡፡

የብሔራዊ ባንክ ገዥ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) የውጭ ምንዛሪ ወደ ሀገር መመለስ ላይ በሚታዩ ክፍተቶች ዙሪያ ከቡና፣ ሰሊጥ እና ጥራጥሬ ላኪዎች ጋር ተወያይተዋል።

በምክክር መድረኩ ባንኩ የሀገሪቱን የውጭ ምንዛሪ ገቢ የመጠበቅ እና የኤክስፖርት ገቢ በወቅቱ እና በግልጸኝነት እንዲመለስ የማድረግ ሃላፊነት እንዳለበት ተጠቁሟል፡፡

ብሔራዊ ባንክ ከሕጋዊ ርምጃ በፊት ከዘርፉ ባለድርሻ አካላት ጋር ገንቢ ውይይት ማድረግን እንደሚያስቀድም ተጠቅሷል፡፡

በዚህም ባንኩ ተግዳሮቶችን ለመፍታት፣ ተገዢነትን ለማሻሻል እና የኢትዮጵያን ኢኮኖሚያዊ ጥቅሞች ለማስጠበቅ ከግል ዘርፉ ጋር ለመስራት ቁርጠኛ መሆኑም ተገልጿል፡፡

ባንኩ ከዚህ ባለፈም ተጠያቂነትና ኃላፊነት የሚሰማው የወጪ ንግድ ልምዶችን የማበረታታት እና የውጭ ምንዛሪ አስተዳደር ሥርዓቱን የማሳደግ ሥራውን እንደሚያጠናክር ነው የተገለጸው ።

#ኢዜአ

በመዲናዋ የግብር ከፋዮችን ቅሬታ አጣርቶ ምላሽ የሚሰጥ አሰራር ሊጀመር ነውአዲስ አበባ ፤ ሕዳር 22/2018 ( ኢዜአ) ፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የግብር ከፋዮችን ቅሬታ ሃላፊዎች በ...
01/12/2025

በመዲናዋ የግብር ከፋዮችን ቅሬታ አጣርቶ ምላሽ የሚሰጥ አሰራር ሊጀመር ነው

አዲስ አበባ ፤ ሕዳር 22/2018 ( ኢዜአ) ፦ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የግብር ከፋዮችን ቅሬታ ሃላፊዎች በተገኙበት አጣርቶ ምላሽ መስጠት የሚያስችል አሰራር ከመጪው ሐሙስ ጀምሮ ተግባራዊ ያደርጋል፡፡

በአዲስ አበባ የግብር አሰባሰብና የገቢዎች አገልግሎት አሰጣጥ ጋር በተያያዘ የሚኖርን ቅሬታ መፍታት የሚያስችል አዲስ አሰራር በከንቲባ ጽ/ቤት ሥር ተዋቅሯል።

አሰራሩ በአስተዳደሩ የገቢዎች ቢሮ ስር በተዘረጋው የቅሬታ አፈታት ሥርዓት ያልረኩ ግብር ከፋዮች ቅሬታዎቻቸውን የሚያቀርቡበት ነው፡፡

በዚህ መሰረትም ከገቢ አሰባሰብ፣ ከሠራተኞች ሥነ ምግባርና አገልግሎት አሰጣጥ ጋር የሚነሱ ቅሬታዎች ዘወትር ሐሙስ ሃላፊዎች በተገኙበት የሚደመጡና ተጣርተው ምላሽ የሚሰጥባቸው ይሆናል፡፡

የተዘረጋው አሰራር ለከንቲባ ጽ/ቤት በሚስጢር ጥቆማ ከሚሰጥበት ነጻ የጥሪ ማዕከል 9977 እና የሚስጢር ሳጥን በተጨማሪ ቅሬታዎችን በአካል ለበላይ አመራር ማቅረብ ያስችላል፡፡

አሰራሩ ከፊታችን ሐሙስ ጀምሮ ወደ ተግባር እንደሚገባ የከተማ አስተዳደሩ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ለኢዜአ የላከው መረጃ ያመለክታል፡፡

ስለሆነም ከመጪው ሐሙስ ሕዳር 25 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ከገቢዎች ጋር ብቻ የተያያዙ ቅሬታዎችን አመራሩ ተቀብሎ እንደሚያስተናግድ ተጠቁሟል፡፡
#ኢዜአ

01/12/2025

የምናስበውን ፍትህ እና መዋቅራዊ ሽግግር ለማምጣት ፈጠራ እና ፍጥነት ያስፈልጋል ብሎ የመደመር መንግሥት ያምናል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)


#ኢዜአ

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የአፍሪካን ትርክት የቀየረ የይቻላል ህያው ምልክት ነው-የኢጋድ አባል ሀገራት የሚዲያ ባለሙያዎችአዲስ አበባ፤ ሕዳር 22/2018 (ኢዜአ)፡-ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳ...
01/12/2025

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የአፍሪካን ትርክት የቀየረ የይቻላል ህያው ምልክት ነው-የኢጋድ አባል ሀገራት የሚዲያ ባለሙያዎች

አዲስ አበባ፤ ሕዳር 22/2018 (ኢዜአ)፡-ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የአፍሪካን ትርክት የቀየረ የይቻላል ህያው ምልክት ነው ሲሉ የ3ኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊና ተሳታፊ የሚዲያ ባለሙያዎች ገለጹ።

በአዲስ አበባ የተካሄደው የ3ኛው የኢጋድ የሚዲያ ሽልማት አሸናፊና ተሳታፊ የሚዲያ ባለሙያዎች ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጎብኝተዋል።

በጉብኝታቸውም ታላቁ የሕዳሴ ግድብ አስድናቂ የምህንድስና ውጤት መሆኑን መመልከታቸውን ጠቅሰው፥ አፍሪካ በራሷ አቅም ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ማሳካት እንደምትችል በማሳየት ትርክት የቀየረ ፕሮጀክት ነው ብለዋል።

የኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት በልዩ ጽናትና በራሳቸው አቅም ግድቡን ማሳካታቸው ለሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ትምህርት የሰጠና የሚደንቅ ደማቅ አሻራ መሆኑን ገልጸዋል።

ግድቡ የፅናት፣ የራስን መቻል እና የአህጉራዊ ኩራትና የአንድነት ብርሃን መሆኑንም ተናግረዋል።

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሌሎች የአፍሪካ ሀገራት ሕዝባቸውን በማስተባበር ግዙፍ ፕሮጀክቶችን ማሳካት እንዳለባቸው ትልቅ ትምህርት መስጠቱንም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ሕዝብና መንግሥት ገንዘባቸውን፣ እውቀታቸውን እና ጉልበታቸውን ሳይሰስቱ ለዓመታት በመትጋት እውን ያደረጉት ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ አፍሪካ በራሷ አቅም ታላላቅ ፕሮጀክቶችን እንደምታሳካ ህያው ምስክር ነው ብለዋል።

አፍሪካውያን ሜጋ ፕሮጀክቶችን በራሳቸው አቅም ማከናወን አይችሉም የሚለውን የተዛባ ትርክት ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ሙሉ ለሙሉ መቀልበሱንም ተናግረዋል።

ኢትዮጵያ የሕዝቧን የተደመረ አቅም በመጠቀም ብሔራዊ ፕሮጀክቷን እውን አድርጋለች ያሉት የሚዲያ ባለሙያዎቹ ፥ ግድቡ አፍሪካውያን ሲተባበሩ የጋራ ህልማቸውን እውን ማድረግ እንደሚችሉ ማረጋገጫ መሆኑን ገልጸዋል።

የአፍሪካን አቅም፣ ታላቅነትና በልጆቿ ጥረት ግቧን ማሳካት እንደምትችል ህያው ማሳያ መሆኑንም አንስተዋል።

ግድቡ ቀጣናዊ ትስስርን የሚያጠናክርና የአየር ንብረት ለውጥን በመከላከል ረገድ ጉልህ አበርክቶ ያለው መሆኑንም የሚዲያ ባለሙያዎቹ ጠቅሰዋል።

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ነብያት ጌታቸው፣ ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በሀገር ውስጥና በውጭ ያሉ ኢትዮጵያውያን ዋጋ ከፍለው ያሳኩት አህጉራዊ ፕሮጀክት መሆኑን ተናግረዋል።

ለመላው አፍሪካውያን የኩራት ምንጭ የሆነው ሕዳሴ ግድብ በአህጉሪቱ አዲስ የይቻላል የለውጥ ጉዞን ያቀጣጠለ መሆኑን ገልጸዋል።

የበለጸገችና እና አንድነቷ የጠነከረ አፍሪካን እውን በማድረግ ሂደት ጉልህ ሚና እንደሚኖረውም ጠቁመዋል።

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም የበርካታ ሀገራት መሪዎች በተገኙበት በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በይፋ መመረቁ ይታወሳል።

#ኢዜአ

01/12/2025

በገበያ ማዕከላቱ ገበያውም መጋዘኑም ሙሉ ነው


#ኢዜአ

Address

Belay Zeleke
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian News Agency posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethiopian News Agency:

Share

Category

Ethiopian News Agency

Ethiopian News Agency is the sole national wire service of Ethiopia which gathers information through its 36 branch offices across the country and disseminates news and related stories as well other productions to public and commercial media across Ethiopia.

Ethiopian News Agency was established in 1942, which makes it the oldest national news agency in Africa.