Ethiopian News Agency

Ethiopian News Agency ENA is the sole national wire service of Ethiopia.
(393)

The 82 years old ENA gathers and disseminates text news, audio and video stories about local and international events to media enterprises and the public. The Ethiopian News Agency (ENA) is the sole national wire service of Ethiopia.

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት (ኢዜአ) ከ1934 ዓ.ም ጀምሮ ላለፉት 82 ዓመታት በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ውስጥ የዜና አገልግሎት ተግባር በማከናወን ላይ የሚገኝ ብቸኛው ተቋም ነው፡፡

የህዳሴ ግድብ የቅኝ ግዛት አስተሳሰብ እንዲያበቃ በማድረግ አዲስ የትብብር ምዕራፍ ከፍቷል - ስዊድናዊው ተመራማሪ እና ፕሮፌሰር አሾክ ስዌንአዲስ አበባ፤ ታህሳስ 21/2018 (ኢዜአ)፦ የታላ...
31/12/2025

የህዳሴ ግድብ የቅኝ ግዛት አስተሳሰብ እንዲያበቃ በማድረግ አዲስ የትብብር ምዕራፍ ከፍቷል - ስዊድናዊው ተመራማሪ እና ፕሮፌሰር አሾክ ስዌን

አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 21/2018 (ኢዜአ)፦ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የአባይ ወንዝ ላይ የቅኝ ግዛት አስተሳሰብ እንዲያበቃ እና አዲስ ምዕራፍ እንዲከፈት ያደረገ ፕሮጀክት መሆኑን በስዊድን ኡፕሳላ ዩኒቨርሲቲ የሰላም እና ግጭት ምርምር ክፍል ፕሮፌሰር አሾክ ስዌን ገለጹ።

ፕሮፌሰር አሾክ ስዌን ከምርምር ስራቸው ባሻገር የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ተቋም(ዩኔስኮ) የዓለም አቀፍ የውሃ ትብብር ሊቀ መንበርም ናቸው።

ፕሮፌሰሩ የህዳሴ ግድብ ተመርቆ ስራ የጀመረበት ጊዜ ኢትዮጵያ በአፍሪካ ዲፕሎማሲ ውስጥ እያደገ የመጣውን ተጽእኖ ፈጣሪነቷ ይበልጥ እያደገ መምጣቱን ሚያሳይ መሆኑን ከኢዜአ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልጸዋል።

ኢትዮጵያ በህዳሴው ግድብ ምርቃት አማካኝነት ለአፍሪካ ጠንካራ መልዕክት ማስተላለፏን ተናግረዋል።

ህዳሴ ግድብ ትልቅ የምህንድስ ስኬት እና የዲፕሎማሲ ድል መሆኑን ጠቅሰው ግንባታው ውጫዊ ጫናን በመቋቋም እና በእቅድ በመመራት ለውጤት መብቃት መቻሉን አመልክተዋል።

ኢትዮጵያ ከግብጽ እና ከአጋሮቿ የደረሰባትን ጫና በመቋቋም ግዙፉን ፕሮጀክት አጠናቃለች ሲሉ ገልጸዋል።

ህዳሴ ግድብ ኢትዮጵያውያን ከመንግስት ጋር በጋራ በመቆም እውን ያደረጉት ብሄራዊ ስኬት መሆኑንም የዩኔስኮው የዓለም አቀፍ የውሃ ትብብር ሊቀ መንበር ተናግረዋል።

ግድቡ አፍሪካ በራሷ ማድረግ ትችላለች የሚለውን እሳቤ በተግባር ገልጦ ማሳየቱን ነው ያነሱት።

የአፍሪካ ሀገራት ከውጭ ፋይናንስን ከመጠበቅ ይልቅ በራሳቸው አቅም ግዙፍ ፕሮጀክቶችን መገንባት እንደሚችሉ የሚያስተምር እንደሆነም ተናግረዋል።

ግድቡ የአባይ ወንዝ የአንድ ሀገር ብቻ ነው በሚል ለረጅም ጊዜ የቆየ የቅኝ ግዛት እሳቤ እንዲያከትም አድርጓል ነው ያሉት።

አባይ ወንዝ ለበርካታ ሀገራት ጥቅም የሚሰጥ መሆኑን የገለጹት ፕሮፌሰሩ አባይን በፍትሃዊነት እና እኩልነት መጠቀም እንደሚቻል አሳይቷልም ብለዋል።

የላይኛው ተፋሰስ ሀገራት የራሳቸውን ወንዞች ለልማት የመጠቀም መብት እንዳላቸውም አስገንዝበዋል።

ህዳሴ ግድብ ለኢትዮጵያ እድገት ቁልፍ ሚና እንደሚጫወት እና የኤሌክትሪክ ኃይል ለህዝቧ፣ ለኢንዱስትሪዋ እና ለከተሟቿ ያስፈልጋታል ሲሉ ተናግረዋል።

ግድቡ ከሀገር አልፎ ለቀጣናው ሀገራት ጠቀሜታዎች እንዳሉት ነው ያስረዱት።

ግብጽ በቀጣናው የኃይል ትብብር ተጠቃሚ መሆን ትችላለች ያሉት ፕሮፌሰሩ የውሃ ጉዳዮች የተጠናጥል እርምጃዎችን ከማድረግ ይልቅ ከተፋሰሱ ሀገራት ጋር በትብብር መስራት እንዳለባት አመልክተዋል።

ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የተፋሰሱ ሀገራት በድንበር ተሻጋሪ የውሃ ሀብቶች በጋራ የማልማት መብት እውቅና እንደሰጠ አንስተው ግብጽ ይህን ልታከብር እንደሚገባ ተናግረዋል።

በሌላ በኩል ኢትዮጵያ የባህር በር የማግኘት ጥያቄዋ ትክክለኛ እንደሆነ አንስተው የባህር በር የማግኘት መብቷን የሚያደናቅፉ እንቅስቃሴዎች ተገቢ እንዳልሆኑ ነው ያነሱት።

የተፋሰሱ ሀገራት በውሃ ሃብቶች አጠቃቀም ላይ ያሉ ጉዳዮችን በውይይት መፍታት እንዳለባቸውም አሳስበዋል።

#ኢዜአ

በተጠባቂው ጨዋታ አርሰናል አስቶንቪላን በማሸነፍ የሊጉን መሪነት አጠናከረ አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 19ኛ ሳምንት መርሃ ግብር አርሰናል አስቶንቪላ...
30/12/2025

በተጠባቂው ጨዋታ አርሰናል አስቶንቪላን በማሸነፍ የሊጉን መሪነት አጠናከረ

አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 19ኛ ሳምንት መርሃ ግብር አርሰናል አስቶንቪላን 4 ለ 1 ረቷል።

ማምሻውን በኤምሬትስ ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ጋብርኤል ማጋሌስ፣ ማርቲን ዙቢሜንዲ፣ ሊያንድሮ ትሮሳርድ እና ጋብርኤል ጄሱስ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል።

ኦሊ ዋትኪንስ ብቸኛውን ጎል ለአስቶንቪላ ከመረብ ላይ አሳርፏል።

አርሰናል በተለይም በሁለተኛው አጋማሽ የወሰደው ብልጫ ጨዋታውን እንዲያሸንፍ አስችሎታል።

በውድድር ዓመቱ 14ኛ ድሉን ያስመዘገበው የሊጉ መሪ አርሰናል ነጥቡን ወደ 45 ከፍ አድርጓል።

ከተከታዩ ማንችስተር ሲቲ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ አምስት ከፍ ማድረግ ችሏል።

ከስምንት የሊግ ተከታታይ ድሎች በኋላ ሽንፈት ያስተናገደው አስቶንቪላ በ39 ነጥብ ሶስተኛ ደረጃን ይዟል።

በሌላኛው መርሃ ግብር ማንችስተር ዩናይትድ እና ዎልቭስ አንድ አቻ ተለያይተዋል።

ጆሹዋ ዚርክዜ ለዩናይትድ፣ ላዲስላቭ ክሬጅቺ ለዎልቭስ ግቦቹን አስቆጥረዋል።

ቼልሲ እና ቦርንማውዝ ሁለት አቻ ተለያይተዋል። ኤንዞ ፈርናንዴዝ በጨዋታ እና ኮል ፓልመር በፍጹም ቅጣት ምት ለቼልሲ ግቦቹን አስቆጥረዋል።

ዴቪድ ብሩክስ እና ጀስቲን ክላይቨርት ለቦርንማውዝ ጎሎቹን ከመረብ ላይ አሳርፈዋል።

በሌሎች ጨዋታዎች ኒውካስትል ዩናይትድ በርንሌይን 3 ለ 1፣ ኤቨርተን ኖቲንግሃም ፎረስትን 2 ለ ዐ አሸንፈዋል።

ዌስትሃም ዩናይትድ እና ብራይተን ያደረጉት ጨዋታ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት ተጠናቋል።

ሴኔጋል፣ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና ቤኒን ጥሎ ማለፉን ተቀላቅለዋል አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦ በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ አራት የመጨረሻ ጨዋታዎች ዛሬ ማምሻውን ...
30/12/2025

ሴኔጋል፣ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ እና ቤኒን ጥሎ ማለፉን ተቀላቅለዋል

አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦ በ35ኛው የአፍሪካ ዋንጫ የምድብ አራት የመጨረሻ ጨዋታዎች ዛሬ ማምሻውን ተደርገዋል።

በታንጀር ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ሴኔጋል ቤኒንን 3 ለ 0 አሸንፋለች።

አብዱላዬ ሴክ እና ሃቢቡ ሞሃመዱ ዲያሎ የማሸነፊያ ግቦቹን አስቆጥረዋል።

የሴኔጋሉ ተከላካይ ካሊዱ ኩሊባሊ በ71ኛው ደቂቃ በቀይ ካርድ ከሜዳ ተሰናብቷል።

ውጤቱን ተከትሎ ሴኔጋል በሰባት ነጥብ ከምድቧ አንደኛ ደረጃን በመያዝ ጥሎ ማለፍ ገብታለች።

ቤኒን በምርጥ ሶስተኝነት ወደ ጥሎ ማለፍ ገብታለች።

በሌላኛው የምድቡ ጨዋታ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ቦትስዋናን 3 ለ 0 አሸንፋለች።

በአል መዲና ስታዲየም በተካሄደው ጨዋታ ጋኤል ካኩታ በጨዋታ እና በፍጹም ቅጣት ምት ሁለት ግቦችን ሲያስቆጥር ናትናኤል ምቡኩ ቀሪዋን ጎል ከመረብ ጋር አገናኝቷል።

ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በሰባት ነጥብ በሴኔጋል በግብ ክፍያ ተበልጣ ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ጥሎ ማለፉን ተቀላቅላለች።

ቦትስዋና ያለ ምንም ነጥብ የመጨረሻውን አራተኛ ደረጃ በመያዝ ከውድድሩ ተሰናብታለች።

https://www.youtube.com/watch?v=z5lTMrX9OFM
30/12/2025

https://www.youtube.com/watch?v=z5lTMrX9OFM

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከልማት አጋሮች ጋር በመተባበር በአዲስ አበባ ወዳጅነት ፓርክ ያዘጋጀው የጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ኤግዚቢሽንና ባዛር ቀርበው የነበሩ ....

የኢትዮጵያ ፖስታ አዳዲስ መተግበሪያዎች አሰራሩን ወደ ላቀ ምዕራፍ የሚያሸጋግሩ ናቸውአዲስ አበባ፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፖስታ አዳዲስ መተግበሪያዎች የዲጂታል ኢትዮጵያን ስ...
30/12/2025

የኢትዮጵያ ፖስታ አዳዲስ መተግበሪያዎች አሰራሩን ወደ ላቀ ምዕራፍ የሚያሸጋግሩ ናቸው

አዲስ አበባ፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ፖስታ አዳዲስ መተግበሪያዎች የዲጂታል ኢትዮጵያን ስትራቴጂ ወደ ተግባር የሚቀይሩና አሰራሩን ወደ ላቀ ምዕራፍ የሚያሸጋግሩ መሆናቸውን የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል ገለጹ።

ዛሬ “የሳጥን አልባ የመልዕክት አገልግሎት”(Virtual post Box) እና “የፖስታ ገበያ” የተሰኙ አዳዲስ መተግበሪያዎች ይፋ ተደርገዋል።

የኢንዱስትሪ ሚኒስትር መላኩ አለበል በመርሃ-ግብሩ እንደገለጹት፤ መተግበሪያዎቹ ኢትዮጵያ በዘመናዊነት ጉዞዋ ለምታስመዘግበው ውጤት ማሳያ ናቸው።

በተለይም የፖስታ ገበያ መተግበሪያ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የሚያጋጥሟቸውን የመገበያያ መሰናክሎች በማቃለል በዓለም አቀፍ ደረጃ ያላቸውን ተወዳዳሪነት ያሳድጋል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፖስታ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዳግማዊ ኃይልዬ በበኩላቸው፤ አገልግሎቱ መልዕክቶችንና ዕቃዎችን ከዓለም ጫፍ እስከ ጫፍ በማድረስ ረጅም ዘመን ያስቆጠረ መሆኑን ገልፀዋል።

ዛሬ ይፋ የሆኑት መተግበሪያዎች ደግሞ ከዘመኑ ቴክኖሎጂ ጋር በማቀናጀት ወደ ፊት የሚያራምዱ መሆናቸውን ነው ያብራሩት።

የሳጥን አልባ የፖስታ ደንበኞች የግል የፖስታ ሳጥን ቁጥር ሳይኖራቸው የራሳቸውን ስልክ ቁጥር እንደ ፖስታ አድራሻ እንዲጠቀሙ የሚያስችል መሆኑንም ገልጸዋል።

ደንበኞች የተላከላቸው ዕቃ ወይም መልዕክት መድረሱን በስልካቸው አማካኝነት ፈጣን መረጃ ያገኛሉ።

ዕቃዎችን ደንበኞች ባሉበት አድራሻ እንዲደርሷቸው በማድረግም ቀደም ሲል የነበረውን የገንዘብ ብክነትና እንግልትም የሚያስቀር መሆኑን አስታውሰዋል።

አዲሱ አሰራር ድርጅቱ ካለው ረጅም ልምድ ጋር ተዳምሮ የደንበኞችን እርካታ ከፍ እንደሚያደርገው ተገልጿል።

#ኢዜአ

30/12/2025

የኢትዮጵያን የባሕር በር ባለቤትነት ጥያቄ እንዴት ይፈጸም ወደሚል ዓለም አቀፍ ቅቡልነት ያለው የዲፕሎማሲ ስኬት ማሸጋገር ተችሏል - ሚኒስትር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ(ዶ/ር)

#ኢዜአ

በክልሉ በግብርና ምርቶች የውጪ ምንዛሪን ለማስገኘት የተከናወነው ስራ ውጤታማ ነውሀዋሳ፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና በግብርና ምርቶች የውጪ ምን...
30/12/2025

በክልሉ በግብርና ምርቶች የውጪ ምንዛሪን ለማስገኘት የተከናወነው ስራ ውጤታማ ነው

ሀዋሳ፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦ በሲዳማ ክልል የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና በግብርና ምርቶች የውጪ ምንዛሪን ለማስገኘት የተከናወነው ስራ ውጤታማ መሆኑ ተገለጸ።

የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋን ጨምሮ ሌሎችም ከፍተኛ አመራሮች በሲዳማ ክልል በሀዋሳ ዙሪያና ሸበዲኖ ወረዳዎች የሚገኙ የበጋ መስኖና የቡና ልማት ስራዎችን ጎብኝተዋል።

በጉብኝቱ ወቅት የግብርና ሚኒስትሩ አዲሱ አረጋ፥ በሁለቱ ወረዳዎች አርሶ አደሮች የምግብ ዋስትናቸውን ለማረጋገጥና ኢኮኖሚያዊ አቅማቸውን ለማሳደግ እየሰሩ ያሉት ስራ በትክክለኛው መንገድ እየተጓዙ ስለመሆኑ ማየት ችለናል ብለዋል።

ሁለቱ ወረዳዎች ቀደም ሲል ሴፍቲኔት ታቅፈው የሚደገፉ ቤተሰቦች ያሏቸው ቀበሌዎች ይበዙባቸው እንደነበር መረዳታቸውን ገልጸዋል።

ክልሉ ከፌዴራል መንግስት ጋር በመቀናጀት በመስኖ ልማት እንዲሳተፉ የመስኖ ውሀ ተቋማትን በመገንባትና የግብዓት አቅርቦት በማሟላት በግብርና ኤክስቴንሽን ስራው ድጋፍ በመደረጉ ውጤታማ መሆን እንደቻሉ መመልከታቸውን ተናግረዋል።

የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና በግብርና ምርቶች የውጪ ምንዛሪን ለማስገኘት በክልሉ የተከናወነው ስራ ውጤታማ ሆኖ እንዳገኙት አመላክተዋል።

እንደ ሀገር በተያዘው ዓመት ከአንድ ሚሊዮን ሄክታር በላይ መሬት በመጀመሪያ ዙር የበጋ መስኖ በሆርቲካልቸር በማልማት 250 ሚሊዮን ኩንታል ምርት ለመሰብሰብ ታቅዶ ወደ ስራ እንደተገባ ሚኒስትሩ ጠቅሰዋል።

በክልሉ አርሶ አደሮች ቀደም ሲል በቆሎና ሌሎች ሰብሎችን በማልማት ከሚያገኙት ጥቅም የበለጠ ጥቅል ጎመን፣ ቲማቲምና ሌሎች አትክልቶችን በማልማት ተጠቃሚ መሆን እንደቻሉም ማየታቸውን ገልጸዋል።

የሲዳማ ክልል እርሻና ተፈጥሮ ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ መምሩ ሞኬ በበኩላቸው፤ በክልሉ ያለውን አቅም በመለየት በእርሻው ዘርፍ 19 ፓኬጆችን በማዘጋጀት ወደ ስራ እንደተገባ ተናግረዋል።

ከእነዚህ ፓኬጆች ስድስቱ ቡና፣ የጓሮ አትክልትና ፍራፍሬ ልማት ላይ ትኩረት ያደረጉ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ በተያዘው ዓመት በበጋ መስኖ 80 ሺህ ሄክታር መሬት በመጀመሪያ ዙር ለማልማት ታቅዶ እስከ አሁን 54 ሺህ ሄክታር መልማቱን ገልጸዋል።

በጉብኝቱ የፌዴራል፣ የክልሉ፣ የዞንና የወረዳ አመራሮች ተሳትፈዋል።

#ኢዜአ

የመደመር መንግስት ሁሉም ዜጋ  እኩል ተሳታፊና ተጠቃሚ የሚሆንበት ሥርዓት እየገነባ  ይገኛል-ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)ባሕርዳር፤ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፡-የመደመር መንግስት ሁሉም...
30/12/2025

የመደመር መንግስት ሁሉም ዜጋ እኩል ተሳታፊና ተጠቃሚ የሚሆንበት ሥርዓት እየገነባ ይገኛል-ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)

ባሕርዳር፤ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፡-የመደመር መንግስት ሁሉም ዜጋ እኩል ተሳታፊና ተጠቃሚ የሚሆንበት ስርዓት እየገነባ ይገኛል ሲሉ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) ገለጹ።

በባሕርዳር ከተማ 123 ነጥብ ሰባት ሚሊዮን ብር በሆነ ወጪ የተገነባ የሴቶችና ህፃናት ማገገሚያ ማዕከል ዛሬ ተመርቆ ተከፍቷል።

በምረቃው ሥነ- ሥርዓት ላይ የተገኙት ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር) እንደገለጹት፤ የመደመር መንግስት ሁሉም ዜጋ እኩል ተሳታፊና ተጠቃሚ የሚሆንበት ሥርዓት እየገነባ ይገኛል።

በባሕርዳር ከተማ የተገነባው የማገገሚያ ማዕከልም የመደመር መንግስት በተለይ ለተጋላጭ የሕብረተሰብ ክፍሎች የሰጠው ትኩረት አንዱ ማሳያ ነው ብለዋል።

ማዕከሉ የተሟላ አገልግሎት እንዲሰጥ በቁሳቁስና ሌሎች የድጋፍ ዓይነቶች አስፈላጊውን እገዛ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።

በምክትል ርዕሰ መስተዳደር ማዕረግ የማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ ሙሉነሽ ደሴ (ዶ/ር) በበኩላቸው፥ ማዕከሉ ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶችና ህፃናት እንዲያገግሙ በመደገፍ ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥር ገልጸዋል።

በቀጣይም ተመሳሳይ ማዕከላትን ወደ ሌሎች ከተሞች የማስፋፋት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል።

የክልሉ ሴቶች፣ ወጣቶችና ማሕበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ብርቱካን ሲሳይ ፤ የማዕከሉ መገንባት ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ተናግረዋል።

ማዕከሉ ‎በሶስት ሺህ 200 ካሬ ሜትር ቦታ ላይ በሶስት ወራት ውስጥ የተገነባ መሆኑን የገለጹት ​​ደግሞ የክልሉ ጤና ቢሮ ኃላፊ አቶ አብዱልከሪም መንግስቱ ናቸው።

በውስጡ የመኝታ፣ የሕክምና፣ የስልጠና፣የአስተዳደርና ሌሎች አገልግሎቶች የሚሰጡ 35 ክፍሎች ያካተተ መሆኑን ተናግረዋል።

በ‎‎ተመሳሳይም በጎንደር ከተማ እየተገነባ ሲሆን ፤ በደሴና በሌሎች ከተሞች በቀጣይ ተደራሽ ለማድረግ ቢሮው ከክልሉ ሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮና የከተማ ስተዳደሮች ጋር እየሰራ ይገኛል ብለዋል።

የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ (ዶ/ር)‎ እና ሌሎች ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች በባሕርዳር ፈለገ ሕይወት ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ግቢ የተቋቋመው ሁለንተናዊ የለውጥ መሪነት ስርዓተ ፆታ እኩልነት የስልጠና ማዕከልንም ጎብኝተዋል።

#ኢዜአ

የአፈርና ውኃ ጥበቃ ስራ የአፈር ለምነትን በመጨመር ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ አስችሏልአዲስ አበባ፤ታኅሣስ 21/2018 (ኢዜአ)፡-ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ሲተገበር የቆየው ግብርና ላይ ...
30/12/2025

የአፈርና ውኃ ጥበቃ ስራ የአፈር ለምነትን በመጨመር ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ አስችሏል

አዲስ አበባ፤ታኅሣስ 21/2018 (ኢዜአ)፡-ባለፉት ዓመታት በኢትዮጵያ ሲተገበር የቆየው ግብርና ላይ የተመሰረተ የዘላቂ ልማት ጥበቃ ፕሮጀክት የአፈር ለምነትን በመጨመር ረገድ አመርቂ ውጤት ማስመዝገቡን ግብርና ሚኒስቴር ገለጸ።

በኢትዮጵያ እኤአ 2022-2025 ሲተገበር የቆየው ግብርና ላይ የተመሰረተ የዘላቂ ልማት ጥበቃ ፕሮጀክት(SCASI) አፈጻጸም ላይ ያተኮረ ውይይት ተካሂዷል።

ፕሮጀክቱ በአማራ፣ ኦሮሚያ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና ደቡብ ኢትዮጵያ ክልሎች በሚገኙ ስምንት ወረዳዎች ላይ ሲተገበር መቆየቱ ተጠቁሟል፡፡

በግብርና ሚኒስቴር የተፈጥሮ ሀብትና የአፈር ለምነት መሪ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሊሬ አብዩ በወቅቱ እንዳሉት፤ ፕሮጀክቱ የአፈርና ውሃ ጥበቃ ሥራዎችን፣ የሰብል ማፈራረቅ ዘዴንና የአርሶ አደሩን ግንዛቤ በማሳደግ ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አበርክቷል።

ይህም በተተገበረባቸው አካባቢዎች የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥና ድህነትን በመቀነስ ረገድ ውጤታማ መሆኑን ጠቁመዋል።

የዓለም የበቆሎና የስንዴ ምርምር ማዕከል የኢትዮጵያ አስተባባሪ ብርሃን አብዱልቃድር በበኩላቸው፤ማዕከሉ የአየር ንብረት ለውጥን መቋቋም የሚችሉና በአጭር ጊዜ የሚደርሱ የሰብል ዝርያዎችን በማውጣትና በማስፋፋት የድርሻውን እየተወጣ መሆኑን ገልጸዋል።

በተለይም በሜካናይዜሽንና በምርጥ ዘር አቅርቦት ላይ የተሰሩ ሥራዎች የአርሶ አደሩ ምርታማነት እንዲጨምር ማድረጋቸውን ተናግረዋል።

በተለይ የስንዴ እና የበቆሎ ዝርያን በማሻሻል ለአርሶ አደሩ ተደራሽ በማድረግ እንደ የአካባቢ ስነ-ምህዳር የሚውሉ ዝርያዎችን እያቀረበ መሆኑን ተናግረዋል።

የአማራ ክልል ግብርና ቢሮ የግብርና ኤክስቴንሽን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር ቀኛዝማች መስፍን ፕሮጀክቱ በአርሶ አደሩ ማሳ ላይ ያመጣው ለውጥ በተግባር መረጋገጡን ገልጸዋል፡፡

የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል የሰብል ልማት ጥበቃና ቴክኖሎጂ ማስፋፊያ ዳይሬክተር ፍቅሩ አቡን በበኩላቸው፥ ፕሮጀክቱ በክልሉ ሁለት ወረዳዎች መተግበሩን ገልጸው፤በቀጣይ የተገኘውን መልካም ተሞክሮ ወደ ሌሎች አካባቢዎች ለማስፋት በትኩረት እንደሚሠራ ገልጸዋል።

#ኢዜአ

በከተማዋ መጪውን የገና በዓል ምክንያት በማድረግ በቂ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች እየቀረቡ ነውአዳማ፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦በአዳማ ከተማ መጪውን የገና በዓል ምክንያት በማድረግ በ...
30/12/2025

በከተማዋ መጪውን የገና በዓል ምክንያት በማድረግ በቂ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች እየቀረቡ ነው

አዳማ፤ ታህሳስ 21/2018(ኢዜአ)፦በአዳማ ከተማ መጪውን የገና በዓል ምክንያት በማድረግ በቂ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች እየቀረቡ መሆናቸውን የከተማዋ አስተዳደር ገለጸ።

የዘንድሮውን የገና በዓል ምክንያት በማድረግ ሸማቾችንና አምራቾችን ለማገናኘት ያለመ የንግድ ትርዒትና ባዛር በአዳማ ተከፍቷል።

የአዳማ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ አቶ ማቲያስ ሰቦቃ በወቅቱ እንደገለፁት፤ በከተማዋ መጪውን የገና በዓል ምክንያት በማድረግ በቂ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች እየቀረቡ ነው።

ለዚህም የአዳማ ኢንቨስትመንት ግሩፕ የግብርናና የእንስሳት ተዋፅኦ ምርቶች የዋጋ ንረትና ገበያ ማረጋጋት ላይ አበረታች ስራ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

ለዝርዝሩ 👉 https://www.ena.et/web/amh/w/amh_8027906

Address

Belay Zeleke
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Ethiopian News Agency posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Ethiopian News Agency:

Share

Category

Ethiopian News Agency

Ethiopian News Agency is the sole national wire service of Ethiopia which gathers information through its 36 branch offices across the country and disseminates news and related stories as well other productions to public and commercial media across Ethiopia.

Ethiopian News Agency was established in 1942, which makes it the oldest national news agency in Africa.