
17/09/2025
በጠ ^ላት ፍቅር የመለከፍ አባዜ
~
በስነ-ልቦና ጥናት ዘርፍ አንዳንድ ግለሰቦች ወይም ቡድኖች ላይ የሚታይ ስቶክሆልም ሲንድረም (Stockholm Syndrome) የሚሰኝ አንድ እጅግ አስገራሚ የሆነ ክስተት አለ። ታጋች፣ ተበዳይ ወይም ተጠቂ የሆነ ሰው ወይም ቡድን፣ በጠላፊው ወይም በጠ^ ላቱ ላይ የአዘኔታ፣ የመውደድ ወይም የታማኝነት ወይም የተባባሪነት ስሜት የሚያዳብርበት ሁኔታ ነው።
የቃሉ መነሻ በ1973 ዓ. ል. በስዊድን፣ ስቶክሆልም ከተማ ውስጥ ከተፈጸመ የባንክ ዘረፋ ጋር የተያያዘ ነው። ዘራፊው ቡድን በባንኩ ውስጥ ያሉ ሰራተኞችን ለስድስት ቀናት ያህል አግቶ ያቆያል። ከታጋቾቹ መካከል አንዳንዶቹ ከጊዜ በኋላ ከጠላፊው ቡድን ጋር የተለየ የመቅረብ ፍላጎት አዳብረው ተገኝተዋል። ከታገቱበት ሲለቀቁም እንኳ ጠላፊው ቡድን ላይ ከመመስከር ይልቅ ጭራሽ ለመከላከል ነበር የሞከሩት።
የፈለገ ማመሀኛ ትንታኔዎች ቢኖሩ እንኳ "አምላካችንን ሰቅለዋል" የሚል እምነት ያለው አካል በዚህ ልክ በ iሁድ ፍቅር ሲወድቅ ማየት የሚገርም ነው።