Yohannes Eshetu

Yohannes Eshetu በዚህ ገፅ ላይ መንፈሳዊ ትምህርቶችና የቴክኖሎጂ ዕውቀቶች ይተላለፋሉ።

👉 ሰሉስ የብሉይ ኪዳን ትርጓሜ አርብ ደግሞ ቅኔ ዘአርብ በሚል ስያሜ የቅኔ ቀን ነው።

27/11/2025

ወደሰቶ ወአእኮተቶ ቅድመ ገጸ ኩሉ ጉባኤ
አፈ ወርቅ እንዘ ትብል ጊዜያተ ክልኤ

ነቢዩ ዳንኤል በባቢሎን ምርኮ በአናብስት ጉድጓድ በተጣለ ጊዜ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል በኢየሩሳሌም የነበረውን ነቢይ ዕንባቆምን "ይህንን ምግብ በባቢሎን በአናብስት ጉድጓድ ላለው ለዳንኤል ውሰድ...
21/11/2025

ነቢዩ ዳንኤል በባቢሎን ምርኮ በአናብስት ጉድጓድ በተጣለ ጊዜ መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል በኢየሩሳሌም የነበረውን ነቢይ ዕንባቆምን "ይህንን ምግብ በባቢሎን በአናብስት ጉድጓድ ላለው ለዳንኤል ውሰድለት" አለው።

ነቢዩ ዕንባቆምም "ባቢሎንን አላውቃትም" ብሎ መለሰለት። ገናናው መልአክ ቅዱስ ሚካኤልም ከጸጉሩ ዘለላ አንዲቷን ይዞ ዳንኤል ካለበት ጉድጓድ አደረሰው። እርሱም የጉድጓዱን መክደኛ ሳይከፍት ገብቶ መግቦት ተመልሷል። በዚህ ጊዜ ነቢዩ ዳንኤል "እነሆ በእግዚአብሔር ፊት የሚቆመው ረዳታችሁ ሚካኤል ይለምንላችሁ" ብሎ ተናግሯል።

ዳግመኛም ባለ ራዕዩ ወልደ ነጎድጓድ ዮሐንስ ቅዱስ ሚካኤል አውሬውን ከሰማይ ወደ ጥልቁ እንደጣለው የተናገረውን ደራሲ ባማረው ቃሉ ጠቅሶታል።

ኦርቶዶክሳዊት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን መጽሐፍ ቅዱስን መሰረት አድርጋ መላእክትን ታከብራለች። በዓላቸውንም ትዘክራለች።

አስቀድሞ እስራኤልን ነጻ ያወጣ ፣ ኋላም ዳንኤልን በግበ አናብስት የመገበ ፣ ለሚጠሩት ሁሉ ፈጥኖ የሚደርሰው ቅዱስ ሚካኤል እኛንም እንደሚያድነን መጽሐፍ ቅዱስን መሰረት አድርገን እናምናለን።

በከመ ይቤ ነቢይ ግበ አናብስት ዘቦአ
በዕደ ዕንባቆም ዘበልአ
መልአክክሙ ሚካኤል እንዘ ይብል አይድአ
ወዮሐንስ ይቤ መጽሐፈ አእምሮ ዘመልአ
ሚካኤል አውደቀ አርዌ ስሱአ

መድኃኔዓለም ክርስቶስ ኢተሀበኒ ለባዕድአስተበቁአከ በልሳነ ሥጋ ክቡድእስመ አልቦ ዘእንበሌከ በቋዒ ዘመድ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ሆይ! ለባዕድ እንዳትሰጠኝ በከበደ የሥጋ አንደበት እለምንሀለው።...
05/11/2025

መድኃኔዓለም ክርስቶስ ኢተሀበኒ ለባዕድ
አስተበቁአከ በልሳነ ሥጋ ክቡድ
እስመ አልቦ ዘእንበሌከ በቋዒ ዘመድ

መድኃኔዓለም ክርስቶስ ሆይ! ለባዕድ እንዳትሰጠኝ በከበደ የሥጋ አንደበት እለምንሀለው። ካንተ በቀር የሚበጅ ዘመድ የለምና።

የፍጥረት ሁሉ ቀዳሚ አዳም የመዳን መንገድ ሩቅ መስሎት በማዕከለ ሲዖል ሲኖር ከገዛ ስጋው የተወለደ ክርስቶስ ኢየሱስ ነጻነትን ሰበከለት።ጨለማን ዕለት ዕለት ሲያይ የነበረ የሰው ፍጥረት ሁሉ ...
07/10/2025

የፍጥረት ሁሉ ቀዳሚ አዳም የመዳን መንገድ ሩቅ መስሎት በማዕከለ ሲዖል ሲኖር ከገዛ ስጋው የተወለደ ክርስቶስ ኢየሱስ ነጻነትን ሰበከለት።

ጨለማን ዕለት ዕለት ሲያይ የነበረ የሰው ፍጥረት ሁሉ በክርስቶስ ኢየሱስ ድንቅ የሆነውን የገነትን ብርሃን ተመለከተ። በመንጸፈ ደይን ወድቆ የነበረ አዳማዊ ባህርይም የቀደመ ክብሩን አገኘ።

ሎቱ ስብሐት ለዘተሰቅለ መልዕልተ ዕጽ ፣ ወአድኃነነ እምዘሲዖል ዳኅጽ

ክብርና ምስጋና ለመድኃኔ ዓለማት ክርስቶስ

29/09/2025

ባለ መልካም ብስራቱ ቅዱስ ገብርኤል የጸና እምነትን አስተምሮናል። የጸና እምነት ዋጋ እንደሚያሰጥም አሳይቶናል። ድንግልን ለማብሰር የተላከው በጸና እምነቱ ነውና!

26/09/2025

የመስቀልን ጎዳና ተከትለን ስንጓዝ ክርስቶስን ከላይ ፣ እናቱ ድንግልንና በዮሐንስ የተመሰሉ ቅዱሳንን በቀራንዮ በተመሰለች ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እናገኛቸዋለን።

ልሳነ ግእዝየአራተኛ ዓመት የኮምፒውተር ሳይንስ ተማሪ ሳለሁ በወቅቱ Android የተባለው የሲስተም መምሪያ  የገነነበት ጊዜ ነበር። ታዲያ የመጨረሻ ዓመት ፕሮጀክት ምን ልስራ እያልኩ ሳስብ ...
18/09/2025

ልሳነ ግእዝ

የአራተኛ ዓመት የኮምፒውተር ሳይንስ ተማሪ ሳለሁ በወቅቱ Android የተባለው የሲስተም መምሪያ የገነነበት ጊዜ ነበር። ታዲያ የመጨረሻ ዓመት ፕሮጀክት ምን ልስራ እያልኩ ሳስብ ለምን የግእዝ መዝገበ ቃላት አልሰራም? በማለት ጽሁፌን አስገባው።

ከዚያም ጽሁፌን በማቀርብበት ጊዜ አንዱ Examiner የሰጠኝ ሃሳብ እስካሁን ድረስ ይከነክነኛል። "ግእዝ እኮ የሞተ ቋንቋ ነው። እዚህ ላይ ጊዜ ከሚጠፋ ለሌላ ቋንቋ ለምን አይሰራም?" ሲለኝ ዝምታን መረጥኩ። በዚያ ጊዜ ከExaminer ጋር መመላለስ ያስመታል።

መልሱን ግን አማካሪዬ በጥሩ ሁኔታ አብራርቶ መለሰለት። Even If it is dead, we have to work on it for it's revival ሲል ልቤ በደስታ ሲሞቅ ይሰማኝ ነበር። አሁን ድረስ አማካሪዬን በጣም ከልቤ አከብረዋለሁ። Thanks Dear Mohammed Yusuf!

ያ ፕሮጀክት በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ከ15 ዩኒቨርስቲዎች ጋር በተደረገው የጥናት ውድድር ላይ የዋንጫ አሸናፊ ነበር። እኛም በA+ ደመደምነው።

አሁን ላይ ይህ ሃሳብ ሲነሳ ለግእዝ የሚወግኑ ሰዎች አስተሳሰብ በጣም ይገርመኛል። እነዚህ ሰዎች በደፈናው "ግእዝ ለምን ተነካብን?" በሚል ምናባዊ አስተሳሰብ ይመልሳሉ እንጂ ግእዝን ለማወቅ እንኳን ፍላጎት የላቸውም።

በግእዝ ቋንቋ ማዜም ፣ ማንበብ ፣ መገልገል የግእዝ ቋንቋ አዋቂነትን አይገልጽም። በተለምዶ የቅኔ ትምህርት የምንለው በመደበኛነት የሰዋስወ ግእዝ ትምህርት ነው። የተዘዋወረ ቀለም ነው። ቅኔ በግእዝ ቋንቋ ውስጥ ያለ አንድ ክፍል ነው እንጂ የግእዝ ቋንቋን በሙሉ የሚገልጽ አይደለም። የግእዝ ቋንቋን በአግባቡ ለመማር ቅኔ ቤት መግባት ያስፈልጋል።

ችግሩ ግን ያለው የአብዛኛው ተማሪ ፍላጎት እና እቅድ ቅኔ መቀኘት ነው። የትምህርቱ ዋነኛ ዓላማ ግን የግእዝን ቋንቋ ጠንቅቆ ማወቅ እና መረዳት ነው። ከእያንዳንዱ ቅኔ ዘረፋ በፊት የግስ እርባታ (Verb Generation with Tags) ከዘረፋው በኋላ ደግሞ የአገባብ ሙያ (Grammatical Feature) የሚሰጠው የግእዝን ቋንቋ ጠንቅቆ ለማወቅ ነው። መምህሩም መርቆ ሲሸኘው ቅኔ ተቀኝቷል በማለት ብቻ አይደለም። ቅኔ ከነአገባቡ ከነእርባ ቅምሩ ፣ ነገረ ጸያፍ ከነአዋጁ ጠንቅቆ ተምሯል ብሎ ነው እንጂ።

አሁን አሁን ግን የመጨረሻ ግቡ ተዘንግቷል። አባቶቻችን ትምህርቱ እንዳያሰለች በቅኔ በኩል ወደ ግእዝ ቤት እንድንገባ መንገዱን ሰርተውልናል። እኛ ግን ወደ ቤቱ ሳንገባ መንገዱ ላይ ቀርተናል።

መፍትሄ

ሞቷል ስንባል አልሞተም እያልን በተራ አጀንዳ ከምንሟገት አለመሞቱን ለምን አናሳይም? ግእዝን እንማረው ፣ እንቅረበው ፣ እንወቀው። Smart ከሆንን ደግሞ ልጆቻችን ላይ እንስራ። የኔታ ጋር ሄደው "ሀ ግእዝ ፣ ሁ ካዕብ" ይበሉ። መልእክተ ዮሐንስ ያንብቡ። ዳዊት ይድገሙ። ወንጌል ይስሙ። ቅኔ ይቁጠሩ ፣ ዜማውን ያዚሙት ፤ ይህ ከሆነ ግእዝ አደገ ተመነደገ ማለት እኮ ነው።

ግእዝ እንማርና ብሉይና ሐዲስን በጣዕመ ልሳን እናንብብ ፣ የጥበብ መጻሕፍትን እንጥገብ ፣ የአለቃ ተክለ ጽዮንን ፣ የአለቃ አድማሱን ፣ የነ ቄሰ ገበዝ ውብሸትን ቅኔ ሰምተን ይበል እንበል።

በመጨረሻም

አለቃ ተክለ ጽዮን ሊቅ ነበሩ። ቅኔውን በጽቡረ ሕሊና ይፈጥሩታል። የአራቱ ጉባኤያት መጻሕፍትን ወስነዋል። እውቀት በቃኝ አይሉም ነበር። ታዲያ አብዛኛው የግእዝ መጻሕፍት የተተርጎሙት ከአረብኛው ነበርና ያንን ቋንቋ ለመማር ከሼሆች ዘንድ እየሄዱ አረብኛውን ጠንቅቀውት ነበር። ትልቁ ሊቅ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌም አረብኛውን ፣ ዕብራይስጡን ፣ ጽርዑን አጥንተዋል። ቋንቋ ያራቅቃል እንጂ አያጣላም።

15/09/2025

በእንተ ግእዝ!
አላከበርነውም። የሆነ አካል ሲንቅብን ግን ይሰማናል። እኛ ያላከበርነውን ማን ያክብርልን?

ሊቃውንቲሃ ለሳሌም እንዘ ንገብር ኩርጓኔዘካርያስሃ ንዜከር በፍና ዘካርያስ ቅኔ
05/09/2025

ሊቃውንቲሃ ለሳሌም እንዘ ንገብር ኩርጓኔ
ዘካርያስሃ ንዜከር በፍና ዘካርያስ ቅኔ

በአንድ ወቅት ወንድሜ Mesfen Tekeste ቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ የአንድ ዲፓርትመንት ኃላፊ ይፈልጉሃል ብሎኝ እኔም ቀጠሮ ሳላከብር በሌላኛው ቀን ከዚህ መልካም ሰው ጋር ተገናኘን።ሀሳባ...
31/08/2025

በአንድ ወቅት ወንድሜ Mesfen Tekeste ቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ የአንድ ዲፓርትመንት ኃላፊ ይፈልጉሃል ብሎኝ እኔም ቀጠሮ ሳላከብር በሌላኛው ቀን ከዚህ መልካም ሰው ጋር ተገናኘን።

ሀሳባችን የጥንታውያን መጻሕፍት (Manuscript) ቅጅዎች በዲጂታል መልኩ ተደራሽ መሆን የሚችሉበትን ሂደት ምን ይመስላል የሚል ነበር። እኔም Digital Manuscript Library መስራት እንደሚቻል እና ለቅድመ ዝግጅቱ የሚያስፈልጉ Technical ሀሳቦችን አቀረብኩለት።

በውይይታችን የተረዳሁት ለቤተ ክርስቲያን ያለውን ቀናዒነት ፣ መልካምነት ፣ ከግል ጥቅም ይልቅ ለቤተ ክርስቲያን ማድላት የሚታዩበት ደግ ሰው መሆኑን ነው። ዕረፍቱ የማይታመን ነበር። ቤተ ክርሰቲያን ትልቅ ሰው አጥታለች።

በቀብሩ ዕለት ብጹዕ አባታችን አቡነ ሕርያቆስ መልካም ውሳኔን እንደ ሀገረ ስብከት ለቤተሰቦቹ ማሳለፋቸውን እየሰማሁ ልጆቹም ገና ንዑሳን መሆናቸውን እየተመለከትኩ ውስጤ ይህንን መወድስ እንደ ነቅዕ እያፈሰሰ ነበር።

ምናለ አምላክ ልጆች ሳያድጉ አባቶችን ባይወስድ ብዬ እሰጥ አገባ ገባሁ። አባት የተለየው ልጅ ህይወት ፤ የመስመር ለውጥ ይኖረዋል። በብዙ ነገር ሊከፋ ይችላል። ብቻ ከባድ ነው።

መወድስ ዘዮሐንስ በእንተ እኁ ተክለ ጻድቅ

ልበ ወልድ የሀዝን በሞተ አቡሁ
ወበድንጋጼ ይነብር እስከ ተሀልፍ ህይወቱ
ዜና ወላዲ የዋህ ለዘሀተተ እምጥንቱ
ከመ ከመ ያዕቆብ ወደቂቁ
እስመ አብ ለዘወለዶሙ ስርጋዌ ውእቱ
ወልደሂ እምዘወለደ
ዘእንበለ ጊዜ ኢይፍልጥ ለአማኑኤል ድልወቱ

ነገርነሰ በቅድመ ወልድ ከመ ዕጸ ባቢሎን ከንቱ
እስመ አቡሁ ኢይመውት ወህያው በመለኮቱ
ወመፍትው ይዘከር ወልድ ዘእንበለ አብ ባህቲቱ
በስዒለ ማይ ወህብስት ከመ አልሀቀቶ ወላዲቱ

ዕረፍተ ነፍስን ለወንድማችን ፣ ለቤተሰቦቹ መጽናናትን ያድልልን!

02/08/2025

ወነአምን በአሐቲ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንተ ላእለ ኩሉ ጉባኤ ዘሐዋርያት

26/07/2025

በእግዚአብሔር ፊት ለሚቆመው ቅዱስ ገብርኤል የልባችንን መሻት እንነግረዋለን። እርሱም ይፈጽምልናል። ለእግዚአብሔር የቀረበ ደግ መልአክ ነውና።

ከቅዱስ ገብርኤል ፣ ከቂርቆስና ኢየሉጣ በረከት ይክፈለን።

Address

Addis Ababa

Telephone

+251921625794

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Yohannes Eshetu posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Yohannes Eshetu:

Share