Yohannes Eshetu

Yohannes Eshetu በዚህ ገፅ ላይ መንፈሳዊ ትምህርቶችና የቴክኖሎጂ ዕውቀቶች ይተላለፋሉ።

👉 ሰሉስ የብሉይ ኪዳን ትርጓሜ አርብ ደግሞ ቅኔ ዘአርብ በሚል ስያሜ የቅኔ ቀን ነው።

ደግ መልአክ ነው። የለመኑትን ፈጥኖ ይሰማል። በጭንቅ ጊዜ ደራሽ ነው። ሚካኤል የሚለው ቃል ከነፍሳችን ጋር ተሳስሯል። ረዳኤ ምንዱባን የተሰኘ ፣ አኃዜ መንጦላእት ፣ ቅሩበ እግዚአብሔር ቅዱስ...
19/06/2026

ደግ መልአክ ነው። የለመኑትን ፈጥኖ ይሰማል። በጭንቅ ጊዜ ደራሽ ነው። ሚካኤል የሚለው ቃል ከነፍሳችን ጋር ተሳስሯል። ረዳኤ ምንዱባን የተሰኘ ፣ አኃዜ መንጦላእት ፣ ቅሩበ እግዚአብሔር ቅዱስ ሚካኤል በህይወታችን ሁሉ ይቅደምልን።

ያሬድ ካህን ተላዌ ጳውሎስ ሐዋርያብርሃነ ዓለም የተሰኘ ቅዱስ ጳውሎስ ወንጌልን በዓለም ዙርያ ለሚገኙ ክርስቲያኖች በቃልም፣ በግብርም ፣ በመጽሐፍም አምልቶ አስተምሯል። ቅድስት ቤተ ክርስቲያን...
19/05/2026

ያሬድ ካህን ተላዌ ጳውሎስ ሐዋርያ

ብርሃነ ዓለም የተሰኘ ቅዱስ ጳውሎስ ወንጌልን በዓለም ዙርያ ለሚገኙ ክርስቲያኖች በቃልም፣ በግብርም ፣ በመጽሐፍም አምልቶ አስተምሯል። ቅድስት ቤተ ክርስቲያንም ብርሃነ ዓለም (የዓለም ብርሃን) እያለች ትጠራዋለች።

ቅዱስ ያሬድም እንደ ሐዋርያው ጳውሎስ ወንጌልን በምልዓት ያስተማረ የቤተ ክርስቲያን ብርሃን ነው። የሰማያዊ መንግስት ወንጌልንም ከግብር ፣ ከቃልና ከድርሰት ባሻገር በሰማያዊ ዜማ የገለጠ ቅዱስ ነው።

ዜማው ዝርው ያልሆነ ፣ ህግ የተወሰነለት ፣ ለነፍስ የተመቸና ሰማያዊቷን ዓለም በተመስጦ የሚያሳይ ነው። ከዚሁ ሁሉ መንፈሳዊ ግብሩ በላይ ግን ቅዱስ ያሬድ የበቃ መናኝ ፣ ሞትን ያልቀመሰ ስውር ነው።

በረከቱ አይለየን!

ታናሽ ወንድማችን ዲያቆን ጥበቡ ተፈራ ከልጅነቱ ጀምሮ ለማኅደረ ስብሐት የተሰጠ ወንድማችን ነው። ዛሬ የህይወቱን ትልቁን ምዕራፍ "ብእሲት ቡርክት" ብሎ ጀምሯል።ሲቀድስ የሚያምርበት ፣ ሲዘምር...
18/05/2026

ታናሽ ወንድማችን ዲያቆን ጥበቡ ተፈራ ከልጅነቱ ጀምሮ ለማኅደረ ስብሐት የተሰጠ ወንድማችን ነው። ዛሬ የህይወቱን ትልቁን ምዕራፍ "ብእሲት ቡርክት" ብሎ ጀምሯል።

ሲቀድስ የሚያምርበት ፣ ሲዘምር የሚሰማ ቤተ ክርስቲያንን ከልብ ያለመሰልቸት የሚያገለግል ወንድም ነው።

ከጥበብ ጎዳና ሳይወጣ በጥበብ ይኖር ዘንድ ምኞታችን ነው።

1. ጉባኤ ቃና

መርዓተ መርዓዊ ቡርክተ ይዌድሳ አንስተ ዐረብ ወሳባ
እስመ ቅድመ ኩሉ ተከስተ ዘተሰወረ ጥበባ

ማኅደረ ስብሐት ኮነት ደብረ ቀርሜሎስ አሐቲ
ነቢየ ተልዕሎ ኤልያስ እስመ አስተርአየ ባቲ

መርዓተ ጥበብ ቡርክት ለዘነሐትት ሐተታ
እስመ በጥበብ ሐነጸት መሰረተ ጽኑዕ ቤታ

2. ዘአምላኪየ

ዘመነ ብህታዌ ክረምት ጸዋሬ ዘኤልያስ ጻማ
አመ ገብአ ወአመ ተመይጠ በዘጸንአ ግርማ
ዮርዳኖስ ለአቤል ወለዳንኤል አርሴማ

3. መወድስ

ብእሲ ኢይድክም በዓለመ ስጋ
ሥላሴ ፈጠሩ በዘኢየሀልቅ ጥበቦሙ
ዘትረድኦ ቡርክተ እንዘ ትጼዋእ በስሙ
ወበህገ ፍጥረት ዘተነግረ
ብዙኃን እንዘ የሀስሱ ብእሲተ ደክሙ
እስከነ ይረክቡ ተምኔቶሙ
እመኒ ይረውጽ ሠረገላ ዘመን ዕድሜሆሙ

መርዓትሰ አመ ታንሶሱ በለቢሰ ጥበብ ቀዲሙ
እምውሳጤ ልቦሙ ያነክሩ እለ ነጸርዋ በዓይኖሙ
ወበልሳና ጥዑም ለአዝማዲሃ ኩሎሙ
ዘይሴኒ ጥበብየ እፎኑመ ትቤሎሙ

ሰላም እብል ለገጽክሙ መደንግፅእምራእየ እሳት ብቁጽዕሩያነ አካል ሥላሴ እንበለ ኅፀፅአብርሃም ነጸረክሙ በታሕተ መንበሩ ዘዕፅአመ ተፋለሰ ወወፅአ እምግብፅሥሉስ ቅዱስ ሆይከሚነድ ፍም እሳት ይል...
15/05/2026

ሰላም እብል ለገጽክሙ መደንግፅ
እምራእየ እሳት ብቁጽ
ዕሩያነ አካል ሥላሴ እንበለ ኅፀፅ
አብርሃም ነጸረክሙ በታሕተ መንበሩ ዘዕፅ
አመ ተፋለሰ ወወፅአ እምግብፅ

ሥሉስ ቅዱስ ሆይ
ከሚነድ ፍም እሳት ይልቅ ለሚያስደነግጠው ፊታችሁ ሰላም እላለሁ!

ያለመጉደል በአካል የምትተካከሉ ሥላሴ ሆይ አብርሃም ከግብጽ ምድር በወጣ ጊዜ ከዛፍ ስር ባለው መቀመጫው ሆኖ ተመለከታችሁ።

የሥላሴ አጋዥነት አይለየን!

ጸሎተ ሳዊሮስ - የሳዊሮስ ጸሎትማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታን ያነጹት ቀዳማዊ ብጹዕ አቡነ ሳዊሮስ ጳጳስ ዘደቡበ ኢትዮጵያ ፤ ደብሯን ካነጹ በኋላ እመቤታችንን "የዘወትር ጸሎቴ ከዚህች ደብር...
09/05/2026

ጸሎተ ሳዊሮስ - የሳዊሮስ ጸሎት

ማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታን ያነጹት ቀዳማዊ ብጹዕ አቡነ ሳዊሮስ ጳጳስ ዘደቡበ ኢትዮጵያ ፤ ደብሯን ካነጹ በኋላ እመቤታችንን "የዘወትር ጸሎቴ ከዚህች ደብር ሰው እንዳይጠፋ ነው" እያሉ ይለምኗት ነበር።

ታዲያ ጸሎታቸው ሰምሮ ፤ እንኳን በዓመታዊ የልደት በዓሏ ቀርቶ በዘወትር እንኳን ብዙ ምዕመናን ከደጇ ይከትማሉ።

በተድባበ ማርያም ካለችውና "ኦሆ በሃሊት" ከተሰኘችው የእመቤታችን ምስል አንድ የሆነችው የማኅደረ ስብሐቷ "ኦሆ በሃሊት ፤ እሺ ባይ" ምስል ስር የብዙ ምእመናን እንባ ታብሷል ፣ ጸሎታቸው ተሰምቷል ፣ የልባቸው መሻትም ተፈጽሟል።

ዛሬም በዕለተ ቀኗ እልፍ አእላፍ ምእመናንን ቤቷን ከበው ሲታዩ ለኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ሃይማኖት ጽናት መሆኗን ያሳያል።

መጋቤ ብሉይ ዮሐንስ እሸቱ

ከጥንታውያኑ ማኅደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያምና ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም አብያተ ክርስቲያን

ማኅደረ ስብሐትየምስጋና ቦታ በሆነችው በጥንታዊቷ ደብራችን በማኀደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የልደቷን መታሰቢያ በዓል በኅብረት እናከብራለን።
08/05/2026

ማኅደረ ስብሐት

የምስጋና ቦታ በሆነችው በጥንታዊቷ ደብራችን በማኀደረ ስብሐት ቅድስት ልደታ ለማርያም የእናታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የልደቷን መታሰቢያ በዓል በኅብረት እናከብራለን።

ጨለማው ይገፈፍ ዘንድ ብርሃን ያስፈልጋል። ብርሃን እውቀት ነው። ዓለም በጨለማ ተይዞ በነበረበት ዘመን ፍጥረቱ ሁሉ ብርሃንን ይሻ ነበር።ብርሃን መገኛ አለው። ለዚህ ስጋዊ ዓለም ፀሐይ ፣ ጨረ...
07/05/2026

ጨለማው ይገፈፍ ዘንድ ብርሃን ያስፈልጋል። ብርሃን እውቀት ነው። ዓለም በጨለማ ተይዞ በነበረበት ዘመን ፍጥረቱ ሁሉ ብርሃንን ይሻ ነበር።

ብርሃን መገኛ አለው። ለዚህ ስጋዊ ዓለም ፀሐይ ፣ ጨረቃና ከዋክብት ብርሃንን ይመግቡታል። ጨለማው መራቁን የምናውቀው ደማቋ ፀሐይ ከምስራቅ ስትወጣ ነው። ምስራቅ የፀሐይ መውጫ ናት።

በኃጢዓት ጨለማ የተያዘ ህዝብ የድኅነትን ብርሃን ይመለከት ዘንድ የብርሃን መውጫ ምስራቅን ይሻል።

ምስራቀ ምስራቃት ማርያም ሙጻአ ፀሐይ

ፀሐይ ጌታን ፣ ብርሃን ክርስቶስን የምታስገኝልን ምስራቂቱ ቅድስት ድንግል ማርያም የተወለደችበት ዕለት የድኅነታችን መጀመርያ ነው።

ጨለማን ለማንሻ ለኛ ፣ የብርሃን ጌታችን መገኛ የምትሆን ድንግል ማርያም ተወለደችልን።

ልባችንን እናንጥፍለትክርስቶስ ኢየሩሳሌምን አይቶ አለቀሰላት። በአህያይቱ ላይ ተጭኖ ወደ ከተማዋ ሲገባም ህዝቡ ሁሉ ልብሶቻቸውን አነጠፉለት።ያ ኩነት ካለፈ 1985 ዓመታት አልፈዋል። አሁን ላ...
04/04/2026

ልባችንን እናንጥፍለት

ክርስቶስ ኢየሩሳሌምን አይቶ አለቀሰላት። በአህያይቱ ላይ ተጭኖ ወደ ከተማዋ ሲገባም ህዝቡ ሁሉ ልብሶቻቸውን አነጠፉለት።

ያ ኩነት ካለፈ 1985 ዓመታት አልፈዋል። አሁን ላይ ክርስቶስ ልብሳችንን ሳይሆን ልባችንን እንድንዘረጋለት ይሻል። ዓለም ያሸነፈችው ፣ ኃጢዓት የወረሰው ፣ እርሱንም የዘነጋው ልባችን በንስሐ መንገድ ላይ ይነጠፍ ዘንድ የተገባ ነው።

ያን ጊዜ ሆሳዕና ብለን እርሱን ለማመስገን የበቃን እንሆናለን። መዳናችን በእርሱ ተደርጓልና።

ሆሳዕና ለወልደ ዳዊት

02/04/2026

ብዙ የማናውቃቸው ነገሮች እንዳሉ ስንረዳ እንደ ኒቆዲሞስ እውነትን ፍለጋ በሌሊት እንወጣለን።

ኢትዮጵያ ለዓለም ምርምርና ለጥበብ እድገት መሠረት ሊሆኑ የሚችሉ በርካታ የትርጓሜ፣ የቁጥርና የፍልስፍና መጻሕፍት ባለቤት ናት።በተለይም የቋንቋዎቻችን ምሥጢርና ጥልቀት ለምዕራቡ ዓለም ቢገለጥ...
16/02/2026

ኢትዮጵያ ለዓለም ምርምርና ለጥበብ እድገት መሠረት ሊሆኑ የሚችሉ በርካታ የትርጓሜ፣ የቁጥርና የፍልስፍና መጻሕፍት ባለቤት ናት።

በተለይም የቋንቋዎቻችን ምሥጢርና ጥልቀት ለምዕራቡ ዓለም ቢገለጥ ትልቅ አድናቆትንና ምርምርን እንደሚጭር ጥርጥር የለውም።

​የእነዚህን የጥበብ መዛግብት በር ለመክፈትና ለዓለም ማኅበረሰብ ተደራሽ ለማድረግ በኩረ ፍስሐ ቀሲስ ዶክተር ኃይለ ኢየሱስ አስናቀ አርአያ የሚሆን ተግባር አከናውነዋል። የአቻ ትርጉም ሥራዎቻቸው በተለይም፦ የእመቤታችንን ውዳሴና ቅዳሴ ትርጉም፣
​ውስብስብና ጥልቅ የሆነውን የባሕረ ሐሳብ መጽሐፍ ፣ ​እና ሌሎች ልዩ ልዩ ጥናታዊ ሥራዎችን ለዓለም አበርክተዋል።

​በመሆኑም፣ በተለይ በውጭው ዓለም የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ደቀ መዛሙርት፣ እነዚህን መጻሕፍት በመግዛትና በማንበብ ለታሪካችሁና ለማንነታችሁ ክብር እንድትሰጡ፣ ዕውቀቱንም ለሌላው እንድታስተዋውቁ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

መወድስ

ለወለተ ባዕል አብርሃም ምድረ አሜሪካ
አምኃ ትርጓሜ አቅረበ ኃይለ ኢየሱስ ኬንያ
አምጣነ ኩሎ ትስህብ በዘይሴኒ ላህያ
ወላቲ ነበበ ቃለ ውዳሴ
ከመ ትስማእ ቃለ ውዳሴሁ እስመ ቀርበት ነያ
እምድኅረ አምጽአ ወአቅረበ
መካልየ ወርቅ ኃምሰ እምነ ርኅቅት ኢትዮጵያ

ከሰተሂ በትምህርቱ ልበ አሜሪካ ልድያ
ዘይሰብክ ዓለማተ ኃይለ ኢየሱስ ሐዋርያ
ወለኁልቆ ዘመን መርዓት ዘድሜጥሮስ አእበያ
ወሰዳ ኀበ ሀለወ ኃይለ ኢየሱስ ዘተመነያ

https://www.facebook.com/ZIMAMPURIFIEDGOLD

Address

Addis Ababa

Telephone

+251921625794

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Yohannes Eshetu posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Yohannes Eshetu:

Share