AMN-Addis Media Network

AMN-Addis Media Network This is the official page of AMN- Addis Media Network ‘Voice of generation.’ stay connected🤳

ወንዞችና የወንዝ ዳርቻዎችን የበከሉ ድርጅቶችና ግለሰቦች 2 ሚሊዮን 592 ሺህ ብር ተቀጡAMN  ጥቅምት 5/2018የአዲስ አበባ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በወንዞችና የወንዝ ዳርቻ...
15/10/2025

ወንዞችና የወንዝ ዳርቻዎችን የበከሉ ድርጅቶችና ግለሰቦች 2 ሚሊዮን 592 ሺህ ብር ተቀጡ

AMN ጥቅምት 5/2018

የአዲስ አበባ አስተዳደር ደንብ ማስከበር ባለስልጣን በወንዞችና የወንዝ ዳርቻ በካይ ቆሻሻና ኬሚካል የለቀቁ ድርጅቶችና ግለሰቦችን መቅጣቱ አስታወቀ።

በንፋስ ስልክ ላፍቶ ኢትዮ ሌዘር ፋብረ‍ኢካ ኬሚካል ፍሳሽ ወደ ወንዝ በመልቀቅ 800ሺህ ብር ሲቀጣ 8 የመኖሪያ ቤትና 1 ድርጅት ደግሞ ባመነጩት ቆሻሻ አወጋገዳቸው ደንብን ተላልፈዉ ወንዞችን በመበከላቸው በድምሩ 592 ሺህ ብር መቀጣታቸዉን ባለስልጣኑ አስታዉቋል።

በተጨማሪም በኮልፌ ቀራኒዮ ክ/ከተማ ረጲ ኮምዶሚኒዮም እና ግራር ሆቴል ፍሳሽ ቆሻሻን ከወንዝ በማገናኘታቸው በድምሩ 600ሺህ ብር፤ በቂርቆስ ክ/ከተማ ዲሊኦፖል እንተርናሽናል ሆቴል 300ሺህ ብር ሲቀጣ በጉለሌ ክ/ከተማ አቶ ሙሉጌታ መንጋ እና አቶ ናትናኤል ገበያው ድርጅት 300 ሺህ ብር ብር ተቀጥተዋል።

ባለስልጣኑ ከዚህ በፊት ለህብረተሰቡ ሰፊ ግንዛቤ መስጠቱን ጠቁሟል።

ይሁን እንጂ ግለሰቦቹ እና ድርጅቶቹ ደንብ ተላልፈዉ በመገኘታቸዉ በድምሩ 2 ሚሊዮን 592 ሺህ ብር ተቀጥተዋል።

ባለስልጣኑ የአካባቢ ብክለት መከላከል እንዲቻል መረጃ በመስጠት የጠቆሙትን የህብረተሰብ ክፍሎች እያመሰገነ በቀጣይ ህብረተሰቡና ተቋማት ከዚህ ዓይነት ድርጊቶች እንዲቆጠቡ አሳስቧል።

15/10/2025

በአዲስ አበባ ከተማ አዲሱ የደመወዝ ማሻሻያ ክፍያ አፈጻጸም በምን ደረጃ ላይ ይገኛል?





15/10/2025

የዓለም የምግብና እርሻ ድርጅት(ፋኦ) ለኢትዮጵያ "ዘላቂ የደን ልማት አያያዝና አጠቃቀም" በሚል ዘርፍ ለኢትዮጵያ አረንጓዴ ዐሻራ ኢኒሼቲቭ እውቅና ሰጥቷል





15/10/2025

በዘውዲቱ መታሰቢያ ሆስፒታል የተደረገው ማስፋፊያ ከዚህ ቀደም የሌሉ የህክምና አገልግሎቶች አንዲጨመሩ ማስቻሉ ተነገረ





የፌዴራል ፖሊስ አመራሮችና አባላት የመሰረተ ልማት ስራዎች ተጠብቀው የዜጎችን ተጠቃሚነት የበለጠ ለማረጋገጥ የህግ የማስከበር ተግባራችንን እናጠናክራለን ሲሉ ገለጹAMN ጥቅምት 5/2018 የኢ...
15/10/2025

የፌዴራል ፖሊስ አመራሮችና አባላት የመሰረተ ልማት ስራዎች ተጠብቀው የዜጎችን ተጠቃሚነት የበለጠ ለማረጋገጥ የህግ የማስከበር ተግባራችንን እናጠናክራለን ሲሉ ገለጹ

AMN ጥቅምት 5/2018

የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አመራሮችና አባላት ከእንጦጦ ፓርክ እስከ አቃቂ ቃሊቲ ድረስ የተሰሩ የኮሪደር ልማት እና ልዩ ልዩ መሰረተ ልማቶች ስራዎችን ዛሬ ጎብኝተዋል።

የፌዴራል ፖሊስ አመራሮችና አባላት በከተማዋ በተገነቡ መሰረተ ልማት ስራዎች እጅግ መደነቃቸዉን ተናግረዋል።

በፌዴራል ፖሊስ የወንጀል መከላከል ጤና አገልግሎት ሃላፊ ዋና ኢንስፔክተር አብደላ አደላ፤ አዲስ አበባን ጨምሮ በመላው አገሪቷ እየተሰሩ የሚገኙ የልማት ስራዎች የሰላም ፍሬ ማሳያዎች መሆናቸውን ተናግረዋል።

የአገር ልማት የሚረጋገጠው ሰላም በአስተማማኝ ሁኔታ ሲሰፍን ብቻ መሆኑን ጠቁመው፤ "ሰላምና ልማት የማይነጣጠሉ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች ናቸው" ብለዋል፡፡

የፌዴራል ፖሊስ ሰላምን የማስጠበቅና ልማትን እንዲፋጠን የማድረግ ተግባርን አጠናክሮ እንደሚቀጥልም ነው የተናገሩት፡፡

በፌዴራል ፖሊስ ሆስፒታል የግዥ ሃላፊ ኮማንደር ባዬ ሽፈራው በበኩላቸው እንደገለጹት፤ የከተማዋ ውበት፣ መሰረተ ልማቶች አገሪቷ ፈጣን እድገት ውስጥ መሆኗን አመላካቾች ናቸው።

ፖሊስ የልማት አደናቃፊ እና የፀረ ሰላም ሃይሎችን እኩይ ተግባር እያከሸፈ መምጣቱን አውስተው፤ ይህን ተግባሩን ወደፊትም አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡

በፌዴራል ፖሊስ የልዩ ፀረ ሽብር ኮማንዶ አባል ዋና ኢንስፔክተር አየለ አሸናፊ፤ በዛሬው ጉብኝታችን አገራችን እየተጓዘችበት ያለውን ከፍታ በተግባር ያየነበትና ያረጋገጥንበት ነው ብለዋል፡፡

የፌዴራል ፖሊስ ረዳት ኢንስፔክተር ማርታ ወረቁ በበኩላቸው፤ የህዝብንና የአገርን ሰላም ለማረጋገጥ የሚከፈለው ዋጋ ለዚህ ዓይነት የልማት ስራዎች አብቅቶናል ብለዋል።

በፌዴራል ፖሊስ የወንጀል መከላከል ተቋም ጥበቃ መምሪያ የሬጅመንት አዛዥ ኮሎኔል ማቲዮስ ሸጋው እንደገለጹት፤ ፖሊስ ህዝብና መንግስት በሚያከናውናቸው የልማት ስራዎች የራሱን አሻራ የማኖር ተግባሩን አጠናክሮ ይቀጥላል ማለታቸዉን ኢዜአ ዘግቧል።

15/10/2025

ኢትዮጵያን ለማፍረስ ከማለም የሚመነጨው የግብፅ ሴራ እና የሀሰት ትርክት





ከጀርመን አደባባይ -  ጋርመንት - ሐጫሉ ጎዳና - ሐጫሉ አደባባይ እየተሰራ ያለው የኮሪደር ልማት የቀንና የምሽት ገፅታ - በምስል (የከንቲባ ጽ/ቤት)
15/10/2025

ከጀርመን አደባባይ - ጋርመንት - ሐጫሉ ጎዳና - ሐጫሉ አደባባይ እየተሰራ ያለው የኮሪደር ልማት የቀንና የምሽት ገፅታ - በምስል (የከንቲባ ጽ/ቤት)

የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ምርጥ የዘላቂ የደን ልማት አለም አቀፍ እውቅና አገኘ AMN ጥቅምት 5/2018የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ምርጥ የዘላቂ የደን ልማት አያያዝ...
15/10/2025

የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ምርጥ የዘላቂ የደን ልማት አለም አቀፍ እውቅና አገኘ

AMN ጥቅምት 5/2018

የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ምርጥ የዘላቂ የደን ልማት አያያዝና አጠቃቀም በሚል ዘርፍ ከዓለም የምግብና እርሻ ድርጅት (ፋኦ) እውቅና አግኝቷል።

ኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ እውቅናውን ያገኘችው በጣሊያን ሮም እየተካሄደ ባለው ‎የዓለም ምግብ ጉባዔ ላይ ነው።

የዓለም የምግብ ጉባኤውም የምስረታ በዓሉ አካል ሲሆን፤ ኢትዮጵያን ጨምሮ በርካታ ሀገራት ተሳትፈዋል።

ድርጅቱ ለኢትዮጵያ "በአረንጓዴ አሻራ ዘላቂ የደን ልማት አያያዝና አጠቃቀም" በሚል ዘርፍ ዓለም አቀፍ እውቅና የሰጠ ሲሆን፤ ‎የኢትዮጵያ መንግስትን ወክለው የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ ሽልማቱን ተቀብለዋል።

የቱሪዝም ሚኒስትር ሰላማዊት ካሳ በመርሃ ግብሩ ባስተላለፉት መልዕክት፥ ፋኦ ርሃብን ለማጥፋት፣ የአየር ንብረት ለውጥ ተጽዕኖን ለመቀነስና የአካባቢ ጥበቃን ለማጠናከር ላለፉት 80 ዓመታት የላቀ አሻራ ማሳረፉን አንስተዋል።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ሀሳብ አመንጪነት የተጀመረው የኢትዮጵያ አረንጓዴ አሻራ መርኃ ግብር ዛሬ በምርጥ የዘላቂ የደን ልማትና ጥበቃ ምሳሌነት እውቅና በማግኘቱ ኮርተናል ብለዋል።

በመርሃ ግብሩ በብዙ ቢሊዮኖች የሚቆጠሩ ችግኞችን በመትከል የደን ሽፋንን ከ17 ነጥብ 2 በመቶ ወደ 23 ነጥብ 6 በመቶ ማሳደጉን ተናግረዋል።

ይህ በመሪ ግልፅ ራዕይና በህዝብ ጠንካራ ተሳትፎ የተሳካና ተስፋችንን ያለመለመ ስኬት ነው ያሉት ሚኒስትሯ፥ ይህንን ተጨባጭ ሥራ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው እንዲጎበኙና በዓይን አይተው እንዲመሰክሩም ጋብዘዋል።

ድርጅቱ ከኢትዮጵያ ጋር ላለው ለረጅም ጊዜ የጸና አጋርነት ያመሰገኑት ሚኒስትሯ በጋራ ጥረታችን ችግኞችን እየተከልን የተሻለ ነገን ለልጆቻችን መገንባት ጀምረናል ብለዋል።

‎የዓለም የምግብና የእርሻ ድርጅት (ፋኦ) ከዚህ ቀደም በምግብ ዋስትና፣ በተመጣጠነ የምግብ አቅርቦትና በስንዴ ምርት የላቀ አፈጻጸም ላሳዩት ቁርጠኝነት ‎የከበረውን የፋኦ አግሪኮላ ሜዳሊያ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መሸለሙ ይታወሳል።

በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የዓለም የምግብና የእርሻ ድርጅት (ፋኦ) 80ኛ የምስረታ ዓመት የድርጅቱን ያለፉት ዓመታት ስራዎች በሚዳስሱ እንዲሁም ቀጣይ ራዕዩን በሚገልጡ ዝግጅቶች እያከበረ እንደሚገኝ ኢዜአ ዘግቧል።

15/10/2025

ዋርካ | የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን እና የከተማዋ ነዋሪዎች ፊት ለፊት የተገናኙበት የውይይት መድረክ ክፍል 2





15/10/2025

በመዲናዋ በበቂ ሁኔታ የሚቀርቡ የዕለት ፍጆታ ምርቶች አላስፈላጊ የዋጋ ጭማሪን ማስቀረታቸው ተጠቆመ





15/10/2025

አዲሱ የደመወዝ ማሻሻያ እስከ ጥቅምት 15 የመስከረም ወር ክፍያ እንደሚፈጸም የአዲስ አበባ ፋይናንስ ቢሮ አስታወቀ





15/10/2025

የኤ ኤም ኤን 24/7 ጥቅምት 05/2018 ዓ.ም የዓለም እንዴት ዋለች መረጃ





Address

5 Kilo
Addis Ababa
251

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when AMN-Addis Media Network posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to AMN-Addis Media Network:

Share

Addis Media Network (AMN)

አዲስ ሚዲያ ኔትወርክ (ኤኤምኤን) አዲስ ቴሌቭዥን ለተሻለ ጥራት በመስራት ላይ ይገኛል በመሆኑም

በ satellite -NSS 12 ethio sat HD

Freq- 11165 mhz

polarization - Horizontal