AMN-Addis Media Network

AMN-Addis Media Network This is the official page of AMN- Addis Media Network ‘Voice of generation.’ stay connected🤳

03/07/2025

ኢትዮጵያ ከጎረቤት ሀገራት ጋር ያላትን የሰላምና የልማት ትብብር አጠናክሮ የማስቀጠል ፍላጎቷ ከፍተኛ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ተናገሩ። ከትናንት እስከ ዛሬ በመነጋገርና በመተባበር ላይ የተመሰረተው የኢትዮጵያ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ተጠናክሮ ይቀጥላል ያሉት ጠቅላይ ሚንስትሩ የጎረቤት ሀገራት ለኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ በጎ ምላሽ ሊሰጡ ይገባልም ብለዋል፡፡

AMN - ሰኔ 26/2017 ዓ.ም

03/07/2025

ስለ አዲስ አበባ ምን ተባለ

AMN - ሰኔ 26/2017 ዓ.ም

03/07/2025

ከተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያዉ ትግበራ በኋላ በግብርና፣ በኢንዱስትሪ ፣በፋይናንስ ፣ በቱሪዝም እና በሌሎችም ወሳኝ የኢኮኖሚ ዘርፎች ኢትዮጵያ እያንሰራራች መምጣቷን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ ለምክር ቤቱ በሰጡት ማብራሪያ አስረድተዋል፡፡ የምጣኔ ሃብት ባለሙያዉ ዱጋሳ ሙሉጌታ(ዶ/ር)
በተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ትግበራ ዙሪያ ሙያዊ ማብራሪያ አላቸዉ፡፡

AMN - ሰኔ 26/2017 ዓ.ም

03/07/2025


03/07/2025

የጠቅላይ ሚንስትሩ ማብራሪያ በፓርላማ

በህገ ወጥ መንገድ ሊሸጥ የነበረ ከ65ሺ ሊትር በላይ ነዳጅ  በቁጥጥር ስር ማዋሉን የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ አስታወቀAMN- ሰኔ 26/2017 በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በህገ ወጥ መንገድ ሊሸ...
03/07/2025

በህገ ወጥ መንገድ ሊሸጥ የነበረ ከ65ሺ ሊትር በላይ ነዳጅ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ አስታወቀ

AMN- ሰኔ 26/2017

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በህገ ወጥ መንገድ ሊሸጥ የነበረ ከ65ሺ ሊትር በላይ ነዳጅ በቁጥጥር ስር ማዋሉን የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ አስታውቋል።

ቢሮው ከነዳጅ አቅርቦት ስርጭት እና ግብይት ጋር በተያያዘ ከ59 ኩባንያዎች፣ ከ129 ማደያ ባለቤቶች እና ከሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር ተወያይቷል።

የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ በአዲስ አበባ የነዳጅ ማደያዎች ባላቸው አቅም ልክ አገልግሎት መስጠት ባለመቻላቸው ተጠቃሚዎችን ለወረፋ እና ለእንግልት በመዳረጋቸው 12 ማደያዎች መታሸጋቸውን ተናግረዋል።

በተጠናቀቀው በጀት አመት ከሐምሌ 1 ጀምሮ በህገ ወጥ መንገድ ሊሸጥ የነበረ ከ65ሺ ሊትር በላይ ነዳጅ በቁጥጥር ስር ማዋሉን ያስታወቀው ቢሮው ህገወጥነት በመከላከል ሂደት ውስጥ ከ5.9 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማስገባቱንም አስታውቋል።

በአሸናፊ በላይ

የህዝበ-ሙስሊሙ የመረዳዳትና የመደጋገፍ ባህል ይበልጥ መዋቅራዊ ስርዓትን የተከተለ እንዲሆን እየተደረገ ነውAMN ሰኔ 26/2017የህዝበ-ሙስሊሙ የመረዳዳትና የመደጋገፍ ባህል ይበልጥ መዋቅራዊ...
03/07/2025

የህዝበ-ሙስሊሙ የመረዳዳትና የመደጋገፍ ባህል ይበልጥ መዋቅራዊ ስርዓትን የተከተለ እንዲሆን እየተደረገ ነው

AMN ሰኔ 26/2017

የህዝበ-ሙስሊሙ የመረዳዳትና የመደጋገፍ ባህል ይበልጥ መዋቅራዊ ስርዓትን የተከተለ እንዲሆን እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ።

የመረዳዳት ሥርዓቱን የተሳለጠ ለማድረግ የዘካ እና የአውቃፍ ኮሚሽን ዛሬ በይፋ ተመስርቷል፡፡

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የኮሚሽኑን ምስረታ በተመለከተ የውይይት መድረክ አካሒዷል፡፡

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሸህ ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ተወካይ ሸህ ኢድሪስ አሊ፤ ዘካ ሰዎች ካላቸው በፐርሰንት ተቀንሶ አቅም ለሌላቸው የሚሰጥበት አግባብ ነው ብለዋል፡፡

አውቃፍ ሰዎች በገዛ ፈቃዳቸው ለማህበረሰብ አገልግሎት ለሚውሉ ጉዳዮች ስጦታ እንዲሰጡ የሚደረግበት መሆኑንም አንስተዋል፡፡
ይህ የዘካና የአውቃፍ ስርዓት ከጥንት ጀምሮ የነበረ ቢሆንም ጊዜያዊ ችግርን ከማስታገስ ውጭ ዘላቂ ሃብትን በመፍጠር ረገድ ጉልህ ሚና እንዳልነበረው ተናግረዋል።

የኮሚሽኑ መመስረት ግለሰቦችም ሆኑ ተቋማት የሚያደርጓቸው ድጋፎች ህግ እና ስርዓት ተበጅቶላቸው፤ ዘመናዊ አሰራርን ተከትሎ ለታለመላቸው ዓላማ እንዲውሉ በማድረግ ድጋፍ የሚሹ ወገኖችን በዘላቂነት ማቋቋም የሚያስችል ነው ብለዋል፡፡
ለሀገራዊ ልማት ትልቅ አቅም እንደሚሆንም እንዲሁ፡፡

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች የኡለማዎች ጉባኤ ምክትል ሰብሳቢ ጄይላን ኸድር(ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ዘካ እና አውቃፍ የእስልምና እምነት ምሰሶዎች ናቸው ማለታዉን ኢዜአ ዘግቧል፡፡
የኮሚሽኑ መቋቋም የህዝበ-ሙስሊሙን የዘመናት ጥያቄ የሚመልስ መሆኑንም ተናግረዋል፡፡

በተበታተነ መንገድ ሲደረግ የነበረው የዘካ እና የአውቃፍ የአሰራር ስርዓት ዘመናዊ እንዲሆን ያደርጋል ነው ያሉት።
በዘካና አውቃፍ ኮሚሽን ምሥረታው ላይ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት ተገኘተዋል፡፡

ኢትዮጵያ በኢንተርፖል ንቁ አባል ሆና መቀጠሏን የኢንተርፖል ፕሬዚዳንት ሜጀር ጀነራል አህመድ ናስር (ዶ/ር) ገለፁAMN- ሰኔ 26/2017 የአለም አቀፉ የፀረ ወንጀል የጋራ ፖሊሳዊ ጥምረት ...
03/07/2025

ኢትዮጵያ በኢንተርፖል ንቁ አባል ሆና መቀጠሏን የኢንተርፖል ፕሬዚዳንት ሜጀር ጀነራል አህመድ ናስር (ዶ/ር) ገለፁ

AMN- ሰኔ 26/2017

የአለም አቀፉ የፀረ ወንጀል የጋራ ፖሊሳዊ ጥምረት ኢንተር ፖል ፕሬዚዳንት ሜጀር ጀነራል አህመድ ናስር (ዶ/ር) ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል ጋር በጋራ መስራት በሚያስችላቸው ጉዳይ ላይ ውይይት አድርገዋል።

እንደ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል ገለፃ ኢትዮጵያ ከኢንተርፖል ጋር ባለፉት ጊዜያት የሰራችው ስራ ውጤታማ መሆኑን በውይይቱ መገለፁን ተናግረው በቀጣይም በጋራ መስራት የሚያስችል ውይይት መደረጉን አብራርተዋል።

በዋናነት የድንበር ዘለል ወንጀሎችን ለመከላከል የሚያስችሉ ሃሳቦች መነሳታቸውን የተናገሩት ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ በተጨማሪም ኢትዮጵያ በኢንተርፖል ውስጥ ስለሚኖራት ሚናና ድጋፍ ዙሪያ መወያየታቸውን ተናግረዋል።

የፕሬዘዳንቱ እዚህ መምጣትም ለኢትዮጵያ ፖሊስ በቀጣይ ትልቅ አቅም የሚፈጥር ነው ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያ በኢንተርፖል ንቁ አባል ሆና ቆይታለች ያሉት የዓለም አቀፉ የፖሊስ ተቋም የኢንተርፖል ፕሬዚዳንት ሜጀር ጀነራል አህመድ ናስር (ዶ/ር)፣ በዚህም የተደራጁ ወንጀሎችን በመዋጋት ረገድ ከፍተኛ ሚና ነበራት፣ ይህም ለኢንተርፖል ያላትን ቁርጠኝነት ያሳየ ነው ብለዋል።

ፕሬዚዳንቱ በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ያሉ የሪፎርም ስራዎችንም ተዘዋውረው ጎብኝተዋል።

በራሄል አበበ

03/07/2025




03/07/2025

“ውሎ አዲስ”

AMN - ሰኔ 26/2017 ዓ.ም የምሽት 1፡00 ዜናዎቻችንን በቀጥታ ይከታተሉ፤

👇👇👇👇👇👇👇

ትክክለኛውን የአዲስ ሚዲያ ኔትዎርክ ዲጂታል ሚዲያ የትስስር አውታሮችን በመቀላቀል ቤተሰብ ይሁኑን!

https://linktr.ee/AddisMediaNetwork

AMN - ሰኔ 26/2017 ዓ.ም

03/07/2025

ሰላሟ የተረጋገጠ፤ ራሷን የቻለች፡ ጠንካራና የበለጸገች ኢትዮጵያ….

መዲናዋን የሚመጥን የሰላምና ፀጥታ ስራ መሰራቱን የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ አሰታወቀAMN- ሰኔ 26/2017 አዲስ አበባ ትክክለኛ አለምአቀፍ የዲፕሎማቲክ ከተማነቷንና...
03/07/2025

መዲናዋን የሚመጥን የሰላምና ፀጥታ ስራ መሰራቱን የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ አሰታወቀ

AMN- ሰኔ 26/2017

አዲስ አበባ ትክክለኛ አለምአቀፍ የዲፕሎማቲክ ከተማነቷንና የሀገሪቱ መዲና መሆኗን የሚመጥን የሰላምና ፀጥታ ስራ መሰራቱን የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ ገልጸዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮና የአዲስ አበባ ደንብ ማስከበር ባለስልጣን የ2017 በጀት ዓመት እቅድ አፈፃፀም ገምግመዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሊዲያ ግርማ በርካታ አለም አቀፍ ጉባኤዎችን የምታስተናግደው አዲስ አበባ ከተማ በከፍተኛ ለውጥ ላይ መሆኗንና ፍፁም ሰላማዊ ከተማ መሆኗን ተናግረዋል።

በከተማዋ የሽብር ድርጊት ሊፈፅሙ የነበሩ የፀረ ሰላም ኃይሎችን እኩይ ተግባር ማክሸፍ መቻሉንና የወንጀል ምጣኔን በመቀነስ ወንጀለኞችን በቁጥጥር ስር ማዋል ላይ ውጤታማ ስራዎች መሰራቱንም ገልጸዋል።

ቢሮ ኃላፊዋ ህዝቡን የሰላም ባለቤት በማድረግ የህግ የበላይነትን በማስከበር ከተማዋ ፍፁም ሰላማዊ እንድትሆንና በተረጋጋ ሁኔታ የልማት እንቅስቃሴዋን እንድታሳልጥ መደረጉንም አንስተዋል፡፡

ህገ ወጥነትን መከላከል፣ ወንጀለኞች እንዲያዙ በማድረግ፣ አዋኪ ድርጊቶችን በመግታት ፣ ህጋዊ የሆነ የንግድ ስርዓት እንዲኖር እንዲሁም ህዝባዊና ሀይማኖታዊ በዓላት ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መንገድ እንዲከበሩ በማድረግ ረገድ የሰላም ሰራዊቱ የነበረው ሚና ከፍተኛ መሆኑንም ገልፀዋል።

የመረጃ ስርዓት አያያዝን ቀልጣፋና ፈጣን በማድረግ በ7/24 የስራ ባህል ህገ ወጥነትን እየተከላከልን ነው ያሉት ወ/ሮ ሊዲያ ከሌሎች አጋር ተቋማት ጋር እና ከአጎራባች ሸገር ከተማ ጋር ስራዎችን በጋራ በመስራት ለውጦች መመዝገባቸውን አብራርተዋል።

ከተማዋ ትክክለኛ አለምአቀፍ የዲፕሎማቲክ ከተማነቷንና የሀገሪቱ መዲና መሆኗን የሚመጥን የሰላምና ፀጥታ ስራ ተሰርቷልም ብለዋል።

በደሳለኝ ሙሀመድ

Address

5 Kilo
Addis Ababa
251

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when AMN-Addis Media Network posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to AMN-Addis Media Network:

Share

Addis Media Network (AMN)

አዲስ ሚዲያ ኔትወርክ (ኤኤምኤን) አዲስ ቴሌቭዥን ለተሻለ ጥራት በመስራት ላይ ይገኛል በመሆኑም

በ satellite -NSS 12 ethio sat HD

Freq- 11165 mhz

polarization - Horizontal