AMN-Addis Media Network

AMN-Addis Media Network This is the official page of AMN- Addis Media Network ‘Voice of generation.’ stay connected🤳

08/08/2026

ከጎሮ አይሲቲ ፓርክ - ቱሉ ዲምቱ እየተሰራ የሚገኘው መንገድ ምን ደረጃ ላይ ይገኛል?





የኦሮሞ ሕዝብ በዘመናት ታሪኩ ውስጥ በማንኛውም ጊዜ የስርዓት መበላሸትን ነው ሲቃወም የኖረው- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)AMN - ነሐሴ 2/2018 ዓ.ም ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ...
08/08/2026

የኦሮሞ ሕዝብ በዘመናት ታሪኩ ውስጥ በማንኛውም ጊዜ የስርዓት መበላሸትን ነው ሲቃወም የኖረው- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

AMN - ነሐሴ 2/2018 ዓ.ም

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የኦሮሞ ሕዝብ በዘመናት ታሪኩ ውስጥ በማንኛውም ጊዜ ከስርዓቱ መበላሸት ውጪ በኢትዮጵያ ላይ ተቃውሞ አያውቅም ሲሉ ጥያቄው ሁልጊዜም በስርዓቱ ላይ እንደነበር ገልጸዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከኦ ቢ ኤን ጋር በነበራቸው ቆይታ የኦሮሞ ሕዝብ አሁን ያለችውን ኢትዮጵያ በመገንባት ሂደት ውስጥ የተጫወተውን ሚና በሰፊው አንስተዋል፡፡

ኢትዮጵያ በዚህ ታላቅ ሕዝብ ተሳትፎ ጨምር የተገነባች ሀገር ናት ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፤ ዛሬ ላይ ኦሮሞው ራሱ ባቆመው ሀገር ውስጥ እየኖረ ይገኛል ብለዋል።

የኦሮሞ ሕዝብ ኢትዮጵያን ከአገዛዝ ወይም ከተጽዕኖ ነፃ ለማውጣት መስዋዕት ከፍሎ ትልቅ ትግል ማድረጉን ጠቅሰው፣ ኢትዮጵያ የኦሮሞ ጀግኖች የሌሉባት ሆና ብቻዋን የተገነባች እንዳልሆነችም አጽንኦት ሰጥተዋል።

የሀገርን ድንበር ከማስመር አንስቶ የኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ እስከ ማቆም ድረስ የኦሮሞ ሕዝብ በሀገር ግንባታ ሂደት ውስጥ የአንበሳውን ድርሻ ተወጥቷል ያሉትጠቅላይ ሚኒስትር ዐብይ አሕመድ(ዶ/ር) ይህ ታላቅ ሕዝብ በታሪኩ ከስርዓቱ በስተቀር በሀገሪቷ ላይ ተቃውሞ አያውቅም ብለዋል፡፡

ኦሮሞ ራሱ በገነባት ሀገር ውስጥ ከሌሎች የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ጋር ተቻችሎ እየኖረ ሲሆን ፣ አሁንም መብቱን አስከብሮ ሌሎችንም አካቶ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።

በፍሬሕይወት ብርሃኑ

08/08/2026

የኦሮሞ ሕዝብ የመጀመሪያ ጥያቄ ምንድን ነው?





08/08/2026

የሀገራችንን ገጽታ የሚያድሱ፣ የከተሞቻችንን ኢኮኖሚያዊ አቅም የሚያጎለብቱ ሜጋ ፕሮጀክቶች
​በባሕር ዳር ከተማ በጥሩ ሂደት ላይ የሚገኘውን የሂልተን ባሕር ዳር ሆቴል የግንባታ ሂደት እንዲሁም የፎር ፖይንትስ ባይ ሸራተን ጣና ሆቴል የጅማሮ ስራዎችን በአካል ተገኝተን ተመልክተናል

ም/ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

08/08/2026

የኦሮሞ ህዝብ በኢትዮጵያ ሀገር ግንባታ ውስጥ ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)





ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)ከኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ (OBN) ጋር ያደረጉት ቆይታ ክፍል 2 ዛሬ ምሽት 2:30 በሁሉም የኤ ኤም ኤን የሚዲያ አማራጮች ይጠብቁን።
08/08/2026

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)ከኦሮሚያ ብሮድካስቲንግ ኔትዎርክ (OBN) ጋር ያደረጉት ቆይታ ክፍል 2 ዛሬ ምሽት 2:30 በሁሉም የኤ ኤም ኤን የሚዲያ አማራጮች ይጠብቁን።

ከመላው ኢትዮጵያ የመጡ የባህልና ስፖርት ጉባኤ ተሳታፊዎች በአዲስ አበባ የተገነቡ ዘመናዊ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን ጎበኙAMN - ነሐሴ 2/2018 ዓ.ምከሁሉም ክልሎች እና ከተማ አስተ...
08/08/2026

ከመላው ኢትዮጵያ የመጡ የባህልና ስፖርት ጉባኤ ተሳታፊዎች በአዲስ አበባ የተገነቡ ዘመናዊ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን ጎበኙ

AMN - ነሐሴ 2/2018 ዓ.ም

ከሁሉም ክልሎች እና ከተማ አስተዳደሮች የተወጣጡ የባህልና ስፖርት ዘርፍ ከፍተኛ አመራሮች ፣ ባለሙያዎች፣ የስፖርትና የጥበባት ማህበራት ፕሬዚዳንቶች እንዲሁም የተጠሪ ተቋማት ኃላፊዎች በአዲስ አበባ ከተማ የተገነቡ ዘመናዊ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎችን እና የኪነ-ጥበብ ማዕከላትን ጎብኝተዋል።

ማዕከላቱና የስፖርት ማዘውተሪያ ሜዳዎች ለወጣቶች ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት እና ለአትሌቲክስ፣ እግር ኳስ እንዲሁም ለተለያዩ የስፖርት አይነቶች ዕድገት ያላቸውን ከፍተኛ ፋይዳ ተሳታፊዎቹ በአድናቆት ገልጸዋል።

በጉብኝቱ ወቅት አስተያየታቸውን የሰጡት የጉባኤው ተሳታፊዎች፣ በአዲስ አበባ የተገነቡት እነዚህ ዘመናዊ የስፖርት ማዘውተሪያ ስፍራዎች እና ወቅቱ በደረሰበት ቴክኖሎጂ የተደራጁ የጥበብ ማዕከላት ለአካባቢው ብቻ ሳይሆን ለአገር አቀፍ የስፖርትና የኪነ-ጥበብ ዕድገት እጅግ የላቀ አስተዋጽኦ እንዳላቸው ጠቁመዋል።

የከተማ አስተዳደሩ ብቁ ፣ ንቁ እና ውጤታማ የሆነ ወጣት ለማፍራት እና ስፖርት ልማቱን ወደ ላቀ ደረጃ ለማስቀጠል እያደረገ ያለው ጥረት የሚበረታታ መሆኑን ተሳታፊዎቹ ገልጸዋል፡፡

የተገነቡት ማዘውተሪያ ስፍራዎች አህጉራዊና ዓለም አቀፍ ውድድሮችን ማስተናገድ የሚያስችል አቅም ያላቸው መሆናቸውን በመጥቀስ ሌሎች ክልሎችም ከዚህ የልማት ተሞክሮ ሊወስዱ እንደሚገባ መናገራቸውን ከአዲስ አበባ ኮሚዩኒኬሽን ቢሮ የተገኘው መረጃ ያመላክታል።

ባለፉት አምስት ዓመታት አዲስ አበባን ጨምሮ በሁሉም ከተሞች ተጀምረው የቆሙ ሕንፃዎች በፍጥነት ተጠናቅቀው ወደ አገልግሎት እንዲገቡ ከፍተኛ ክትትልና ድጋፍ ተደርጓል፡፡ አንድ ሕንፃ መሠረት ወ...
08/08/2026

ባለፉት አምስት ዓመታት አዲስ አበባን ጨምሮ በሁሉም ከተሞች ተጀምረው የቆሙ ሕንፃዎች በፍጥነት ተጠናቅቀው ወደ አገልግሎት እንዲገቡ ከፍተኛ ክትትልና ድጋፍ ተደርጓል፡፡ አንድ ሕንፃ መሠረት ወጥቶለት አንድ ሁለት ዐሠርት ዓመታትን ሳይጠናቀቅ ማቆየት የተለመደ ነገር ሆኖ ነበር፡፡ ይህ የከተማውን ገጽታ ከማጥፋት ባሻገር ኢኮኖሚያዊ ጫናው ከፍተኛ ነው፡፡ ከባንክ ብድር ስምምነት ውጭ ገንዘብ ማሸሻ ሆኗል፡፡ በዚያውም ልክ ባልለሙ የከተማው ሕንፃዎች የተነሣ የንግድና የግብይት ቦታ ኪራይ እንዲወደድ አድርጓል፡፡ አካሄዱ በኢኮኖሚው ውስጥ የማይንቀሳቀስ ገንዘብ እየፈጠረ ንግድ ለመጀመር ትልቅ ካፒታል እንዲጠይቅ ሲያደርግ ነበር፡፡

አዲስ አበባ ከዚህ ችግር ፈጥና እየወጣች ነው፡፡ ተጨማሪ ቦታዎች በመልሶ ማልማትና በኮሪደር ልማት ለንግድና ለግብይት ተስማሚ ተደርገው ለምተዋል፡፡

የመደመር መንግሥት ገጽ ከ254 - 255

08/08/2026

ከአማዞን እስከ ዓድዋ ድል መታሰቢያ





Address

5 Kilo
Addis Ababa
251

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when AMN-Addis Media Network posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to AMN-Addis Media Network:

Shortcuts

Share