LELA News

LELA News Amharic News Media

ለጡረተኞች ጭማሪ!በኢትዮጵያ የጡረተኞች ዝቅተኛ ወርሃዊ ክፍያ 4,669 ብር ሊሆን !ከቀጣይ ሐምሌ ወር ጀምሮ በሚጀምረው አዲስ ክፍያ ለዋና ጡረተኞቹ ከ 1500 እስከ 2000 ብር ጭማሪ መደረ...
29/06/2025

ለጡረተኞች ጭማሪ!
በኢትዮጵያ የጡረተኞች ዝቅተኛ ወርሃዊ ክፍያ 4,669 ብር ሊሆን !
ከቀጣይ ሐምሌ ወር ጀምሮ በሚጀምረው አዲስ ክፍያ ለዋና ጡረተኞቹ ከ 1500 እስከ 2000 ብር ጭማሪ መደረጉን ሰምተናል።

በዚህም መሰረት 3113 ብር የነበረው ዝቅተኛ የዋና ጡረተኛ ተከፋይ ወደ 4,669 ብር ከፍ ብሏል።
በኢትዮጵያ ዋና እና ተተኪ የግል ጡረተኛ ተከፋይ ብዛት ሀያ ሺ ይጠጋል።

ከእነዚህ ተከፋዮች መሀል 146 ሺ ፣136 ሺ እና 126 ሺ እና 106 ሺ የሚከፈላቸው አራት ከፍተኛ ጡረተኛ ተቀባዮች አሉ።

ተተኪ ጡረተኞች የዋናው ጡረተኛ ተከፋይ ግማሹን እንደሚያገኙ ይታወቃል።
Via:-Fidel post

በነበረበት ይቀጥላል!!የሐምሌ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት እንደሚቀጥል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገለጸ የሐምሌ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ከዛሬ...
28/06/2025

በነበረበት ይቀጥላል!!

የሐምሌ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በነበረበት እንደሚቀጥል የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገለጸ

የሐምሌ ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ ከዛሬ ሰኔ 21 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በሰኔ ወር ሲሸጥ በነበረበት የመሽጫ ዋጋ እንዲቀጥል በመንግሥት መወሰኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ገለጸ፡፡

ሚኒስትሩ ጨምሮ እንደገለፀዉ የነዳጅ ማደያዎች እና ኩባንያዎች በነዳጅ ውጤቶች ግብይት አዋጁና በአሠራር መመሪያው መሠረት ውሳኔውን ተግባራዊ በማድረግ ህብረተሰቡን በቅንነትና በታማኝነት እንዲያገለግሉ በጥብቅ አሳስባለሁ ብሏል!

ሱፐር ስፖርት ልዩ ቻናል የፊታችን ሰኞ ይዘጋልየኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግን ጨምሮ የተለያዩ ጨዋታዎችን በአማርኛ ቋንቋ በቀጥታ ስርጭት ለተመልካቾች ሲያሰራጭ የቆየው ዲ ኤስ ቲቪ ሱፐር ስፖርት ል...
28/06/2025

ሱፐር ስፖርት ልዩ ቻናል የፊታችን ሰኞ ይዘጋል

የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግን ጨምሮ የተለያዩ ጨዋታዎችን በአማርኛ ቋንቋ በቀጥታ ስርጭት ለተመልካቾች ሲያሰራጭ የቆየው ዲ ኤስ ቲቪ ሱፐር ስፖርት ልዩ ቻናል ከፊታችን ሰኞ ሰኔ 23 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ስርጭቱን እንደሚያቋርጥ ኤቨንት አዲስ ሚዲያ ከቻናሉ ያገኘው መረጃ ያመለክታል።

በተጨማሪም ቻናሉ የተለያዩ የስፖርት ይዘቶችን በሌሎች የሱፐር ስፖርት ቻናሎች መከታተል ትችላላችሁ ብሏል።

በያዝነው ዓመት ከወራት በፊት ካናል ፕላስ ቻናልም ከኢትዮጵያ የሚዲያ ዘርፍ ስርጭቱን አቋርጦ መውጣቱ ይታወሳል።

ደረጄ የመኪና ስጦታውን ተረከበየጋዜጠኛ ደረጄ ኃይሌ /ኃይሌ ዘ በቅሎ ቤት/ የ60ኛ ዓመት ልደት በማስመልከት ከታሜሶል ኮምኒኬሽንስ ባለቤትና ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሰለሞን ከበረ የ 3 ነጥብ...
27/06/2025

ደረጄ የመኪና ስጦታውን ተረከበ

የጋዜጠኛ ደረጄ ኃይሌ /ኃይሌ ዘ በቅሎ ቤት/ የ60ኛ ዓመት ልደት በማስመልከት ከታሜሶል ኮምኒኬሽንስ ባለቤትና ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሰለሞን ከበረ የ 3 ነጥብ 4 ሚልየን ብር ግምት ያለው የ BYD E 2 መኪና ስጦታ ተበርክቶለታል።

ዛሬ ሰኔ 20/2017 ዓ.ም የጋዜጠኛ ደረጄ ኃይሌ ወዳጅ ዘመድ እንዲሁም አድናቂዎች በተገኙበት በታሜሶል ኮምኒኬሽን ቢሮ የመኪና ቁልፍ ርክክብ መርሐግብር ተከናውኗል።

ጋዜጠኛ ደረጄ በተመሳሳይ ሁኔታ ከጃምቦ ሪልስቴት የመኖርያ ቤት ስጦታ መቀበሉና ለሶስት ዓመታት የድርጅቱ ብራንድ አምባሳደር ለመሆን መስማማቱ በትላንትናው ዕለት መገለፁ ይታወሳል።
( )

"ኢራንን አመሰግናለሁ" – ፕሬዝዳንት ትራምፕ፤ "ለሰጠችን ደካማ ምላሽ እና ለቅድመ ማስጠንቀቂያው"ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ በኢራን እና በአሜሪካ መካከል የነበረውን የጦርነት ስጋት ሙሉ በ...
24/06/2025

"ኢራንን አመሰግናለሁ" – ፕሬዝዳንት ትራምፕ፤ "ለሰጠችን ደካማ ምላሽ እና ለቅድመ ማስጠንቀቂያው"

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ፣ በኢራን እና በአሜሪካ መካከል የነበረውን የጦርነት ስጋት ሙሉ በሙሉ ያረገበ በሚመስል መግለጫ፣ ኢራን ለሰጠችው "ደካማ" የአጸፋ ምላሽ እና ለሰጠችው የቅድመ ማስጠንቀቂያ ምስጋና አቅርበዋል።

ፕሬዝዳንቱ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት አዲስ መልዕክት፣ የኢራንን ምላሽ "እጅግ በጣም ደካማ" ሲሉ የገለጹት ሲሆን፣ ዩናይትድ ስቴትስም ጥቃቱን "በጣም ውጤታማ በሆነ መንገድ" መመከቷን አስታውቀዋል።

"ኢራን የኑክሌር ተቋሞቿን ማውደማችንን ተከትሎ፣ እጅግ በጣም ደካማ የሆነ ምላሽ ሰጥታለች፤ ይህንንም እንጠብቅ ነበር" ብለዋል። "በአጠቃላይ 14 ሚሳኤሎች ተተኩሰው ነበር፤ ከእነዚህ ውስጥ 13ቱን መትተን ጥለናል፤ አንደኛው ደግሞ ጉዳት ወደማያደርስ አቅጣጫ ስለነበር 'በነጻ ለቀነዋል'። አንድም አሜሪካዊ ጉዳት እንዳልደረሰበት እና ምንም አይነት ውድመት እንዳልተፈጠረ ስገልጽ በደስታ ነው።"

"ከሁሉም በላይ አስፈላጊው ነገር፣ በውስጣቸው የነበረውን ሁሉ ከ'ሲስተማቸው' ውስጥ ማውጣታቸው ነው፤ ተስፋ እናደርጋለን ከዚህ በኋላ ጥላቻ አይኖርም። ኢራን የሰው ህይወት እንዳይጠፋና ማንም እንዳይጎዳ ላደረገችው የቅድመ ማስጠንቀቂያ ላመሰግናት እወዳለሁ።"

"ምናልባት ኢራን አሁን በክልሉ ውስጥ የሰላምንና የስምምነትን መንገድ መቀጠል ትችል ይሆናል፤ እኔም እስራኤል ይኸንኑ እንድታደርግ በሙሉ ልብ አበረታታታለሁ። ለዚህ ጉዳይ ትኩረት ስለሰጣችሁ አመሰግናለሁ!"

ይህ የፕሬዝዳንት ትራምፕ መግለጫ፣ በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የነበረውን ቀጥተኛ ወታደራዊ ፍጥጫ በይፋ የሚያጠናቅቅ ይመስላል። ፕሬዝዳንቱ የኢራንን ምላሽ "ደካማ" በማለት የአሜሪካንን የበላይነት ቢያሳዩም፣ በተመሳሳይ ጊዜ ለሰላም በር በመክፈትና ምስጋና በማቅረብ ሁኔታው እንዲረጋጋ ያላቸውን ፍላጎት አመላክተዋል።

የፕሬዝዳንቱ ጥሪ እስራኤልንም ማካተቱ፣ አሁን ትኩረት የተደረገበት የእስራኤልና የኢራን ግጭት እንዲቆም የሚገፋፋ ሲሆን፣ ቀጣናው ከገባበት የጦርነት አዙሪት እንዲወጣ የሚያደርግ ነው ተብሎለታል።

ኳታር በኢራን ለተቃጣባት ጥቃት ተመጣጣኝ ምላሽ እንደምትሰጥ አስታወቀች*****************የኳታር መከላከያ ሚኒስትር፥ ኢራን ኳታር በሚገኘው አል-ኡዴይድ የጦር ሰፈር ላይ ሚሳኤል ተኩሳ...
23/06/2025

ኳታር በኢራን ለተቃጣባት ጥቃት ተመጣጣኝ ምላሽ እንደምትሰጥ አስታወቀች
*****************

የኳታር መከላከያ ሚኒስትር፥ ኢራን ኳታር በሚገኘው አል-ኡዴይድ የጦር ሰፈር ላይ ሚሳኤል ተኩሳለች፤ በዚህም ኢራን የኳታርን ሉዓላዊነት ተዳፍራለች ብለዋል።

ኳታር ከኢራን ለተቃጣበት ጥቃት ተመጣጣኝ ምላሽ የመስጠት መብቷ በዓለም አቀፍ ሕግ የተጠበቀ መሆኑን ሚኒስትሩ ጠቅሰዋል።

አክለውም፥ የኳታር የአየር መከላከያ ሥርዓት የከኢራን የተተኮሱ ሚሳኤሎችን በማክሸፍ ጥቃቱን መመከቱንም ተናግረዋል።

የአሜሪካ የመከላከያ ዲፓርትመንት (ፔንታጎን)፣ ኢራን በኳታር በሚገኘው አል ኡደይድ የአየር ጦር ሰፈር ላይ በርካታ የአጭርና የመካከለኛ ርቀት ሚሳይሎችን መተኮሷን በይፋ አረጋግጧል። ይህ ማረ...
23/06/2025

የአሜሪካ የመከላከያ ዲፓርትመንት (ፔንታጎን)፣ ኢራን በኳታር በሚገኘው አል ኡደይድ የአየር ጦር ሰፈር ላይ በርካታ የአጭርና የመካከለኛ ርቀት ሚሳይሎችን መተኮሷን በይፋ አረጋግጧል። ይህ ማረጋገጫ የወጣው ኢራን የበቀል ጥቃት መሰንዘሯን ካወጀች ከሰዓታት በኋላ ነው።

ስማቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ አንድ ከፍተኛ የመከላከያ ባለሥልጣን ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት፣ ጥቃቱ መፈጸሙ የተረጋገጠ ሲሆን፣ በአሁኑ ሰዓት የደረሰውን ጉዳት መጠን ለመገምገም ዝርዝር ምርመራ እየተካሄደ ነው።

ይህ የፔንታጎን ማረጋገጫ የኢራንን መግለጫ የሚያጠናክር ነው። የኢራን አብዮታዊ ጥበቃ ጓድ ቀደም ብሎ ባወጣው መግለጫ፣ ለአሜሪካ የኑክሌር ተቋማት ጥቃት ምላሽ ለመስጠት "የድል ብስራት" በተባለ ዘመቻ የአሜሪካን ጦር ሰፈሮች ኢላማ ማድረጉን አስታውቆ ነበር።

ኳታር በበኩሏ የአየር መከላከያ ሥርዓቶቿ ጥቃቱን በተሳካ ሁኔታ እንዳመከኑትና ምንም አይነት የህይወትም ሆነ የንብረት ጉዳት አለመድረሱን ገልጻለች። ሆኖም፣ የአሜሪካ ጦር የጉዳት ግምገማ እያካሄድኩ ነው ማለቱ፣ አንዳንድ ሚሳይሎች መከላከያውን አልፈው ጉዳት አድርሰው ሊሆን ይችላል የሚል ግምት እንዲፈጠር አድርጓል።

በአል ኡደይድ የአየር ጦር ሰፈር ወደ 10,000 የሚጠጉ የአሜሪካ ወታደሮች የሚገኙ ሲሆን፣ ጥቃቱን ተከትሎ ሁሉም ባሉበት እንዲጠለሉ ትዕዛዝ ተሰጥቷቸው ነበር። ይህ ቀጥተኛ የኢራን ጥቃት በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ፍጥጫ ወደ አዲስና አደገኛ ምዕራፍ ያሸጋገረ ሲሆን፣ የዋይት ሀውስ ቀጣይ ምላሽ በከፍተኛ ስጋት እየተጠበቀ ነው።

(ዘ-ሐበሻ )

ኢራን ኳታር በሚገኘው የአሜሪካ ጦር ሰፈር ላይ ጥቃት ፈጸመች!ኢራን ኳታር በሚገኘው የአሜሪካ ጦር ሰፈር ላይ የሚሳኤል ጥቃት ፈጸመች፡፡ አሜሪካ ከቀናት በፊት እንዳስጠነቀቀችዉ በኢራን ላይ ለ...
23/06/2025

ኢራን ኳታር በሚገኘው የአሜሪካ ጦር ሰፈር ላይ ጥቃት ፈጸመች!

ኢራን ኳታር በሚገኘው የአሜሪካ ጦር ሰፈር ላይ የሚሳኤል ጥቃት ፈጸመች፡፡ አሜሪካ ከቀናት በፊት እንዳስጠነቀቀችዉ በኢራን ላይ ለፈፀመችዉ ጥቃት የበቀል እርምጃ ከወሠደች እርምጃዋን አጠናክራ እንደምትቀጥል ማስጠንቀቋ ይታወሳል!

የኢራን ፓርላማ የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ እንዲዘጋ የቀረበውን ውሳኔ አፀደቀ!የኢራን ፓርላማ በዓለም ላይ በጣም አስፈላጊ ከሆኑ የነዳጅ ኤክስፖርት መንገዶች አንዱ የሆነውን የሆርሙዝ ወሽመጥ ባ...
22/06/2025

የኢራን ፓርላማ የሆርሙዝ የባህር ወሽመጥ እንዲዘጋ የቀረበውን ውሳኔ አፀደቀ!

የኢራን ፓርላማ በዓለም ላይ በጣም አስፈላጊ ከሆኑ የነዳጅ ኤክስፖርት መንገዶች አንዱ የሆነውን የሆርሙዝ ወሽመጥ ባህርን ለመዝጋት የቀረበውን ረቂቅ ውሳኔ ማፅደቁን አል አረቢያ ዘግቧል።

ሰቂቁ ይፅደቅ እንጂ የመጨረሻው ውሳኔ ለከፍተኛው የጸጥታ እና ወታደራዊ ባለስልጣናት የሚተው ነው መሆኑን የኢራን ሚዲያዎችን ጠቅሶ አል አረቢያ ዘግቧል።

ይህ ርምጃ በቴህራን እና በዋሽንግተን መካከል ያለው ውጥረት እየተባባሰ በመጣበት ወቅት የአሜሪካ የአየር ጥቃት በኢራን የኒውክሌር ፋሲሊቲዎች ላይ ያነጣጠረ እና ቴህራን በእስራኤል ላይ ያደረሰችውን የአጸፋ የሚሳኤል ጥቃት ተከትሎ የተወሰደ ስለመሆኑ ተነግሯል።

የሆርሙዝ ወንዝ የዓለም ኢነርጂ የደም ቧንቧ የሚባልለት ሲሆን፤ በግምት 20 - 30 በመቶ የሚሆነው የዓለማችን የነዳጅ ዘይት በሆርሙዝ ሰርጥ ላይ ያልፋል።

የዚህ ሰርጥ መዘጋት ዓለም አቀፍ የኢነርጂ ደህንነት ላይ ስጋትን የሚደቅን ተደርጎ ይወሰዳል።

ሰርጡ ከተዘጋ የነዳጅ ዘይት ዋጋ ከፍተኛ ጭማሪ እና የአቅርቦት መቆራረጥ ያስከትላል ተብሏል።

Gazette Plus ጋዜጣ ፕላስ

የአሜሪካን ጥቃት ተከትሎ ኢራን እስራኤል ላይ በባለስቲክ ሚሳኤል የታገዘ ጥቃት መፈጸም ጀመረች።በጥቃቱ ምክንያት በአሁኑ ወቅት በእስራኤል ሃይፋ እና ቴል አቪቭ ከተሞች ውጥረት መንገሱን በርካ...
22/06/2025

የአሜሪካን ጥቃት ተከትሎ ኢራን እስራኤል ላይ በባለስቲክ ሚሳኤል የታገዘ ጥቃት መፈጸም ጀመረች።

በጥቃቱ ምክንያት በአሁኑ ወቅት በእስራኤል ሃይፋ እና ቴል አቪቭ ከተሞች ውጥረት መንገሱን በርካታ ዓለማቀፍ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።

ይሁንና በእስራኤል በኩል እስካሁን ስለጥቃቱ የተሰጠ ማረጋገጫ የለም።

የኢራን ወታደራዊ ኃይልን ምንጭ ያደረገው ፋርስ ኒውስ፥ ኢራን ቤን ጉሪዮን አየር ማረፊያን እና የባዮሎጂካል ጥናት ማዕከልን የጥቃቱ ዒላማ ማድረጓን ዘግቧል።

የአሜሪካን የቦምብ ድብደባ ተከትሎ የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራጋቺ "አሜሪካ በኢራን ሰላማዊ የኒውክሊየር ተቋማት ላይ የፈጸመችው አስነዋሪ ጥቃት የማያባራ መዘዝ ያስከትላል" ሲሉ መዛታቸው አይዘነጋም።

(Arts)

ኢራን በአሜሪካ ለተፈጸመባት ጥቃት አጸፋዊ ርምጃ እወስዳለሁ አለችኢራን በሦስት የኒውክሌር ማዕከላት ላይ አሜሪካ ለፈጸመችባት ጥቃት የአጸፋ ርምጃ ለመውሰድ ሁሉም አማራጮች በጠረጴዛ ላይ ናቸው...
22/06/2025

ኢራን በአሜሪካ ለተፈጸመባት ጥቃት አጸፋዊ ርምጃ እወስዳለሁ አለች

ኢራን በሦስት የኒውክሌር ማዕከላት ላይ አሜሪካ ለፈጸመችባት ጥቃት የአጸፋ ርምጃ ለመውሰድ ሁሉም አማራጮች በጠረጴዛ ላይ ናቸው ስትል አስጠንቅቃለች።

አሜሪካ ከሰዓታት በፊት ግዙፉን ፎርዶው የኒውክሌር ተቋም ጨምሮ በሦስት የኢራን ኒውክሌር ማዕከላት ላይ የተሳካ የቦምብ ድብደባ መፈጸሟን ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ተናግረዋል።

የአሜሪካን የቦምብ ጥቃት አስደንጋጭ ሲሉ የገለጹት የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ ፥ ጥቃቱ ዘላለማዊና የማያባራ ጥፋት ያስከትላል ብለዋል።

ሀገራቸው ልዑላዊነቷን ለመከላከል በአሜሪካ ላይ የአጸፋ ርምጃ ለመውሰድ ሁሉንም አማራጮች ትመለከታለች፤ አማራጮችም በጠረጴዛ ላይ ናቸው ሲሉ አስጠንቅቀዋል፡፡

አሜሪካ በፎርዶው፣ ናታንዝ እና ኢስፋሃን የኒውክሌር ጣቢያዎች ላይ ከፈጸመችው የቦምብ ጥቃት በኋላ ፕሬዚዳንት ትራምፕ በሰጡት መግለጫ ፥ ኢራን በፍጥነት ወደ ሰላም መምጣት አለባት ብለዋል፡፡

ኢራን ወደ ሰላም የማትመጣ ከሆነ በቀጣይ ሌሎች ኢላማዎች ላይ ከፍ ያለ ጥቃት እንፈጽማለን ሲሉ አስጠንቅቀዋል፡፡

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሕግ አገልግሎት መምሪያ በአቶ ትዝታው ሳሙኤል ላይ ክስ መሰረተ።የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤ/ክርስትያን  ሕግ አገልግሎት መምሪያ ለኢትዮጵያ ፌዴራል...
17/06/2025

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሕግ አገልግሎት መምሪያ በአቶ ትዝታው ሳሙኤል
ላይ ክስ መሰረተ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤ/ክርስትያን ሕግ አገልግሎት መምሪያ ለኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ባቀረበው ክስ እንደተጠቀሰዉ
በወንጀል ተጠርጣሪ /ተከሳሽ - አቶ ትዝታው ሳሙኤል
ነዋሪነቱን በውጪ ሃገር በማድረግ የቤተክርስቲያኒቱ የበላይ ውሳኔ ሰጪ አካልን ለማዋረድ፣ ለመስደብ እና የምዕመኑን ስሜት ለመንካት ብሎም በሀገሪቱ ውስጥ ሁከትና ብጥብጥ እንዲነሳ በማሰብ በተለያዩ የመረጃ ማሰራጫ መንገዶች እና ከ5000 በላይ ተከታዮች ባሉት የራሱ የዪቲዩብ ቻናል በመጠቀም ከፍተኛ ቅስቀሳ ሲያደርግ መቆየቱን ገልጿል።

በማያያዝም ግለሰቡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ብፁዓን አባቶችን፣ በየገዳማቱ ውስጥ የሚገኙ ገዳማውያን መነኮሳትና አገልጋዮችን በማለት፣ እንዲሁም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን በማለት፣ ሲቀሰቅስ የቆየ መሆኑን የገለጸው መምሪያው ግለሰቡ በተጨማሪም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የምትገለገልባቸውን ሃይማኖታዊ የፀሎት፣ የታሪክ ፣ የገድላትና ድርሳናት መጻሕፍትን ሲል መቆየቱን ጠቅሷል::

የቤተ/ክርስትያኗ ህግ ክፍል ባቀረበዉ ክስ እንደጠቀሰዉ ግለሠቡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በቅድስና የምታከብራቸውንና የምትዘክራቸውን ቅዱሳን አባቶች እና እናቶችን ናቸው ማለቱንም ጠቅሷል።

የህግ ክፍሉ በጠቅላላዉ ሰባት ነጥቦችን ያካተተ የወንጀል ዝርዘርሮችን በመግለጽም ነዉ ክስ ያቀረበዉ!

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when LELA News posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to LELA News:

Share