LELA News

LELA News Amharic News Media

ለ43 ዓመታት የኢትዮጵያ መገለጫ የነበረ 🔥🔥
09/06/2026

ለ43 ዓመታት የኢትዮጵያ መገለጫ የነበረ 🔥🔥


''ኢትዮጵያ ሆይ ደስ ይበልሽ" ለ45 ዓመታት የተዘመረ እና በኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ ያገለገለ ብሄራዊ የህዝ...

ኢትዮጵያ ሆይ ...
08/06/2026

ኢትዮጵያ ሆይ ...

''ኢትዮጵያ ሆይ ደስ ይበልሽ" ለ45 ዓመታት የተዘመረ እና በኢትዮጵያ ለረጅም ጊዜ ያገለገለ ብሄራዊ የህዝ...

"በመጀመርያ አርሲ በወገኖቻችን ላይ በደረሰው የሞት አደጋ የተሰማኝን ሀዘን እየገለፅኩ  ሀዘኑ የደረሰባቹ የአካባቢው ነዋሪዎች እንዲሁም ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ  ፈጣሪ መፅናናቱን እንዲስጠን...
06/06/2026

"በመጀመርያ አርሲ በወገኖቻችን ላይ በደረሰው የሞት አደጋ የተሰማኝን ሀዘን እየገለፅኩ ሀዘኑ የደረሰባቹ የአካባቢው ነዋሪዎች እንዲሁም ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ፈጣሪ መፅናናቱን እንዲስጠን እየፀለይኩ በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ እስታድዮም ላቀርበው የነበረው የሙዚቃ ዝግጅት መሰረዜን እና ኮንሰርቱንም እማልሳተፍ መሆኔን በትህትና እገልፃለሁ ። በስተመጨረሻም ለኤቨንቱ አዘጋጆች ለተፈጠረው ነገር እጅግ ይቅርታ እጠይቃለሁ። እግዝያብሔር ይብቃቹ ይበለን!"
ድምጻዊ

  እንደፃፉት 😭😭ማንነትና ሐይማኖትን ሰበብ አድርጎ ሰዎችን መጨፍጨፍ የሚከለክለውን የተባበሩት መንግስታት የጂኖሳይድ ኮንቬንሽን ኢትዮጵያ እአአ ጁላይ 11 ቀን 1949 ዓ.ም መፈረም ብቻ ሳይ...
03/06/2026

እንደፃፉት 😭😭
ማንነትና ሐይማኖትን ሰበብ አድርጎ ሰዎችን መጨፍጨፍ የሚከለክለውን የተባበሩት መንግስታት የጂኖሳይድ ኮንቬንሽን ኢትዮጵያ እአአ ጁላይ 11 ቀን 1949 ዓ.ም መፈረም ብቻ ሳይሆን ስምምነቱን Ratify በማድረግ ማንነትና ሐይማኖት ሰበብ ያደረገ ጭፍጨፋ የሕግ ተጠያቂነትን እንዲያስከትል የተስማማች የመጀመርያዋ ሀገር ናት።

ይህ የሆነው ከ77 አመት በፊት በአባቶቻችንና በአያቶቻችን ዘመን ነው። ዛሬ ከ77 ዓመት በኋላ ግን የሕጉ ፋይዳና የሰው ልጅ ክቡርነት ውሉ ጠፍቶን ፊት ለፊት አዛኝ መሳይ ቅቤ አንጓች በዝግ በር ጂኖሳይድን የሚያሞግሰና የሚያቆለጳጵስ ዜጋ እንደ አሸን ያፈራች አሳፋሪና ዘግናኝ ሀገር መገለጫ ሆነናል።

የጸጥታ ተቋማት ዜጎችን ከጂኖሳይደሮች መከላከል፣ ሕግ ማስከበር፣ ማክበርና ሰላምን ማረጋገጥ የተሳናቸው መሆኑ ሳያንስ የመንግስት ሚዲያዎች የሚመለከታቸው የሰብአዊ መብት ተቋማት የተጨፈጨፉ ንጽሃን ዜጎችን ሞት ለመዘረከርና ለመዘገበ የሚጸየፉና የሚተናነቃቸው ሆነዋል።

ኢትዮጵያ አለም አቀፍ ስምምነቱ ግዴታ የሚጥልባቸው በተለይ ሐይማኖትና ማንነትን መሰረት አድርገው ጂኖሳይድ የሚፈጽሙ ላይ ተጠያቂነት የሚያስከትለውን ስምምነት በ1949 Ratify ስታደርግ ሕግን ልታስከበር ጥፋተኞችን ልትቀጣ ተስማምታለች። በ1950 ዎቹም ይህንኑ ስምምነት በቀጥታ ወደ ህጎቿ በማዋሃድ ወንጀሉንና ተጠያቂነቱን በ1957 ዓ.ም የወንጀለኛ መቅጫ ሕጎቿ ውስጥ አካታለች።

መንግስት መፍትሔ ሊሰጠን ይገባል። ግፍን፣ ጭካኔንና ጭፍጨፋን አንለምድም። ዝም አንለም ማለት አለብን። የተባበሩት መንግስታት በዓለም አቀፍ ደረጃ ያጸደቀውን ጂኖሳይድን የመከላከል ስምምነትን እንዲያከብር፣ እንዲያስከብርና ሕጉን እንዲያስፈጽም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤ/ክርስቲያን ያለማሰለስ አቤት ማለት አለባት። ዓለም ይስማ ዓለም ይፍረድ !!!

እግዜአብሔር በአርሲ ለተጨፈጨፉ ኦርቶዶክሳውያን ጽድቅን ለቤተሰቦቻቸውና ለምዕመናን መጽናናትን እንዲሰጥ እመኛለሁ!!!

መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክበስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡‹‹ወረሰዩ አብድንቲሆሙ ለአግብርቲከ መብልዐ ለአዕዋፈ ሰማይ፣ ወሥጋሆሙኒ ለጻድቃኒከ ለአራዊተ ገዳም፦...
03/06/2026

መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፡፡

‹‹ወረሰዩ አብድንቲሆሙ ለአግብርቲከ መብልዐ ለአዕዋፈ ሰማይ፣ ወሥጋሆሙኒ ለጻድቃኒከ ለአራዊተ ገዳም፦ የአገልጋዮችህንም በድኖች ለሰማይ ወፎች መብል አደረጉ፥ የቅዱሳንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት።››
(መዝሙረ ዳዊት ፸፰፥፪)

በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሽርካ፣ በሆንቆሎ፣ በዋቤ እና በሙኔሳ ወረዳዎች በመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችንና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ስለደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የሰማነው በተሰበረ ልብ ነው።
የእምነት ነፃነት ተደፍሮ መቶ ዓመታት ያስቆጠረው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በተቃጠለበት፣ እንዲሁም የካራ ኩፍቴና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን በተዘረፈበት በዚህ ክፉ ቀን፤ በርካታ ምእመናን በግፍ መሰዋታቸውና በመቶዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ከቀዬአቸው መፈናቀላቸው ቤተ ክርስቲያናችንን በእጅጉ ያሳዘነ ክስተት ነው።

የሰላም፣ የፍቅርና የታሪክ ማህደር የሆነችው ቤተ ክርስቲያን በምድራዊ መከራ ውስጥ ያሉትን ምእመናን በምታጽናናበት በዚህ ወቅት ራሷ በፈተና ውስጥ ሆና ከመቸገሯም በላይ በአርሲ ምድር በተደጋጋሚ የሚስተዋለው በደልና ግፍ በሁላችንም ልቡና ውስጥ "እስከ መቼ?" የሚል የቁጭት እና የኀዘን ጥያቄን ፈጥሯል።

በመሆኑም ይህ መከራ እያበቃ ሳይሆን እየሰፋ በመምጣቱ የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅና ሰላምን የማስፈን አደራ የተጣለባችሁ የጸጥታ አካላትና በየመዋቅሩ ያላችሁ ሓላፊዎች ከምንም በላይ ታሪክ የሚጠይቃችሁ በሥልጣን ዘመናችሁ ለዜጎች ደኅንነት በምትከፍሉት ዋጋ ነውና ይህንን የጥቃት ሰንሰለት በማስቆምና ወንጀለኞችን ለሕግ በማቅረብ ከታሪክ ባለዕዳነት ትድኑ ዘንድ በቤተ ክርስቲያናችን ስም አበክረን እናሳስባለን።

በየአካባቢው የምትገኙ ምእመናንና መላው ኢትዮጵያውያንም በወንድማማችነት መንፈስ ተጋግዛችሁ፣ የተፈናቀሉ ወገኖችን በመደገፍና በጸሎት ከቤተክርስቲያናችን ጎን እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

በመጨረሻም ቤተ ክርስቲያናችን ለሰላም፣ ለይቅርታና ለሰው ልጆች ክብር ሁል ጊዜ የምትቆም መሆኑን በመግለጽ ይህንን የኀዘን ሰዓት አምላካችን በምሕረቱ ያሳልፍልን፣ የሞቱትን ነፍሶቻቸውን በመንግሥቱ ይቀበልልን፣ የተጎዱትንም በቸርነቱ ያጽናናልን በማለት አባታዊ የኀዘን መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን።

እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!!

ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!
አሜን።

አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ

© የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት

ሐውለት አህመድ (ፒኤችዲ) እንደፃፉት!...***ይቺም ሻማ ሰልችታለች!===============በአገራችን ለሚቀጥሉት ብዙ አሥርት ዓመታት ምናልባትም አሁን በሕይወት የምንገኝ ሰዎች በአጠቃላይ ...
02/06/2026

ሐውለት አህመድ (ፒኤችዲ) እንደፃፉት!...
***
ይቺም ሻማ ሰልችታለች!
===============
በአገራችን ለሚቀጥሉት ብዙ አሥርት ዓመታት ምናልባትም አሁን በሕይወት የምንገኝ ሰዎች በአጠቃላይ ሳናይ የምንሞተው ነገር የመንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት ''ኃላፊነቴን በአግባቡ ስላልተወጣሁ ሥራዬን በፈቃዴ ለቅቄያለሁ፤ ከ'ኔ የተሻለ ሰው ይምራው'' የሚለው ነው።

በአርሲ ዞን በኦርቶዶክስ ክርስትና አማኞች እና አብያተ-ክርስትያናት ላይ በተደጋጋሚ ጥቃቶች እየተሰነዘሩ ብዙ ሰው በአሰቃቂ ሁኔታ ሞተ፤ አብያተ-ክርስትያናት እና ቅርሶችም ወደሙ፤ በነዋሪዎቹ ዘንድ ሥጋትና ጥርጣሬ ሰፈነ።

ይሄን ተደጋጋሚ ጥቃት ለማስቀረት የተሠራ ሥራ አለ? ሰላም ማስከበር 100% የክልሉ መንግሥት ሥራ አይደለም እንዴ? ምን አድርጓል? ሰላም ማስከበር ካቃታቸው በኢትዮጵያ ሕግ መሠረት ''አልቻልንም፤ የፌዴራል መንግሥት ጣልቃ ይግባልን'' ይባላል እኮ! መቼም ''እኔ ለዚህ ኃላፊነት ብቁ ሆኜ አልተገኘሁም፤ የተሻለ ብስለትና ልምድ ያለው ሰው ይተካኝ'' የሚሉ ኃላፊዎችን በሕይወት እያለን እንደማናይ ዕሙን ነው።

ሰው ባለቀ ቁጥር ይቺን ሻማ ብልጭ ማድረግ ምን ፋይዳ አለው? ይሰለቻል። የክልሉ መንግሥት ለዚህ ዞን ልዩ ትኩረት ሰጥቶ ሕዝቡን ይጠብቅ። በጊዜ መፍትሔ ካልተሰጠው የዚህ ዳፋ የማይተርፈው ሰው የለም።

እንደ አንድ ተርታ ዜጋ በደረሰው ጉዳት ሐዘኔን ለመግለጽ እወዳለሁ። 😥

ፒኤስጂ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን በድጋሚ አሸነፈ የፈረንሳዩ እግር ኳስ ክለብ ፒኤስጂ አርሰናልን በማሸነፍ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን በድጋሚ አንስቷል፡፡ፒኤስጂ ከአስቸጋሪ አጀማ...
30/05/2026

ፒኤስጂ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን በድጋሚ አሸነፈ

የፈረንሳዩ እግር ኳስ ክለብ ፒኤስጂ አርሰናልን በማሸነፍ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን በድጋሚ አንስቷል፡፡

ፒኤስጂ ከአስቸጋሪ አጀማመር በኋላ አርሰናልን 4 ለ 3 በሆነ ውጤት በመርታት ነው ለሁለተኛ ተከታታይ ዓመት የሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን ማሳካት የቻለው፡፡

ጨዋታው በጀመረ በ6ኛው ደቂቃ ካይ ሃቨርትዝ ለአርሰናል የመሪነቷን ግብ አስቆጥሮ የመጀመሪያው አጋማሽ በአርሰናል 1 ለ 0 መሪነት ተጠናቅቋል፡፡

ይሁን እንጂበሁለተኛው አጋማሽ ፒኤስጂ በ65ኛው ደቂቃ በኡስማን ዴምቤሌ የፍጹም ቅጣት ምት ግብ አቻ ሆኗል።

መደበኛ የጨዋታ ጊዜው በአቻ ውጤት መጠናቀቁን ተከትሎም ጨዋታው ወደ ተጨማሪ 30 ደቂቃ ያመራ ሲሆን፥ በዚህም ሳይሸናነፉ ቀርተዋል።

በመጨረሻም የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫ አሸናፊን ለመለየት በተሰጠ የመለያ ምት ፒኤስጂ አርሰናልን በማሸነፍ የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ዋንጫን በድጋሚ ማንሳት ችሏል።

ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች******************በነገው ዕለት በርካታ ህዝብ የሚታደምበት የህዝብ ንቅናቄ በመስቀል አደባባይ ይደረጋል።በመሆኑም፣ ፕሮግሙ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ የ...
25/05/2026

ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶች
******************

በነገው ዕለት በርካታ ህዝብ የሚታደምበት የህዝብ ንቅናቄ በመስቀል አደባባይ ይደረጋል።

በመሆኑም፣ ፕሮግሙ ተጀምሮ እስከሚጠናቀቅ የሚከተሉት መንገዶች ለተሽከርካሪ ዝግ እንደሚሆኑ የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል፦

• ከመገናኛ በባንቢስ ሱፐር ማርኬት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ኡራኤል አደባባይ ላይ
• ከጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ ጥላሁን አደባባይ ወይም መሿለኪያ ላይ፤ ለከባድ ተሽከርካረዎች አጎና ሲኒማ ላይ
• ከሜክሲኮ ወደ መስቀል አደባባይ ለገሐር መብራት ላይ
• ከንግድ ባንክ ወደ አዲስ አበባ ስቴዲየም ቴሌ መ/ቤት ላይ
• ከፒያሳ በአምባሳደር ቴአትር ወደ መስቀል አደባባይ ሀራምቤ ሆቴል ላይ
• ከአራት ኪሎ ወደ መስቀል አደባባይ ብሔራዊ ቤተ መንግሥት ላይ
• ከሜክሲኮ ወደ መስቀል አደባባይ ለገሐር መብራት ላይ
• በቦሌ መንገድ ወደ መስቀል አደባባይ ኦሎፒምያ ወይም ደንበል አደባባይ ላይ

መንገዶቹ ከሌሊቱ 10 ሰዓት ጀምሮ ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅ ለተሽከርካሪ ዝግ መሆናቸውን የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል።

መረጃው ከተላለፈበት ጊዜ ጀምሮ በተጠቀሱት አካባቢዎች ለአጭርም ሆነ ለረጅም ጊዜ ተሽከርከካሪ አቆሞ መሄድ የተከለከለ መሆኑን ዋና ጠቅላይ መምሪያው ገልጿል።

አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ የጠየቀው ዋና መምሪያው፤ የከተማዋ ህዝብ ሁሌም እያደረገው ላለው ቀና ትብብር ምስጋና አቅርቧል።

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when LELA News posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to LELA News:

Share