LELA News

LELA News Amharic News Media

ኅሊና እና ሀገር-------------------(አርክቴክ ዮሐንስ መኮንን - የግል አስተያየት)ማንኛውም ሰው እንደ አንድ ግለሰብ የራሱ እምነትና ፍላጎት አለው። እንደ ጉዳዩ ክብደትና ቅለት ደ...
09/08/2026

ኅሊና እና ሀገር
-------------------
(አርክቴክ ዮሐንስ መኮንን - የግል አስተያየት)

ማንኛውም ሰው እንደ አንድ ግለሰብ የራሱ እምነትና ፍላጎት አለው። እንደ ጉዳዩ ክብደትና ቅለት ደግሞ ይህንን የግል ፍላጎቱን «የእኔ» ለሚለው ቡድን ሲል አሳልፎ ሊሰጥ ይችላል። የአንድ ቡድን እምነትና ፍላጎት በአባላቱ ፈቃደኝነት ላይ የተመሰረተ የመሰባሰቢያ አጀንዳ ነው። ነገር ግን የሀገር ጉዳይ ከግልም ይሁን ከቡድን እምነታችንና ፍላጎታችን ጋር ተቃራኒ እና ተገዳዳሪ ሆኖ ሲመጣ «የቱ ይቅደም?» ለሚለው ጥያቄ የምንሰጠው መልስ በታሪክ ፊት የምንታወስበት ዋንኛ ጉዳይ የሚሆን ይመስለኛል። የህሊናዬን ፍርድ እና የሀገሬን ጥቅም በማስቀደም የቡድን ፍላጎቴን እተዋለሁ ወይስ ሀገሬን ለቡድኔ ፍላጎት እሰዋታለሁ?

በአሁኑ ወቅት በጠረጴዛ ዙሪያ ባሰባሰቡን አገራዊ የምክክር መድረኮች ላይ የሚንጸባረቁ ሃሳቦች ከዚህ ውጪ አይደሉም። የግል፣ የቡድን እና የሀገርን ጥቅም ማስታረቅ ዋነኛ ፈተናችን ሆኖ ወጥቷል። በእርግጥ ነገሩ ግን እንደ መናገር ቀላል አይደለም፤ እጅግ ውስብስብና ከባድ ነው! በጉባኤው ላይ ተመካካሪዎች ይህንን ሚዛን ለመጠበቅ ሲጨነቁ፣ ሲጥሉና ሲያነሱ ታዝቤአለሁ።

ለዚህ ጥሩ ማስታወሻ የሚሆነኝ ስለ ከተሞች እጣ ፈንታና የወደፊት አኗኗራችን ስንመክር ያጋጠመኝ ኩነት ነው። ከምስራቅ የሀገራችን ክፍል የመጣ አንድ ወንድማችን በአስተርጓሚ በቡድን ስብሰባችን ላይ ያቀረበው ሃሳብ እጅግ ልብ ይነካል፤

«እኛ እኮ እንደ ማህበረሰብ የታሪክና የባለቤትነት ጥያቄ ነበረን። የኔ ቡድን ከዚህ አቋም ፍንክች እንዳንል አስጠንቅቆኝ ነበር የላከኝ። አሁን እዚህ መጥቼ የሌሎች ኢትዮጵያውያን ወገኖቼን እምነት፣ ስጋትና ፍላጎት ሳዳምጥ... ይዤ የመጣሁትን "የእኔ ብቻ" የሚለውን ሃሳብ ለማቅረብ ኢትዮጵያውያንን አፈርኩ!» አለን።

ይህ ወንድሜ ከግልም ሆነ ከቡድን አጥር አንጻር ሲመዝነው የጋራ የሆነው የሀገር ጉዳይ ከብዶት ከህሊናው ጋር ያደረገውን ታላቅ የሞራል ሙግት እገነዘባለሁ። እንደሀገር የጋራ እጣ ፈንታችን እና የሁላችንም የህልውና ጉዳይ መሆኑ ሲገባው "የእኔ ብቻ" የሚለው ነባር ትረካ ሚዛን ሊደፋለት አልቻለም።

ሁሉም ሰው ግን እንዲህ አይነት የላቀ የሞራል ልዕልና ያለው አቋም ያራምዳል ማለት አይደለም። ከብሔር፣ ከሃይማኖትና ከፓርቲ አጥር ተሻግሮ ሀገርንና የጋራ መኖሪያችንን ማየት የሚቸገረው አሁንም ሞልቷል።

በተለይ እንደሀገር የጋራችን በሆኑ ፍላጎቶች ላይ የተወጠሩ አጀንዳዎችን ከመጠን በላይ በሁለት ጫፍ እየተጓተቱ ያለመጠን መለጠጥ መዘዙ ቀላል አይመስለኝም። ሀገርንና የጋራ ጥቅማችንን አስቀድመን መሃል ላይ መቆም ካልቻልን፤ "የኔ ካልሆነ ሞቼ እገኛለሁ" ብለን ይዘነው በመጣነው አቋም ላይ ተቸንክረን የምንቀር ከሆነ ወደ አማካይ መንገድ የሚያቀራርብ አይሆንም።

የሌሎች ሀገሮች ልምድ ምን ያሳየናል?

በሰሜን አየርላንዱ የጉድ ፍራይደይ ስምምነት (Good Friday Agreement - 1998) በቤልፋስት (Belfast) ከተማና አካባቢዋ የካቶሊክና የፕሮቴስታንት ማህበረሰቦች "የከተማዋ/የቀጠናው ባለቤት እኔ ነኝ" በሚል ለሦስት አሥርታት ያህል በደም አፍሳሽ ጦርነት ውስጥ ነበሩ። በምክክሩ ወቅት የቤልፋስትና የሰሜን አየርላንድ የባለቤትነት እጣ ፈንታ በቀጥታ ከሚወሰን ይልቅ፣ “Principle of Consent” (የጋራ ስምምነት መርህ) በመጠቀም ጉዳዩ በጊዜ ሂደት እንዲቆይ አደረጉ። አጀንዳውን Park አደረጉት፤ ይህም ሀገሪቱን ከእርስ በእርስ ጦርነት አዳናት።

በደቡብ አፍሪካው ምክክር (1991–1993) ወቅት፣ የነጮቹ አፓርታይድ መንግሥት እና የኤን.ኤን.ሲ (ANC) ዋና ከተማዋን፣ የመሬት ባለቤትነትን እና የስልጣን ክፍፍልን በተመለከተ እጅግ የተወጠረና "የኔ ካልሆነ ሞቼ እገኛለሁ" የሚል አቋም ነበራቸው። በወቅቱ ድርድሩ እንዳይፈርስ ያደረገው "Sunset Clauses" (ጊዜያዊ ማቆያ ድንጋጌዎች) የሚል ስልት ነበር።

አጨቃጫቂ የነበሩ የመሬትና የከተሞች ባለቤትነት/አስተዳደር ጉዳዮችን ለጊዜው አቆይተው (Park አድርገው)፣ አስቀድመው ሀገራዊ ሕገ-መንግሥቱንና የሽግግር መንግሥቱን መሠረት ጣሉ። ከጊዜ በኋላ ሕዝቡ እርስ በእርስ የመተማመን ደረጃው ሲያድግና ስጋቱ ሲቀንስ፣ የቆዩት አጀንዳዎች በሰላማዊ መንገድና በፓርላማ ውይይት መፍትሔ አገኙ።

እኛስ ምን እናድርግ?

የምዕራባውያኑን "Parking the issue" የድርድር ጥበብ ብንጠቀምስ? እጅግ ባላመቹና ባላቀቃረቡን፣ ከዚህ በላይ ብንገፋቸው ምናልባትም ማኅበራዊ መሠረታችንን የሚንዱ አጀንዳዎችን ለጊዜው ብናቆያቸውስ? ነገሮችን አቆይተን ሀገር የምትቀጥልበትን እና የሁላችንም የሆነውን የጋራ ወርቃማውን አማካይ እስክናገኝ የተካረሩ አጀንዳዎችን በይደር መተው አይበጅ ይሆን?
_____________

በጨዋነት እንወያይበት!

ስፔን የ23ኛው ዓለም ዋንጫ ሻምፒዮን ሆነች********************በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ ስፔን አርጀንቲናን 1 ለ 0 በማሸነፍ የዓለም ዋንጫ አሸናፊ ሆናለች።የጨዋታው መ...
19/07/2026

ስፔን የ23ኛው ዓለም ዋንጫ ሻምፒዮን ሆነች
********************

በ23ኛው ዓለም ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ ስፔን አርጀንቲናን 1 ለ 0 በማሸነፍ የዓለም ዋንጫ አሸናፊ ሆናለች።

የጨዋታው መደበኛ ክፍለ ጊዜ ያለ ግብ በመጠናቀቁ አሸናፊውን ለመለየት 30 ደቂቃ ተጨምሯል።

በጭማሪው ክፍለ ጊዜ 106ኛው ደቂቃ ላይ ፌራን ቶሬስ ያስቆጠራት ግብ ስፔንን አሸናፊ አድርጋለች።

በዚህም ስፔን ከ16 ዓመታት በኋላ ውድድሩን አሸንፋ በታሪኳ ለሁለተኛ ጊዜ የዓለም ዋንጫ ባለቤት ሆናለች።

ክቡራን አድናቂዎቼ አዲሱ ገላገላ የአስቴር ትዝታዎች ፪ የተሰኘው አልበሜ በዩቲዩብ ቻናሌ ላይ https://www.youtube.com/asteraweke በቅርቡ ይለቀቃል::  ቻናሌን ስብስክራይብ...
08/07/2026

ክቡራን አድናቂዎቼ

አዲሱ ገላገላ የአስቴር ትዝታዎች ፪ የተሰኘው አልበሜ በዩቲዩብ ቻናሌ ላይ https://www.youtube.com/asteraweke በቅርቡ ይለቀቃል:: ቻናሌን ስብስክራይብ በማድረግ ቀዳሚ ተመልካች ይሁኑ::

እወዳችሁአለሁ::

Dear beloved fans,

I’m happy to inform you that my new album entitled “Gela Gela - Aster’s Ballads #2” is coming to my YouTube channel https://www.youtube.com/asteraweke Soon!

Please subscribe my channel.

As always, I love you!

For more than 30 years, singer/songwriter Aster Aweke has been entertaining audiences across the globe. Her songs have become anthems to her fans in Ethiopia, as well as to Ethiopians living abroad, and she continues to win the hearts and minds of world music lovers. "Ewedihalehu" (I Love You), her....

አስቴር አወቀ - የማይበርድ ፍም ያላት ኮኮብ(በእውቀቱ ስዩም)በኪነጥበብ ሁለት አይነት ችሎታ አለ፤ የመጀመርያው አብነት የሚባል ነው፤ ‘አብነት’ የሚለውን ቃል የተዋስሁት ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክ...
08/07/2026

አስቴር አወቀ - የማይበርድ ፍም ያላት ኮኮብ
(በእውቀቱ ስዩም)

በኪነጥበብ ሁለት አይነት ችሎታ አለ፤ የመጀመርያው አብነት የሚባል ነው፤ ‘አብነት’ የሚለውን ቃል የተዋስሁት ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ሊቃውንት አንድምታ ተርጉዋሚዎች ሲሆን ‘ዋና ምንጭ’ ወይም ኦሪጅናል ማለት ይሆናል፤ አስቴር አወቀ እንዲህ አይነት ከያኒ ናት፤ አንዳንዴ አልፎሂያጅ ዘፈን ሰምተን -እገሊትኮ አስቴርን ትመስላለች -እንላለን፤ አስቴርን የሚያስመስሉ ሰዎች ችሎታ እንዳላቸው ባይካድም ችሎታቸው አምሳል ነው፤ በዚህ ምድር ብዙ አምሳሎች ሲኖሩ አብነት ግን አንድ ለናቱ ነው፤

አስቴር የሚለው ስም የልደት ይሁን የግብር ስም በቅጡ ባላውቅም በልኩዋ የተሰራ ይመስለኛል ፤ አስቴር ማለት ትርጉሙ ኮኮብ ማለት ነው፤ ከኮኮቦች ሁሉ የምትበልጥ ኮኮብ -ደመና የማይሰውራት፤
የጠረፍ ላይ ብርቅ መብራት -

ያስቴር ድምጥ ዝም ብሎ ድምጥ አይደለም፤ ዜማዋ የትዝታችን ማስተርተርያ ነው፤ የሆነ ዘፈኑዋን ስትሰሚ አንድ የሚያስደስት የሚያስተክዝ የግል ታሪክሽ ቁራጭ ድቅን ይልብሻል፤ እኔ ዜማዋን ስሰማ በለጋነቴ ያለፉ ክረምቶች በፊቴ እንደ ፉርጎ ተከታትለው ያልፋሉ ፤ ከማጀት እየተመዘዘ የሚመጣ የጎመን መአዛ ይሸተኛል፤ በምኝታ ቤታችን መስኮት በኩል ተመዝዞ የሚወጣው ሙጃ ይታየኛል፤

ያስቴር በሁለት በኩል እድለኛ ናት፤ ባንድ በኩል መሰል የሌለው ተሰጥኦ ይዛ ተወለደች፤ በሌላ በኩል፣ በጣም ሀያል የሙዚቃ ባለሙያዎችን እና ደራሲዎችን መጎዳኘት ቻለች፤ ( እነ ደረጀ መኮንን ፣ እነ ጥላየ ገብሬ፣ አነ አበጋዝ፣ ከድርሰት እነ አበበ መለሰ ይልማ ገብረአብ ፣ ያየህራድ አላምረውን እና ሌሎችን ማለቴ ነው)

አስቱ፣ ከሰሞኑ የተመረጡ ዘፈኖችዋን እንደገና ሰርታ ለዲጂታሉ ትውልድ አቅርባለች፤ እኛ ከካሴት ክር እስከ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ ድረስ የተዘረጋ ትውልድ አባሎች ይህንን እድሳት እንዴት ተቀበልነው? ከለውጥ ሰውረኝ ማለት ይቻላል? አክሱምና ላሊበላም ከጠጋኝ እጅ አላመለጡም፤ በበኩሌ የሙዚቃ ክህነት ያላቸው እንደ ሰርዐፍሬ ስብሀት አይነት ሰዎች የተሰማቸውን ቢያጋሩን ደስ ይለኛል፤ ገጣሚና ጋዜጠኛ ቴዎድሮስ ጸጋየ ሙዚቃ የሚመዝን የሰላ ጆሮ እንዳለው አውቃለሁ፤ የሱን ምዘና ብሰማ እወዳለሁ፤

ያስቴር የድምፅ አቅም ከምገምተው በላይ ሆኖ ነው ያገኘሁት፤ በርግጥ አስቴር በአፍላ ዘመን አዘፋፈኑዋ ላይ ልባችንን የሚያቀልጠው ልስልስ ቃና ከስሞ ,የሆነ ዘመን ላይ በፈረጠመ ቃና የተተካ ይመስላል፤ አንዳንዴ ከዘፈኑ የድርሰት ሀሳብና መንፈስ የሚርቅ ይመስላል፤ አንዲያም ሆኖ ምቾት አይነሳም፤

ከታደሰው ውስጥ ‘ባይኔ ሙሉሙሉን’ ከሁሉ አብልጨ መርጫለሁ፤

አስቴር ለህይወታችን ቅመም ሆና በጤና እንድትኖር ምኞቴ ነው፤

Artist: Aster AwekeAlbum: Gela Gela - Aster's Ballads : Ba...

አሳዛኝ ዜናአንጋፋዋ ድምፃዊት ራሔል ዮሐንስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየች!በኢትዮጵያ የሙዚቃ ታሪክ ውስጥ በተለይም በዘመን አይሽሬ (Oldies) እና በባህላዊ ስራዎቿ የብዙዎችን ልብ የማረከችው...
05/07/2026

አሳዛኝ ዜና
አንጋፋዋ ድምፃዊት ራሔል ዮሐንስ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየች!
በኢትዮጵያ የሙዚቃ ታሪክ ውስጥ በተለይም በዘመን አይሽሬ (Oldies) እና በባህላዊ ስራዎቿ የብዙዎችን ልብ የማረከችው አንጋፋዋ ድምፃዊትና የዜማ ደራሲ ራሔል ዮሐንስ** ከዚህ ዓለም በሞት መለየቷ ተሰምቷል።

የጥበብ አሻራ እና መንፈሳዊ ህይወት

የማይረሱ ስራዎቿ፦
"አራዳ"፣ "ምኒልክ"፣ "ይዳኘኝ ሰው" እና በርካታ ስራዎቿን ለህዝብ ያበረከተች ድንቅ አርቲስት ነበረች።

የህይወት ምዕራፍ ለውጥ፦
በቅርብ ዓመታት ውስጥ ሙሉ በሙሉ ከዓለማዊ ሙዚቃ ርቃ፣ ህይወቷን ሙሉ በሙሉ ለመንፈሳዊ አገልግሎት (ለመዝሙር) ሰጥታ እንደነበር ይታወሳል።

የቤተሰብ ህይወት
ድምፃዊት ራሔል ዮሐንስ የሁለት ወንድና የአራት ሴት ልጆች እናት እንዲሁም የበርካታ የልጅ ልጆች አያት ነበረች።

>ለቤተሰቦቿ፣ ለአድናቂዎቿና ለመላው የጥበብ አፍቃሪያን መጽናናትን እንመኛለን። ፈጣሪ ነፍሷን በገነት ያኑርልን!

🛑 ብዙዎችን ያሳዘነ ድርጊት 😡😡👇
28/06/2026

🛑 ብዙዎችን ያሳዘነ ድርጊት 😡😡👇

በየጥጋጥግ፣ በሳጥን ውስጥ እና በየመጋዘኑ ተጥለው አቧራ ለብሠው የነበሩ የድሮ ካሴቶችና የሙዚቃ ሸክላዎች ...

27/06/2026

አሁን ስራ ስፈታ ዝምብዬ ከምቀመጥ "ለምን ፍራፍሬዎችን ደረጃ አልሰጣቸውም?" ስል አሰብኩ። ከዚህ የበለጠ ምን አንገብጋቢ ጉዳይ አለ?

፨ ሀብሀብን መጨረሻ ላይ ነው ያደረግኩት። ለዚህ ተክል ምንም ነው ፍላጎት የሌለኝ። ውሀ መጠጣት የማይወድ ሰው ፍራፍሬ ነው የሚመስለኝ። መልኩን አሳምሮ ስለሚቀመጥ ቡፌ ላይ ወከባ ለመፍጠር ይጠቅማል። ከዘ በዘለለ ግን ሸክሙ ነው የሚብሰው። ጥቅሙ እንዲገባኝ ወይም መስለም አለብኝ መሰለኝ። እነሙሔ ነፍሳቸው ነው😅 (የኛ ሀገር ሙስሊሞች ግን ፍቱ አረቦቹ'ኮ ውሀ ስሌላቸው ነው🙄)
......2/10

፨ ሸንኮራ ጣፋጭነቱ ጥያቄ የለውም። መልኩም ያምራል። በተለይ የማሳው።

የሸንኮራ ችግር አስተሻሸጉ ላይ ነው ያለው።
በጥርስህ ነው የምትልጠው። ማኘኩ ደግሞ ብርድ ልብስ መርገጥ በለው። አስቸጋሪ ከመሆኑ የተነሳ ሸንኮራ እየበላህ ሌላ ምንም ነገር መስራት አትችልም። ማሰብ ራሱ አትችልም (ድምፁ ይረብሽሀል)

ስኳርን የፈጠሩት ሸንኮራን ሳያኝኩ የሚበሉበትን መንገድ ፍለጋ የወጡ ሰዎች እንደሆኑ አልጠራጠርም።
......5.5/10

፨ ፓፓዬ ጣዕሙ ጥሩ ነው። ቁምነገረኛ ሀብሀብ በሉት። ወይም ጅላጅል ማንጎ በሉት። የምታዘጋጅልህ ሴት ከሌለች ግን ጥንቅር ብሎ ቢቀር ይሻላል። ኮተቱ ብዙ ነው።
......6.3/10

፨ ማንጎ ጥሩ ጁስ ይወጣዋል። በእጅ ለመብላት ግን አይመችም። ይጨማለቃል (በተለይ የድሮው ማንጎ) አዲሱ ደግሞ ውድ ነው። በየቦታውም አይገኝም።
......7/10

፨ አናናስ ጣዕሙ አንደኛ ነው። ዲዛይኑም ያምራል።

ሁለት ነገሮች ናቸው አናናስን ወደኋላ የሚመልሱት።

አንደኛ ውድ ነው። ውድ ነው ማለት ደሞ ለማምረት አልያም ለማጓጓዝ የሚያስቸግር ተክል ነው ማለት ነው።

ሁለተኛ ሀይ ሜይንቴናንስ ነው። በቢለዋ ማዘጋጀት አለብህ። የተረፈውን በፌስታል ሸፍነህ ማስቀመጥ ይኖርብሀል። ምናምን ምናምን። ለወንደ ላጤ አይሆንም። በስንፍና ሰዓት የምትጠቀመው ፍራፍሬ አይደለም።
......7.8/10

፨ ሙዝን የሚበልጥ አትክልት መኖሩ ይገርማል። ምክኒያቱም ሙዝ እንከን የለሽ ነው። ለመብላት አያስቸግር። ለመላጥ አያስቸግር። ለማምረት አያስቸግር። ዋጋውም ጥሩ ነው። እናት የሆነ ተክል ነው (ቁላ ቢመስልም ዳሩ) ብቻ የሚጣፍጥ ቅቤ ከዛፍ ላይ መብቀሉ ይገርማል።

ከሙዝ የማይገባኝ ሱቅ ላይ ለዘመናት ተንጠልጥሎ ኑሮ እኔ ቤት ሲገባ በሰላሳ ደቂቃ ውስጥ ፋንቱ ማንዶዬን የሚመስለው ነገር ነው። ኪሎ ከገዛሁ ግማሹን ቅርጫቱ ነው የሚበላው። ልክ ወደ ትዳር ሲገቡ አመላቸውን የሚለዋወጡትን ችኮች ነው የሚመስለው። ሁለቱም የበረንዳው ናቸው።
......8/10

፨ አቮካዶ የትም ቦታ የምትበላው ነገር አይደለም። ዝግጅት የሚፈልግ ነገር ነው። ግን It's worth it. እንደ ፓፓዬ እና ሀብሀብ Scam አይደለም። ይጠግናል። ከምንም ነገር ጋር፤ በዬትኛውም ሰዓት ይበላል። ይሁን እንጂ...ጣዕሙ የሌሎቹን ያሕል ራሱን ችሏል ለማለት አልደፍርም። ጥፍጥና ይጎለዋል። ወይም እስክትለምደው ድረስ ራስህን ማስገደድ ይኖርብሀል።

ብዙ ቅሬታ የለኝም እዚህ ፍሬ ላይ። ሰፍ የምልለት ነገርም አይደለም።

አቮካዶ ስበላ እናቴ ደስ የሚላት ይመስለኛል። ሀላፊነት የሚሰማው ሰው ምግብ ነው። በቤተሰብ የመጣችልህ ሴት አይነት ቫይብ ነው ያለው። ሮማንስ የለም በመሐከላችሁ። "በጊዜ ሒደት ትወዳታለህ!" ይሉሀል ግን እርገጠኛ አይደለህም።
......8.3/10

፨ Apple is excellent. ለጤና እጅግ ጠቃሚ ነው። ጣፋጭ ነው። መልከ መልካም ነው። የሚጣለው ነገሩ ጥቂት ነው።
መንገድ ላይ ብትገምጠው እንደ ሸንኮራ አያንገዳግድህም። እንደ ማንጎ አይጨማለቅም። እንደ ሙዝም ልጣጩን የት ልጣለው ብለህ አትጨነቅም።

The only problem i have with Apple is...it's not affordable. እግዜር ለምን አፕሏን እንዳትበሉ እንዳላቸው የሚገባህ ዋጋውን ስትሰማ ነው😑

መንግስት ብትሆንና ህዝብህን አፕል ማብላት ብትፈልግ የሆነ ኢንደስትሪን መጉዳት ይኖርብሀል። የመንግስት ሰራተኛ ብትሆንና አፕል መብላት ቢያምርህ በእግርህ ወደ ስራ መሔድ ይጠበቅብሀል። ከአፕሉ የምታገኘውን ቀልብ...ኢኮኖሚካል ቀውሱ ይወስድብሀል።

ሁሌም ጊዮን አልያም ሸራተን እንድትወስዳት የምትጠብቅ ቺክ ጋር የፍቅር ግንኙነት እንደመመስረት በለው። የከፈልከው ብር አናት የሚያዞር ከመሆኑ የተነሳ ቤት ገብታችሁ ልትተኛት አትሻም። ቁንጅናዋን የሚጋርድ ወጭ ነዋ ያስወጣችህ!
......9/10

፨ ብርቱካን!...
..ስለብርቱካን ምንም ከማለቴ በፊት አንድ ጥያቄ ልጠይቅ። ማንጎ የሚባል ሰው ታውቃላቹህ? አፕል የሚባል አጎት አለህ? ሸንኮራ የሚሏት አክስት አለችሽ? ከብርቱካን ውጭ ሰዎች ለልጃቸው መጠሪያ እስኪያደርጉት የተወደደ ፍሬ ምንድን ነው?

ይሕ የሆነው ያለምክኒያት አይደለም። ብርቱካን is an absolute perfection! እግዜር ለመኖሩ አንደኛው ኢቪደንስ ነው ልልም እችላለሁ🙂

ሽፋኑ ውስጡን በደንብ ከልሎት ስለቆመ እንደነ ፓፓዬ ቆዳው ላይ የሚፈጠር ችግር በቀላሉ ወደ ውስጥ ይገባል ብለህ አትሰጋም። ጠረኑ ደግሞ እጅግ ማራኪ ከመሆኑ የተነሳ እንደ ዕጣን የሚጠቀሙት አሉ።

ሳይዙ ያልበዛ ያላነሰ ነው። አንድ በልተህ በቃኝ ለማለት ይመቻል። ለሸክም፣ በኪስ ለመያዝም፤ ወርውሮ ለማቀበልም ይሆናል።

በዛ ላይ የውስጥ ልብስ ስላለው እንደ ከፈትከው እንደ ሌሎቹ መዝረብረብ አይጀምርም። በስነስርዓቱ ተደርድሮ ነው የሚጠብቅህ። በቀላሉ የወደድከውን ማንሳት ትችላለህ። ሳይዛቸውም አንዴ አንስቶ ለመጉረስ የሚመች ነው።

ጣዕሙ እንደ ሎሚ የኮመጠጠ እንደ ሸንኮራ የጣፈጠም አይደለም። በማር እና በኮምጣጤ መሐል ያለ ፐርፌክት ባላንስ ነው። ሁሉም ፍራፍሬዎች የሚሰጡህን ሴንሴሽን ብርቱካን ውስጥ ታገኘዋለህ ማለት ይቻላል። Simply magnificent.
......10/10

Via mivkel_azmeraw

ከሚሰራበት ድርጅት ውስጥ ተሽከርካሪ በመሰወርና አካሉ እንዲበተን ያደረገ ግለሰብ ከስድስት ግብረ አበሮቹ ጋር በቁጥጥር ስር ዋለ።                                       ...
24/06/2026

ከሚሰራበት ድርጅት ውስጥ ተሽከርካሪ በመሰወርና አካሉ እንዲበተን ያደረገ ግለሰብ ከስድስት ግብረ አበሮቹ ጋር በቁጥጥር ስር ዋለ።
***
አበራ መረሳ የተባለው ተጠርጣሪ ወንጀሉን የፈፀመው ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ/ም በአሽከርካሪነት ተቀጥሮ ከሚሰራበት ቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 3 ልዩ ቦታው ስታዲየም አካባቢ ከሚገኝ አንድ የኮንስትራክሽን ድርጅት ነው፡፡

ተጠርጣሪው ወንዶሠን አባተ፣ ሶይብ ሙኒር፣ ክንዱ ደጉ፣ ስንታየሁ ተመስገንን፣ ብሩክ ግርማ፣ ባህሉ ሲሳይ ከተባሉ አባሪዎቹ ጋር በመመሳጠር ግምቱ 18 ሚሊየን ብር የሚያወጣ የሠሌዳ ቁጥር ኮድ 3 አ/አ 48 4 05 HILUX ፒካፕ ተሽከርካሪን ከድርጅቱ ይዞ በመውጣት ከአንድ ግለሰብ ጋር በ 6መቶ ሺ ብር ለመሸጥ ተስማምቷል።

ግለሰቡ ቀደም ብሎ የሽያጩን ቀብድ 110 ሺህ ብር በመቀበልና ከግብረ አበሮቹ ጋር በመሆን አዳማ ከተማ ላይ የተሽከርካሪውን አካል በመነቃቃልና በመበታተን በአንድ መጋዘን ውስጥ አስቀምጧል፡፡

የወንጀል ድርጊቱን ሲያጣራ የነበረው በቦሌ ክ/ከተማ ፖሊስ ዋና መምሪያ የአደይ አበባ ስታዲየም አካባቢ ፖሊስ መምሪያ ሲሆን ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ/ም ከሀገር መከላከያ፣ ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት እንዲሁም ከአዳማ ከተማ ፖሊስ ጋር በመቀናጀት በወንጀሉ ተሳታፊ የሆኑ በአጠቃላይ 7 ተጠርጣሪዎችን ከነ ኤግዚቢቱ በቁጥጥር ሊያውልም ችሏል፡፡

የመንግስትም ሆና የግል ድርጅቶች ሠራተኞችን ሲቀጥሩ የሠራተኞቻቸውን ማንነት የሚገልጽ አስፈላጊ ሠነዶች አሟልተው መሆን እንዳለበት የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ መልዕክቱን አስተላልፏል።

ዘገባ፦ ዋና ሳጅን ደጀኔ ኡልፋታ [አዲስ አበባ ፖሊስ]

የትዝታ እና የሐቂባ ሚስጥራዊ ኮድ 🔥🔥
21/06/2026

የትዝታ እና የሐቂባ ሚስጥራዊ ኮድ 🔥🔥

ወደ 1960ዎቹ እና 70ዎቹ የሙዚቃ ወርቃማ ዘመን እንመለስ። አዲስ አበባ በዘመናዊ ሙዚቃ ስትናወጥ፣ ታላቁ...

ነፍስ ይማር!አንጋፋው የሙዚቃ ፕሮዲውሠር እና ማናጀር አዲስ ገሠሠ ከዚህ አለም ድካም ማረፉ ተሠምቷል።ከጃኖ ባንድ ምስረታ እስከ አለም አቀፍ መድረኮች ለሃገራችን ሙዚቃ እድገት ያበረከተዋ አሰ...
19/06/2026

ነፍስ ይማር!
አንጋፋው የሙዚቃ ፕሮዲውሠር እና ማናጀር አዲስ ገሠሠ ከዚህ አለም ድካም ማረፉ ተሠምቷል።
ከጃኖ ባንድ ምስረታ እስከ አለም አቀፍ መድረኮች ለሃገራችን ሙዚቃ እድገት ያበረከተዋ አሰተዋጽኦ ይዘርዘር ቢባል ቦታ አይበቃውም። የዳሎል ባንድ አባል እና የድምጻዊ ቴዲ አፍሮ ማናጀር በመሆን ሲያገለግል የቆየው አንጋፋው ባለሙያ አዲስ ከዚህ አለም በመለየቱ የተሠማንን ጥልቅ ሃዘን እየገለጽን ለቤተሠቦቹ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹ እና ለስራ ባልደረቦቹ መጽናናትን እንመኛለን።

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when LELA News posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to LELA News:

Shortcuts

Share