EyohaMedia

EyohaMedia Official Page of EyohaMedia, The premier destination to watch and share original videos related to Ethiopia.
(1)

የሮማ ካቶሊካዊት ቤተ-ክርስቲያን አዲሱ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳስ ሮበርት ፕሬቮስት መሆናቸው ታውቋል።ቤተ-ክርስቲያኒቱን ሲመሩ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳስ ሊዎ 14ኛ ተብለው ይጠራሉ። የ69 ዓመት እድሜ ባለፀ...
08/05/2025

የሮማ ካቶሊካዊት ቤተ-ክርስቲያን አዲሱ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳስ ሮበርት ፕሬቮስት መሆናቸው ታውቋል።

ቤተ-ክርስቲያኒቱን ሲመሩ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳስ ሊዎ 14ኛ ተብለው ይጠራሉ።

የ69 ዓመት እድሜ ባለፀጋ የሆኑት ሮበርት ፕሬቮስት የመጀመሪያው አሜሪካዊ የሮማ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳስ ሆነዋል።

አንድ ሊትር ቤንዚን 122 ብር ከ53 ሳንቲም ሲገባ አንድ ሊትር ነጭ ናፍጣ 116 ብር ከ49 ሳንቲም  ገባ።የኢፌዴሪ ንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚንስቴር ዛሬ ለነዳጅ አቅራቢ ድርጅቶች ባሰራጨዉ ...
08/05/2025

አንድ ሊትር ቤንዚን 122 ብር ከ53 ሳንቲም ሲገባ አንድ ሊትር ነጭ ናፍጣ 116 ብር ከ49 ሳንቲም ገባ።

የኢፌዴሪ ንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚንስቴር ዛሬ ለነዳጅ አቅራቢ ድርጅቶች ባሰራጨዉ ሰርኩላር ከዛሬ ሚያዚያ 30/2017 ዓ/ም ምሽት 12 ሠዓት ጀምሮ የነዳጅ ምርቶች ላይ የዋጋ ጭማሪ ተደርጓል።

በዚህም መሰረት ፦

➡ አንድ ሊትር ቤንዚን 122 ብር ከ53 ሳንቲም

➡ አንድ ሊትር ነጭ ናፍጣ 116 ብር ከ49 ሳንቲም

➡ አንድ ሊትር ኬሮሲን 116 ብር ከ49 ሳንቲም ገብቷል።

በሌላ በኩል ፦

🔴 የአውሮፕላን ነዳጅ 113 ብር ከ20 ሳንቲም ከነበረበት ወደ 109 ብር ከ56 ሳንቲም ዝቅ ብሏል።

🔴 አንድ ሊትር ከባድ ጥቁር ናፍጣ 106 ብር ከ75 ሳንቲም ከነበረበት ወደ 104 ብር ከ08 ሳንቲም ዝቅ ብሏል።

🔴 አንድ ሊትር ቀላል ጥቁር ናፍጣ 109 ብር ከ22 ሳንቲም ከነበረበት 106 ብር 77 ሳንቲም ዝቅ ብሏል።

ኢትዮጵያን ከልብ፣ በእውቀት እና በርኅራኄ ያገለገሉት ስመ ጥሩ የልብ ሐኪም፣ ሰብዓዊ ተሳታፊ እና ሀገራዊ ጀግና ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ ከዚህ አለም ድካም አርፈዋል። ነፍስ ይማር‼️
04/05/2025

ኢትዮጵያን ከልብ፣ በእውቀት እና በርኅራኄ ያገለገሉት ስመ ጥሩ የልብ ሐኪም፣ ሰብዓዊ ተሳታፊ እና ሀገራዊ ጀግና ዶ/ር ፍቅሩ ማሩ ከዚህ አለም ድካም አርፈዋል።
ነፍስ ይማር‼️

የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የሀዘን መግለጫ ፦" የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን የጳጳሳት ጉባኤ ዛሬ በሰማነው እጅግ አሳዛኝ ዜና የብጹዕ ወቅዱስ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ ከ...
21/04/2025

የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን የሀዘን መግለጫ ፦

" የኢትዮጵያ ካቶሊክ ቤተክርስቲያን የጳጳሳት ጉባኤ ዛሬ በሰማነው እጅግ አሳዛኝ ዜና የብጹዕ ወቅዱስ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ፍራንችስኮስ ከዚህ አለም ድካም ማረፍ የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለጽን መላው ካቶሊካውያን እና በጎ ፈቃድ ላላቸው ሰዎች ሁሉ ለቅዱስ አባታችን ዘለዓለማዊ እረፍት በጸሎት አብራችሁ እንድትሆኑ ጥሪ እናቀርባለን።

ጌታ ሆይ ለሞቱት ሰዎች
የዘላለም እረፍት ስጣቸው
የዘላለም ብርሃን አብራላቸው
በሰላም አሳርፋቸው። "

ፖፕ ፍራንሲስ አረፉየሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ፖፕ ፍራንሲስ በ88 ዓመታቸው ማረፋቸውን ቫቲካን አስታውቃለች፡
21/04/2025

ፖፕ ፍራንሲስ አረፉ
የሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ፖፕ ፍራንሲስ በ88 ዓመታቸው ማረፋቸውን ቫቲካን አስታውቃለች፡

አርቲስት ሰለሞን ተካልኝ አረፈ። ግለሰቡ የህመም ሰሜት ተሰምቶት ሆስፒታል እንደደረሰ ነው ያረፈው ሲሉ ምንጮች ነግረውናል። የሞቱ መንስኤ ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ አልታወቀም።ምን...
21/04/2025

አርቲስት ሰለሞን ተካልኝ አረፈ። ግለሰቡ የህመም ሰሜት ተሰምቶት ሆስፒታል እንደደረሰ ነው ያረፈው ሲሉ ምንጮች ነግረውናል። የሞቱ መንስኤ ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ አልታወቀም።
ምንጭ- ዘሐበሻ

ከ14 ዓመት መለያየት በኃላ አርቲስት ገነት ንጋቱ እና  አርቲስት ሙሉጌታ ጀዋሬ በድጋሚ ተሞሽረዋል::ሁሉቱም በማልቀስ ደስታቸውን የገለፁ ሲሆን ሁሉንም ነገር ለፈጣሪ ሰጥተን ድጋሚ ትዳርን አ...
20/04/2025

ከ14 ዓመት መለያየት በኃላ አርቲስት ገነት ንጋቱ እና አርቲስት ሙሉጌታ ጀዋሬ በድጋሚ ተሞሽረዋል::

ሁሉቱም በማልቀስ ደስታቸውን የገለፁ ሲሆን ሁሉንም ነገር ለፈጣሪ ሰጥተን ድጋሚ ትዳርን አንድ ብለን ጀምረናል ያሉት ጥንዶች መልካም ምኞታችሁን ተመኙልን ብለዋል::

መልካም የትዳር ዘመን‼️

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ መልካም የትንሳኤ በዓል ይሁንላችሁ
20/04/2025

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ መልካም የትንሳኤ በዓል ይሁንላችሁ

የጌዲዮን ሙላቱ ስርዓተ ቀብር ተፈፀመበመቄዶንያ የአረጋውያንና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል ቀደምት ተገልጋይ የነበረው የጌዲዮን ሙላቱ ስርዓተ ቀብር መቄዶንያ የአረጋውያንና የአእምሮ ህሙማን...
13/04/2025

የጌዲዮን ሙላቱ ስርዓተ ቀብር ተፈፀመ

በመቄዶንያ የአረጋውያንና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል ቀደምት ተገልጋይ የነበረው የጌዲዮን ሙላቱ ስርዓተ ቀብር መቄዶንያ የአረጋውያንና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል ፊት ለፊት በሚገኘው አያት መድኃኒዓለም ቤተክርስቲያን ተፈፅሟል።

በስርዓት ቀብሩ ላይ የመቄዶንያ የአረጋውያንና የአእምሮ ህሙማን መርጃ ማዕከል መስራች እና ዋና ሥራ አስኪያጅ ቢኒያም በለጠ እንዲሁም የማዕከሉ አረጋውያንና ወደጆቹ መገኘታቸውን የማዕከሉ መረጃ ያመላክታል።

ጌዲዮን በበርካታ ሆስፒታሎች የልብ ሕክምና ሲደረግለት የነበረ ሲሆን፥ በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በድንገተኛ ሕክምና ክፍል ተኝቶ ልዩ ክትትል እየተደረገለት በትናንትናው ዕለት ሚያዝያ 4 ቀን 2017 ዓ.ም በተወለደ በ37 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።

"ቀለል ያለውን አድርጎልኛል እግዚአብሔር ይመስገን በዚህ ሳምንት ወደ ስራ እመለሳለሁ ‼️" ሰይፉ ፋንታሁንጨርሶ ይማርህ ሰይፉ ወንድማችን🙏
12/04/2025

"ቀለል ያለውን አድርጎልኛል እግዚአብሔር ይመስገን በዚህ ሳምንት ወደ ስራ እመለሳለሁ ‼️" ሰይፉ ፋንታሁን

ጨርሶ ይማርህ ሰይፉ ወንድማችን🙏

ቀብር  | በመቄዶንያ ማህበረሰብ፣ በጎብኚዎቻችንና በረጂዎቻችን ዘንድ ተወዳጅ የነበረውና የመቄዶንያ ቀደምት ተገልጋይ የነበረው ጌዲዮን ሙላቱ በዛሬው ዕለት በማረፉ እጅግ ከፍተኛ ሀዘን ተሰምቶ...
12/04/2025

ቀብር

| በመቄዶንያ ማህበረሰብ፣ በጎብኚዎቻችንና በረጂዎቻችን ዘንድ ተወዳጅ የነበረውና የመቄዶንያ ቀደምት ተገልጋይ የነበረው ጌዲዮን ሙላቱ በዛሬው ዕለት በማረፉ እጅግ ከፍተኛ ሀዘን ተሰምቶናል።

ጌዲ በ1980 ዓ.ም አዲስ አበባ ጎላ ሚካኤል አከባቢ ተወልዶ ያደገ ሲሆን በ1999 ዓ.ም የ19 ዓመት ወጣት ሆኖ ባጋጠመው ድንገተኛ አደጋ በስትሮክ ምክንያት ከአንገቱ በታች ፓራላይዝድ ሆኖ ሰውነቱን ማዘዝና በአንደበቱ መናገር አይችልም ነበር።

እናትና አባቱ ከሱ ጉዳት በፊት ስለሞቱ አክስቱ እየተንከባከበችው ጎላ ሚካኤል በሚገኘው ጠባብ ቤት ውስጥ ለብዙ ዓመታት የአልጋ ቁራኛ ሆኖ እየተሰቃየ የኖረ ሲሆን በ2005 ዓ.ም ወደ መቄዶንያ ማዕከል ሲገባ መናገር የማይችለው ጌዲ ደስታውን የገለፀው በብዙ እንባ ነበር፡፡

ጌዲ በመቄዶንያ ግቢ ውስጥ ልዩ መኝታ ክፍል ተሰጥቶት በየዕለቱ ልዩ ልዩ እንክብካቤና ህክምና እየተሰጠው በደስታ ይኖር ነበር፡፡

በተለያዩ ትልልቅ ሆስፒታሎች የልብ ህክምና ሲደረገለት የነበረ ሲሆን በጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በድንገተኛ ህክምና ክፍል ተኝቶ ልዩ ክትትል እየተደረገለት በዛሬው ዕለት ሚያዝያ 4 ቀን 2017 ዓ.ም ረፋድ 5:00 ሰዓት በህክምና ላይ እያለ በ37 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቶናል፡፡

ህይወቱን ለማትረፍ የጥቁር አንበሳ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ስፔሻሊስት ሐኪሞችና የጤና ባለሙያዎች ከፍተኛ ርብርብ አድርገው የነበረ ሲሆን ላደረጉት ርብርብ እጅግ አድርገን ለማመስገን እንወዳለን።

ለመቄዶንያ መስራቾች ብንያምና እሌኒ፣ ለአረጋውያኑና አዕምሮ ህሙማኑ፣ ለመቄዶንያ ሰራተኞችና በጎ ፈቃደኞች እንዲሁም ለጎብኚዎቻችንና ለለጋሾቻችን በሙሉ መፅናናትን እንመኛለን።

ፈጣሪ ነፍሱን በአፀደ ገነት ያኑርልን!

የጌዲዮን ሙላቱ የቀብር ስነ-ስርዓት ነገ ረፋድ መቄዶንያ ፊትለፊት አያት መድኃኒዓለም ቤ/ክ ይከናወናል

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1446ኛ ኢድ አለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1446ኛ ኢድ አል-ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ!  ኢድ ሙባረክ!
30/03/2025

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1446ኛ ኢድ አለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1446ኛ ኢድ አል-ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ!
ኢድ ሙባረክ!

Address

Africa Avenue/Bole Road
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when EyohaMedia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to EyohaMedia:

Share