EyohaMedia

EyohaMedia Official Page of EyohaMedia, The premier destination to watch and share original videos related to Ethiopia.

ነገ የሚዘጉ መንገዶች ይፋ ሆኑ።ነገ መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ/ም በመስቀል አደባባይ ከሚከበረው የመስቀል ደመራ በዓል ጋር በተያያዘ ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊ...
25/09/2025

ነገ የሚዘጉ መንገዶች ይፋ ሆኑ።

ነገ መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ/ም በመስቀል አደባባይ ከሚከበረው የመስቀል ደመራ በዓል ጋር በተያያዘ ለተሽከርካሪ ዝግ የሚሆኑ መንገዶችን የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ይፋ አደርጓል።

በዚህም መሠረት ፦

- ከቅዱስ ኡራኤል አደባባይ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል አደባባይ፣

- ከቦሌ አቅጣጫ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ኦሎምፒያ አደባባይ ላይና ታች እንዲሁም ግራና ቀኝ፣

- ከመስቀል ፍላወር ወደ ኦሎምፒያ የሚወስደው መንገድ ጋዜቦ አደባባይ፣

- ከአጎና ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ለከባድ ተሽከርካሪ አጎና ሲኒማ አጠገብ እንዲሁም ለቀላል ተሽከርካሪ ጥላሁን አደባባይ (አራተኛ ክፍለ ጦር)፣

- ከለገሀር መብራት ወደ መስቀል አደባባይ ለገሀር መብራት፣

- ከቴሌ ማቋረጫ ወደ ስታድዮም ለሚጓዙ ቴሌ ማቋረጫ፣

- ከራስ ሆቴል ወደ ስታድየም ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች ራስ ሆቴል፣

- ከሐራምቤ መብራት ወይም ከአምባሳደር ሲኒማ ወደ መስቀል አደባባይ ሃራምቤ መብራት፣

- ከብሔራዊ ቤተ መንግስት ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ብሔራዊ ቤተ መንግስት አጠገብ፣

- ከዛንቺስ ሼል ወደ ባምቢስ የሚወስደው መንገድ ከዛንቺስ ሼል አጠገብ፣

- ከጁፒተር ሆቴል ወደ ECA የሚወሰደው መንገድ ባምቢስ ሳልኮት ህንፃ አጠገብ ከነገ መስከረም 16 ቀን 2018 ዓ/ም ከረፋዱ 4፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ መርሀ ግብሩ ፍፃሜ ድረስ መንገድ ይዘጋል።

በተገለፁት መስመሮች ላይ ተሽከርካሪዎችን ለአጭርም ይሁን ለረዥም ጊዜ ማቆም የተከለከለ መሆኑን ፖሊስ አሳስቧል።

አሽከርካሪዎች አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ጥሪ ቀርቧል።

ህብረተሰቡ ለፀጥታ ስጋት የሆኑ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙት በ011-1-11-01-11 እንዲሁም በ991 ነፃ የስልክ መስመር ጥቆማ እንዲሰጥ ጥሪ ተላልፏል።

አትሌት ሸዋረግ  አለን አማረ አረፈች   | አትሌቷ ትላት በአዲስ አበባ ዙሪያ በልምምድ እያለች ነው የድካም ስሜት ተሰምቷት ወደ ሆክፒታል ተወሰዳ  እንዳረፈች ነው የደረሰኝ መረጃ የሚጠቁመው...
24/09/2025

አትሌት ሸዋረግ አለን አማረ አረፈች
| አትሌቷ ትላት በአዲስ አበባ ዙሪያ በልምምድ እያለች ነው የድካም ስሜት ተሰምቷት ወደ ሆክፒታል ተወሰዳ እንዳረፈች ነው የደረሰኝ መረጃ የሚጠቁመው ።
ኑሮዋን በላቲን አሜሪካ ሜክስኮ ያደረገችው ፤ አለሽኝ የ2025 የሲውድን ስቶኮልም ማራቶን አሸናፊ ስትሆን ለልምምድ አዲስ አበባ መጥታ ነው ህይወቷ ያለፈው።
አትሌቷ የቀድሞ አትሌት አለነ አማረ ልጅ ስትሆን የቀድሞ አትሌት አለነ አማረ ደግሞ ኑሮውን በአሜሪካ ኒዮርክ ካደረገ ከ25 አመት በላይ ሆኖቷል።
Shewarge Alene, our 2025 Stockholm Marathon champion.
Mexico City Marathon - 2012 & 2014
Santiago de Chile Marathon - 2013 & 2014
Maratón Internacional Lala - 2014
Via

ኬንያ ለአትሌቶቿ የገንዘብ ሽልማት አበረከተችየኬንያ መንግስት ለአትሌቶች የገንዘብ ሽልማት ያበረከተ ሲሆን፤ በተጠናቀቀው የቶኪዮ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኬንያ በአጠቃላይ በ11 ሜዳሊያዎች...
24/09/2025

ኬንያ ለአትሌቶቿ የገንዘብ ሽልማት አበረከተች

የኬንያ መንግስት ለአትሌቶች የገንዘብ ሽልማት ያበረከተ ሲሆን፤ በተጠናቀቀው የቶኪዮ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ኬንያ በአጠቃላይ በ11 ሜዳሊያዎች ሁለተኛ ሆና አጠናቃለች።

በዚህም መሠረት ፡-

የወርቅ ሜዳሊያ አሸናፊዎች - 3 ሚሊዮን ሽልንግ ($23,000) ለእያንዳንዳቸው
የብር ሜዳሊያ አሸናፊዎች - 2 ሚሊዮን ሽልንግ ($15,000) ለእያንዳንዳቸው
የነሐስ ሜዳሊያ አሸናፊዎች - 1 ሚሊዮን ሽልንግ ($7,000) ለእያንዳንዳቸው
ተበርክቶላቸዋል፡፡

 " እስራኤል እና ፍልስጤም ጎን ለጎን በሰላም መኖር ይችላሉ " - ማክሮንፈረንሳይ ለፍልስጤም አገርነት በይፋ ዕውቅና ሰጠች።በኒው ዮርክ የተባበሩት መንግሥታት ጉባዔ ላይ የፈረንሳዩ ፕሬዝዳን...
23/09/2025



" እስራኤል እና ፍልስጤም ጎን ለጎን በሰላም መኖር ይችላሉ " - ማክሮን

ፈረንሳይ ለፍልስጤም አገርነት በይፋ ዕውቅና ሰጠች።

በኒው ዮርክ የተባበሩት መንግሥታት ጉባዔ ላይ የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ኢማኑኤል ማክሮን ለፍልስጤም አገርነት ዕውቅና ሰጥተዋል።

የፈረንሳዩ ፕሬዝዳንት ማክሮን በጋዛ ያለው ጦርነት መቆም እንዳለበትና ታጋቾች መለቀቅ እንደሚገባቸው ገልጸዋል።

" ማብቂያ የሌለው አጥፊ ጦርነት መገታት አለበት። ከኃያልነት በላይ መብትን ማክበር መቅደም አለበት " ብለዋል።

ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በመካከለኛው ምሥራቅ ዘላቂ ሰላም ማስፈን አንደተሳነው ፕሬዝዳንቱ ጠቅሰዋል።

" የሁለት አገራት መፍትሔን ለመተግበር የተቻለንን ማድረግ አለብን። እስራኤል እና ፍልስጤም ጎን ለጎን በሰላም መኖር ይችላሉ " ብለዋል።

ኡስማን ዴምቤሌየ2025 ባሎንዶር አሸናፊ ( ንጉሥ )  ሆኗል   | የ2025 ባሎንዶር አሸናፊን ( ንጉሥ ) ለማሳወቅ ብራዚላዊው የእግር ኳሱ ጥበበኛ ሮናልዲኒሆ ወደ መድረኩ ወጣ። ቪቲኒሃ ሦ...
23/09/2025

ኡስማን ዴምቤሌ
የ2025 ባሎንዶር አሸናፊ ( ንጉሥ ) ሆኗል
| የ2025 ባሎንዶር አሸናፊን ( ንጉሥ ) ለማሳወቅ ብራዚላዊው የእግር ኳሱ ጥበበኛ ሮናልዲኒሆ ወደ መድረኩ ወጣ።
ቪቲኒሃ ሦስተኛ ፣
ሞ ሳላህ አራተኛ መሆናቸው ከመድረክ ተገልፆል።
የቀሩት ኡስማን ዴምቤሌ እና ላሚን ያማል ተፋጠዋል።
የባላንዶር እጩዎች ቤተሰቦች ብቻ ሳይሆን ዝግጅቱን በቀጥታ የሚመለከት ሁሉ ጉጉት ውስጥ ሰጠመ።
ሮናልዲኒሆ ጎቾ የባሎንዶሩን አዲሱን ንጉሥ ስሙን በክብር ጠራው ።
ኡስማን ዴምቤሌ
የ2025 ባሎንዶር አሸናፊ ሆኗል።

የባሏን ገደይ ይቅር ያለችው ሚስት‼️አሪዞና — ዛሬ በአሪዞና ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕን ጨምሮ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በተገኙበት የቻርሊ ከርክ የቀብር ስነስርዓት ላይ፣ ባለቤቱ ኤሪካ ...
22/09/2025

የባሏን ገደይ ይቅር ያለችው ሚስት‼️
አሪዞና — ዛሬ በአሪዞና ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕን ጨምሮ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች በተገኙበት የቻርሊ ከርክ የቀብር ስነስርዓት ላይ፣ ባለቤቱ ኤሪካ ከርክ አስደንጋጭ በሆነ ንግግር የባሏን ገዳይ ይቅር እንዳለች ተናገረች። ኤሪካ እንዲህ ብላለች፡- "እሱንም ይቅር ብዬዋለሁ፣ ምክንያቱም ክርስቶስ ያደረገው እንደሱ ነው፤ ቻርሊም ቢሆን የሚያደርገው እንዲሁ ነው።" ኤሪካ ንግግሩን ያደረገችው፣ በተለያዩ ሚዲያዎች እንደተዘገበው ከሆነ፣ ከባሏ ሞት በኋላ ገዳዩን ይቅር ማለቷ ብዙዎችን አስገርሟል፤ ሆኖም ለብዙዎች እንደ ትልቅ የይቅርታ ምሳሌ ሆኖ ታይቷል።

" ሦስት ሀገር ሆነን ነው የሄድነው፤ አንተዋወቅም!! "ኢትዮጵያ በቶኪዮ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከ34 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ያለ ወርቅ ሜዳልያ ማጠናቀቋን ተከትሎ፣  የኦሎምፒክ ...
22/09/2025

" ሦስት ሀገር ሆነን ነው የሄድነው፤ አንተዋወቅም!! "

ኢትዮጵያ በቶኪዮ የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና ከ34 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ያለ ወርቅ ሜዳልያ ማጠናቀቋን ተከትሎ፣ የኦሎምፒክ ሻምፒዮኑ አትሌት ሰለሞን ባረጋ ለውድቀቱ ዋነኛ ምክንያት የነበረውን የውስጥ ችግር በዝርዝር አጋልጧል። ሰለሞን ከ"ኢትዮ ራነርስ" ጋር ባደረገው ቃለ-መጠይቅ፣ በቡድኑ ውስጥ የነበረው "አብሮ አለመስራት" እና የዝግጅት ክፍተቶች ለውጤቱ መጥፋት ዋነኛ መንስኤ መሆናቸውን በምሬት ተናግሯል።

"ትልቁ ችግራችን እና የውጤት መጥፋት ምክንያት አብሮ አለመስራታችን ነው" ያለው ሰለሞን፣ በ10,000 ሜትር ውድድር ላይ ከበሪሁ አረጋዊ እና ከዮሚፍ ቀጀልቻ ጋር የነበራቸውን ግንኙነት ሲገልጽ "ሶስታችን ሶስት ሀገር ሆነን ነው የሄድነው" ብሏል።

"አንተዋወቅም፤ አያውቀኝም፤ አላውቀውም። ውድድሩ ስንገባ አልተነጋገርንም" ሲል በግልጽ ተናግሯል። ይህም በቡድን መሮጥ በሚጠይቅ የረጅም ርቀት ውድድር ላይ አትሌቶቹ ምንም አይነት የጋራ ስልት እንዳልነበራቸው ያሳያል።
ሰለሞን የፌዴሬሽኑን የዝግጅት ሂደትም በጽኑ ተችቷል። "ሆቴል መግባታችን ትልቁ ዓላማው አብሮ ለመስራት ነው" ያለው አትሌቱ፣ ነገር ግን አሰልጣኞቻቸው ከእነሱ ጋር እንዳልነበሩ እና የጋራ የልምምድ እቅድ እንዳልነበራቸው ገልጿል።
"ቶኪዮ ሆነን እኮ ትሬኒንግ በራሳችን እንደፈለግን ነው የምንወጣው። ማንም የሚያዝ፣ ማንም የሚከታተል የለም" በማለት በሻምፒዮናው ወቅት እንኳን የነበረውን የቁጥጥር መላላት አጋልጧል።

አትሌቶቹ በቀደሙት ውድድሮች (ለምሳሌ ኦሎምፒክ) ይቀርብባቸው የነበረውን ትችት በመስጋት በውድድሩ ወቅት ውሳኔ ለመውሰድ እንደተቸገሩ ሰለሞን ተናግሯል። "ትላንት የተወቀስንበትን እናውቃለን፤ ያንን እያሰብክ ገብተህ እንደገና ስህተት እሰራለሁ ብለህ ትጠነቀቃለህ" ብሏል። ሰለሞን በቀጣይ ሀገሩን ወክሎ ሲሮጥ "ነገሮች ካልተስተካከሉ በቀር" በዚህ መልኩ እንደማይቀጥል ጠንከር ያለ መልዕክት አስተላልፏል። የአትሌት ሰለሞን ቃለ-መጠይቅ፣ የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ውድቀት ከግለሰብ አትሌቶች ብቃት በላይ የሆነ የቡድን ስራ፣ የዝግጅት እና የአመራር ችግር ውጤት መሆኑን ያጋለጠ ነው። ፌዴሬሽኑ በቀጣይ እነዚህን መሰረታዊ ችግሮች ለመፍታት ምን አይነት እርምጃ ይወስዳል የሚለው በጉጉት ይጠበቃል።

የትምህርት ሚኒስቴር መልዕክት!...በ2017 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ የማለፊያ ውጤት ላመጣችሁ ተማሪዎች በሙሉ፤በ2017 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃ...
22/09/2025

የትምህርት ሚኒስቴር መልዕክት!...

በ2017 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ የማለፊያ ውጤት ላመጣችሁ ተማሪዎች በሙሉ፤

በ2017 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ የዩኒቨርስቲ መግቢያ ውጤት ያመጣችሁና ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ) ለመማር ፍላጎት ያላችሁ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ እና የትምህርት መስክ ምርጫችሁን በየትምህርት ቤታችሁ በተወከሉ መምህራን በኩል እስከ መስከረም 14/2018 ዓ.ም ድረስ ማስተካከል የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

ማሳሰቢያ፡-

1. የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ከ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ጀምሮ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ተማሪዎችን ስሚቀበል ምርጫችሁ ውስጥ ማካተት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።

2.አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ አዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ እና አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲዎች ምርጫ ውስጥ የማይካተቱ መሆኑ እናሳውቃለን።

በአዲስ አበባውና በአንዳንድ አካባቢዎች መብራት ተለቋል‼"አዎ መብራት ተቋርጧል!" -የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በአዲስ አበባ እና በተወሰኑ የክልል ከተሞች በከፊል የኃይል መቋረጥ ተከስቷል!...
21/09/2025

በአዲስ አበባውና በአንዳንድ አካባቢዎች መብራት ተለቋል‼

"አዎ መብራት ተቋርጧል!"
-የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል

በአዲስ አበባ እና በተወሰኑ የክልል ከተሞች በከፊል የኃይል መቋረጥ ተከስቷል!

ከሰበታ ቁጥር 1 የኃይል ማከፋፊያ ጣቢያ ወደ ጥቁር አንበሳ ኃይል ማከፋፊያ ጣቢያ፤ ከጥቁር አንበሳ ኃይል ማከፋፊያ ጣቢያ ወደ አዲስ ዌስት ወይም ኮልፌ ማከፋፈያ ጣቢያ በተዘረጋዉ 132 ኪ.ቮ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ መደበኛ የጥገና ሥራ ሲከናወን ውሏል፡፡

ይሁንና ጥገናው ተጠናቆ መስመር በሚሞከርበት ጊዜ በተፈጠረ የመስመሮች መነካካት በአዲስ አበባ እና በተወሰኑ የክልል ከተሞች የኃይል አቅርቦት ተቋርጧል ሲል ጠቁሟል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባወጣው መግለጫ የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት ርብርብ እየተደረገ በመሆኑ መስመር በተቋረጠባቸው አካባቢዎች የምትገኙ ደንበኞቻችን በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እንጠይቃለን ብሏል።

አርሰናል እና ማንችስተር ሲቲ አቻ ተለያዩ   |  በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የአምስተኛ ሳምንት ተጠባቂ  መርሃ ግብር  አርሰናል እና ማንችስተር ሲቲ አንድ አቻ ተለያይተዋል።ማምሻውን በኤምሬት...
21/09/2025

አርሰናል እና ማንችስተር ሲቲ አቻ ተለያዩ

| በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የአምስተኛ ሳምንት ተጠባቂ መርሃ ግብር አርሰናል እና ማንችስተር ሲቲ አንድ አቻ ተለያይተዋል።

ማምሻውን በኤምሬትስ ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ አርሊንግ ሃላንድ በዘጠነኛው ደቂቃ ያስቆጠራት ጎል ሲቲ መሪ ሆኖ ነበር።

ይሁንና ተቀይሮ የገባው ጋብርኤል ማርቲኔሊ በ93ኛው ደቂቃ አርሰናል አቻ ያደረገችውን ወሳኝ ግብ ከመረብ ላይ አሳርፏል።

በጨዋታው አርሰናል የኳስ ቁጥጥር ብልጫ የወሰደ ሲሆን የቆሙ ኳሶችን ተጠቅሞ ግብ ለማስቆጠር ጥረት ሲያደርግ ታይቷል።

ማንችስተር ሲቲ በመልሶ ማጥቃት የጨዋታ ስልት እና በፈጣን ሽግግር ወደ ተጋጣሚው የግብ ክልል በመድረስ ግብ የማስቆጠር ስትራቴጂን ተግብሯል።

ውጤቱን ተከትሎ አርሰናል በ10 ነጥብ ሁለተኛ ደረጃን ይዟል።

ማንችስተር ሲቲ በሰባት ነጥብ ዘጠነኛ ደረጃ ላይ ይገኛል።

ዛሬ በተደረጉ ሌሎች የአምስተኛ ሳምንት መርሃ ግብሮች ሰንደርላንድ እና አስቶንቪላ አንድ አቻ ሲለያዩ የቦርንማውዝ እና ኒውካስትል ዩናይትድ ጨዋታ ያለ ግብ በአቻ ውጤት ተጠናቋል።

21/09/2025
ጭማሪው አልተራዘመም‼️ከያዝነው መስከረም ወር ጀምሮ ለመንግሥት ሠራተኞች ይፋ የተደረገው የደሞዝ ማሻሻያ አልተራዘመም፣ከመስከረም ወር ጀምሮ ታሳቢ የተደረገ የደመወዝ ክፍያ ይፈፀማል።"ተራዝሟል...
21/09/2025

ጭማሪው አልተራዘመም‼️
ከያዝነው መስከረም ወር ጀምሮ ለመንግሥት ሠራተኞች ይፋ የተደረገው የደሞዝ ማሻሻያ አልተራዘመም፣ከመስከረም ወር ጀምሮ ታሳቢ የተደረገ የደመወዝ ክፍያ ይፈፀማል።
"ተራዝሟል የሚለው መረጃ ከየት እንደመጣ አላውቅም። መረጃው ለህዝብ ይፋ ከተደረገ ጀምሮ ከመስከረም የሚጀምር የደሞዝ ጭማሪ ለማስፈፀም ስራ ስንሰራ ቆይተናል"- ሲሉ የሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ባልደረባ ተናግረዋል።
በዚህም አዲስ የደሞዝ ማሻሻያ መሰረት ዝቅተኛው የመንግሥት ሠራተኛ ደሞዝ ከብር 4,760 ወደ ብር 6,ዐዐዐ እንዲያድግ መደረጉ ይታወሳል። በተጨሜሪም ከፍተኛው የመንግሥት ሠራተኛ ደሞዝ ከብር 21,492 ወደ ብር 39,000 እንዲሁም የዲግሪ ተመራቂ መነሻ ደመወዝ ከብር 6,940 ወደ ብር 11,500 መደረጉ በወቅቱ ይፋ ተደርጎ ነበር። ይህም ለደመወዝ የሚወጣውን ጠቅላላ ዓመታዊ የመንግሥት ወጪ 56ዐ ቢሊዮን ብር ያደርሰዋል ተብሏል።
#መሰረትሚዲያ

Address

Africa Avenue/Bole Road
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when EyohaMedia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to EyohaMedia:

Share