EyohaMedia

EyohaMedia Official Page of EyohaMedia, The premier destination to watch and share original videos related to Ethiopia.
(1)

“ብርቱዋ ገበሬ በፈተና ላይ ናት›— የበረከት ገበሬዋ ወቅታዊ የጤና ሁኔታ መረጃአዲስ አበባ — መጋቢት 12 ፣ 2018 ዓ.ም ለብዙዎች የጥንካሬ ተምሳሌትና የሥራ ወዳድነት ተምሳሌት የሆነችው ...
21/03/2026

“ብርቱዋ ገበሬ በፈተና ላይ ናት›— የበረከት ገበሬዋ ወቅታዊ የጤና ሁኔታ መረጃ
አዲስ አበባ — መጋቢት 12 ፣ 2018 ዓ.ም ለብዙዎች የጥንካሬ ተምሳሌትና የሥራ ወዳድነት ተምሳሌት የሆነችው በረከት ገበሬዋ፣ በአሁኑ ወቅት በፅኑ ታማ በሕክምና ላይ እንደምትገኝ ታውቋል። "ወደ ሥራዋ ለምን አልተመለሰችም?" በሚል ከደጋፊዎቿ ለቀረቡ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች ምላሽ የሚሆን መረጃ ከቅርብ ምንጮች ለማግኘት ተችሏል።
በረከት ገበሬዋ በእስር ላይ በነበረችበት ወቅት በገጠማት የጤና መታወክ ምክንያት በፖሊስ ሆስፒታል ተኝታ የነበረ ቢሆንም፣ በወቅቱ በቂ የሕክምና እርዳታ ባለማግኘቷ በጤናዋ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባታል።
እንደ ምንጮቻችን ገለጻ፣ የበረከት ሕመም ከደም መረጋት (Blood Clotting) ጋር የተያያዘ ሲሆን ለህይወቷም አስጊ ነው ተብሏል::
ከእስር ከተፈታች በኋላ በተለያዩ የመንግሥት እና የግል ሆስፒታሎች የሕክምና ክትትል ስታደርግ ቆይታለች።
ይሁን እንጂ ካለፈው ቅዳሜ ጀምሮ ጤንነቷ በእጅጉ አሳሳቢ ደረጃ ላይ በመድረሱ፣ በአሁኑ ሰዓት በጦር ኃይሎች ሪፈራል ሆስፒታል ተኝታ በልዩ ባለሙያዎች ጥብቅ ክትትል እየተደረገላት ይገኛል።
የጤና ባለሙያዎቹ የሚያደርጉት ጥረት ተሳክቶ፣ በቅርቡ ሙሉ ጤንነቷ ተመልሶ ከሆስፒታል አልጋ እንድትነሳ ልባዊ ጸሎታችን ነው።
በረከት ገበሬዋ ለብዙ ኢትዮጵያውያን ሴቶች የሥራ ክብርን ያስተማረች የቁምነገር ተምሳሌት ናት።
ይህንን አስቸጋሪ ጊዜ በድል ተወጥታ፣ ፈጣሪ ሙሉ ጤንነቷን እንዲመልስላትና ዳግም ወደ የምትወደው የእርሻ ሥራዋ እንድትመለስ ከልብ እንመኛለን።
ፈጣሪ ምሕረቱን ይላክልሽ 🙏
ጉርሻ page

"በቅርቡ ለታጨሁት የ Best Female Artist of 2026 ካሸነፍኩ ከ $55,000 ሽልማቴ ግማሹን ለቤተክርስቲያን እሰጣለሁ" አርቲስት ቬሮኒካ አዳነመልካም ዕድል‼️
18/03/2026

"በቅርቡ ለታጨሁት የ Best Female Artist of 2026 ካሸነፍኩ ከ $55,000 ሽልማቴ ግማሹን ለቤተክርስቲያን እሰጣለሁ" አርቲስት ቬሮኒካ አዳነ

መልካም ዕድል‼️

 የዒድ አልፈጥር በዓል አርብ (ጁምዓ) ይውላል።ዛሬ የሸዋል ወር ጨረቃ ባለመታየቷ 1447ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል ከነገ ወዲያ አርብ (ጁምዓ) ተከብሮ ይውላል።ዒድ ሙባረክ !
18/03/2026



የዒድ አልፈጥር በዓል አርብ (ጁምዓ) ይውላል።

ዛሬ የሸዋል ወር ጨረቃ ባለመታየቷ 1447ኛው የዒድ አልፈጥር በዓል ከነገ ወዲያ አርብ (ጁምዓ) ተከብሮ ይውላል።

ዒድ ሙባረክ !

የአርቲስት ሰራዊት ፍቅሬ እናት አርፈዋል‼️የተወዳጁ አርቲስት ሠራዊት ፍቅሬ ወላጅ እናት ወ/ሮ በለጥሻቸው ማመጫ በተወለዱ በ89 አመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።የቀብር ሥነ -ስነ ስርዓ...
16/03/2026

የአርቲስት ሰራዊት ፍቅሬ እናት አርፈዋል‼️
የተወዳጁ አርቲስት ሠራዊት ፍቅሬ ወላጅ እናት ወ/ሮ በለጥሻቸው ማመጫ በተወለዱ በ89 አመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።
የቀብር ሥነ -ስነ ስርዓታቸው ማክሰኞ መጋቢት 8ቀን 2018ዓ/ም በየካ ቅዱስ ሚካኤል ከቀኑ 9:00 ሠዓት የሚፈፀም ሲሆን የመኖሪያ ቤታቸው ካዛንቺስ እንደራሴ ሆቴል ጀርባ ይገኛል።
ነፍስ ይማር‼️

የአርቲስት ታደለ ሮባ እናት ወይዘሮ ብርቱካን ብሩ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩየታዋቂው ድምፃዊ ታደለ ሮባ እናት ወይዘሮ ብርቱካን ብሩ ዛሬ ቅዳሜ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካ...
07/03/2026

የአርቲስት ታደለ ሮባ እናት ወይዘሮ ብርቱካን ብሩ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ
የታዋቂው ድምፃዊ ታደለ ሮባ እናት ወይዘሮ ብርቱካን ብሩ ዛሬ ቅዳሜ የካቲት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸው ተሰምቷል። የእናታችን የወይዘሮ ብርቱካን ብሩ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ነገ እሁድ የካቲት 29 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ላይ በቅዱስ አማኑኤል ቤተክርስቲያን የሚፈጸም ይሆናል።

የአርቲስቱ አድናቂዎች፣ የሙያ ባልደረቦች እና ወዳጅ ዘመዶች በነገው ዕለት በቦታው በመገኘት ለእናታችን የመጨረሻ ሽኝት በማድረግ በሐዘኑ እንድትካፈሉ ጥሪ ቀርቧል። ለወንድማችን አርቲስት ታደለ ሮባ እና ለመላው ቤተሰቡ መጽናናትን እየተመኘን፣ ለእናታችን ነፍስ በአፀደ ገነት ያኑርልን እያልን ጥልቅ ሐዘናችንን እንገልጻለን።
ምንጭ: ጉርሻ page

በነገው ዕለት በአዲስ አበባ ለተሽከርካሪዎች ዝግ የሚሆኑ መንገዶች ይፋ ሆነዋል‼️በነገው ዕለት በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ የሚከናወነውን የኢፍጣር መርኃ ግብር ምክንያት በማድረግ የተወሰኑ...
06/03/2026

በነገው ዕለት በአዲስ አበባ ለተሽከርካሪዎች ዝግ የሚሆኑ መንገዶች ይፋ ሆነዋል‼️
በነገው ዕለት በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ የሚከናወነውን የኢፍጣር መርኃ ግብር ምክንያት በማድረግ የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ እንደሚደረጉ የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ አስታወቀ።
አዲስ አበባ፤ የካቲት 27 ቀን 2018 ዓ/ም (አዲስ ፖሊስ)፡- በእስልምና እምነት ተከታዮች ዘንድ በመስቀል አደባባይ ከሚካሄደው ታላቁ የኢፍጣር መርኃ ግብር ጋር ተያይዞ የተወሰኑ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ ይደረጋሉ።
በዚህም መሰረት፡-
- ከመገናኛ ወደ መስቀል አደባባይ የሚወስደው መንገድ ቅዱስ ኡራኤል ቤተክርስቲያን
- ከወሎ ሰፈር ወደ መስቀል አደባባይ ኦሎምፒያ
- ከጎተራ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ አሽከርካሪዎች ለከባድ መኪናዎች አጎና ሲኒማ፤ ለሌሎች ተሽከርካሪዎች ጥላሁን አደባባይ ጋር ዝግ የሚደረግ ይሆናል፡፡
- ከጦር ኃይሎች በሜክሲኮ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ተሽከርካሪዎች በተለምዶ አጠራሩ ክቡ ባንክ አካባቢ
- ከፒያሳ በቸርችል ጎዳና ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ሐራምቤ መብራት ላይ
- ከ4 ኪሎ በውጭ ጉዳይ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ብሔራዊ ቤተ መንግስት መስቀለኛው ላይ
- ከአዋሬ አካባቢ በካሳንቺስ ወደ መስቀል አደባባይ ለሚመጡ ኢንተርኮንትኔታል አካባቢ ከቀኑ 5፡00 ሰዓት ጀምሮ የኢፍጧር ፕሮግራሙ እስከሚጠናቀቅበት ሰዓት ድረስ ዝግ ይደረጋሉ።
በተገለፁት መንገዶች ላይ ለአጭርም ሆነ ለረጅም ሰዓታት ተሽከርካሪዎችን አቁሞ መሄድ የተከለከለ ሲሆን ለፀጥታ ስጋት የሆኑ አጠራጣሪ ነገሮች ሲያጋጥሙም በነጻ የስልክ መስመሮች 990፣ 991፣ 987፣ 816 እንዲሁም በ011-1-26-43-59፣ 011-5-52-63-02/03፣ 011-5-52-40-77፣ 011-5-54-36-78 እና 011-5-54-36-81 እንዲሁም በእጅ ስልኮች የዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያን (Citizen Engagement Application) EFPApp በመጠቀም ጥቆማ መስጠት እንደሚገባም የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ጥሪውን አስተላልፏል።

በሳምንት እስከ 137 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት ገቢ እያጣ ያ'ለው የኢትዮጵያ አየር መንገድየኢትዮጵያ አየር መንገድ በመካከለኛው ምሥራቅ እየተካሄደ ባለው ጦርነት ምክንያት በሳምንት 160 በረራ...
06/03/2026

በሳምንት እስከ 137 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት ገቢ እያጣ ያ'ለው የኢትዮጵያ አየር መንገድ
የኢትዮጵያ አየር መንገድ በመካከለኛው ምሥራቅ እየተካሄደ ባለው ጦርነት ምክንያት በሳምንት 160 በረራዎችን ለመሰረዝ እየተገደደ መሆኑን ገለጸ። በዚህም አየር መንገዱ በሳምንት እስከ 137 ሚሊዮን ዶላር የሚገመት ገቢ እንደሚያጣ አስታውቋል። የኢትዮጵያ አየር መንገድ ጦርነት ከመቀስቀሱ አስቀድሞ ወደ መካከለኛው ምሥራቅ አገራት መንገደኞችን እንዲሁም ጭነቶችን ያመላልሳልስ የነበረ ሲሆን በተለይ ደግሞ ወደ ዱባይ በቀን ሦስቴ ወደ ሻርጃ ደግሞ አንዴ ይበር ነበር።

በወጪም ደረጃ የመካከለኛው ምሥራቅ አገራት ከፍተኛ የነዳጅ አምራች በመሆናቸው እና ቀጠናው ሰላም አለመሆኑ በነዳጅ ዋጋ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እንደሚያሳርፍ ተገልጿል። አሜሪካ እና እስራኤል ከኢራን ጋር የሚያደርጉት ጦርነት በመካከለኛው ምሥራቅ ያለውን የአየር ጉዞ አስተጓጉሎ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን እንዳይንቀሳቀሱ አድርጓል። የመካከለኛው ምሥራቅ አገራት የአየር ክልላቸውን ዘግተው የሚቆዩ ከሆነ እና ጦርነቱ ካልቆመ ከባህረ ሰላጤው አገራት ወደ አውሮፓ፣ አፍሪካ እና እስያ የሚሄዱ ተጓዦች ተጨማሪ ተግዳሮቶች ይገጥማቸዋል ተብሎ ይታመናል።

'አስተናጋጆችም ህይወት አላቸው‼️ፋሲካ አስተናጋጅ ናት ፡ ታዋቂው ዩትዩበር አይሾውስፒድ በአገራችን ካደረገው ጉዞ ልንረሳው ያልቻልነውን ጭውውት የሰጠችን ሙያዋንም አገሯንም ያስከበረች ጎበዝ ...
05/03/2026

'አስተናጋጆችም ህይወት አላቸው‼️

ፋሲካ አስተናጋጅ ናት ፡ ታዋቂው ዩትዩበር አይሾውስፒድ በአገራችን ካደረገው ጉዞ ልንረሳው ያልቻልነውን ጭውውት የሰጠችን ሙያዋንም አገሯንም ያስከበረች ጎበዝ ወጣት ነች።

የህይወቷ ከባዱ ጊዜ አባቷን ያጣችበት ቀን ነበር፡ ከአንድ አመት በፊት ማለት ነው።

ህይወት ይቀጥል የለ..የሃዘን ረፍቷን ጨርሳ ወደ ወደስራዋ ስትመለስ ሃዘኗ ግን ገና ከሷ ጋር አልጨረሰም ነበር።
እናም ቀን ላይ እንግዶቿን ምንም እንዳልተፈጠረ እየሳቀች አስተናግዳ ማታ ቤቷ ስትገባ አባቷን እያሰበች ታለቅሳለች ፡
ቀን ስትስቅ ያያት ተስተናጋጅ ምናልባት ትእዛዝ ቆየብኝ ብሎ ተቆጥቷት ይሆናል ወይም ውሃ ብርጭቆዬ ላይ አልቀዳሽም ብሎ ገላምጧት አመናጭቋት ይሆናልደ

ፋሲካ እንዲህ ትላለች

''እባካችሁ አስተናጋጆችን ተረዷቸው (ተረዱን)፡ እየሳቅን በፈገግታ ምናስተናግደው ለሙያችን ፍቅር እንጂ ምንም ችግር ሳይገጥመን ቀርቶ አይደለም። እኛም የራሳችን ህይወት አለን።''

ፋሲካ ልክ ናት

ምናልባት ዛሬ የተቆጣሃት አስተናጋጅ፣ ቤት ውስጥ የታመመች እናቷን አስቀምጣ አንተ ፊት እየሳቀች ይሆናል ፡
ምናልባትም ዛሬ ያመናጨቅሽው አስተናጋጅ የቤት ኪራይ በዝቶበት ጎዳና ላለመውጣት እየታገለ ይሆናል ፣
መስተንግዶ ሙያ ነው፡ አስተናጋጆችም ሰው ናቸው። ስለዚህ በመስተንግዶ ሲያስደስቱን እያመሰገንን ሲሳሳቱም በክብር እንንገራቸው፡ እነሱም እንደሰው የሚኖሩት ህይወት አላቸው‼️

Via- Getahun Assefa

የሼህ አላሙዲ 4ሚሊዮን ብር እና የአዲስአበባ መስተዳድር የቤት ስጦታ‼️ለ10 ዓመታት በአልጋ ላይ የቆየችው ሕፃን ብሌን አሸናፊ የ4 ሚሊዮን ብር ድጋፍና የመኖሪያ ቤት ተበረከተላት።በአንጎል ...
04/03/2026

የሼህ አላሙዲ 4ሚሊዮን ብር እና የአዲስአበባ መስተዳድር የቤት ስጦታ‼️

ለ10 ዓመታት በአልጋ ላይ የቆየችው ሕፃን ብሌን አሸናፊ የ4 ሚሊዮን ብር ድጋፍና የመኖሪያ ቤት ተበረከተላት።

በአንጎል ውስጥ ውሃ መቋጠር እና ግፊት መጨመር (Hydrocephalus) ምክንያት ላለፉት 10 ዓመታት በአልጋ ላይ የቆየችው ሕፃን ብሌን አሸናፊ ወደ ውጭ ሀገር ሄዳ ለምትታከምበት የ4 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ተደርጎላታል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ በሕፃኗ መኖሪያ ቤት ተገኝተው ድጋፉን ለወላጅ አባቷ አስረክበዋል።

የሕፃን ብሌን አባት ወጣት አሸናፊ በጽዳት ሠራተኝነት እየተገኘ እናት በሌሉበት ብሌንን፣ ታናሽ እህቷን፣ አካል ጉዳተኛ እህቱን እና አቅመ ደካማ እናቱን የሚንከባከብ ጠንካራ ወጣት መሆኑንም ከንቲባዋ ገልጸዋል።

ቤተሰቡ በአሁኑ ወቅት የሚኖርበት ቤት ለሕፃኗ ጤና አስቸጋሪ በመሆኑ፣ አስተዳደሩ የተሻለ የመኖሪያ ቤት እንዲያገኙ መወሰኑንም አስታውቀዋል።

ለሕፃን ብሌን አጠቃላይ የሕክምና ወጪ የሚውለውን 4 ሚሊዮን ብር የሸፈኑት ሼህ ሙሐመድ ሁሴን አሊ አል አሙዲ መሆናቸውን የጠቀሱት ከንቲባ አዳነች፣ ለባለሀብቱ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

ከንቲባዋ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባጋሩት መልእክትም ሕፃኗ አስፈላጊውን ሕክምና አግኝታ እንደ እኩዮቿ የምትቦርቅበትና ትምህርት ቤት የምትሄድበት ጊዜ ቅርብ እንዲሆንም መልካም ምኞታቸውን ገልጸዋል።

Via- EBC

ሰበር ዜና፡ የ1 ሚሊዮን ተከታዮች ፈተና በድል ተጠናቀቀ!በኢትዮጵያ የቲክቶክ ታሪክ አዲስ ሪከርድ ተመዝግቧል፤ ዘማሪ ገብረዮሐንስም የአዲስ መኪና ባለቤት ሊሆን ነውአዲስ አበባ — ባለፉት 48...
04/03/2026

ሰበር ዜና፡ የ1 ሚሊዮን ተከታዮች ፈተና በድል ተጠናቀቀ!

በኢትዮጵያ የቲክቶክ ታሪክ አዲስ ሪከርድ ተመዝግቧል፤ ዘማሪ ገብረዮሐንስም የአዲስ መኪና ባለቤት ሊሆን ነው

አዲስ አበባ — ባለፉት 48 ሰዓታት መላውን የኢትዮጵያ የቲክቶክ ማህበረሰብ ሲያነጋግር የቆየውና በታዋቂው ቲክቶከር አዶናይ አስተባባሪነት የተጀመረው "የ1 ሚሊዮን ተከታዮች ፈተና" ግቡን መምታቱ በይፋ ተረጋገጠ።

የSmile Dental Clinic የቲክቶክ ገጽ ተከታዮች ቁጥር 1 ሚሊዮን እንዲሞላ የተቀመጠው ግብ፣ በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ ውስጥ በስኬት ተጠናቋል። ይህን ተከትሎም ክሊኒኩ ለታዋቂው መንፈሳዊ ዘማሪ ገብረዮሐንስ ቃል የገባው አዲስ መኪና በቅርቡ እንደሚረከብ ታውቋል።

የዘመቻው ዋና አቀንቃኝ አዶናይ፣ ግቡ መሳካቱን ተከትሎ ለደጋፊዎቹ ባስተላለፈው መልእክት፡-

"ይህ የሁላችንም ድል ነው! ኢትዮጵያውያን በአንድነት ከቆምን የማይቻል ነገር የለም። ለዘማሪው ደስታ ምክንያት ለሆናችሁ ሁሉ ምስጋና ይገባችኋል" በማለት ደስታውን ገልጿል።

Smile Dental Clinic በገባው ቃል መሰረት፣ የቲክቶክ ገጹን 1 ሚሊዮን ላደረሱለት ተጠቃሚዎች ምስጋናውን እያቀረበ፣ ለዘማሪ ገብረዮሐንስ የተዘጋጀውን አዲስ መኪና የሚያስረክብበትን ፕሮግራም በቅርቡ እንደሚያሳውቅ ይጠበቃል።

ይህ ክስተት በኢትዮጵያ ዲጂታል ማህበረሰብ ውስጥ ትልቅ ትርጉም አለው። ማህበራዊ ሚዲያ ለመዝናኛ ብቻ ሳይሆን ለበጎ አድራጎት እና ለታላላቅ ስኬቶች እንዴት መዋል እንደሚችል ተግባራዊ ትምህርት የሰጠ ክስተት ሆኖ ይመዘገባል።

ለዘማሪ ገብረዮሐንስ የእንኳን ደስ አለዎት መልእክትዎን በኮሜንት ያስፍሩ!

ልዩ ዘገባ፡ የSmile Dental Clinic እና የአዶናይ የቲክቶክ ፈተና ለዘማሪ ገብረዮሐንስቲክቶከሩ አዶናይ በማህበራዊ ሚዲያ ያልተጠበቀ እና ትልቅ ግብ ሰንቆ አዲስ የቲክቶክ ቻሌንጅ (C...
01/03/2026

ልዩ ዘገባ፡ የSmile Dental Clinic እና የአዶናይ የቲክቶክ ፈተና ለዘማሪ ገብረዮሐንስ

ቲክቶከሩ አዶናይ በማህበራዊ ሚዲያ ያልተጠበቀ እና ትልቅ ግብ ሰንቆ አዲስ የቲክቶክ ቻሌንጅ (Challenge) ይዞ ብቅ ብሏል።

ይህ ፈተና ያነጣጠረው በታዋቂው ዘማሪ ገብረዮሐንስ ላይ ነው።

* ዓላማው የSmile Dental Clinic የቲክቶክ ገጽ ተከታዮችን ቁጥር ማሳደግ።

* ግቡ በሚቀጥሉት 48 ሰዓታት (2 ቀናት) ውስጥ 1 ሚሊዮን አዳዲስ ተከታታዮችን ማፍራት።
ሽልማቱ፦

ግቡ ከተሳካ ስፖንሰሩ Smile Dental Clinic ለዘማሪ ገብረዮሐንስ አዲስ መኪና በስጦታ ለማበርከት ቃል ገብቷል።

የቲክቶክ እና የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎች ይህን ታሪካዊ ግብ በሁለት ቀናት ውስጥ ለማሳካት ከፍተኛ ርብርብ እያደረጉ ይገኛሉ።

ይህን ትልቅ ቻሌንጅ ለመደገፍ እና ዘማሪ ገብረዮሐንስን ተጠቃሚ ለማድረግ፦

* የቲክቶክ ገጹን Follow ያድርጉ (ሊንኩን መጀመሪያው ኮሜንት ላይ ያገኙታል)።

* ይህ መረጃ ለብዙዎች እንዲደርስ Share ያድርጉ።
ለበጎነት እንተባበር! Come on guys!

🙏🙏🙏

Via : ጉርሻ page

ታዋቂው ጋዜጠኛና የጥበብ ሰው ተመስገን ባዲሶ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ተፈጸመ​  | በኢትዮጵያ የጋዜጠኝነትና የሥነ-ጽሑፍ ዘርፍ ጉልህ አሻራ ያሳረፈውና በብዙኃኑ ዘንድ "የማይረሳውና ጨዋታ አዋቂ...
01/03/2026

ታዋቂው ጋዜጠኛና የጥበብ ሰው ተመስገን ባዲሶ የቀብር ሥነ-ሥርዓት ተፈጸመ

​ | በኢትዮጵያ የጋዜጠኝነትና የሥነ-ጽሑፍ ዘርፍ ጉልህ አሻራ ያሳረፈውና በብዙኃኑ ዘንድ "የማይረሳውና ጨዋታ አዋቂው" እየተባለ የሚጠራው ተመስገን ባዲሶ፣ ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ በ51 ዓመቱ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።

​የጋዜጠኛው የቀብር ሥነ-ሥርዓት ዛሬ የካቲት 21 ቀን 2018 ዓ.ም በብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ ቤተክርስቲያን፣ ወዳጅ ዘመዶቹና የሙያ ባልደረቦቹ በተገኙበት በክብር ተፈጽሟል።

​የሕይወት ታሪክና የሥራ ዘመኑ
​ተመስገን ባዲሶ ታህሳስ 16 ቀን 1967 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ "አውቶቢስ ተራ ደጃዝማች ገነሜ ትምህርት ቤት" ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከአባቱ ከአቶ ባዲሶ ባደታና ከእናቱ ከወይዘሮ ባዬሽ ዳዊት ተወለደ።

ትምህርቱን በደጃዝማች ገነሜ ትምህርት ቤት የጀመረው ተመስገን፣ ገና በወጣትነቱ ለጥበብና ለንባብ የነበረው ፍቅር ለየት ያለ እንደነበር ይነገርለታል።

​በ1985 ዓ.ም "የፍቅር ማህደር" በተሰኘ ጋዜጣ ላይ ታሪኮችን በመጻፍ የጀመረ ሲሆን፣ ከዚያም ባለፉት ዓመታት በበርካታ ታዋቂ ህትመቶች ላይ በመሳተፍ ለአንባቢዎች ምክርና እውቀትን ሲያጋራ ቆይቷል። ከእነዚህም መካከል ቃልኪዳን፣ ጽጌረዳ፣ ማክዳ፣ እንኮይ እና ሮዝ መጽሔቶች እና ሊቢሮ፣ ኔሽን እና ሆሊዴይ በተሰኙ ጋዜጣዎች ላይ ተሳትፏል።

​ተመስገን ባዲሶ በህትመት ውጤቶች ብቻ ሳይወሰን በቴሌቪዥን መስኮትም ተወዳጅነትን አትርፏል።
​ከ1999 - 2002 ዓ.ም፡ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን (ኢቲቪ) "ጉራማይሌ" ፕሮግራም ላይ በጋዜጠኝነት ሰርቷል።
​ከ2005 - 2007 ዓ.ም "ጉራማይሌ ቶክ ሾው" በዩቲዩብ ላይ አስተማሪና አዝናኝ ፕሮግራሞችን በማቅረብ የሚዲያ ዘርፉን አገልግሏል።

​በማህበራዊ ሚዲያ በነበረው ንቁ ተሳትፎና ተፅዕኖ ፈጣሪነት በስነጽሁፍ ዘርፍ በባህር ዳር ከተማ በተካሄደው ሶስተኛው የ"ጣና አዋርድ" ሽልማት አሸናፊ መሆን መቻሉም የሚታወስ ነው።

​ተመስገን ከሙያው ባለፈ በደግነቱና ለሰዎች በነበረው አሳቢነት ይታወቃል። ጓደኞቹን በማስተባበር የተቸገሩ ወገኖችን እስከ እለተ ሞቱ ድረስ ሲረዳ የቆየ ሲሆን፣ በተለይም ​ከከተማ ርቀው የሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት እንዳይዘጉና አገልግሎታቸው እንዳይቋረጥ በገንዘብና በቁሳቁስ ድጋፍ ሲያደርግ ቆይቷል።

​ተመስገን ባዲሶ ባደረበት ሕመም በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ የካቲት 20 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።

Address

Africa Avenue/Bole Road
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when EyohaMedia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to EyohaMedia:

Share