Arada Muslim Youth

Arada Muslim Youth Religious youths organization 🕌

ከአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት የተሰጠ መግለጫ።የአባታችን የክቡር ዶ/ር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር እድሪስ ሞት በሁላችንም ዘንድ ከፍተኛ የሐዘን ድባብ ፈጥሮብን መቆየቱ ...
30/10/2025

ከአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት የተሰጠ መግለጫ።

የአባታችን የክቡር ዶ/ር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር እድሪስ ሞት በሁላችንም ዘንድ ከፍተኛ የሐዘን ድባብ ፈጥሮብን መቆየቱ ይታወቃል። ተቀዳሚ ሙፍቲ እስከ ሕልፈተ ሕይወታቸው ድረስ በብዙ መልኩ ኢስላምንና ሙስሊሞችን ሲያገለግሉ የኖሩ አባት ነበሩ። በተለይ ለአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ደግሞ ተቋሙን በመሪነት ከአስር ዓመታት በላይ የመሩና አሻራቸውን ያስቀመጡ መሪያችን እንደመሆናቸው ኃዘናችን ጥልቅ መሆኑን ከዚህ በፊት ባወጠናቸው ተከታታይ መግለጫዎች መግለጻችን ይታወሳል።

አሁን በድጋሚ አላህ (ሱ.ወ) ምህረቱን እንዲለግሳቸዉና ጀነተል ፊርደዉስን ማረፊያቸዉ ያደርግላቸዉ ዘንድ አላህን እንማጸነዋለን። በማስከተልም ከሰሞኑ ከታዩ ሁነቶች ጋር በተያያዘ በቀጣይ ነጥቦች ላይ የምክር ቤቱን አቋም እንደሚከተለው ለመግለጽ እንወዳለን።

1. ለሕዝበ ሙስሊሙ አንድነት የመስራት ታሪክ ያላቸው ሙፍቲ ሞት ሕዝባችን በሀዘን ዉስጥ በነበረበት ሁኔታ ከቀብር ስፍራቸው ጋር ተያይዞ አላስፈላጊ የሆኑ ንትርኮች መነሳታቸው አሳዝኖናል። መሰል ዉዝግቦች ስሜትና ቡድንተኝነት ሲታከልባቸው ሙፍቲ ሲለፉለት የነበረውን አንድነትን ከማስጠበቅ በተቃራኒ ሕዝባችንን ወዳልሆነ ንትርክ፣ ጭቅጭቅ እና ክፍፍል የሚያመራ አደገኛ ነገር ነው።

2. ተቀዳሚ ሙፍቲ የተቀበሩበት ቦታ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፕላንና ልማት ኮሚሽን በደብዳቤ ቁጥር አ/አ/ፕ/ል/ኮ02/910/2013 በቀን 05/10/13 በተፃፈ ደብዳቤ ከቅይጥ መኖሪያነት ወደ መካነ መቃብርነት የተቀየረ መሆኑን ለማረጋገጥ ችለናል፡፡ ስለሆነም ስፍራውን በአዲስ አበባ ውስጥ እንደሚገኙት የሕዝበ ሙስሊሙ መካነ መቃብሮች በመቁጠር በአስራ ሁለተኛ መካነ መቃብርነት እውቅና ሰጥተነዋል።

በመሆኑም የመቃብር ስፍራውም ተጨማሪ የማስፋሪያ ጥያቄ ለመንግስት ከማቃረባችን በተጨማሪ እንደሌሎቹ መካነ መቃብሮች ማንኛውም ሙስሊም ሲሞት የሚቀበርበት በመሆኑ ለመካነ መቃብሩ አስፈላጊውን ጥበቃ፣ ድጋፍ እና ክትትል በመጅሊሱ በኩል እንደሚደረግለት ማሳወቅ እንወዳለን። ስለሆነም ከአሁን በኋላ ከመካነ መቃብሩ ጋር በተያያዘ የሚደረጉ ማንኛውም ዓይነት አጀንዳዎች ሊቆሙ እንደሚገባ አናሳስባለን።

3. ከዚህ በኋላ የተለያዩ አጅንዳዎችን ምክንያት በማድረግ በሕዝባችን መካካል ክፍፍልን የሚፈጥሩና የሚያባብሱ እንዲሁም ሰላምን የሚያደፈርሱ ንትርኮች፣ ጭቅጭቆች እና ውግዘቶች እንዲቆሙ እናሳስባለን። ዉይይትን፥ መማማርንና መተሳሰብን ዓላማ ያላደረጉ መልዕክቶች በማህበራዊ ሚዲያም ሆነ በማንኛውም መድረክ እንዳይተላለፉ ጥሪ እናደርጋለን።

4. ለየትኛውም ሃይማኖታዊ አለመግባባቶች መፍትሄ ፍለጋው መንገዱ አላህ እንደነገረን መመለሻችን ቁርኣንና የነብያችን (ሰ.ዐ.ወ.) ፈለግ(ሱና) ዋቢ በማደረግ ሊሆን ይገባል። በዚህ ረገድ አርዓያዎቻችን መልዕክተኛው (ሰ.ዐ.ወ.) እና ሰሀቦቻቸው(ረ.ዐ.) ናቸው። ዑለሞችና ዱዓቶች የሕዝባችንን የዲን ግንዛቤና እውቀትን ለማስፋት የምታደርጓቸው አስተምህሮቶች፥ ዳዕዋዎች፥ በመልካም የማዘዝና ከመጥፎ የመከልከል ጥረቶች ከስሜት በራቀ፤ በእውቀት፣ በጥበብና በለዘብታ ቃል የተላበሰ መሆኑን ባረጋገጠ መልኩ ሊቀጥል እንደሚገባ እናሳስባለን።

5. አንዳንድ አካላት የተፈጠረውን ሁኔታ ሲጠብቁት እንደነበረ መልካም አጋጣሚ በማየት የራሳቸውን ድብቅ ፍላጎትና ዓላማን ለማሳካት ሕዝቡን የሚያሳዝኑ ድርጊቶችንና ንግግሮችን በማድረግ የሕዝባችንን ሐዘን አባብሰዋል። ምክር ቤቱ በምርጫ የተጣለበትን ታላቅ አደራ ለመወጣት በቁርጠኝነት የሚንቀሳቀስ

የሀገር ዋርካ ለሆኑት አባታችን ክቡር ዶ/ር ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ክብራቸውን፣ አበርክቷቸውንና አባትነታቸውን በሚመጥን መልኩ ደማቅ የሽኝት መርሃ ግብር በግዙፉ ሚሊኒየም አዳራሽ ተደርጎላቸ...
20/10/2025

የሀገር ዋርካ ለሆኑት አባታችን ክቡር ዶ/ር ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ክብራቸውን፣ አበርክቷቸውንና አባትነታቸውን በሚመጥን መልኩ ደማቅ የሽኝት መርሃ ግብር በግዙፉ ሚሊኒየም አዳራሽ ተደርጎላቸዋል።

በዚህ መርሃ ግብር ላይ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳይ ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሐጅ ኢብራሂም ቱፋ፣ የኢፌድሪ ፕሬዝደንት ታየ አጽቀ ስላሴ፣ የቀድሞው ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን፣ የኢትዮጵያ ኃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ዋና ፀሐፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ፣ ታላላቅ የኃይማኖት አባቶች፣ ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች፣ የሀገር ሽማግሌዎች፣ ቤተሰቦቻቸው፣ ወዳጆቻቸውን ጨምሮ በሺዎች የሚቆጠር ኢትዮጵያዊ ያለ ኃይማኖት ልዩነት በመገኘት ለእኚህ አባት ያለውን ፍቅር በተግባር አሳይቷል።

ሥርዓተ ቀብራቸው ከቀኑ 10 ሰዓት ላይ የሚፈጸም ይሆናል።

አባታችንን አላህ ምንዳቸውን ከፍ አድርጎ በጀነተል ፊርደውስ ይመንዳቸው። አሚን።

የሙፍቲ ሀጅ ኡመር ኢድሪስ ጀናዛ የሶለተል ጅናኢዝ እየተሰገደ ይገኛል!የቀድሞው የፌደራል መጅሊስ ፕሬዝዳንት የክቡር ዶ/ር ሙፍቲ ሀጅ ኡመር ኢድሪስ ጀናዛ ፒያሳ በሚገኘው የኑር መስጂድ የሶላተ...
20/10/2025

የሙፍቲ ሀጅ ኡመር ኢድሪስ ጀናዛ የሶለተል ጅናኢዝ እየተሰገደ ይገኛል!

የቀድሞው የፌደራል መጅሊስ ፕሬዝዳንት የክቡር ዶ/ር ሙፍቲ ሀጅ ኡመር ኢድሪስ ጀናዛ ፒያሳ በሚገኘው የኑር መስጂድ የሶላተል ጀናኢዝ እና የዱአ መርሀግብር እየተደረገ ይገኛል።

በፒያሳ በሚገኘው ኑር መስጂድ ታላላቅ መሻይሆች እና የሙፍቲ ሀጅ ኡመር ኢድሪስ ደረሶች እንዲሁም በርካታ ሙስሊም ማህበረሰብ በተገኘበት ሶላተል ጀናዛ ተሰግዷል።

ከቀኑ 8 ሰአት ጀምሮ በሚሊኒየም አዳራሽ ከፍተኛ የመንግስት ኃላፊዎች በተገኙበት የሽኝት ፕሮግራም ከተከናወነ በኋላ ከቀኑ አስር ሰአት ስርዓት ቀብራቸው እንደሚፈፀም ተገልጿል።

ኑር መስጊድ በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ በሰላተል ጀናዛ ወቅት የተገኘው ህዝብ አጃይብ ነበር።ተወዳጅ የሃገር አባት ወደአሄራ ሄደዋል😢
20/10/2025

ኑር መስጊድ በተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ
በሰላተል ጀናዛ ወቅት የተገኘው ህዝብ አጃይብ ነበር።

ተወዳጅ የሃገር አባት ወደአሄራ ሄደዋል😢

ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑንየተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ሥርዓተ ቀብር ዛሬ 10 ሰዓት ይፈፀማል***************የተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስን ሥርዓተ ቀብር ለማስፈፀም ...
20/10/2025

ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን

የተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስ ሥርዓተ ቀብር ዛሬ 10 ሰዓት ይፈፀማል
***************

የተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ኢድሪስን ሥርዓተ ቀብር ለማስፈፀም የተቋቋመው ኮሚቴ በሰጠው መግለጫ መሠረት፥ ሥርዓተ ቀብራቸው ዛሬ 10 ሰዓት ላይ በኑዛዜያቸው መሠረት ኃይሌ ጋርመንት ሰፈራ ከአዲሱ አትክልት ተራ ትንሽ ዝቅ ብሎ ቁርዓን ያስተምሩበት በነበረው መስጂድ ቅጥር ግቢ ውስጥ ይፈፀማል።

ሶላተል ጀናዛ ለበርካታ ዓመታት ባስተማሩበት እና ፒያሳ በሚገኘው ኑር (በኒ) መስጂድ ዝሁር (ከቀኑ 6 ሰዓት) ላይ ይከናወናል።

ከቀኑ 8 ሰዓት ጀምሮ ደግሞ በአዲስ አበባ ሚሌኒየም አዳራሽ ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት የአስከሬን ሽኝት ፕሮግራም ይከናወናል።

በኢትዮጵያ  ለመጀመሪያ  ጊዜ የተካሄደው ሀገር አቀፍ የሐዲስ ሂፍዝ ውድድር ተጠናቀቀ።••••••••••••••••••••••••••••••••••••••መስከረም  25፣ 2018 ዓ.ል| ረቢዑል ሳኒ...
05/10/2025

በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደው ሀገር አቀፍ የሐዲስ ሂፍዝ ውድድር ተጠናቀቀ።

••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
መስከረም 25፣ 2018 ዓ.ል| ረቢዑል ሳኒ 13 1447 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ

በአፍሪካ ለሁለተኛ ጊዜ በኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደው ሀገር አቀፍ የሐዲስ ሂፍዝ የማጣሪያ ውድድር ተጠናቀቀ።

በማጠቃለያው የሞሮኮው ንጉስ መሐመድ ስድስተኛ ፋውንዴሽን ዋና አስተባባሪ ዶክተር አብዱልሀሚድ አል አለሚ ውድድሩ ስለሚኖረው ፋይዳ አብራርተዋል።

ዋና አስተባባሪው በሐዲስ ሂፍዝ ውድድር ከኢትዮጵያ ዑላማ ጉባኤ የትምህርት ካሪኩለም ዘርፍ ጋር በመተባባር በተደረገው የሐዲስ ሂፍዝ ውድድር የመጀመሪያው የሆነው የማጣሪያውን ወድድሩ አሸናፊ የሆኑትን አሳውቀዋል።

በዚሁ መሰረት ፦

40 ሐዲስ በመሐፈዝ

1ኛ አብዱሰመድ አሚን አህመድ
2ኛ በከር ሐጂ ቃዲ
3ኛ. ሐ ምዛ ሙሳ

35 ሐዲስ በመሐፈዝ

1ኛ. ሙኹዲን አብዱራሒም አፈንዲ
2ኛ. ኻሊድ ሐጅ አደም
3ኛ. ፈይሰል ሽብሬ ኬዳዶ

25 ሐዲስ በመሐፈዝ

1ኛ. ኢማዱዲን ዑስማን ሳሊህ
2ኛ. አብዱራህማን ሳፊ ዑመር
3ኛ. ኢብራሂም አብዱ ጃርሶ

ማጠሪያውን ያለፉ እና የዚህ ውድድር አሸናፊ መሆናቸውን ገልፀዋል።

በሶስቱ ዘርፎች አንደኛ የወጡ ሶስቱ አሸናፊዎች በሕዳር ወር በሞሮኮ በሚደረገው ውድድር ኢትዮጵያን ወክለው ይሳተፋሉ ።

የመካነ ሰላሙን ጭፍጨፋ ተዋቸው በማህበራዊ ሚዲያ ተንጫጭተው ከዛ ይረሱታል ለሚሉ ደናቁራት ማስታወስ የሚያስፈልገው1ኛ የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን የትግል ታሪክና      ስልት 2ኛ በዚህ ዘመን የማ...
05/10/2025

የመካነ ሰላሙን ጭፍጨፋ ተዋቸው በማህበራዊ ሚዲያ ተንጫጭተው ከዛ ይረሱታል ለሚሉ ደናቁራት ማስታወስ የሚያስፈልገው
1ኛ የኢትዮጵያ ሙስሊሞችን የትግል ታሪክና
ስልት
2ኛ በዚህ ዘመን የማህበራዊን ሚድያ ተፅእኖ ምን ያህል ትልቅ ነገር እንደሆነ ማስታወስ ያስፈልጋል።

ለማንኛውም ወደተግባሩ ምዕራፍ ስንገባ የከለላ ከተማ አስተዳደር እስልምና ጉዳዮች ም/ቤት መግለጫ ጅማሮን ማድነቅ ግድ ይለናል።

በኢትዮጵያ የመጀመርያው የሐዲስ ሂፍዝ ውድድር ዛሬ ይካሄዳል።••••••••••••••••••••••••••••••••••••••መስከረም  25፣ 2018 ዓ.ል| ረቢዑል ሳኒ 13 1447 ዓ.ሒ بِس...
05/10/2025

በኢትዮጵያ የመጀመርያው የሐዲስ ሂፍዝ ውድድር ዛሬ ይካሄዳል።

••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
መስከረም 25፣ 2018 ዓ.ል| ረቢዑል ሳኒ 13 1447 ዓ.ሒ
بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
አዲስ አበባ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የዑለማ ጉባዔ እና የሞሮኮ ንጉሥ ሙሐመድ 6ኛ ፋውንዴሽን ጋር በመተባበር ሐገር አቀፍ ሀዲስን በቃል ማጥናት(ነብያዊ ሀዲስ ሂፍዝ) ውድድር አዘጋጅቷል።

በአህጉራችን አፍሪካ ለሁለተኛ ጊዜ በሐገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ በዛሬው ዕለት ዕሁድ መስከረም 25፣ 2018 ዓ.ል( ረቢዑል ሳኒ 13 ፣ 1447 ዓ.ሒ ) በስካይ ላይት ሆቴል የሚደረገው ውድድር በሶስት ደረጃ ተከፍሎ ውድድሩ ይደረጋል ተብሏል።

ተወዳዳሪዎቹ 100 ሀዲሶችን በቃል በመሐፈዝ 40 ሀዲሶችን ከሙጧ አል ማሊክኪ ፣35 ሀዲሶችን ከሶሂህ አል ሙስሊም ከነ ሰነዶቹና ትርጉማቸው (ሃዲሳዊ ትንታኔያቸው) ቀሪው 25 ሀዲሶች ከሶሂህ አል ቡኻሪና ከሶሂህ አል ሙስሊም የአህካም ሀዲሶችን ማወቅና መተንተል ይጠበቅባቸዋል ተብሏል።

ውድድሩ ከደቂቃዎች በኋላ የሚጀምር ሲሆን ተጨማሪ መረጃዎችን ይዘን የምንመለስ ይሆናል።

እዩልን እነዚህን ፅንፈኞች በምንም አይነት አመክንዮ እና የትግል ሂደት ማሳመኛ የሌለውን መስጊድ ገብቶ ኢማሙን እና ሰጋጆችን ከገደሉ እና ካስገደሉ ቡሃላ ተፀፀተው ስህተታቸውን አምነው ምህረት...
04/10/2025

እዩልን እነዚህን ፅንፈኞች
በምንም አይነት አመክንዮ እና የትግል ሂደት ማሳመኛ የሌለውን መስጊድ ገብቶ ኢማሙን እና ሰጋጆችን ከገደሉ እና ካስገደሉ ቡሃላ ተፀፀተው ስህተታቸውን አምነው ምህረትና ይቅርታን ከመጠየቅ ይልቅ ድንፋታቸውን ጥጋብና ድድብናቸውን አደባባይ ሲያሰጡት!!
#እንዳይረሳ
#ለታሪክይቀመጥ

 #የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዬች ከፍተኛ ምክር ቤትበመካነ ሰላም በመስጊድ ውስጥ በግፍ በአባታችንና ወንድሞቻችን ላይ ለተፈፀም የግፍ ጭፍጨፋ ያወጣው መግለጫ!
04/10/2025

#የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዬች ከፍተኛ ምክር ቤት

በመካነ ሰላም በመስጊድ ውስጥ በግፍ በአባታችንና ወንድሞቻችን ላይ ለተፈፀም የግፍ ጭፍጨፋ ያወጣው መግለጫ!

Address

Arada Sub-city
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Arada Muslim Youth posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share