Arada Muslim Youth

Arada Muslim Youth Religious youths organization 🕌

በአዲስ አበባ መስጂዶች ምርጫ መቼ ይካሄዳል?የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ምርጫ የሚካሄድባቸውን ቀናት ዝርዝር ይፋ አድርጓል።በአዲስ አበባ የ2017 ምርጫ አስፈፃሚ ቦርድ...
30/07/2025

በአዲስ አበባ መስጂዶች ምርጫ መቼ ይካሄዳል?

የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ምርጫ የሚካሄድባቸውን ቀናት ዝርዝር ይፋ አድርጓል።

በአዲስ አበባ የ2017 ምርጫ አስፈፃሚ ቦርድ ፅ/ቤት ከመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ጋር ውይይት አደርጓል።

በውይይቱ ወቅት ምርጫ በየትኞቹ ቀናት እንደሚካሄድ እና የሚመረጡ ተወካዮች ትውውቅ መቼ እንደሚካሄድ ይፋ ተደርጓል።

የቦርዱ ሰባሳቢ አቶ ጅብሪል ዑስማን በአዲስ አበባ 326 የምርጫ ማዕከላት መኖራቸውን ገልፀው፣ከሰኔ 18 እስከ ሐምሌ 13 ፣2017 ዓ.ል ጀምሮ በ11ዱም ክፍለ ከተሞች የተጀመረው የመራጮች ምዝገባ ሂደቱ ፍፁም ሰላማዊ እንደነበር ተናግረዋል።

በቴክኖሎጂ የተደገፈው የምርጫ ምዝገባ የተመዝጋቢዎችን መረጃ ወደ መረጃ ቋት የማስገባት ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን አቶ ጅብሪል ገልፀዋል።

ቦርዱ የምርጫውን ሂደት ለሕዝበ ሙስሊሙ ተደራሽ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት የሚዲያ ተቋማት ከፍተኛ ሚና ስላላቸው አጠናክረው እንዲቀጥሉ የቦርዱ አባል ዶክተር ኢብራሂም ሙሉሸዋ ጥሪ አቅርበዋል።

የምርጫ ሂደቱም በአዲስ አበባ ምን እንደሚመስል የወጣው መርሃግብር ይፋ ሆኗል።

በዚህም መሠረት፦

የዑለማ ዘርፍ ትውውቅ ነሐሴ 2/17 ከቀኑ 8:30
የምሁራን ዘርፍ ትውውቅ ነሐሴ 4/17 ከጧቱ 3:00
የወጣቶች ዘርፍ ትውውቅ ነሐሴ 4/17 ከጧቱ 3:00 ጀምሮ
የሴቶች ዘርፍ ትውውቅ ነሐሴ 4/17 ከቀኑ 8:30
የስራ ማሕበረሰብ ዘርፍ ትውውቅ ነሐሴ 4/17 ከ8:30 ይካሄዳል።

ከነሐሴ 9 እስከ ነሐሴ 11/17 ዓ.ል በአምስት ዘርፎች የሚደረገው ምርጫ ይደረጋል።

በዚህም መሰረት ፦

የዑለማ ዘርፍ ምርጫ ነሐሴ 9/17 ከቀኑ 8:30 እስከ ቀኑ 11:00 ]የምሁራን ዘርፍ ምርጫ ነሐሴ 9/17 ከጧቱ 3:00 6:30
የወጣቶች ዘርፍ ምርጫ ነሐሴ 11/17 ከጧቱ 3:00 እስከ 6:30
የሴቶች ዘርፍ ምርጫ ከነሐሴ 11/17 ከሰዓት 8:00 እስከ 11 ሰዓት
የስራ ማሕበረሰብ ዘርፍ ምርጫ ከ8:00 እስከ ቀኑ 11:00 ይካሄዳል

ነሐሴ 9/17 በዑለማ ዘርፍ የሚጀመረው የመጅሊስ ምርጫ በተቀመጠው ቀን እና ሰዓት ላይ መራጩ በመገኘት ኢስላማዊ ኅላፊነታቸውን እንዲወጡ ቦርዱ ጥሪውን አቅርቧል።

••••••••••
የአራዳ ክ/ከተማ ሙስሊም ወጣቶች ሊግ ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
Facebook | https://www.facebook.com/Honeybadgerstube
Telegram | https://t.me/+0cG9-taq2jhhMDk0
Tiktok | tiktok.com/
Youtube | https://youtube.com/?si=2XCJV6tmnkXMLfB7

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የዲያስፖራ ምክር ቤት ማቋቋም ጀምሯል።•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••• ሐምሌ 23፣ 2017 ዓ.ል |  ሰፈረ  ...
30/07/2025

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የዲያስፖራ ምክር ቤት ማቋቋም ጀምሯል።

••••••••••••••••••••••••••••••••••••••••
ሐምሌ 23፣ 2017 ዓ.ል | ሰፈረ 5፣ 1447 ዓ.ሒ

بِسْمِ ٱللَّهِ ٱلرَّحْمَٰنِ ٱلرَّحِيمِ
•••••••••••••••••••••••••••••••••••••••

አዲስ አበባ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት የዲያስፖራ ምክር ቤት በማቋቋም ላይ እንደሚገኝ ተግልጿል።

ይህንን አስመልክቶ የጠቅላይ ምክርቤቱ የስራ አስፈፀሚ ኮሚቴ አባል እና የሰላም የክልልና ዲያስፓራ ዘርፍ ተጠሪ ሐጂ ሙስጠፋ ናስር፣ የጠቅላይ ምክርቤቱ የፕሬዝደንት ጽ/ቤት ኃላፊ ዑስታዝ አቡበከር አህመድ እንዲሁም ምክትል አስኪያጅና የዲያስፓራ ምክርቤት አስተባባሪ ሐጂ አብዱልአዚዝ አሎ በጋራ መግለጫ ሠጥተዋል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ የሰላም ክልልና ዲያስፓራ ዘርፍ ላለፉት ሶስት አመታት የዲያስፓራውን ተሳትፎ ለማረጋገጥ ሲሰራ መቆየቱን የተናገሩት ሼይኽ ሙስጠፋ ናስር ምክርቤቱ መቋቋም በሚችልበት ዙሪያ ጥናቶች እንዲካሄዱ በማድረግና ኮሚቴ በማዋቀር ሲሰራ መቆየቱን በመግለጫው አንስተዋል።

ዘርፉ በመላው ዓለም ላይ የሚገኙ ሙስሊም ዲያስፓራዎችን በሁለንተናዊ መልኩ የሚያገለግል ምክርቤት እንዲቋቋም የሰራው ስራ ውጤታማ ሆኖ ሂደቱ መጀመሩን ነው ሼይኽ ሙስጠፋ የተናገሩት።

ጠቅላይ ምክርቤቱ ተቋማዊ ከፍታውን ለማስጠበቅ የተለያዩ ስራዎች ሲሰራ መቆየቱን የተናገሩት ዑስታዝ አቡበክር አህመድ ምክርቤቱ በውጪ የሚኖሩ ሙስሊም ትውልደ ኢትዮጵያውያንን ጥቅም የሚያስከብር እንደሚሆን ተናግረዋል።

ትውልደ ኢትዮጵውያኑ ለሀገራቸው ለወገናቸው እንዲሁም ለዲናቸው የሚያበረክቱትን አስተዋፅኦ በተደራጀና ተቋማዊ ቅርፅ ባለው መንገድ ለማድረግ ትልቅ እድል የሚሰጥ መሆኑንም አንስተዋል።

በሶስት የአለማችን ክፍሎች (ቀጠናዎች) ምክር ቤቱ እየተቋቋመ መሆኑን የተናገሩት ዑስታዝ አቡበከር ይኸው ምክር ቤት ከውጪ ጉዳይ ሚኒስቴርና በመላው ዓለም ከሚገኙ ኤምባሲዎችና ቆንስላ ፅ/ቤቶች ጋር በትብብር እንደሚሰራ ተናግረዋል።

የጠቅላይ ምክር ቤቱ ምክትል ስራ አስኪያጅና የዲያስፓራ ምክር ቤት አስተባባሪ ሐጂ አብዱልአዚዝ አሎ በመላው ዓለም የሚኖሩ ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞችን ተሳታፊነት የሚያረግጥ ስራ በጠቅላይ ምክር ቤቱ ሲሰራ መቆየቱን ተናግረዋል።

በዚህም ምክርቤቱን የማቋቋም ሂደቱ መጀመሩን እና በአፍሪካ ፣ሰሜን አሜሪካ ፣እና መካከለኛው ምስራቅ ቀጠና የተለያዩ ሀገራት ላይ የማቋቋም ሂደት ላይ መሆኑን ተናግረዋል።

በሰሜን አሜሪካ በሚኒሶታ ስቴት፣ የጽ/ቤት ማቋቋም ሂደቱ የተጠናቀቀ ሲሆን ፣ ዋሺንግተን ካሊፎርኒያ እና ካናዳ የምስረታ ሂደቱ እየተከናወነ መሆኑን ነው ሐጂ አብዱልአዚዝ ገልፀዋል።

በመካከለኛው መስራቅ ቀጠና በሦስት አገራት ጽ/ቤቱን ለመቋቋም የሚያስችል መደላድል ለመፍጠር ውይይቶች እየተከናወኑ መሆኑን ያነሱት ሐጂ አብዲልዓዚዝ አሎ በደቡብ አፍሪካ የማቋቋም ሂደት መጀመሩን እና በሳምንታት ጊዜ ውስጥ እንደሚጠናቀቅ ገልፀዋል።

ወደፊት ጽ/ቤቶቹ መቋቋምን ተከትሎ የዲያስፖራ ምክር ቤት በቀጣይ እንደሚቋቋም ነው ሐጅ አብዱልዓዚዝ የገለፁት።

••••••••••

የአራዳ ክ/ከተማ ሙስሊም ወጣቶች ሊግ ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
Facebook | https://www.facebook.com/Honeybadgerstube
Telegram | https://t.me/+0cG9-taq2jhhMDk0
Tiktok | tiktok.com/

በሐገራዊ ጉዳዮች ላይ ሁሌም ተሳትፏችን ይረጋገጣል። ተፈጥሮን መጠበቅ ከኢስላማዊ ተልዕኮዋችን አንዱ ነው።••••••••••የአራዳ ክ/ከተማ ሙስሊም ወጣቶች ሊግ ሕዝብ ግንኙነትይከታተሉን | Fo...
29/07/2025

በሐገራዊ ጉዳዮች ላይ ሁሌም ተሳትፏችን ይረጋገጣል። ተፈጥሮን መጠበቅ ከኢስላማዊ ተልዕኮዋችን አንዱ ነው።

••••••••••
የአራዳ ክ/ከተማ ሙስሊም ወጣቶች ሊግ ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | https://www.facebook.com/Honeybadgerstube
ቴሌግራም | https://t.me/+0cG9-taq2jhhMDk0
ቲክቶክ / tiktok.com/

የአለማችን አሳሳቢ ችግሮች ከሆኑት መካካል ከፍተኛ የሙቀት መጨመር (Global Warming) አንዱ ነው። ከፍተኛ የሙቀት መጨመር በተለይም በታዳጊ ሃገሮች ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ ይገኛል። ይ...
29/07/2025

የአለማችን አሳሳቢ ችግሮች ከሆኑት መካካል ከፍተኛ የሙቀት መጨመር (Global Warming) አንዱ ነው። ከፍተኛ የሙቀት መጨመር በተለይም በታዳጊ ሃገሮች ከፍተኛ ጉዳት እያደረሰ ይገኛል። ይህን ጉዳት ለመከላከል አንዱ መፍትሄ ዛፎችን መትከል ነው። ሀገራችን የከፍተኛ ሙቀት ችግሮች ተጋላጭ እንደመሆኗ መጠን ችግሩን ለመከላከል ባለፉት አመታት ከፍተኛ የችግኝ መትከል መርሃ ግብሮች ተከናውነዋል።

የምንኖርበትን ከባቢ ከጉዳት መጠበቅና መንከባከብ ነብያዊ (ሰዐወ) አደራ ነው። ቂያማ ነገ መሆኑን ቢያውቅ እንኳ በእጁ የያዘውን ችግኝ ይትከላት የሚል አስተምህሮ ባለቤት እንደሆነ ህዝብ በችግኝ ተከላዎች ላይ ላቅ ያለ ተሳትፎ እንዲኖረን ይጠበቃል።

በዚህም መሰረት በሃገር አቀፍ ደረጃ የፊታችን ሃሙስ በሚደረገው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ላይ የኢትዬጲያ ሙስሊም ወጣቶች ካውንስል ተሳትፎ ለማድረግ ዝግጅቱን አጠናቋል። በሃገራችን በሚገኙ በተለያዩ አካባቢዎች በጎ ፍቃደኞችን በማስተባበር 1 ሚሊየን ችግኝ የመትከል መርሃ ግብር አዘጋጅቷል::
••••••••••
የአራዳ ክ/ከተማ ሙስሊም ወጣቶች ሊግ ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | https://www.facebook.com/Honeybadgerstube
ቴሌግራም | https://t.me/+0cG9-taq2jhhMDk0
ቲክቶክ / tiktok.com/

28/07/2025
Alhamdulilah 🙏❤ወደ ጋዛ የእርዳታ መኪኖች መግባት መጀመራቸው ተገለጸ።ሀምሌ 20/2017የሰብዓዊ እርዳታ ቁሳቁሶችን የያዙ መኪኖች ከግብፅ ወደ ጋዛ ጉዞ መጀመራቸው ተገልጿል።ከትላንት ...
27/07/2025

Alhamdulilah 🙏❤

ወደ ጋዛ የእርዳታ መኪኖች መግባት መጀመራቸው ተገለጸ።

ሀምሌ 20/2017

የሰብዓዊ እርዳታ ቁሳቁሶችን የያዙ መኪኖች ከግብፅ ወደ ጋዛ ጉዞ መጀመራቸው ተገልጿል።

ከትላንት በስቲያ ጉዞ የጀመሩት መኪኖች 100 ሲሆኑ የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦቶችንና 840 ቶን ዱቄትና ሌሎችንም የምግብ ፓኬጆች ማካተታቸው ተገልጿል።

••••••••••
የአራዳ ክ/ከተማ ሙስሊም ወጣቶች ሊግ ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | https://www.facebook.com/Honeybadgerstube
ቴሌግራም | https://t.me/+0cG9-taq2jhhMDk0
ቲክቶክ / tiktok.com/

26/07/2025

Big shout out to my newest top fans! Fuad Mubarek, ኢማን አብዱል ጀሊል

25 የደግነት ዓመታት
25/07/2025

25 የደግነት ዓመታት

በሂጅራ ባንክ ሲካሄድ የቆየው የሲራራ አዋርድ የሥራ ፈጠራ ውድድር አሸናፊ ይፋ ተደረገሙሉ ለሙሉ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት በሚሰጠው ሂጅራ ባንክ፤ ሥራ ፈጣሪ እና ትጉህ ወጣቶችን ለማበረ...
25/07/2025

በሂጅራ ባንክ ሲካሄድ የቆየው የሲራራ አዋርድ የሥራ ፈጠራ ውድድር አሸናፊ ይፋ ተደረገ

ሙሉ ለሙሉ ከወለድ ነጻ የባንክ አገልግሎት በሚሰጠው ሂጅራ ባንክ፤ ሥራ ፈጣሪ እና ትጉህ ወጣቶችን ለማበረታት በሚል ውጥን ሲካሄድ የቆየው የሲራራ አዋርድ የሥራ ፈጠራ ውድድር በዛሬው ዕለት በተከናወነው የሽልማት መርሐ ግብር ሲጠናቀቅ አሸናፊው ይፋ ተደርጓል፡፡

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ኃላፊዎች፣ የመንግሥት ተቋማት ከፍተኛ ሥራ አመራሮች፣ የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት፣ የባንኩ ማኔጅመንት እና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች በተገኙበት በድምቀት በተከናወነው መርሐ ግብር ላይ ውድድሩን በአንደኛነት ያሸነፈው ተወዳዳሪ ዶ/ር ሚልኪያስ አሕመድ መሆኑ ይፋ ተደርጓል፡፡

አሸናፊው ተወዳዳሪ ለግብርና ምርታማነት በጣም አስፈላጊ የሆነ እና ለአፈር ማዳበሪያነት የሚውል ኦርጋኒክ ማዳበሪያ ከእንስሳት አጥንት በመፍጠር የማኅበረሰቡን ችግር የሚያቃል የፈጠራ ውጤት በማበርከቱ የሦስት ሚልዮን የቀርደል ሐሰን ፋይናንስኪንግ እና የ 300 መቶ ሺሕ ብር ተሸላሚ ሆኗል።

ሁለተኛ ደረጃን በመያዝ ያጠናቀቀው ዩሱፍ ዓሊ የገበሬዎችን የዕለት ተዕለት አድካሚና ኋላ ቀር የአሠራር ዘዴዎችን ወደ ተሻሻለ ደረጃ ለማምጣት በማሰብ የእህል ማጨጃ ማሽንን በመሥራት እና ለገበያ የማቅረብ የፈጠራ ሐሳብ በማቅረብ አሸንፏል፡፡ ለዚህ ተወዳዳሪ የአንድ ሚሊዮን ቀርደል ሐሰን ፋይናንሲንግ እና የ200 መቶ ሺሕ ብር ተበርክቷል፡፡

በሦስተኛነት ያሸነፈው ሙሐመድ ጁሐር በትንሽ ኃይል የሚሠራ የዶሮ እንቁላል ማፈልፈያ ማሽን በመሥራት 500 ሺ የቀርድ ፋይናንሲንግ ሺልማት እንዲሁም 100 መቶ ሺሕ ተሸላሚ ሆኗል። በተጨማሪም ጣሂር ኢሳ እና ኢስሐቅ ጋሊ በጋራ እንዲሁም ኢብራሂም ዓሊ በቅደም ተከተል 4ኛ እና 5ኛ ደረጃን በመያዝ ውድድሩን አጠናቀዋል።

••••••••••
የአራዳ ክ/ከተማ ሙስሊም ወጣቶች ሊግ ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | https://www.facebook.com/Honeybadgerstube
ቴሌግራም | https://t.me/+0cG9-taq2jhhMDk0
ቲክቶክ / tiktok.com/

25/07/2025

አላህ ሆይ!
ቤተሰባችን የሚባረክበት፤
መልካም መልካሙን የምንሰማበት፤
ልቅናህን የምናስተነትንበት፤
ከኩራት የምንላቀቅበት፤
በመተናነስ የምንደምቅበት፤
በሰለዋት የምናሸበርቅበት፤
ከዱዓ የማንዘናጋበት፤
ውብ ጁምዓ አድርግልን!

የኦሮሚያ መጅሊስ ለገዛው የዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ቀሪ ክፍያ የሚውል የገቢ ማሰባሰቢያ መረሃ ግብር በነገው ዕለት እንደሚያካሂድ ገለፀ! -ሐምሌ 17/2017የኦሮሚያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከ...
24/07/2025

የኦሮሚያ መጅሊስ ለገዛው የዋና መስሪያ ቤት ህንፃ ቀሪ ክፍያ የሚውል የገቢ ማሰባሰቢያ መረሃ ግብር በነገው ዕለት እንደሚያካሂድ ገለፀ!

-ሐምሌ 17/2017

የኦሮሚያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክርቤት በአዲስአበባ ከተማ ቦሌ ክ/ከተማ በቦሌ ቡልቡላ ወረዳ 12 ባለ 11 ወለል (G+10 ) የሆነ ዘመናዊ ህንጻ ግዢ መፈጸሙ የሚታወስ ነው።

የኦሮሚያ መጅሊስ ህንፃ ግዢውን የፈፀመው በ300 ሚሊዮን ብር መሆኑን የገለፀ ቢሆንም የተከፈለው ክፍያ 100 ሚሊዮን ብር ብቻ መሆኑን በመግለጫው ላይ ተነስቷል።

የኦሮሚያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሸይኽ ጋሊ ሙክታር እንዳሉት ህዝበ ሙስሊሙን በመተማመን የህንፃው ግዢ እንደተፈፀመ በመግለፅ ቀሪው የ200 ሚሊዮን ብር ክፍያ እንዲጠናቀቅ ሁሉም የድርሻውን እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።

ለህንፃው ቀሪ 200 ሚሊዮን ያልተጠናቀቀ ክፍያ ለመክፈል በነገው ዕለት ጁመዓ ሀምሌ 18/2017 በአዲስ አበባ ከተማ፣ በሸገር ከተማ እና በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ ዞኖችና ወረዳዎች ሙስሊሞችን ያሳተፈ የገቢ መሰባሰቢያ ፕሮግራም እንደሚካሄድ ገልፀዋል።

በዛሬው መግለጫ ላይ የተገኙት ኡስታዝ አህመዲን ጀበል ባስተላለፉት መልዕክት የኦሮሚያ መጅሊስ ላከናወነው የህንፃ ግዢ ምስጋናቸውን አቅርበው ያለበት እዳ እንዲከፈል ሁላችንም የድርሻችን ልንወጣ ይገባል ብለዋል።

የኦሮሚያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ላለፉት ዓመታት ሰፊውን የኦሮሚያ ሙስሊም የሚወክል ህንፃ እንዳልነበረው በዛሬው መግለጫ ላይ የተነሳ ሲሆን ይህን የህንፃ ግዢ ለፈፀሙ የኦሮሚያ መጅሊስ አመራሮች በዝግጅቱ ላይ የተገኙ ኡስታዞች አመስግነዋል።

ህዝበ ሙስሊሙም የኦሮሚያ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ያለበትን እዳ እንዲከፈል በነገው ዕለት በሚካሄደው የገቢ ማሰባሰቢያ መርኅግብር ላይ በንቃት እንዲሳተፍ ጥሪ ቀርቧል።

••••••••••
የአራዳ ክ/ከተማ ሙስሊም ወጣቶች ሊግ ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
ፌስቡክ | https://www.facebook.com/Honeybadgerstube
ቴሌግራም | https://t.me/+0cG9-taq2jhhMDk0
ቲክቶክ / tiktok.com/

Address

Arada Sub-city
Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Arada Muslim Youth posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share