
30/07/2025
በአዲስ አበባ መስጂዶች ምርጫ መቼ ይካሄዳል?
የአዲስ አበባ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ምርጫ የሚካሄድባቸውን ቀናት ዝርዝር ይፋ አድርጓል።
በአዲስ አበባ የ2017 ምርጫ አስፈፃሚ ቦርድ ፅ/ቤት ከመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች ጋር ውይይት አደርጓል።
በውይይቱ ወቅት ምርጫ በየትኞቹ ቀናት እንደሚካሄድ እና የሚመረጡ ተወካዮች ትውውቅ መቼ እንደሚካሄድ ይፋ ተደርጓል።
የቦርዱ ሰባሳቢ አቶ ጅብሪል ዑስማን በአዲስ አበባ 326 የምርጫ ማዕከላት መኖራቸውን ገልፀው፣ከሰኔ 18 እስከ ሐምሌ 13 ፣2017 ዓ.ል ጀምሮ በ11ዱም ክፍለ ከተሞች የተጀመረው የመራጮች ምዝገባ ሂደቱ ፍፁም ሰላማዊ እንደነበር ተናግረዋል።
በቴክኖሎጂ የተደገፈው የምርጫ ምዝገባ የተመዝጋቢዎችን መረጃ ወደ መረጃ ቋት የማስገባት ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉን አቶ ጅብሪል ገልፀዋል።
ቦርዱ የምርጫውን ሂደት ለሕዝበ ሙስሊሙ ተደራሽ ለማድረግ በሚደረገው ጥረት የሚዲያ ተቋማት ከፍተኛ ሚና ስላላቸው አጠናክረው እንዲቀጥሉ የቦርዱ አባል ዶክተር ኢብራሂም ሙሉሸዋ ጥሪ አቅርበዋል።
የምርጫ ሂደቱም በአዲስ አበባ ምን እንደሚመስል የወጣው መርሃግብር ይፋ ሆኗል።
በዚህም መሠረት፦
የዑለማ ዘርፍ ትውውቅ ነሐሴ 2/17 ከቀኑ 8:30
የምሁራን ዘርፍ ትውውቅ ነሐሴ 4/17 ከጧቱ 3:00
የወጣቶች ዘርፍ ትውውቅ ነሐሴ 4/17 ከጧቱ 3:00 ጀምሮ
የሴቶች ዘርፍ ትውውቅ ነሐሴ 4/17 ከቀኑ 8:30
የስራ ማሕበረሰብ ዘርፍ ትውውቅ ነሐሴ 4/17 ከ8:30 ይካሄዳል።
ከነሐሴ 9 እስከ ነሐሴ 11/17 ዓ.ል በአምስት ዘርፎች የሚደረገው ምርጫ ይደረጋል።
በዚህም መሰረት ፦
የዑለማ ዘርፍ ምርጫ ነሐሴ 9/17 ከቀኑ 8:30 እስከ ቀኑ 11:00 ]የምሁራን ዘርፍ ምርጫ ነሐሴ 9/17 ከጧቱ 3:00 6:30
የወጣቶች ዘርፍ ምርጫ ነሐሴ 11/17 ከጧቱ 3:00 እስከ 6:30
የሴቶች ዘርፍ ምርጫ ከነሐሴ 11/17 ከሰዓት 8:00 እስከ 11 ሰዓት
የስራ ማሕበረሰብ ዘርፍ ምርጫ ከ8:00 እስከ ቀኑ 11:00 ይካሄዳል
ነሐሴ 9/17 በዑለማ ዘርፍ የሚጀመረው የመጅሊስ ምርጫ በተቀመጠው ቀን እና ሰዓት ላይ መራጩ በመገኘት ኢስላማዊ ኅላፊነታቸውን እንዲወጡ ቦርዱ ጥሪውን አቅርቧል።
••••••••••
የአራዳ ክ/ከተማ ሙስሊም ወጣቶች ሊግ ሕዝብ ግንኙነት
ይከታተሉን | Follow us፡
Facebook | https://www.facebook.com/Honeybadgerstube
Telegram | https://t.me/+0cG9-taq2jhhMDk0
Tiktok | tiktok.com/
Youtube | https://youtube.com/?si=2XCJV6tmnkXMLfB7