Inside Ethiopia

Inside Ethiopia ፔጃችንን ላይክ በማድረግ ፈጣን እና ተአማኒነት ያላቸውን መረጃዎች በፍጥነት እንዲደርሶ ያድርጉ

የ25 ሰዎች ሕይወት አለፈ😥በሰሜን ወሎ ዞን ዳውንት ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ25 ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡አደጋው ከኩርባ ከተማ ወደ ደሴ ሲጓዝ የነበረ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ  በመገ...
23/01/2025

የ25 ሰዎች ሕይወት አለፈ😥

በሰሜን ወሎ ዞን ዳውንት ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ25 ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡

አደጋው ከኩርባ ከተማ ወደ ደሴ ሲጓዝ የነበረ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ በመገልበጡ መድረሱን የወረዳው ፖሊስ ጽ/ቤት ሃላፊ ም/ኢንስፔክተር ጌታቸው አራጌ ተናግረዋል፡፡

በደረሰው አደጋም ለሕልፈት ከተዳረጉት በተጨማሪ 14 ሰዎች ላይ ከባድ እና 15 ሰዎች ላይ ደግሞ ቀላል ጉዳት መድረሱን ገልጸዋል።

ጉዳት የደረሰባቸው ዜጎች በደላንታና ደሴ ሆስፒታሎች ሕክምና እየተከታተሉ እንደሚገኙ መጥቀሳቸውንም የዞኑ ኮሙኒኬሽን መረጃ ያመላክታል፡፡

?🤔
23/01/2025

?🤔

  ከ105ሚሊዮን በላይ አንባቢዎች ያሉት የአሜሪካው Time መጽሔት በእትሙ ስለ ትናንቱ የአዕላፍ ዝማሬ ፕሮግራም ሰፋ ያለ ዘገባ አውጥቷል።በዘገባው👉በኢትዮጵያ ከመቶ ሰዎች 62ቱ የኦርቶዶክስ...
07/01/2025


ከ105ሚሊዮን በላይ አንባቢዎች ያሉት የአሜሪካው Time መጽሔት በእትሙ ስለ ትናንቱ የአዕላፍ ዝማሬ ፕሮግራም ሰፋ ያለ ዘገባ አውጥቷል።
በዘገባው
👉በኢትዮጵያ ከመቶ ሰዎች 62ቱ የኦርቶዶክስ እመነት ተከታይ መሆናቸውን
👉በአለም ከሩሲያ ቀጥሎ ሰፊ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ህዝብ ያለባት አገር መሆኗን አክትቷል።
👉ከዚህ በተጨማሪም ስለ አዕላፍ ዝማሬ አጀማመርና ሂደት፣ ስለ የኦርቶዶክስ እምነት በአላት ሰፋ ያሉ ትንታኔዎችን ለአንባቢዎቹ አስነብቧል።

ድምጻዊ ቴድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) የአድዋ በአልን አስመልክቶ ያስተላለፈው መልዕክት።
29/02/2024

ድምጻዊ ቴድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) የአድዋ በአልን አስመልክቶ ያስተላለፈው መልዕክት።

ነቢያት ጌታ "ይወርዳል ይወለዳል" ብለው የተናገሩት ትንቢት እንዲፈጸም ተመኝተው ጾሙ ጸለዩ:: እኛ ስለምን እንጾማለን? ክርስቶስ ተወልዶ ፣ ተጠምቆ ፣ አስተምሮ ፣ ተሰቅሎ ፣ ሞቶ ፣ ተነሥቶ...
24/11/2023

ነቢያት ጌታ "ይወርዳል ይወለዳል" ብለው የተናገሩት ትንቢት እንዲፈጸም ተመኝተው ጾሙ ጸለዩ:: እኛ ስለምን እንጾማለን? ክርስቶስ ተወልዶ ፣ ተጠምቆ ፣ አስተምሮ ፣ ተሰቅሎ ፣ ሞቶ ፣ ተነሥቶ ፣ ዐርጎ ፣ በአባቱ ቀኝ አይደለምን? አሁን ለምን እንጾማለን? ብለን እናስባለን::

ጌታ በእኔና አንተ ልብ ውስጥ እውነት ተወልዶአልን? እውነት የእኛ ልብ እንደ ቤተልሔም ግርግም ለክርስቶስ ማደሪያ ሆኖአል? ማደሪያ አሳጥተን ከእናቱ ጋር አልመለስነውም?

የጥምቀቱ ትሕትና በእኛ ልብ መቼ ደረሰ? የስቅለቱ ሕማም መች በእኛ ሕሊና ተጻፈ? የትንሣኤው ተስፋ የዕርገቱ ልዕልና በእኛ ልቡና መቼ ዐረፈ?

ስለዚህ ነቢያት "ውረድ ተወለድ" ብለው የጾሙትን ጾም እንጾማለን:: ጌታ ሆይ በእኔ ሕይወትም ውስጥ ውረድ ተወለድ የእኔን ሰውነት ማደሪያህ አድርገው:: ሕዋሳቶቼ ከኃጢአት አርፈው እንደ ቤተልሔም ግርግም ማደሪያህ ይሁኑ::

የቤተልሔም እንስሳት ትንፋሽ ገበሩልህ ፣ የቢታንያ ድንጋዮች ዘማሪ ቢጠፋ ሊዘምሩ ዝግጁ ነበሩ ፣ የቤተ መቅደስ መጋረጃ ለክብርህ ተቀደደ ፣ ጨረቃ ላንተ ደም ለበሰች ፣ ፀሐይ ስላንተ ጨለመች ፣ ከዋክብት ለስምህ ረገፉ ፣ ዓለቶች ለፍቅርህ ተሰነጠቁ::

ከቤተልሔም እንስሳት ፣ ከቢታንያ ድንጋዮች ፣ ከቤተ መቅደስ መጋረጃ እኔ እንዴት አንሼ ልገኝ? የቢታንያ ድንጋይ ያወቀህን ያህል ሳላውቅህ ፣ የቤተ መቅደስ መጋረጃ የተረዳህን ያህል ሳልረዳህ እንዴት ልኑር?

ዓለት ላንተ ሲሰነጠቅ የኔ ልብ ለምን ከዓለት ደነደነ? ጨረቃ ደም ስታለቅስ እኔ መከራህ ለምን አልተሰማኝም?
ሙታን በሞትህ ሲነሡ እኔ ምነው ከኃጢአት ሞት መነሣት ተሳነኝ?

ለዚህ ነው በእኔ ሕይወት ገና አልተወለድክም የምለው::

ስለዚህ ጌታ ሆይ የነቢያትህን ጾም ጸሎት ሰምተህ የወረድህ የተወለድህ ጌታ ሆይ በእኔም ሕይወት ውረድ ተወለድና እኔም ከመላእክት ጋር አብሬ ልዘምር ፣ ከሰብአ ሰገል ጋር ሥጦታህን ልቁጠር ፣ ከእረኞች ጋራ ልደነቅ:: ልደትህ ሳይገባኝ ምጽዓትህ እንዳይደርስብኝ እርዳኝ::

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ጾመ ነቢያት 2015 ዓ.ም. የተጻፈ

ጋምቤላ‼በጋምቤላ ክልል ኢንታግ ወረዳ በተቀሰቀሰ ግጭት የሰዎች ህይወት ማለፉ ተሰምቷል።ግጭቱ ትናንት አኝዋክና ኔዎር መካከል እንደተፈጠረ የአካባቢው የመረጃ ምንጮች ጠቁማለች።ወደ ዋና ከተማ ...
16/11/2023

ጋምቤላ‼

በጋምቤላ ክልል ኢንታግ ወረዳ በተቀሰቀሰ ግጭት የሰዎች ህይወት ማለፉ ተሰምቷል።ግጭቱ ትናንት አኝዋክና ኔዎር መካከል እንደተፈጠረ የአካባቢው የመረጃ ምንጮች ጠቁማለች።ወደ ዋና ከተማ እንዳይስፋፋ በሚል የፌደራል መንግስቱ የፀጥታ ኃይሎች ወደ ስፍራው አቅንተዋል።

😁😁 ወደዉ አይስቁ አለከወደ ሶማሊያ ፑንትላንድ የተሰማው ዜና ፈገግታን የሚጭር ሆኗል።"የኢትዮጵያውን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድን በመምሰሌ የደህንነት ስጋት ስላለብኝ ጥበቃ ይደረግልኝ" ...
16/11/2023

😁😁 ወደዉ አይስቁ አለ

ከወደ ሶማሊያ ፑንትላንድ የተሰማው ዜና ፈገግታን የሚጭር ሆኗል።

"የኢትዮጵያውን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድን በመምሰሌ የደህንነት ስጋት ስላለብኝ ጥበቃ ይደረግልኝ" ያሉት በፑንትላንድ ግዛት የዋኢዮ ወረዳ አስተዳዳሪ ኢሳቅ አህመድ ሀሰን በሶማሊያ ሶሻል ሚዲያዎች የእለቱ ሳቅ የሚጭር መነጋገሪያ ሆኗል።

ሰውዬው በሶሻል ሚዲያ ብቅ ብለው በአፍ ሶማሊ ቋንቋ "አብይን ትመስላለህ እያሉ ህይወቴን አደጋ ውስጥ የከተቱብኝ ሰዎች አሉ። እኔ ሳልሆን አብይ ነው እኔን የሚመሰለው። በዚህ ምክንያት ለህይወቴ ሰለሰጋሁ ያለጠባቂ መንቀሳቀስ አቁሜለሁ።

በዛ ላይ የአባቱ እና አባቴ ስም አንድ ነው። ወደ ኢትዮጵያ የሄድኩት በመለስ ዘመን ነው አሁን መሄድ ብፈልግም ለደህንነቴ ስጋት ስላለብኝ ጠባቂ ያስፈልገኛል።" ብለዋል።

በፑንትላንድ ግዛት የዋኢዮ ወረዳ አስተዳዳሪ ይህን መልእክት ያስተላለፉት ለቀልድ ይሁን የምራቸውን ግን የታወቀ ነገር የለም።

እናንተ ምን አላችሁ? ይመሳሰሉ?

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በ2016 ዓ.ም ወደ ቲክኒክና ሙያ መግቢያ ነጥብ ይፋ አድርጓል።
16/11/2023

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በ2016 ዓ.ም ወደ ቲክኒክና ሙያ መግቢያ ነጥብ ይፋ አድርጓል።

የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ጥቅምት 5/2016 በፃፈው ደብዳቤ ከላይ ተያይዟል።ዝርዝሩ ከታች አለ።“የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በአብክመ የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ አስተዳደር ...
17/10/2023

የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ጥቅምት 5/2016 በፃፈው ደብዳቤ ከላይ ተያይዟል።ዝርዝሩ ከታች አለ።

“የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በአብክመ የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ አስተዳደር ውስጥ በሰሜኑ ጦርነት ምክንያት ለተከታታይ ሁለት ዓመታት ተቋርጦ ከቆየ በኋላ ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ ዲስትሪክቱን ጎንደር በማድረግ አገልግሎት ሲሰጥ የቆየ መሆኑ የአደባባይ ሚስጥር ነው።

ነገር ግን በአሁኑ ሰዓት የተዘረጋው ሲስተም ወደ ተሟላ ስራ እንዲገባ በዞናችን የሚገኙ ማእከላት በምንጠይቅበት ሰዓት ሲስተሙን ሊያጓትቱ የሚችሉና በህዝብ ዘንድ ቅሬታን የሚያስነሱ ማለትም በአራቱም የአገልግሎት ማእከላት /ዳንሻ፣ ባህከር ፣ አድረመጥና ሁመራ / የሚገኙ ሞያተኞችን ደሞዝ ወደ ሽሬ ዲስትሪክት የማዛወር ፍላጎት እንዳለ ተረድተናል።

በመሆኑም በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል በቀደመው ይቀጥል በሚል አገልግሎቱን ወደ ትግራይ ለማሻገር መሞከር የአገልግሎት አሰጣጡን ከማወሳሰቡም በላይ በህዝቡ ዘንድ ቅሬታ የሚፈጥር መሆኑን ከግምት ውስጥ በማስገባት ከጎንደር ዲስትሪክት የተዘረጋውን ሲስተም በተሟላ መልኩ በማስጀመር እየተሰጠ ያለውን አገልግሎት የበለጠ እንዲሳለጥ እንጠይቃለን!”

አቶ አሸተ ደምለው ተድላ የወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን ዋና አስተዳዳሪ

Hmmmmm ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ለግብፁ አቻቸዉ መልዕክት ላኩየኤርትራ መንግስት ከፍተኛ የልዑካን ቡድን ከሰሞኑ በግብፅ ጉብኝት እያደረገ ነበር።በኤርትራዉ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኦስማን...
15/10/2023

Hmmmmm
ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ለግብፁ አቻቸዉ መልዕክት ላኩ

የኤርትራ መንግስት ከፍተኛ የልዑካን ቡድን ከሰሞኑ በግብፅ ጉብኝት እያደረገ ነበር።

በኤርትራዉ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኦስማን ሳሌህ እና በፕሬዚዳንቱ አማካሪ የማነ ገብረዓብ የተመራዉ ልዑክ በዛሬዉ እለት ከፕሬዚዳንት ኢሳያስ የተላከዉን መልዕክት ለግብፁ አቻቸዉ ማድረሳቸዉን ዳጉ ጆርናል ከኤርትራ የመረጃ ሚኒስቴር ተመልክቷል።

ሁለቱ ሀገራት የሱዳኑን ግጭት ለማስቆም በቅርበት እየሰሩ ሲሆን ይህንንም ለመፈጸም ፕሬዚዳንቶቹ በቅርቡ መገናኘታቸዉ አይዘነጋም። የኤርትራዉ የመረጃ ሚኒስቴትር እንዳለዉ ፥ የፕሬዚዳንት ኢሳያስ መልእክት በሱዳን ችግር ላይ ያተኮረ ሲሆን ጦርነቱን ለማስቆም የሚደረገውን ጥረት በማበረታታት ዘላቂ ሰላምን ለማረጋገጥ ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ያለመ ነው ብሏል።

ፕሬዝዳንት አልሲሲም ፤ የኤርትራዉ አቻቸዉ ለሱዳን ላሳዩት ጠንካራ ቁርጠኝነት እና ወዳጅነት አመስግነው ኤርትራ እና ግብፅ በጉዳዩ ላይ ተመሳሳይ አቋም እንዳላቸው ተናግረዋል።

ከፍተኛ የልዑካን ቡድኑ ከግብፅ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሜህ ሽኩሪ ጋር በተመሳሳይ ርዕሰ ጉዳይ እና የሁለትዮሽ ግንኙነት እና ትብብርን በማሳደግ ላይ መወያየታቸው አይዘነጋም።

በበረከት ሞገስ

"ይህ እንዳይመጣ ብዙ ተማጽኖ ስናቀርብ የነበረ ቢሆንም ሽበት እና ክህነት የማይከበርበት ዘመን ላይ ደርሰን ለዚህ ኀዘን በቅተናል። በኀዘን የተጎዳችሁ አባቶችና እናቶችም ይህ ቢሆን ኖሮ እያላ...
14/10/2023

"ይህ እንዳይመጣ ብዙ ተማጽኖ ስናቀርብ የነበረ ቢሆንም ሽበት እና ክህነት የማይከበርበት ዘመን ላይ ደርሰን ለዚህ ኀዘን በቅተናል። በኀዘን የተጎዳችሁ አባቶችና እናቶችም ይህ ቢሆን ኖሮ እያላችሁ ራሳችሁን እንዳትጎዱ፤ የእናንተ መጎሳቆል የሞቱትን ቀና አያደርግምና ልባችሁን እንድታበረቱ እናሳስባለን ምክንያቱም መቃብር መጨረሻችን ያልሆነ የትንሣኤ ሕዝብ ነን"--- ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት
እኚህ የሀይማኖት አባታችን ሰላም ይውረድ፣ በአንድ ወቅት ደግሞ ድምፄ ታፈነ ስላሉ በአክቲቪስት እና ባለስልጣናት ጭምር " ጁንታ" ሲባሉ፣ እንደተራ ግለሰብ ፌስቡክ ላይ ሲሰደቡ ነበር። በአንድ ወቅት እኔንም "ለምን ቃለ መጠይቅ አደረግክላቸው" ተብሎ ብዙ ጉምጉምታ እና ማስፈራርያ ነበር (ጭራሽ ቃለ መጠይቁን ያደረግኩት እኔ ባልሆንም)።
በረከትዎ ይደርብን አባታችን።

የትግራይ አካባቢዎች ከፍተኛ የሃዘን ድባብ ውስጥ ናቸው።ጥቅምት 2 በይፋ የታወጀው የትግራይ ሰማእታት የሃዘንና የክብር ቀን ስነ-ሰርአት ተከትሎ የክልሉ ከተሞችና ገጠሮች በከፍተኛ የሃዘን ድባ...
14/10/2023

የትግራይ አካባቢዎች ከፍተኛ የሃዘን ድባብ ውስጥ ናቸው።

ጥቅምት 2 በይፋ የታወጀው የትግራይ ሰማእታት የሃዘንና የክብር ቀን ስነ-ሰርአት ተከትሎ የክልሉ ከተሞችና ገጠሮች በከፍተኛ የሃዘን ድባብ ውስጥ ይገኛሉ።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ በትግራይ ያለው የሃዘንና የመርዶ ስነ-ሰርአትና ተዛማጅ ጉዳዮች አፈፃፀም በሚከተለው ሪፓርታዥ አጋርቶናል።

ዓርብ ጥቅምት 2/2016 ዓ.ም ከሰዓት በኃላ በክልሉ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕረዚደንት ጌታቸው ረዳ የሃዘንና የክብር ስነ-ሰርአቱ መታወጅ ተከትሎ ከ1:00 ሰዓት አመሻሽ ጀምሮ ከማይጨው እስከ ሸራሮ በ500 ኪሎ ሜትር ርቀት አከባቢ የሚገኙ ከተሞች ሰማእታት የሚዘክር ሻማ ያበሩ ሲሆን ፤ በሌሊቱ በቤተከርስትያንና በመስጊዶች ቅዳሴና ፀሎት እንዲሁም ዱዓ ሲያደርጉ አድረዋል።

ጥቅምት 3 ጠዋት 12:00 ሰዓት የክልሉ ባንዴራ ዝቅ ብሎ ሲውለበለብ ፤ በመቐለ ጥቅምት 3 ከምሽቱ 1:00 ሰማእታትዋ ለማሰብ የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕረዚደንትና ካቤኔያቸው ፣ የህወሓት ሊቀመንበርና የከተማው ነዋሪ በተገኘበት ጥዋፍ አብርታለች።

የሃዘንና የክብር ስነ-ሰርአቱ ለማስፈፀም የወጣ መመሪያ የሚከለክላቸው ነገሮች ተፈፃሚነታቸው ከጥቅምት 3 ጀምሮ መሆኑ በመመሪያ የተቀመጠ ቢሆንም እንደ መጠጥ ቤት የመሳሰሉ አገልግሎት ሰጪዎች በራሳቸው ፍላጎት ጥቅምት 2 ከሰአት በኃላ ጀምሮ ዘግተዋል።

ጥቅምት 2 ከሌሊቱ 8:00 ሰዓት ጀምሮ በተሰው ቤተሰቦች መኖሪያ ይፋዊ የመርዶ ስነ-ሰርአት የተካሄደ ሲሆን የመርዶ ስነ-ሰርአቱ የሚያከናውኑት ፦
- የአገር ሽማግሌ
- የሃይማኖት አባቶች
- ታጋዩ ሲሰዋ በአጠገቡ የነበረ የአይን ምስክር
- ከነባር ታጋይ የተወጣጡ ኮሚቴ ሲሆኑ ቤተሰቡ ሲያረዱ ከመንግስት የተላከ የክብር መግለጫ የምስክር ወረቀትና የትግራይ ባንዴራ በመስጠት ነው።

መርዶ ከተነገረ በኃላ የተሰዋ ታጋይ ቤተሰብ ኮሚቴው አረጋግቶ በማጀብ እና በመምራት መርዶ ወደ ተነገሩ ሌሎች ቤተሰቦች ጋር በማቀላቀል ወደ መሰባሰብያ ቦታ ወስደዋቸዋል።

ከጥዋቱ 12:30 በየአከባቢው መርዶ የተነገረው ሁሉም ወደየ መገናኛ ቦታ ተሰባሰበ። በቦታው ደርሶ ልክ 1:00 ሰአት ከጠዋቱ በአገር ውስጥና ከአገር ውጭ የሚኖር ትግራዋይ በሚድያ የሚመራ የአንድ ደቂቃ የህሊና ፀሎት ተደርጓል።

ከህሊና ፀሎት በኋላ የተሰዋ ቤተሰብ አባል እንደየ እምነቱ ወደ ሚመለከተው የማምለክያ ቦታ በህዝብ ታጅቦ ተጓዘ።

በእምነት ማስፈፀምያ ቦታ እንደየ እምነቱ የሚሰጠው ፀሎተ ፍትሃት፣ ዱዓና መፅናኛ የሃይማኖት አስተምህሮ ከተሰጠ በኃላ ከጊዚያዊ አስተዳደሩ የተላከ መልእክት በንባብ ቀርቧል።

በቤተ እምነት የተካሄደው ፍፃሜ ከተጠቃለለ በኃላ የሰማእታት ቤተሰብ በህዝቡ በመታጀብ ወደየ ቤታቸው ተመልሰዋል።

በየሃይማኖት ማምለኪያ ቦታዎቹ ከሚፈፀም ስነ-ሰርአት ጎን ለጎን በትግራይና ድምፂ ወያነ ቴሌቪዥን በቀጥታ ስርጭት የተላለፈ በሰማእታት የመታሰብያ ሃወልት በክብር መዝገብ ፅሁፍ የማኖርና የአበባ ጉንጉን የማስቀመጥ ስነ-ሰርአት ተከናውኗል።

መቐለ ጨምሮ ማይጨው፣ መኾኒ፣ ዓዲጉዶም፣ ውቕሮ፣ ዓብዪ ዓዲ፣ ዓዲግራት፣ ዓድዋ፣ አክሱም፣ ሽረ፣ ሸራሮና ሌሎች ከተሞች በከፍተኛ የሃዘን ድባብ ውስጥ ሲሆኑ እንደ ባንክ የመሳሰሉ አገልግሎት ሰጪዎች የሃዘንና የክብር ቀን ስነ-ሰርአቱ ለማስፈፀም አስመልክቶ በወጣ መመሪያ መስረት ዝግ ሆነው ውለዋል።

የትግራይ ሰማእታት የሃዘንና የክብር ቀን ስነ-ሰርአት በተለያዩ ፕሮግራሞች በመቀጠል ጥቅምት 6 በህዝባዊ ሰልፍ እንደሚጠቃለል የወጣው መርሃ ግብር ያስረዳል።

መረጃው ተዘጋጅቶ የተላከው ከመቐለ የቲክቫህ ቤተሰብ አባል ነው።

ፎቶ፦ ከላይ ተያይዟል

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Inside Ethiopia posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Inside Ethiopia:

Share