ጦራ ከተማ አሰተዳደር ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • ጦራ ከተማ አሰተዳደር ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት

ጦራ ከተማ አሰተዳደር ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ከተፎካካሪነት ወደ መሪነት!!

ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ የስልጤ ዞን ቅርንጫፍ በሀገራችን እግር ኳስ ባለታሪክ የነበረው ወንድማችን ሳዳት ጀማል ህልፈት የተሰማውን እጅግ ጥልቅ ሀዘን ገለፀ======================...
01/10/2025

ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ የስልጤ ዞን ቅርንጫፍ በሀገራችን እግር ኳስ ባለታሪክ የነበረው ወንድማችን ሳዳት ጀማል ህልፈት የተሰማውን እጅግ ጥልቅ ሀዘን ገለፀ
==================================
ወንድም ሳዳት ጀማል በኢትዮጵያ እግር ኳስ ባለታሪክ ነው። በተለይም ብሔራዊ ቡድናችንን በግብ ጠባቂነት; በሴቶች ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝነት እና በስልጤ ዞን የታዳጊዎች እግር ኳስ ፕሮጀክት (ሳዳትና ከማል የታዳጊዎች ፕሮጀክት) ከወንድም ከማል አህመድ ጋር በመተባበር መስርቶ ማሰልጠን ሀገሩን ያገለገለባቸው ጥቂት አብነቶች ናቸው። በተለያዩ ጥልፍልፍ የፖለቲካ ችግሮች ምክንያት በሁለት እግሩ ቆሞ መሄድ ባቃተው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ የነበሩትን ጥልፍልፍ ችግሮች ተቋቁመው አሻራቸውን ካሳረፉ ዜጎቻችን አንዱ በነበረው ወንድማችን ሞት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለፅን ለቤተሰቦቹ ለወዳጅ ዘመዶቹና ለመላው የሀገራችን ህዝብ ባጠቃላይ እንዲሁም ለእግር ኳስ ቤተሰቡ በተለይ መፅናናትን; ለወንድማችን ዘላለማዊ የሰላም ረፍትን (ጀነትን) እንመኛለን!!

የወራቤ ከተማችን ከፍታ የሁላችንም ከፍታ ነውና ለዕድገቷ የሁላችንም ርብርብ ይገባታል። ህዝባችን የሚመራው ታማኝና እውነተኛ መሪ ካገኘ ተዓምር መስራት እንደሚችል በተደጋጋሚ አሳይቷል። የዛሬው...
20/09/2025

የወራቤ ከተማችን ከፍታ የሁላችንም ከፍታ ነውና ለዕድገቷ የሁላችንም ርብርብ ይገባታል። ህዝባችን የሚመራው ታማኝና እውነተኛ መሪ ካገኘ ተዓምር መስራት እንደሚችል በተደጋጋሚ አሳይቷል። የዛሬውም የዚሁ ነፀብራቅ ነው።

የሀገራችን ኩራትና ብሔራዊ ኃብታችን የሆናችሁት ብርቅዬዎቹ የሀይረንዚ ልዩ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ልጆቻችን በ2017 ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ያስመዘገባችሁት ውጤት በእናንተና በታ...
15/09/2025

የሀገራችን ኩራትና ብሔራዊ ኃብታችን የሆናችሁት ብርቅዬዎቹ የሀይረንዚ ልዩ 2ኛ ደረጃ ት/ቤት ልጆቻችን በ2017 ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ያስመዘገባችሁት ውጤት በእናንተና በታታሪ መምህራኑ እንዲሁም በት/ቤቱ የመማር ማስተማር አመራርነት (Instructional leadership) ብቃት ከነበረን መተማመን አኳያ የሚገርመን ባይሆንም እንደተለመደው ሀገራችንንና ህዝባችንን ከፍ ስላደረጋችሁ አላህ ከፍ ያድርጋችሁ ብሎ መመረቅ እና የደስታ መግለጫና ምስጋና ስለሚገባችሁ እንኳን ደስ ኣላችሁ!!!; እንኳን ደስ ኣለን!!!❤️❤️❤️
በዚህ አጋጣሚ በሀገራችን የትምህርት ስርዓት ላይ ከፖሊሲና ቀረፃና ስትራተጂ ዕይታ ጀምሮ ያለው ዘርፈ ብዙና እጅግ ውስብስብ የሆነ አሳሳቢ የትምህርት ጥራት ችግሮች መፍትሄ ትምህርት መር ብሔራዊ ስትራቴጂን በአማራጭነት እንዲታይም እናሳስባለን!!!

Freedom and Equality Partyነጻነትና እኩልነት ፓርቲ“ሚዛናዊ እና ምክንያታዊ ፖለቲካ”​​ ህዳሴ ግድብ ምጣኔ ሀብታዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ እና  ጂኦ ፖለቲካዊ ኃይል ነው!!በግድቡ ግንባ...
09/09/2025

Freedom and Equality Party
ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ
“ሚዛናዊ እና ምክንያታዊ ፖለቲካ”
​​

ህዳሴ ግድብ ምጣኔ ሀብታዊ፣ ዲፕሎማሲያዊ እና ጂኦ ፖለቲካዊ ኃይል ነው!!
በግድቡ ግንባታ ያሳየነውን አንድነት ሰላምን በማስፈን እንድገመው!!
ግድቡ በመጠናቀቁ መላው ኢትዮጵያን እንኳን ደስ አለን!!
ኢትዮጵያውያን ለረዢም ዘመናት አባይን ገድበው ለመጠቀም ሲመኙ፣ ጉጉታቸወን ለማሳካት ባለመቻላቸው ሲቆጩ ኖረዋል። በርካታ ትውልድ ለአባይ ሲቀኝ እና ሲያንጎራጉር አባይም እንጉርጉሮውን እየሰማ የሀገሩን ለም አፈር ተሸክሞ ድንበሯን አቋርጦ ለሺህ አመታት ሲፈስ ኖሯል። ዘመን አልፎ ዘመን፣ ትውልድ አልፎ ትውልድ እየተተካ በኢትዮጵያ ዘመን አቆጣጠር በወርሀ መጋቢት 2003 የአባይ የሺህ ዓመታት ታሪክ ሊቀየር በጉባ ተራሮች መካከል የአባይ ማሰሪያ ገመድ ተዘረጋ፣ ህዳሴ ግድብ ተወለደ። ግድቡ ላለፉት አስራ አራት አመታት ሲገነባ ቆይቶ እነሆ ዛሬ ሊመረቅ በቅቷል። እንኳን ደስ አለን!!

ህዳሴ ግድብን ለመገንባት በርካታ ኢትዮጵያውያን ገንዘባቸውን፣ ጉልበታቸውን እና እውቀታቸውን አፍሰዋል። ህዳሴ ግድብ ኢትዮጵያውያን ከዳር እስከ ዳር አሻራቸውን ያሳረፉበት የኢትዮጵያውያን የአንድነት ማሳያ ሀውልት ነው። ህዳሴ ግድብ የፖለቲካም ሆነ የአስተሳሰብ የልዩነት አጥሮችን ተሻግሮ መላ የሀገራችንን ህዝቦች አንድ ያደረገ ብሄራዊ ሀብት እና ኩራት ነው። ህዳሴ ግድብ በድህነት ለሚማቅቁ እልፍ ኢትዮጵያውያን ተስፋ፣ በጨለማ ለሚኖሩ ሚሊዮኖች ብርሀን ነው። ከአፍሪካ ግዙፍ የሆነው ህዳሴ ግድብ ሀገራችን በአፍሪካም ሆነ በዓለም ያላትን ጂኦ ፖለቲካዊ ቦታ ከፍ የሚያደርግ ወደር የሌለው ብሄራዊ አቅም ነው። ህዳሴ የኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን የመላው አፍሪካውያን ተስፋ እና ኩራት ነው።

ግድቡ የሚያመነጨው ከፍተኛ ኃይል ለሀገራችን ኢኮኖሚ ማንሰራራት ትልቅ አቅም ይፈጥራል። ህዳሴ ግድቡ እና በግድቡ ላይ የተፈጠረው ትልቅ ሀይቅ ለበርካታ ኢትዮጵያውያን የስራ እድል በመፍጠር በርካቶች ከድህነት እንዲወጡ ያስችላል። ግድቡ ሀገራችን ከጎረቤቶቷ ጋር በኃይል አቅርቦት እና በምጣኔ ሀብት እንድትተሳሰር በማድረግ ከራሷ አልፎ ለጎረቤቶቿ ሰላም እና እድገት አወንታዊ አስተዋጾ እንደሚያበረክት ይጠበቃል።

ህዳሴ ግድብ ላለፉት በርካታ አስርት ዓመታት ኢትዮጵያን ያስተዳደሩ የሀገራችን መሪዎች፣ ዲፕሎማቶች፣ ኢትዮጵያውያን ማሀንዲሶች፣ የዓለም ዓቀፍ ህግ ባለሙያዎች፣ የሚዲያ እና የምጣኔ ሀብት ባለሟሎች፣ የመከላከያ እና ደህንነት አባላት እና አመራሮች በተለያየ ደረጃ አሻራቸውን ያስቀመጡበት እውነተኛ ብሄራዊ ቅርስ ነው። ሁሉም ላደረጉት አስተዋጾ እና ለከፈሉት መስዋአትነት ከፍተኛ ምስጋና ይገባቸዋል። ለግድቡ ግንባታ እውቀት እና ጉልበታቸውን ሳይሳሱ አበርክተው ፍጻሜውን ለማየት ላልታደሉ የሀገራችን የቁርጥ ቀን ልጆች ምስጋና እና ክብር ይድረሳቸው።

የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ አባላት እና አመራሮች በዚህ ታላቅ ሀገራዊ ፕሮጀክት መጠናቀቅ ታላቅ ደስታ እና ኩራት ተሰምቶናል። ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ይህ ታላቅ ግድብ ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ኢትዮጵያውያን ያሳየነውን አንድነት እና ትብብር የሀገራችንን ሰላም በማስፈን ልንደግመው ይገባል ሲል በዚህ ታሪካዊ አጋጣሚ መልእክቱን ያስተላልፋል።

በድጋሚ እንኳን ደስ አለን!!

ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ
ጳጉሜ 4፣ 2017
አዲስ አበባ
www.fepethiopia.com
Email: [email protected]
Tell: +251 113 81 00 80

08/09/2025
የፓርቲያችን 2ኛ መደበኛ ጉባኤ በምርጫ ቦርድ ጸደቀ!!፟*************************************************ሚያዝያ 26፣ 2017 በአድዋ ድል መታሰቢያ የተካሄደው የ...
18/08/2025

የፓርቲያችን 2ኛ መደበኛ ጉባኤ በምርጫ ቦርድ ጸደቀ!!
፟*************************************************
ሚያዝያ 26፣ 2017 በአድዋ ድል መታሰቢያ የተካሄደው የነእፓ 2ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ በኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ጸድቋል። ቦርዱ ሀምሌ 22፣ 2017 ባደረገው ስብሰባ፣ በቦርዱ ታዛቢዎች እና በነእፓ የቀረበውን የጉባኤ ሪፖርት ከአዋጁ አንጻር መርምሮ ማጽደቁን ለፓርቲው በጻፈው ደብዳቤ አስታውቋል።

የፖለቲካ ፓርቲዎች ህጋዊነታቸው ለማስቀጠል ቢያንስ በሶስት ዓመት አንድ ጊዜ ጉባኤ ማድረግ ግዴታ አለባቸው። ይህንኑ መሰረት በማድረግ ፓርቲያችን ሚያዝያ 26፣ 2017 2ኛ መደበኛ ጉባኤውን አድርጓል።

አንድ ጉባኤ የተሳካ እንዲሆን፣ አዋጁን፣ የቦርዱን የአሰራር ሂደት እንዲሁም የፓርቲውን መተዳደሪያ ደንብ እና መመሪያዎች ታሳቢ ባደረገ ሁኔታ በከፍተኛ ጥንቃቄ ማቀድ እና መፈጸም ይፈልጋል።

ጉባኤውን በተሳካ ሁኔታ ለማካሄድ የነእፓ በተለያየ ደረጃ የሚገኙ የነእፓ አደረጃጀቶች፣ አባላት እና አመራሮች ከፍተኛ አስተዋጾ አድርገዋል። ከፍተኛ ዝግጅት የተደረገበት ጉባኤ በቦርዱ እውቅና ማግኘቱ የስኬቱ ዋና ማሳያ ነው።

ጉባኤችን እንዲሳካ በተለያየ መንገድ አስተዋጾ ላደረጋችሁ የፓርቲያችን የብሄራዊ፣ የክልል፣ የዞን፣ የወረዳ/የከተማ አደረጃጀት አመራሮች፣ አባላት፣ ጉባኤው በተሳካ ሁኔታ እንዲካሄድ በገንዘብ፣ በጊዜ፣ በጉልበት አስተዋጾ ላደረጋችሁ የፓርቲያችን አባላት እና ደጋፊዎች ላደረጋችሁት አስተዋጾ በድጋሚ የላቀ ምስጋና እያቀረብን፣ 2ኛ መደበኛ ጉባኤችን በቦርዱ በመጽደቁ እንኳን ደስ ያላችሁ እንላለን።

ነእፓ 2ኛ መደበኛ ጉባኤ አዘጋጅ
አብይ ኮሚቴ

ነሀሴ 12፣ 2017
አዲስ አበባ

በየመን የባህር ዳርቻ ላይ በደረሰ አሰቃቂ የጀልባ መስጠም አደጋ "ከ68 በላይ ኢትዮጵያውያን ህይወት" ማለፉን ተከትሎ፣ የነፃነትና እኩልነት ፓርቲ ጥልቅ ሀዘን እንደተሰማው ገለፀ፣ዓለም አቀፉ...
06/08/2025

በየመን የባህር ዳርቻ ላይ በደረሰ አሰቃቂ የጀልባ መስጠም አደጋ "ከ68 በላይ ኢትዮጵያውያን ህይወት" ማለፉን ተከትሎ፣ የነፃነትና እኩልነት ፓርቲ ጥልቅ ሀዘን እንደተሰማው ገለፀ፣

ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (IOM) እንዳስታወቀው፣ 154 ኢትዮጵያውያንን የጫነች ጀልባ እሁድ ማለዳ ስትሰጥም፣ 68ቱ ህይወታቸው አልፏል፣ 74ቱ የውሃ ሲሳይ ሆነዋል፣ 12ቱ ብቻ ከሞት ተርፈዋል።

ይህ አሰቃቂ ክስተት፣ በሀገሪቱ አሁንም በርካታ ዜጎች በስደት በባህር ለስራ ፍለጋ ወደተለያዩ ሀገራት ዜጎች እንደሚሰደዱ የሚያሳይ ነው በመሆኑም መንግስት አሁንም ዜጎች በሀገራቸው የተረጋጋ ኑሮ እንዲኖሩ የሚያስችሉ ሁኔታዎችን መፍጠር እንዳለበት እናሳስባለን።

የነፃነትና እኩልነት ፓርቲ በደረሰው አደጋ የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ገልጾ፣ ለሟቾች ቤተሰቦች መጽናናትን ተመኝቷል።

መንግስት የደረሰውን አደጋ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን መፍትሄ እንዲያበጅ ጥሪውን ያስተላልፋል።

ዜጎች በህገ-ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች ሳይታለሉ በህጋዊ መንገድ ብቻ የውጭ ሀገር የሥራ ሥምሪት ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየገለፅን ለሟች ቤተሰቦች መፅናናትን እንመኛለን።

ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ!
✍✍ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት
ቴሌግራም ቻናላችን ☞☞☞
https://t.me/+_956ZXyo_ak4NTc8y
የአባልነት መመዝገቢያ ቅጽ (አማርኛ)
https://forms.gle/hxVzqzMDbuJmLBsC8

05/07/2025

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Mahamed Masebo, Shafi Jemal

25/06/2025

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Dki New, ያኡሚ ያባባ

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ጦራ ከተማ አሰተዳደር ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share