
18/08/2025
የፓርቲያችን 2ኛ መደበኛ ጉባኤ በምርጫ ቦርድ ጸደቀ!!
፟*************************************************
ሚያዝያ 26፣ 2017 በአድዋ ድል መታሰቢያ የተካሄደው የነእፓ 2ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ በኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ጸድቋል። ቦርዱ ሀምሌ 22፣ 2017 ባደረገው ስብሰባ፣ በቦርዱ ታዛቢዎች እና በነእፓ የቀረበውን የጉባኤ ሪፖርት ከአዋጁ አንጻር መርምሮ ማጽደቁን ለፓርቲው በጻፈው ደብዳቤ አስታውቋል።
የፖለቲካ ፓርቲዎች ህጋዊነታቸው ለማስቀጠል ቢያንስ በሶስት ዓመት አንድ ጊዜ ጉባኤ ማድረግ ግዴታ አለባቸው። ይህንኑ መሰረት በማድረግ ፓርቲያችን ሚያዝያ 26፣ 2017 2ኛ መደበኛ ጉባኤውን አድርጓል።
አንድ ጉባኤ የተሳካ እንዲሆን፣ አዋጁን፣ የቦርዱን የአሰራር ሂደት እንዲሁም የፓርቲውን መተዳደሪያ ደንብ እና መመሪያዎች ታሳቢ ባደረገ ሁኔታ በከፍተኛ ጥንቃቄ ማቀድ እና መፈጸም ይፈልጋል።
ጉባኤውን በተሳካ ሁኔታ ለማካሄድ የነእፓ በተለያየ ደረጃ የሚገኙ የነእፓ አደረጃጀቶች፣ አባላት እና አመራሮች ከፍተኛ አስተዋጾ አድርገዋል። ከፍተኛ ዝግጅት የተደረገበት ጉባኤ በቦርዱ እውቅና ማግኘቱ የስኬቱ ዋና ማሳያ ነው።
ጉባኤችን እንዲሳካ በተለያየ መንገድ አስተዋጾ ላደረጋችሁ የፓርቲያችን የብሄራዊ፣ የክልል፣ የዞን፣ የወረዳ/የከተማ አደረጃጀት አመራሮች፣ አባላት፣ ጉባኤው በተሳካ ሁኔታ እንዲካሄድ በገንዘብ፣ በጊዜ፣ በጉልበት አስተዋጾ ላደረጋችሁ የፓርቲያችን አባላት እና ደጋፊዎች ላደረጋችሁት አስተዋጾ በድጋሚ የላቀ ምስጋና እያቀረብን፣ 2ኛ መደበኛ ጉባኤችን በቦርዱ በመጽደቁ እንኳን ደስ ያላችሁ እንላለን።
ነእፓ 2ኛ መደበኛ ጉባኤ አዘጋጅ
አብይ ኮሚቴ
ነሀሴ 12፣ 2017
አዲስ አበባ