01/10/2025
ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ የስልጤ ዞን ቅርንጫፍ በሀገራችን እግር ኳስ ባለታሪክ የነበረው ወንድማችን ሳዳት ጀማል ህልፈት የተሰማውን እጅግ ጥልቅ ሀዘን ገለፀ
==================================
ወንድም ሳዳት ጀማል በኢትዮጵያ እግር ኳስ ባለታሪክ ነው። በተለይም ብሔራዊ ቡድናችንን በግብ ጠባቂነት; በሴቶች ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝነት እና በስልጤ ዞን የታዳጊዎች እግር ኳስ ፕሮጀክት (ሳዳትና ከማል የታዳጊዎች ፕሮጀክት) ከወንድም ከማል አህመድ ጋር በመተባበር መስርቶ ማሰልጠን ሀገሩን ያገለገለባቸው ጥቂት አብነቶች ናቸው። በተለያዩ ጥልፍልፍ የፖለቲካ ችግሮች ምክንያት በሁለት እግሩ ቆሞ መሄድ ባቃተው የኢትዮጵያ እግር ኳስ ታሪክ የነበሩትን ጥልፍልፍ ችግሮች ተቋቁመው አሻራቸውን ካሳረፉ ዜጎቻችን አንዱ በነበረው ወንድማችን ሞት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለፅን ለቤተሰቦቹ ለወዳጅ ዘመዶቹና ለመላው የሀገራችን ህዝብ ባጠቃላይ እንዲሁም ለእግር ኳስ ቤተሰቡ በተለይ መፅናናትን; ለወንድማችን ዘላለማዊ የሰላም ረፍትን (ጀነትን) እንመኛለን!!