ጦራ ከተማ አሰተዳደር ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • ጦራ ከተማ አሰተዳደር ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት

ጦራ ከተማ አሰተዳደር ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ከተፎካካሪነት ወደ መሪነት!!

የፓርቲያችን 2ኛ መደበኛ ጉባኤ በምርጫ ቦርድ ጸደቀ!!፟*************************************************ሚያዝያ 26፣ 2017 በአድዋ ድል መታሰቢያ የተካሄደው የ...
18/08/2025

የፓርቲያችን 2ኛ መደበኛ ጉባኤ በምርጫ ቦርድ ጸደቀ!!
፟*************************************************
ሚያዝያ 26፣ 2017 በአድዋ ድል መታሰቢያ የተካሄደው የነእፓ 2ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ በኢትዮጵያ ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ጸድቋል። ቦርዱ ሀምሌ 22፣ 2017 ባደረገው ስብሰባ፣ በቦርዱ ታዛቢዎች እና በነእፓ የቀረበውን የጉባኤ ሪፖርት ከአዋጁ አንጻር መርምሮ ማጽደቁን ለፓርቲው በጻፈው ደብዳቤ አስታውቋል።

የፖለቲካ ፓርቲዎች ህጋዊነታቸው ለማስቀጠል ቢያንስ በሶስት ዓመት አንድ ጊዜ ጉባኤ ማድረግ ግዴታ አለባቸው። ይህንኑ መሰረት በማድረግ ፓርቲያችን ሚያዝያ 26፣ 2017 2ኛ መደበኛ ጉባኤውን አድርጓል።

አንድ ጉባኤ የተሳካ እንዲሆን፣ አዋጁን፣ የቦርዱን የአሰራር ሂደት እንዲሁም የፓርቲውን መተዳደሪያ ደንብ እና መመሪያዎች ታሳቢ ባደረገ ሁኔታ በከፍተኛ ጥንቃቄ ማቀድ እና መፈጸም ይፈልጋል።

ጉባኤውን በተሳካ ሁኔታ ለማካሄድ የነእፓ በተለያየ ደረጃ የሚገኙ የነእፓ አደረጃጀቶች፣ አባላት እና አመራሮች ከፍተኛ አስተዋጾ አድርገዋል። ከፍተኛ ዝግጅት የተደረገበት ጉባኤ በቦርዱ እውቅና ማግኘቱ የስኬቱ ዋና ማሳያ ነው።

ጉባኤችን እንዲሳካ በተለያየ መንገድ አስተዋጾ ላደረጋችሁ የፓርቲያችን የብሄራዊ፣ የክልል፣ የዞን፣ የወረዳ/የከተማ አደረጃጀት አመራሮች፣ አባላት፣ ጉባኤው በተሳካ ሁኔታ እንዲካሄድ በገንዘብ፣ በጊዜ፣ በጉልበት አስተዋጾ ላደረጋችሁ የፓርቲያችን አባላት እና ደጋፊዎች ላደረጋችሁት አስተዋጾ በድጋሚ የላቀ ምስጋና እያቀረብን፣ 2ኛ መደበኛ ጉባኤችን በቦርዱ በመጽደቁ እንኳን ደስ ያላችሁ እንላለን።

ነእፓ 2ኛ መደበኛ ጉባኤ አዘጋጅ
አብይ ኮሚቴ

ነሀሴ 12፣ 2017
አዲስ አበባ

በየመን የባህር ዳርቻ ላይ በደረሰ አሰቃቂ የጀልባ መስጠም አደጋ "ከ68 በላይ ኢትዮጵያውያን ህይወት" ማለፉን ተከትሎ፣ የነፃነትና እኩልነት ፓርቲ ጥልቅ ሀዘን እንደተሰማው ገለፀ፣ዓለም አቀፉ...
06/08/2025

በየመን የባህር ዳርቻ ላይ በደረሰ አሰቃቂ የጀልባ መስጠም አደጋ "ከ68 በላይ ኢትዮጵያውያን ህይወት" ማለፉን ተከትሎ፣ የነፃነትና እኩልነት ፓርቲ ጥልቅ ሀዘን እንደተሰማው ገለፀ፣

ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (IOM) እንዳስታወቀው፣ 154 ኢትዮጵያውያንን የጫነች ጀልባ እሁድ ማለዳ ስትሰጥም፣ 68ቱ ህይወታቸው አልፏል፣ 74ቱ የውሃ ሲሳይ ሆነዋል፣ 12ቱ ብቻ ከሞት ተርፈዋል።

ይህ አሰቃቂ ክስተት፣ በሀገሪቱ አሁንም በርካታ ዜጎች በስደት በባህር ለስራ ፍለጋ ወደተለያዩ ሀገራት ዜጎች እንደሚሰደዱ የሚያሳይ ነው በመሆኑም መንግስት አሁንም ዜጎች በሀገራቸው የተረጋጋ ኑሮ እንዲኖሩ የሚያስችሉ ሁኔታዎችን መፍጠር እንዳለበት እናሳስባለን።

የነፃነትና እኩልነት ፓርቲ በደረሰው አደጋ የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ገልጾ፣ ለሟቾች ቤተሰቦች መጽናናትን ተመኝቷል።

መንግስት የደረሰውን አደጋ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን መፍትሄ እንዲያበጅ ጥሪውን ያስተላልፋል።

ዜጎች በህገ-ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች ሳይታለሉ በህጋዊ መንገድ ብቻ የውጭ ሀገር የሥራ ሥምሪት ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየገለፅን ለሟች ቤተሰቦች መፅናናትን እንመኛለን።

ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ!
✍✍ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት
ቴሌግራም ቻናላችን ☞☞☞
https://t.me/+_956ZXyo_ak4NTc8y
የአባልነት መመዝገቢያ ቅጽ (አማርኛ)
https://forms.gle/hxVzqzMDbuJmLBsC8

05/07/2025

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Mahamed Masebo, Shafi Jemal

25/06/2025

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Dki New, ያኡሚ ያባባ

16/06/2025
ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) ለመላ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን መልካም ኢድ አል አድሀ (አረፋ) በዓል ይመኛል። በዓሉ የደስታ፣ የጤና እና የሰላም ይሁን። ኢድ ሙባረክ!! ነጻነትና እኩልነት ...
05/06/2025

ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) ለመላ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን መልካም ኢድ አል አድሀ (አረፋ) በዓል ይመኛል።
በዓሉ የደስታ፣ የጤና እና የሰላም ይሁን።
ኢድ ሙባረክ!!

ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ
ግንቦት፣ 2017

21/05/2025
18/05/2025

አድስም ሆነ ነባር የፓርቲያችን አባላት በሙሉ በonline የአባላት ምዝገባ መጀመራችን ቢቆይም አሁንም አባል ሆነው የፓርቲውን መታወቂያ ለመውሰድ ፍላጎት ከለዎት በ 0936101920 ደውለው የሚፈለግቦትን መረጃ አመልተው በማቅረብ እንድሞሉ በአክብሮት እንጠይቃለን።

የአንድ ፖለቲካ ድርጅት ቀጣይነት እና ጥንካሬ ምክንያት የሚሆነዉ ጥራት ያለው አባል በብዛት በማፍራት ረገድ ያለመታከት በመስራት መሆኑን ነእፓ ያምናል።

በመሆኑም ፓርቲያችንን ከህዝብ ጋር ይበልጥ ለማስተዋወቅና ሰፊ ቁጥር ያላቸውን አባላት ለማፊራት የመደበኛ ስራዎችን በተሟላ ሁኔታ ከመስራት ባሻገር በዘመቻ መልክ በአጭር ጊዜ ዉስጥ ብዙ አባላት ለማፍራት እየተደረጌ ያለው እንቅስቃሴ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የበኩላችሁን ኃላፍነት እንድትወጡ በአክብሮት እንጠይቃለን።

እናመሠግናለን!!

ጤናማ ሀገር ለመገንባት የጤና ባለሙያዎች መብት ይከበር!!*********************************************ለረዥም ጊዜ የመብት ጥያቄ ሲያነሱ የቆዩ የሀገራችን የጤና ባለ...
15/05/2025

ጤናማ ሀገር ለመገንባት የጤና ባለሙያዎች መብት ይከበር!!
*********************************************
ለረዥም ጊዜ የመብት ጥያቄ ሲያነሱ የቆዩ የሀገራችን የጤና ባለሙያዎች ባለፉት ጥቂት ሳምንታት ጥያቄዎቻቸው መልስ እንዲያገኙ በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች ድምጻቸውን በማሰማት ላይ ይገኛሉ። የጤና ባለሙያዎቹ ላነሷቸው መሰረታዊ የመብት ጥያቄዎች ምላሽ ባለማግኘታቸው ከግንቦት 5 ጀምሮ ከፊል የስራ ማቆም አድማ ማድረጋቸውን የገለጹ ሲሆን፣ የጤና ባለሙያዎቹ ላነሱት የመብት ጥያቄ መንግስት እስከ አሁን የሰጠው መልስ የለም።

የጤና አገልግሎት ከመሰረታዊ የሰው ልጅ ፍላጎቶች መካከል አንዱ ሲሆን፣ መንግስታት ለዜጎቻቸው ማቅረብ ከሚገባቸው አገልግሎቶች መካከል ዋነኛው ነው። ሀገራት ለዜጎቻቸው በቂ እና ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ለመስጠት ከፍተኛ ሀብት ይመድባሉ። መንግስታት ከዓመት በጀታቸው ውስጥ ለጤና ዘርፍ እስከ 15 በመቶ እንዲመድቡ ዓለም አቀፍ ተቋማት ይመክራሉ።

ይሁን እንጂ ሀገራችን ለጤናው ዘርፍ የሰጠችው ትኩረት እጅግ ዝቅተኛ ሲሆን፣ መንግስት ለዘርፉ የሚመድበው ከአራት በመቶ ያነሰ ዓመታዊ በጀት ለዚህ ጥሩ ማሳያ ነው። ለዘርፉ ተገቢው ሀብት ባለመመደቡ ምክንያት በቂ እና ጥራት ያላቸው የጤና ተቋማትን መገንባት፣ የመድሃኒት፣ የህክምና መሳሪያ እና ግብአቶችን ማቅረብ አልተቻለም። ዘርፉ ተገቢውን ትኩረት ባለማግኘቱ ምክንያት በከተማም ሆነ በገጠር ዜጎች ለከፋ የጤና ችግር ተጋልጠዋል።

ለሀገራችን የጤና ዘርፍ መውደቅ ምክንያት ከሆኑ ጉዳዮች መካከል ለጤና ባለሙያዎች የተሰጠው ዝቅተኛ ዋጋ እና ክብር ዋነኛው ነው። የጤና ባለሙያዎች ክቡር የሆነውን የሰው ልጅ ህይወት የመታደግ የሙያ እና የሞራል ኃላፊነት የተሸከሙ የአንድ ሀገር መድህን ናቸው። የጤና ባለሙያዎች የሌሎችን ጤና ለመጠበቅ ጤናቸውን ለአደጋ የሚያጋልጡ፣ የሌሎችን ህይወትን ለመታደግ ህይወታቸውን መስዋእት የሚያደርጉ የሀገር ባለውለታዎች ናቸው። ይሁን እንጂ ለሀገር እና ለዜጎች ከፍተኛ ውለታ የሚውሉ የጤና ባለሙያዎች ከሚሰጡት አገልግሎት አንጻር የሚከፈላቸው ክፍያ እና ጥቅማ ጥቅም እጅግ አነስተኛ ነው።

እንደ ሰው ለመኖር የሚያስችል በቂ ደመወዝ ይከፈለን ብለው ድምጻቸውን በማሰማት ላይ የሚገኙት የጤና ባለሙያዎች፣ ራሳቸውን እና ቤተሰቦቻቸውን በህይወት ለማቆየት የሚያስፈልጋቸውን መሰረታዊ አገልግሎቶችን ለማግኘት ተመጣጣኝ ክፍያ እንዲከፈላቸው በሰላማዊ እና በሰለጠነ መንገድ ጥያቄ በማቅረብ ላይ ይገኛሉ። ድምጻቸውን በማሰማት ላይ የሚገኙት የጤና ባለሙያዎች ራሳቸውን እና ቤተሰቦቻቸውን ለመመገብ፣ ቤት ተከራይቶ ለመኖር፣ ልጆቻቸውን ለማስተማር፣ የጤና መድህን ለማግኘት እንዳልቻሉ በምሬት እየገለጹ ነው። የጤና ባለሙያዎች ኢኮኖሚያዊ ችግር በሀገራችን እየከፋ በመጣው ከፍተኛ የኑሮ ውድነት ምክንያት ይበልጥ ተባብሷል።

ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ የጤና ባለሙያዎች ያነሷቸው ጥያቄዎች ተገቢ እና ወቅታዊ ናቸው ብሎ በጽኑ ያምናል። የጤና ባለሙያዎች ለሀገር እና ለህዝብ ለሚውሉት ከፍተኛ ውለታ ተመጣጣኝ ክፍያ፣ የራሳቸው እና የቤተሰቦቻቸውን መሰረታዊ ፍላጎቶች ማሟላት የሚችሉበት ወሮታ እና ጥቅማ ጥቅም ሊያገኙ ይገባል ብሎ ነእፓ ያምናል።

ይህንን ታሳቢ በማድረግ፣
1. መንግስት የጤና ባለሙያዎች ላነሷቸው የመብት ጥያቄዎች አፋጣኝ እና አወንታዊ ምላሽ እንዲሰጥ ነእፓ ያሳስባል፣

2. ዜጎች ሰብዓዊ እና ዴሞክራሲያዊ መብቶቻቸውን ለማስከበር ህጋዊ እና ሰላማዊ በሆነ መንገድ ተቃውሞ ማሰማት ህገ መንግስታዊ መብት ነው ብሎ ነእፓ ያምናል። በመሆኑም የጤና ባለሙያዎች በሰላማዊ እና በሰለጠነ መንገድ እያቀረቡ ያለውን የመብት ጥያቄ ከመመለስ ይልቅ፣ የፖለቲካ ጥያቄ አስመስሎ ለማቅረብ የሚደረጉ ሙከራዎች፣ ማስፈራራት፣ ማሸማቀቅ እና እስር በአፋጣኝ እንዲቆም ነእፓ ያሳስባል፣

3. የጤና ባለሙያዎች ባለፉት ቀናት ከፊል የስራ ማቆም አድማ በማድረግ ላይ እንደሚገኙ እና ለጥያቄዎቻቸው እስከ ግንቦት 9 መልስ ካላገኙ ከፍ ያለ እርምጃ ሊወስዱ እንደሚችሉ እየገለጹ ይገኛሉ። በመሆኑም በሀገራችን የጤና ዘርፍ ላይ የከፋ ችግር ከመፈጠሩ አስቀድሞ የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ለችግሩ ዘላቂ መፍትሄ ለማበጀት ከጤና ባለሙያዎቹ ጋር እንዲነጋገር ነእፓ ጥሪውን ያቀርባል፣

4. የሀገራችን የጤና ባለሙያዎች መብታቸውን ለማስከበር በማድረግ ላይ ባሉት እንቅስቃሴ፣ አስቸኳይ የህክምና አገልግሎት የሚሹ ወገኞች ጉዳት እንዳይደርስባቸው እስከ አሁን በማድረግ ላይ ላሉት እንክብካቤ ነእፓ አድናቆቱን እየገለጸ፣ ይህ ኃላፊነት የተሞላበት ተግባር በቀጣይ በሚያደርጉት የመብት ማስከበር ሂደት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ነእፓ በአክብሮት ይጠይቃል፣

5. የሀገራችን የጤና ዘርፍ ያሉበትን ውስብስብ የመሰረተ ልማት፣ የግብዓት፣ የሰው ኃይል፣ የአስተዳደር፣ የፍትሀዊነት እና ተደራሽነት ወዘተ ችግሮችን ለመቅረፍ ሁለንተናዊ የፖሊሲ ማሻሻያ እንዲደረግ ነእፓ ጥሪውን ያቀርባል፣

6. ለሀገር እና ለህዝብ ከፍተኛ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙ የጤና ባለሙያዎች፣ መምህራን እንዲሁም የመንግስት እና የግሉ ዘርፍ ሰራተኞች፣ መብቶቻቸውን ለማስከበር የሚያደርጉትን ህጋዊ እና ሰላማዊ ትግል ሁሌም የሚደግፍ እና ለመብቶቻቸው መከበር ከጎናቸው የሚቆም መሆኑን ነእፓ ያረጋግጣል።

ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ
ግንቦት 7፣ 2017

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ጦራ ከተማ አሰተዳደር ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share