ጦራ ከተማ አሰተዳደር ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት

  • Home
  • Ethiopia
  • Addis Ababa
  • ጦራ ከተማ አሰተዳደር ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት

ጦራ ከተማ አሰተዳደር ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት ከተፎካካሪነት ወደ መሪነት!!

በየመን የባህር ዳርቻ ላይ በደረሰ አሰቃቂ የጀልባ መስጠም አደጋ "ከ68 በላይ ኢትዮጵያውያን ህይወት" ማለፉን ተከትሎ፣ የነፃነትና እኩልነት ፓርቲ ጥልቅ ሀዘን እንደተሰማው ገለፀ፣ዓለም አቀፉ...
06/08/2025

በየመን የባህር ዳርቻ ላይ በደረሰ አሰቃቂ የጀልባ መስጠም አደጋ "ከ68 በላይ ኢትዮጵያውያን ህይወት" ማለፉን ተከትሎ፣ የነፃነትና እኩልነት ፓርቲ ጥልቅ ሀዘን እንደተሰማው ገለፀ፣

ዓለም አቀፉ የስደተኞች ድርጅት (IOM) እንዳስታወቀው፣ 154 ኢትዮጵያውያንን የጫነች ጀልባ እሁድ ማለዳ ስትሰጥም፣ 68ቱ ህይወታቸው አልፏል፣ 74ቱ የውሃ ሲሳይ ሆነዋል፣ 12ቱ ብቻ ከሞት ተርፈዋል።

ይህ አሰቃቂ ክስተት፣ በሀገሪቱ አሁንም በርካታ ዜጎች በስደት በባህር ለስራ ፍለጋ ወደተለያዩ ሀገራት ዜጎች እንደሚሰደዱ የሚያሳይ ነው በመሆኑም መንግስት አሁንም ዜጎች በሀገራቸው የተረጋጋ ኑሮ እንዲኖሩ የሚያስችሉ ሁኔታዎችን መፍጠር እንዳለበት እናሳስባለን።

የነፃነትና እኩልነት ፓርቲ በደረሰው አደጋ የተሰማውን ጥልቅ ሐዘን ገልጾ፣ ለሟቾች ቤተሰቦች መጽናናትን ተመኝቷል።

መንግስት የደረሰውን አደጋ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን መፍትሄ እንዲያበጅ ጥሪውን ያስተላልፋል።

ዜጎች በህገ-ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች ሳይታለሉ በህጋዊ መንገድ ብቻ የውጭ ሀገር የሥራ ሥምሪት ተጠቃሚ እንዲሆኑ እየገለፅን ለሟች ቤተሰቦች መፅናናትን እንመኛለን።

ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ!
✍✍ ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት
ቴሌግራም ቻናላችን ☞☞☞
https://t.me/+_956ZXyo_ak4NTc8y
የአባልነት መመዝገቢያ ቅጽ (አማርኛ)
https://forms.gle/hxVzqzMDbuJmLBsC8

05/07/2025

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Mahamed Masebo, Shafi Jemal

25/06/2025

Shout out to my newest followers! Excited to have you onboard! Dki New, ያኡሚ ያባባ

16/06/2025
ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) ለመላ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን መልካም ኢድ አል አድሀ (አረፋ) በዓል ይመኛል። በዓሉ የደስታ፣ የጤና እና የሰላም ይሁን። ኢድ ሙባረክ!! ነጻነትና እኩልነት ...
05/06/2025

ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) ለመላ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን መልካም ኢድ አል አድሀ (አረፋ) በዓል ይመኛል።
በዓሉ የደስታ፣ የጤና እና የሰላም ይሁን።
ኢድ ሙባረክ!!

ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ
ግንቦት፣ 2017

21/05/2025
18/05/2025

አድስም ሆነ ነባር የፓርቲያችን አባላት በሙሉ በonline የአባላት ምዝገባ መጀመራችን ቢቆይም አሁንም አባል ሆነው የፓርቲውን መታወቂያ ለመውሰድ ፍላጎት ከለዎት በ 0936101920 ደውለው የሚፈለግቦትን መረጃ አመልተው በማቅረብ እንድሞሉ በአክብሮት እንጠይቃለን።

የአንድ ፖለቲካ ድርጅት ቀጣይነት እና ጥንካሬ ምክንያት የሚሆነዉ ጥራት ያለው አባል በብዛት በማፍራት ረገድ ያለመታከት በመስራት መሆኑን ነእፓ ያምናል።

በመሆኑም ፓርቲያችንን ከህዝብ ጋር ይበልጥ ለማስተዋወቅና ሰፊ ቁጥር ያላቸውን አባላት ለማፊራት የመደበኛ ስራዎችን በተሟላ ሁኔታ ከመስራት ባሻገር በዘመቻ መልክ በአጭር ጊዜ ዉስጥ ብዙ አባላት ለማፍራት እየተደረጌ ያለው እንቅስቃሴ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የበኩላችሁን ኃላፍነት እንድትወጡ በአክብሮት እንጠይቃለን።

እናመሠግናለን!!

ጤናማ ሀገር ለመገንባት የጤና ባለሙያዎች መብት ይከበር!!*********************************************ለረዥም ጊዜ የመብት ጥያቄ ሲያነሱ የቆዩ የሀገራችን የጤና ባለ...
15/05/2025

ጤናማ ሀገር ለመገንባት የጤና ባለሙያዎች መብት ይከበር!!
*********************************************
ለረዥም ጊዜ የመብት ጥያቄ ሲያነሱ የቆዩ የሀገራችን የጤና ባለሙያዎች ባለፉት ጥቂት ሳምንታት ጥያቄዎቻቸው መልስ እንዲያገኙ በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች ድምጻቸውን በማሰማት ላይ ይገኛሉ። የጤና ባለሙያዎቹ ላነሷቸው መሰረታዊ የመብት ጥያቄዎች ምላሽ ባለማግኘታቸው ከግንቦት 5 ጀምሮ ከፊል የስራ ማቆም አድማ ማድረጋቸውን የገለጹ ሲሆን፣ የጤና ባለሙያዎቹ ላነሱት የመብት ጥያቄ መንግስት እስከ አሁን የሰጠው መልስ የለም።

የጤና አገልግሎት ከመሰረታዊ የሰው ልጅ ፍላጎቶች መካከል አንዱ ሲሆን፣ መንግስታት ለዜጎቻቸው ማቅረብ ከሚገባቸው አገልግሎቶች መካከል ዋነኛው ነው። ሀገራት ለዜጎቻቸው በቂ እና ጥራት ያለው የጤና አገልግሎት ለመስጠት ከፍተኛ ሀብት ይመድባሉ። መንግስታት ከዓመት በጀታቸው ውስጥ ለጤና ዘርፍ እስከ 15 በመቶ እንዲመድቡ ዓለም አቀፍ ተቋማት ይመክራሉ።

ይሁን እንጂ ሀገራችን ለጤናው ዘርፍ የሰጠችው ትኩረት እጅግ ዝቅተኛ ሲሆን፣ መንግስት ለዘርፉ የሚመድበው ከአራት በመቶ ያነሰ ዓመታዊ በጀት ለዚህ ጥሩ ማሳያ ነው። ለዘርፉ ተገቢው ሀብት ባለመመደቡ ምክንያት በቂ እና ጥራት ያላቸው የጤና ተቋማትን መገንባት፣ የመድሃኒት፣ የህክምና መሳሪያ እና ግብአቶችን ማቅረብ አልተቻለም። ዘርፉ ተገቢውን ትኩረት ባለማግኘቱ ምክንያት በከተማም ሆነ በገጠር ዜጎች ለከፋ የጤና ችግር ተጋልጠዋል።

ለሀገራችን የጤና ዘርፍ መውደቅ ምክንያት ከሆኑ ጉዳዮች መካከል ለጤና ባለሙያዎች የተሰጠው ዝቅተኛ ዋጋ እና ክብር ዋነኛው ነው። የጤና ባለሙያዎች ክቡር የሆነውን የሰው ልጅ ህይወት የመታደግ የሙያ እና የሞራል ኃላፊነት የተሸከሙ የአንድ ሀገር መድህን ናቸው። የጤና ባለሙያዎች የሌሎችን ጤና ለመጠበቅ ጤናቸውን ለአደጋ የሚያጋልጡ፣ የሌሎችን ህይወትን ለመታደግ ህይወታቸውን መስዋእት የሚያደርጉ የሀገር ባለውለታዎች ናቸው። ይሁን እንጂ ለሀገር እና ለዜጎች ከፍተኛ ውለታ የሚውሉ የጤና ባለሙያዎች ከሚሰጡት አገልግሎት አንጻር የሚከፈላቸው ክፍያ እና ጥቅማ ጥቅም እጅግ አነስተኛ ነው።

እንደ ሰው ለመኖር የሚያስችል በቂ ደመወዝ ይከፈለን ብለው ድምጻቸውን በማሰማት ላይ የሚገኙት የጤና ባለሙያዎች፣ ራሳቸውን እና ቤተሰቦቻቸውን በህይወት ለማቆየት የሚያስፈልጋቸውን መሰረታዊ አገልግሎቶችን ለማግኘት ተመጣጣኝ ክፍያ እንዲከፈላቸው በሰላማዊ እና በሰለጠነ መንገድ ጥያቄ በማቅረብ ላይ ይገኛሉ። ድምጻቸውን በማሰማት ላይ የሚገኙት የጤና ባለሙያዎች ራሳቸውን እና ቤተሰቦቻቸውን ለመመገብ፣ ቤት ተከራይቶ ለመኖር፣ ልጆቻቸውን ለማስተማር፣ የጤና መድህን ለማግኘት እንዳልቻሉ በምሬት እየገለጹ ነው። የጤና ባለሙያዎች ኢኮኖሚያዊ ችግር በሀገራችን እየከፋ በመጣው ከፍተኛ የኑሮ ውድነት ምክንያት ይበልጥ ተባብሷል።

ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ የጤና ባለሙያዎች ያነሷቸው ጥያቄዎች ተገቢ እና ወቅታዊ ናቸው ብሎ በጽኑ ያምናል። የጤና ባለሙያዎች ለሀገር እና ለህዝብ ለሚውሉት ከፍተኛ ውለታ ተመጣጣኝ ክፍያ፣ የራሳቸው እና የቤተሰቦቻቸውን መሰረታዊ ፍላጎቶች ማሟላት የሚችሉበት ወሮታ እና ጥቅማ ጥቅም ሊያገኙ ይገባል ብሎ ነእፓ ያምናል።

ይህንን ታሳቢ በማድረግ፣
1. መንግስት የጤና ባለሙያዎች ላነሷቸው የመብት ጥያቄዎች አፋጣኝ እና አወንታዊ ምላሽ እንዲሰጥ ነእፓ ያሳስባል፣

2. ዜጎች ሰብዓዊ እና ዴሞክራሲያዊ መብቶቻቸውን ለማስከበር ህጋዊ እና ሰላማዊ በሆነ መንገድ ተቃውሞ ማሰማት ህገ መንግስታዊ መብት ነው ብሎ ነእፓ ያምናል። በመሆኑም የጤና ባለሙያዎች በሰላማዊ እና በሰለጠነ መንገድ እያቀረቡ ያለውን የመብት ጥያቄ ከመመለስ ይልቅ፣ የፖለቲካ ጥያቄ አስመስሎ ለማቅረብ የሚደረጉ ሙከራዎች፣ ማስፈራራት፣ ማሸማቀቅ እና እስር በአፋጣኝ እንዲቆም ነእፓ ያሳስባል፣

3. የጤና ባለሙያዎች ባለፉት ቀናት ከፊል የስራ ማቆም አድማ በማድረግ ላይ እንደሚገኙ እና ለጥያቄዎቻቸው እስከ ግንቦት 9 መልስ ካላገኙ ከፍ ያለ እርምጃ ሊወስዱ እንደሚችሉ እየገለጹ ይገኛሉ። በመሆኑም በሀገራችን የጤና ዘርፍ ላይ የከፋ ችግር ከመፈጠሩ አስቀድሞ የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ለችግሩ ዘላቂ መፍትሄ ለማበጀት ከጤና ባለሙያዎቹ ጋር እንዲነጋገር ነእፓ ጥሪውን ያቀርባል፣

4. የሀገራችን የጤና ባለሙያዎች መብታቸውን ለማስከበር በማድረግ ላይ ባሉት እንቅስቃሴ፣ አስቸኳይ የህክምና አገልግሎት የሚሹ ወገኞች ጉዳት እንዳይደርስባቸው እስከ አሁን በማድረግ ላይ ላሉት እንክብካቤ ነእፓ አድናቆቱን እየገለጸ፣ ይህ ኃላፊነት የተሞላበት ተግባር በቀጣይ በሚያደርጉት የመብት ማስከበር ሂደት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ነእፓ በአክብሮት ይጠይቃል፣

5. የሀገራችን የጤና ዘርፍ ያሉበትን ውስብስብ የመሰረተ ልማት፣ የግብዓት፣ የሰው ኃይል፣ የአስተዳደር፣ የፍትሀዊነት እና ተደራሽነት ወዘተ ችግሮችን ለመቅረፍ ሁለንተናዊ የፖሊሲ ማሻሻያ እንዲደረግ ነእፓ ጥሪውን ያቀርባል፣

6. ለሀገር እና ለህዝብ ከፍተኛ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙ የጤና ባለሙያዎች፣ መምህራን እንዲሁም የመንግስት እና የግሉ ዘርፍ ሰራተኞች፣ መብቶቻቸውን ለማስከበር የሚያደርጉትን ህጋዊ እና ሰላማዊ ትግል ሁሌም የሚደግፍ እና ለመብቶቻቸው መከበር ከጎናቸው የሚቆም መሆኑን ነእፓ ያረጋግጣል።

ነጻነትና እኩልነት ፓርቲ
ግንቦት 7፣ 2017

የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የሀሳብ የበላይነትን በማስፈን ሁሉን አቀፍ የመድብለ ፓርቲ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ኢንዲጎለብት አስተዋፆው የጎላ ነው" ሚያዝያ 30/17 ጦራ ኮሙዩኒኬሽን በስ...
08/05/2025

የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት የሀሳብ የበላይነትን በማስፈን ሁሉን አቀፍ የመድብለ ፓርቲ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት ኢንዲጎለብት አስተዋፆው የጎላ ነው"

ሚያዝያ 30/17 ጦራ ኮሙዩኒኬሽን

በስልጤ ዞን የላንፍሮ ምርጫ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ የምክር ቤት ውይይት እና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናና የጋራ በምክርቤቱ የአመራር ምርጫ አካሄዷል።

በመተዳደሪያ ደንቦችና በሌሎች አጃንዳዎች የተዘጋጀ የስልጠና ሰነድ የስልጤ ዞን የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ የምክር ቤት አባልና ኤዜማ ፓርቲ የላንፍሮ ምርጫ ክልል ተወካይ በአቶ ንጉሴ ፍቃዱ ቀርቦ ሰፊ ውይይት ተካሂዶበታል።

የጋራ ምክር ቤቱን የውይይት መድረኩ ያስጀመሩት የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ የምክር ቤት የሥራ አስፈፃሚ ኮሜቴ አባል የሁኑት አቶ ፈድሉ ጅዋር የላንፍሮ ምርጫ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ የምክር ቤት ስብሰባ አቶ በይሬ ኮረምጣና ኤዜማ ፓርቲ የላንፍሮ ምርጫ ክልል ተወካይ በአቶ ንጉሴ ፍቃዱ ምክር ቤቱ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎች በሀገራዊ ጉዳዮች ላይ በጋራ የሚወያዩበትና ችግሮችን የሚፈቱበት አግባብ በመፍጠር ረገድ አይነተኛ ሚና ይኖረዋል በለዋል

በሀገሪቱ የተለያዩ የፖለቲካ ምህዳር ውስጥ ሰላማዊ የፖለቲካ ሂደቶችን ማስተዋወቅ በተለይም በምርጫ ወቅት ልዩነቶችን በመፍታት እና ሰላማዊ ተሳትፎን ለማሳደግ እንደሚያግዝም ነው ያመላከቱት።

ለሰላማዊ ውሳኔዎች ቅድሚያ በመስጠት የፖለቲካ አለመግባባቶችን ለመፍታት ውይይት እና ሰላማዊ መፍትሄዎችን ለማስፋፋት ጥረት ይደረጋልም ተብለዋል ..።

ምክር ቤቱ የህዝቡን ጥቅም በሚያረጋግጡ ጉዳዮች ላይ በጋራ ይሰራል ምክር ቤቱ በአጀንዳዎች ላይ መግባባትን በመፍጠር እና ሊከሰቱ የሚችሉ አለመግባባቶችን በማጥበብ ፤ አሳታፊነት ፣ግልፀኝነት፣ ፍትሃዊነት ፣ዴሞክራሲን ማጠናከር፣ ትብብርን እና ውይይትን በማበረታታት የበለጠ ጠንካራ እና ሁሉን አቀፍ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት እንዲጎለብት የበኩሉን አስተዋፅኦ ያደርጋል።

የላንፍሮ ምርጫ ክልል የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት በተካሄደው ጉባኤ ላይ የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ ተወካይ አቶ ፈድሉ ኤርጊቾ የምክር ቤቱ ዋና ሰብሳቢ አድርጎ ሾሟል።

በተጨማሪም ምክር ቤቱ ላንፍሮ ወረዳ አስተዳደር ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ በይሬ ኮርማጣ ምክትል ሰብሳቢ እንዲሁም የኢዜማ ተወካ የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ(ኢዜማ) ተወካይ አቶ ሁሴን እዶ ፀሃፊ አድርጎ ሹሟል።

Address

Addis Ababa

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ጦራ ከተማ አሰተዳደር ነፃነትና እኩልነት ፓርቲ ቅርንጫፍ ፅ/ቤት posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share