
09/06/2025
ቦታው ቤተ ክርስቲያን ነው
ዝናብ እየዘነበ ነው
ወይ ሚስቱ ወይ እኅቱ ወይም ቅርብ ጓደኛው ነች ዝናብ ጸጉሯን እንዳያገኛት እርሱን ዝናብ እየመታው ወንበር እንደ ጃንጥላ ተሸክሞላት ቆሟል
ምናልባት አንዳንድ ሰዎች ቦታው ላይ ሆነን ስናይ አይ ወንድ ልጅ ሲያፈቅር ምናምን ብለን በተጣመመ መልኩ ልናየው እንችል ይሆናል ሴት ልጅን ሊጎዱ ከሚችሉ ነገሮች እንዴት ማዳን እንዳለብን እንዴትና በምን አይነት ዘዴ ልንከባከባትና ክብር ልንሰጣት እንደሚገባን የሚያሳይ ነው
እርገጠኛ ነኝ እንዴት ወንበር ተሸክሞ አያስጠልለኝም የሚል ሐሳብ አእምሮዋ ውስጥ አይመጣም ነበር ለምን ወንበር አልዘረጋልኝም የሚል ወቀሳም አትሰነዝርበትም ነበር ግን እርሷን ለማዳን ካለው ጽኑ ፍላጎት የተነሣ ይህ ሐሳብ ብልጭ አለለትና ለእርሷ ካለው ጥንቃቄ የተነሣ አጠገቡ ያለውን ነገር እርሷን ለማዳን ተጠቀመበት
እንዲያው እርሷን ሆነን ስናስበው ደግሞ ማንም ሊያስበው የማይችለውን ይሄንን ተግባር እርሷ ብቻ ተጠልላበት ስታይ ምን ያህል በቅን ሐሳቡ ትደመም ይሆን?
እኔ እራሱ በወንበር ስር መጠለል መኖሩን ያወኩት ገና ከዚህ ሰው ነው😍
ለሰዎች እንክብካቤ ማድረግ ያለብን ሰዎች በሚጠብቁትና በሚያስቡት ወይም በተለመደ ነገር ብቻ አይተንና ባናደርግላቸው ይታዘቡናል ብለን ሳይሆን ለእነርሱ ማድረግ በምንችለው አቅማችን ሁሉ መሆን አለበት
ለሰዎች የምናደርገው እንክብካቤ ቅን ሐሳባችንን የሚጠይቅ እንጂ የግድ ብዙ ወጭና ውድ ማቴሪያል በማዘጋጀት አይደለም
#ማርያም #መዝሙር #መስቀል