አምባዬ EOTC MEDIA

አምባዬ EOTC MEDIA የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ በጸሎት ያግዙን። የአምባዬ ቲዩብ የዩቱዩብ ቻናል SUBSCRIBE እያደረጋችሁ ትምህርቶችን እና መዝሙሮችን እንዲደርሶት

ቦታው ቤተ ክርስቲያን ነው ዝናብ እየዘነበ ነውወይ ሚስቱ ወይ እኅቱ ወይም ቅርብ ጓደኛው ነች ዝናብ ጸጉሯን እንዳያገኛት እርሱን ዝናብ እየመታው ወንበር እንደ ጃንጥላ ተሸክሞላት ቆሟልምናልባት...
09/06/2025

ቦታው ቤተ ክርስቲያን ነው
ዝናብ እየዘነበ ነው
ወይ ሚስቱ ወይ እኅቱ ወይም ቅርብ ጓደኛው ነች ዝናብ ጸጉሯን እንዳያገኛት እርሱን ዝናብ እየመታው ወንበር እንደ ጃንጥላ ተሸክሞላት ቆሟል
ምናልባት አንዳንድ ሰዎች ቦታው ላይ ሆነን ስናይ አይ ወንድ ልጅ ሲያፈቅር ምናምን ብለን በተጣመመ መልኩ ልናየው እንችል ይሆናል ሴት ልጅን ሊጎዱ ከሚችሉ ነገሮች እንዴት ማዳን እንዳለብን እንዴትና በምን አይነት ዘዴ ልንከባከባትና ክብር ልንሰጣት እንደሚገባን የሚያሳይ ነው

እርገጠኛ ነኝ እንዴት ወንበር ተሸክሞ አያስጠልለኝም የሚል ሐሳብ አእምሮዋ ውስጥ አይመጣም ነበር ለምን ወንበር አልዘረጋልኝም የሚል ወቀሳም አትሰነዝርበትም ነበር ግን እርሷን ለማዳን ካለው ጽኑ ፍላጎት የተነሣ ይህ ሐሳብ ብልጭ አለለትና ለእርሷ ካለው ጥንቃቄ የተነሣ አጠገቡ ያለውን ነገር እርሷን ለማዳን ተጠቀመበት
እንዲያው እርሷን ሆነን ስናስበው ደግሞ ማንም ሊያስበው የማይችለውን ይሄንን ተግባር እርሷ ብቻ ተጠልላበት ስታይ ምን ያህል በቅን ሐሳቡ ትደመም ይሆን?
እኔ እራሱ በወንበር ስር መጠለል መኖሩን ያወኩት ገና ከዚህ ሰው ነው😍

ለሰዎች እንክብካቤ ማድረግ ያለብን ሰዎች በሚጠብቁትና በሚያስቡት ወይም በተለመደ ነገር ብቻ አይተንና ባናደርግላቸው ይታዘቡናል ብለን ሳይሆን ለእነርሱ ማድረግ በምንችለው አቅማችን ሁሉ መሆን አለበት
ለሰዎች የምናደርገው እንክብካቤ ቅን ሐሳባችንን የሚጠይቅ እንጂ የግድ ብዙ ወጭና ውድ ማቴሪያል በማዘጋጀት አይደለም

#ማርያም #መዝሙር #መስቀል

29/05/2025
 #እናመሰግናለን🙏 የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት በርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የግንቦት 19 ቀን 2017 ዓ.ም የመጨረሻ  የጉባኤ ውሎ አስመልክቶ የብፁዓን አባቶች አስተምሮ በተመለከ...
28/05/2025

#እናመሰግናለን🙏

የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት በርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የግንቦት 19 ቀን 2017 ዓ.ም የመጨረሻ የጉባኤ ውሎ
አስመልክቶ የብፁዓን አባቶች አስተምሮ በተመለከተ ቋሚ ሲኖዶስ ውሳኔ መሠረት የሊቃውንት ጉባኤ በሦስት ብፁዓን አባቶች ማለትም በብፁዕ አቡነ ፊልጶስ ሊቀ ጳጳስ ; በብፁዕ አቡነ በርናባስ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ሊቀ ጳጳስ በተላለፉ ትምህርቶች ላይ ያቀረበውን የስህተት ትምህርት የሚያሳይ አስተያየት እና የውሳኔ ሐሳብ ቀርቧል። ምልዓተ ጉባኤውም የሦስቱን አባቶች አስተያየት አዳምጦ የሚከተለውን ውሳኔ አሳልፏል ።
በሦስቱ ብፁዓን አባቶች ማለትም በብፁዕ አቡነ ፊልጶስ ሊቀ ጳጳስ ; በብፁዕ አቡነ በርናባስ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ጳጳስ ጥፋታቸውን አምነው በቅዱስ ሲኖዶስ ፊት ቀርበው ይቅርታ በመጠየቅ ;በሊቃውንት ጉባኤ የቀረበው እውነተኛ የቅድስት ቤተክርስቲያን አስተምህሮ የሚያምኑ እና የሚያስተምሩ መሆኑን በመግለጽ ለተፈጠረው ስህተት ይቅርታ ጠይቀዋል።
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ይቅርታቸውን በመቀበል ያስተላለፉትን የስህተት ትምህርት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት ( ) ቀርበው በቅዱስ ሲኖዶስ ፊት የሰጡትን የእምነት ክህደት ቃል አስተምህሯቸውን አርመውና አስተካክለው እንዲያስተላልፉ መመሪያ ሰጥቷል።
ወደፊትም ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትና መምህራን የሃይማኖት ትምህርት ሳይሸራረፍ ለትውልድ ለማስተላለፍ ጥንቃቄ እንዲያደርጉና በአከራካሪ ጉዳዮች በግለሰብ ደረጃ ምላሽ እንዳይሰጥ ጉባዔው ወስኗል ።

ዘገባው የ 👉 📡 የመገናኛ ብዙኃን ሥርጭት አገልግሎት ድርጅት 🎥 ነው

ዲያቆን ታደሰ ወርቁ ታሰሩ ‼️በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በስብከት አገልግሎቱ፣በተለያዩ ስልጠናዎች ላይ ስልጠና በመስጠት፣በተለይም ተሃድሶውያንን በመዋጋት የምናውቀው ዲያቆን ...
18/05/2025

ዲያቆን ታደሰ ወርቁ ታሰሩ ‼️

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በስብከት አገልግሎቱ፣በተለያዩ ስልጠናዎች ላይ ስልጠና በመስጠት፣በተለይም ተሃድሶውያንን በመዋጋት የምናውቀው ዲያቆን ታደሰ ወርቁ ዛሬ በፀጥታ ኃይሎች መወሰዱ ተሰማ።

እንደሚታወቀው የቅዱስ ሶኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በሚካሄድበት ወቅት በተለይም የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የጠቅላይቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ በሚመረጥበት ግዜ ሁሉ ለቤተክርስቲያን ይታገላሉ የሚባሉ ወንድሞች እና እህቶች ይታሰራሉ፡፡ ዛሬም ዲያቆን ታደሰ ወርቁ ታስሯል።

የቅዱስ ሲኖዶስን ጸሐፊ እና የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅን መምረጥ የመንፈስ ቅዱስ እና የብፁዓን አባቶች ድርሻ ነው፡፡ በዚህ ወቅት የሚታሰር አንዳችም ሰው መኖር የለበትም ።ወንድማችንን እንድትፈቱት እንጠይቃለን ።

Address

Addis Ababa
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when አምባዬ EOTC MEDIA posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share