Koolu Times

Koolu Times Odeeffannoo haqaaf gurra uummataa

02/01/2026

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 75ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን በማስመልከት የጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ(ዶ/ር)ጉብኝት:-

ከግንዛቤ ጉድለት የመነጭ የስም ማጥፋት ዘመቻ - ስለ "አሻራ የጋራ መኖሪያ መንደር" እውነታው ምንድን ነው?ሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያ "አዳነች አበቤ ንግድ ባንክን ሿሿ ሰራችው" በሚል ርዕስ ...
25/12/2025

ከግንዛቤ ጉድለት የመነጭ የስም ማጥፋት ዘመቻ - ስለ "አሻራ የጋራ መኖሪያ መንደር" እውነታው ምንድን ነው?

ሰሞኑን በማህበራዊ ሚዲያ "አዳነች አበቤ ንግድ ባንክን ሿሿ ሰራችው" በሚል ርዕስ የሚዘዋወረው ጽሁፍ የቤቶች ግንባታን እና የሪል ስቴት አሰራርን ካለመረዳት የመነጨ ፍጹም የተሳሳተ መረጃ ነው። ትችቱ እውቀት ላይ ያልተመሰረተና የሰዎችን ስም ለማጥፋት ታስቦ የተዘጋጀ በመሆኑ፣ እውነታውን ለህዝብ ግልጽ ማድረግ አስፈላጊ ሆኗል።

1. የ "Gross Area" እና "Net Area" ልዩነት (ያልተረዳችሁት ትልቁ ነጥብ): በማንኛውም የጋራ መኖሪያ ህንፃ (Apartment) ግንባታ ላይ Gross Area (ጠቅላላ ስፋት) እና Net Area (የውስጥ ስፋት) የሚባሉ መለኪያዎች አሉ።

👉 Net Area: በአራቱ ግድግዳዎች ውስጥ ያለውን የመኖሪያ ክፍል ስፋት ብቻ የሚለካ ነው።

👉 Gross Area: የግል ክፍሉን ስፋት ጨምሮ፣ የጋራ መጠቀሚያዎችን (ኮሪደር፣ ደረጃ፣ ሊፍት፣ እና የግድግዳ ውፍረት) በየቤቱ ድርሻ ተከፋፍሎ የሚታከልበት ነው።

2. ካርታ የሚሰራው በ Gross Area ነው! የከተማ አስተዳደሩም ሆነ የትኛውም ሪል ስቴት ካርታ የሚያዘጋጀው በ Gross Area ነው። የንግድ ባንክ ሰራተኞችም ሆኑ ባንኩ ክፍያ የፈጸሙት የጋራ መጠቀሚያዎችን (Common areas) ጨምሮ ለያዙት ጠቅላላ ይዞታ ነው። መሬት ላይ ያለው ሴራሚክ ብቻ ተቆጥሮ "ካሬው ጎደለ" ማለት፣ ስለ ህንፃ ግንባታ እና የባለቤትነት ህግ ምንም አለማወቅ ነው። "52 ካሬው በ76 ካሬ ተጻፈ" የሚለው ቅሬታ፣ ያ 24 ካሬ ልዩነት የቤቱ ድርሻ የሆነው የጋራ መተላለፊያ እና የህንፃው አካል መሆኑን ካለመረዳት የመነጨ ነው።

3. "ሿሿ" ወይስ ህጋዊ አሰራር? የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ግዙፍ እና በባለሙያዎች የተሞላ ተቋም ነው። እንዲህ ያለውን ትልቅ ግዥ ሲፈጽም በኢንጂነሮች እና በህግ ባለሙያዎች ጥናት አድርጎ እንጂ በግርግር አይደለም። ከተማ አስተዳደሩም የህንፃ ስታንዳርድን ጠብቆ ያስረከበ እንጂ ማጭበርበር አልፈጸመም።

4. የስም ማጥፋት ወንጀልና ኃላፊነት፡ እውነታውን ሳያጣሩ፣ ተቋማትን እና ግለሰቦችን በሌሉበት "አጭበረበሩ" ብሎ መክሰስ ህጋዊ ተጠያቂነት የሚያስከትል የስም ማጥፋት ወንጀል ነው። የፖለቲካ ትችት ማቅረብ መብት ቢሆንም፣ የቴክኒክ እውቀትን መሰረት ያላደረገ የሀሰት ወሬ ማሰራጨት ግን ህዝብን ማሳሳት እና ተቋማትን ማዳከም ነው።

ማጠቃለያ፡ መሬት ላይ ያረፈ የግል ቪላ ቤት እና የጋራ መኖሪያ ህንፃ (Apartment) የካሬ አሰላልፋቸው የተለያየ መሆኑን ይገንዘቡ። ካላወቁ መጠየቅ እንጂ በለየለት ስህተት ተቋማትን መወንጀል አይገባም።

ስምምነቱ ለሰላም እንጂ ለዳግም ጦርነት አልነበረም!የፕሪቶሪያው ስምምነት የትግራይን ሕዝብ ከጦርነት እሳት ለመታደግ የተፈረመ ታሪካዊ ሰነድ ነው። ሆኖም "የክልሉን ህዝብ አስተዳድራለሁ" የሚለ...
23/12/2025

ስምምነቱ ለሰላም እንጂ ለዳግም ጦርነት አልነበረም!

የፕሪቶሪያው ስምምነት የትግራይን ሕዝብ ከጦርነት እሳት ለመታደግ የተፈረመ ታሪካዊ ሰነድ ነው።

ሆኖም "የክልሉን ህዝብ አስተዳድራለሁ" የሚለው አካል መሣሪያ በመቅበር፣ ስምምነቱን በመጣስና ዳግም ወታደራዊ ቅስቀሳ በማድረግ ሕዝቡን ለሌላ እልቂት እየጋበዘው ይገኛል።

የፕሪቶሪያ ስምምነት የጦርነት ማቆሚያ እንጂ የዳግም ዝግጅት መደበቂያ አይደለም!

መሣሪያ ከቀበረበት ማውጣትና ለጦርነት መቀስቀስ በሕዝቡ የሰላም ጥማት መነገድ እና ቁማር መጫወት ነው።

የትግራይ ሕዝብ ሰላም እንጂ ተጨማሪ ጥይት አያስፈልገውም።

20/12/2025

አይ ፋኖ🤣🤣🤣🤣

15/12/2025
ጧሪና ደጋፊ ለሌላቸው አቅመ ደካሞች፣ ለአካል ጉዳተኞች እና አገርን ለረጅም ጊዜ ላገለገሉ ባለውለታዎች የሕይወት ብርሃን ፈንጥቋል። ለብዙ ዘመን በችግር ውስጥ የነበሩ ቤተሰቦች ከአስቸጋሪ ሁኔ...
14/12/2025

ጧሪና ደጋፊ ለሌላቸው አቅመ ደካሞች፣ ለአካል ጉዳተኞች እና አገርን ለረጅም ጊዜ ላገለገሉ ባለውለታዎች የሕይወት ብርሃን ፈንጥቋል። ለብዙ ዘመን በችግር ውስጥ የነበሩ ቤተሰቦች ከአስቸጋሪ ሁኔታ ወጥተው የዘላቂ መኖሪያ ቤት ባለቤቶች ሲሆኑ ማየት ታላቅ ደስታ ነው።

በጎነት ለመለመች!

በዚህ ዕጣ አወጣጥ ሥነ-ሥርዓት ላይ በሃሴት የፈነደቁ እናቶች፣ አባቶችና ወጣቶችን ስናይ አይናችን በእምባ ተሞላ። ይህ እንባ የንጹህ ደስታ እና አመስጋኝነት እንባ ነው። የአስተዳደሩ አመራሮች ለእነዚህ የህብረተሰብ ክፍሎች የሰጡት ትኩረት እና የተሳካው ርምጃ ለሌሎች አካላት ሁሉ ምሳሌና አርአያ የሚሆን ነው።

እነዚህ አቅመ ደካማና አገር ባለውለታ ዜጎች የመጠለያ ዕድል ማግኘታቸው የከተማ አስተዳደሩ ኃላፊነት የተሞላበት እና ሕዝባዊነትን ያጎላ ተግባር ነው። ይህ ድርጊት በሕዝብና በአስተዳደር መካከል ያለውን ትስስር የሚያጠነክርና ኢትዮጵያ የምትፈልገው ሰብአዊ ልማት አካል ነው።

07/12/2025

ኢትዮጵያ ከተመፅዋችነት ተላቃ የአፍሪካ የስንዴ ምርት ቁንጮ ሆናለች ሲል አልሹሩቅ አል አረቢያ ዘግቧል:: የረሃብና የተመፅዋችነት ዘመን መሻገሯን የገለፀው ሚዲያው
ኢትዮጵያ ባለፈው አመት ለመጀመሪያ ጊዜ በታሪኳ በስንዴ ምርት እራሷን መቻሏን ገልጿል::

ኢትዮጵያ ለዘመናት ስሟ በረሃብ ሲጠራ ቢቆይ አሁን ይህ ታሪክ መቀየሩን አልሹሩቅ በሪፖርታዥ አቅርቧል::
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ቁጥር አንድ የስንዴ አምራች በመሆን ታሪክ መስራቷን ገልጿል::

የኢትዮጵያ መንግስት በተከተለው የግብርና ፖሊሲ ምክንያት የስንዴ ምርትን በእጥፍ በማሳደግ ሀገሪቱን ከተረጂነት ማላቀቁን ሚዲያው ዘግቧል::

የኢትዮጵያ የስንዴ ምርት ማደግ ሥስት ምክንያቶችን ገልጿል::

1-ከፍተኛ የመስኖ እርሻ መስፋት
2-ምርጥ ዘር እና ዘመናዊ ቴክኖሎጂ መጠቀም
3- አዲስ የግብርና ፖሊሲ መከተል መሆኑን ገልጿል::

ኢትዮጵያ 112 ሚሊየን ሄክታር መሬት ያላት መሆኑን: ከዚህ ውስጥ 38 ሚሊየን ሄክታር ለግብርና ምቹ መሆኑን ገልጿል:: ይህም በአመት በአንድ የግብርና ወቅት ብቻ 100 ሚሊየን ኩንታን ስንዴ ለማምረት እንደሚያስችል ገልጿል::
በ2023 የስንዴ ምርት ከ15 ሚሊየን ቶን ወደ 23 ሚሊየን ቶን በ2024 ማደጉን ገልጿል:: ኢትዮጵያ የአመት የስንዴ ፍጆታ 8 ሚሊየን ቶን ብቻ መሆኑን አልሹሩቅ ቢዝነስ በ4/12/2024 በአረብኛ ባወጣው ዘገባ ገልጿል::

ግንባታው በርካታ የሥራ ዕድሎችን እና የእውቀት ሽግግርን ፈጥሯል!ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ
22/11/2025

ግንባታው በርካታ የሥራ ዕድሎችን እና የእውቀት ሽግግርን ፈጥሯል!
ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ

21/10/2025

ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አቤቤ የለውጡ መንግስት ለኢትዮጵያ ህዝብ ያበረከታት የለውጡ ገፀ በረከት ናቸው።

21/10/2025

ወ/ሮ ዝናሽ ታያቸው በዘመናዊ የዓለም ፖለቲካ ታሪክ ውስጥ ተቀዳሚ የሚያደርጋቸውን ሁለተናዊ ለውጥ ማምጣት የቻሉ ቀዳማይት እመቤት ናቸው ።

Address

Addis Ababa
1000

Website

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Koolu Times posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Koolu Times:

Share