SHEGER FM 102.1 RADIO

SHEGER FM 102.1 RADIO SHEGER 102.1FM 'Yenanetew Radio' is the first private radio station in Ethiopia. We are proud to be Ethiopian and we love our country more than anything!
(4)

Hear us live on www.ShegerFM.com, dedicated phone numbers, and mobile Apps. ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬዲዮ መስከረም 23፣2000 ዓ.ም ሥራ የጀመረ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ የግል ኤፍ ኤም ሬዲዮ ጣቢያ ነው፡፡

ይህ ከአዲስ አበባ በ250 ኪሎ ሜትር ክበብ ውስጥ ፕሮግራም እንዲያሰራጭ ፈቃድ አግኝቶ የረጅም ጊዜ የሬዲዮ ሥራ ልምድ ባላቸው ባለሙያዎች የተቋቋመው ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬዲዮ በአጭር ጊዜ ውስጥ በአድማጮች ዘንድ ተወዳጅነትን ሊያተርፍ ችሏል፡፡

ሸገር 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡

፡ የሸገር ዓላማ ከወገናዊነት የነፃ ትክክለኛ የሕዝብ ድምፅ መሆን፣ ሥነ ምግባርን የጠበቀ የጋዜጠኝነት መርህን መከተልና የተሣካለት የኢንፎቴይመንት (Information & Entertainment) ሬዲዮ ጣቢያ መሆን ነው፡፡

ጣቢያችን ለማንም ባለመወገን ለሁሉም በታማኝነትና በመልካም ሥነ ምግባር መልካም አገልግሎት በመስጠት የሚያምንና ለእነዚህም እሴቶች ትልቅ ክብር የሚሰጥ ሬዲዮ ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው!
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!

ታህሳስ 3/2018 ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ የተከፈለ ካፒታሉ 5 ቢሊዮን ብር  እንደደረሰ ተናገረ፡፡ይህም  ትልቅ ስኬት ነው ብሏል፡፡በ2016 በጀት ዓመት የባንኩ የተከፈለ ካፒታል 2.4 ቢሊዮ...
12/12/2025

ታህሳስ 3/2018

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ የተከፈለ ካፒታሉ 5 ቢሊዮን ብር እንደደረሰ ተናገረ፡፡

ይህም ትልቅ ስኬት ነው ብሏል፡፡

በ2016 በጀት ዓመት የባንኩ የተከፈለ ካፒታል 2.4 ቢሊዮን ብር እንደነበር ያስታወሰው ባንኩ በአንድ ዓመት ውስጥ የ102 በመቶ አድገት በማምጣት 5 በሊዮን ብር አንደደረሰ ተናግሯል፡፡

ባንኮች ካፒታላቸውን 5 ቢሊዮን ብር እንዲያደርሱ ብሔራዊ ባንክ ያስቀመጠውን መስፈርት ያስታወሰው ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ ከጊዜ ገደቡ በፊት ማሳካት መቻሉ በባስለክሲዮኖቹ እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ዘንደ ያለውን ተቀባይነት ከጊዜ ወደ ጊዜ አያደገ መመጣቱን ያሳያል ብሏል፡፡

ይህ በመሳካቱ ባንኩ ከሎሎች ባንኮች ጋር መዋሃድ ሳይጠበቅበት እንዲቀጥል እንደሚያስችለው አና የመዋሃድም እቅድ አንደሌለው ተናግሯል፡፡

ይህ እንዲሳካም በተለይ ባለአክሲዮኞች ከፍተኛ አስተዋጾ ማድረጋቸው ተጠቅሷል፡፡

ግሎባል ባንክ ኢትዮጰየ በ2017 በጀት ዓመት ከ 5.56 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ማግኘቱን በአመታዊ ሪፖርቱ ተናግሯል፡፡

ይህም ባለፈው ዓመት ከተመዘገበው ጋር ሲነፃፀር የ37 በመቶ ጨማሪ ማሳየቱን ተጠቅሷል፡፡

የባንኩ ጠቅላላ ሃብት በበጀት ዓመቱ መጨረሻ 34.4 ቢሊዮን መድረሱ የተነገረ ሲሆን ይህም ከቀዳሚው ዓመት ጋር ሲነጻጸር የ 42 በመቶ እድገት አሳይቷል ተብሏል፡፡

ግሎባል ባንክ ኢትዮጵያ በ2017 በጀት ዓመት 7.53 ቢሊዮን ብር ተቀማጭ ገንዘብ መሰብሰቡን በሪፖርቱ ጠቅሷል፡፡

የባንኩን አጠቃላይ ተቀማጭ 25.75 ቢሊዮን ብር በላይ ደርሷል ተብሏል፡፡

ባንኩ በበጀት ዓመቱ ከታክስ፣ ከመጠባበቂያ እና ሌሎች ተቀናሾች በፊት ከ 1.17 ቢሊዮን ብር አትርፌያለሁ ይህም ከቀዳሚው አመት ጋር ሲመሳከር የ33 በመቶ ብልጫ አለው ብሏል፡፡

የቅርንጫፎቹ ብዛት 237፣ የደንበኞቹ ቁጥር ደግሞ 1.8 ሚሊዮን መድረሳቸወንም አስረድቷል፡፡

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://youtube.com/?si=MIGhci0wINMYwCmw
Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1
Facebook፡ https://web.facebook.com/Sheger102.1
WhatsApp : https://whatsapp.com/channel/0029VaAOnG9J3juypE0M4G1O
X : https://x.com/shegerfm?s=2

ከደምሴ ጽጌ ልበወለድ “ፍቅሯን በፍቅሬ” - በተፈሪ አለሙ  https://youtu.be/O4BL0NYx_Rc
12/12/2025

ከደምሴ ጽጌ ልበወለድ “ፍቅሯን በፍቅሬ” - በተፈሪ አለሙ

https://youtu.be/O4BL0NYx_Rc

SHEGER 102.1FM 'Yenanetew Radio' is the first private radio station in Ethiopia. We are proud to be Ethiopian and we love our country more than anything!Sheg...

ታህሳስ 3/2018 ከዚህ ቀደም ያልተለመዱ አዳዲስ በሴቶች እና ህፃናት ላይ እየደረሱ ላሉ ጥቃቶች፤ ጥፋተኞችን ተጠያቂ የሚያደርግ በቂ የህግ ማዕቀፍ የለም ተባለ፡፡የሴቶችን እና ማህበራዊ ጉዳ...
12/12/2025

ታህሳስ 3/2018

ከዚህ ቀደም ያልተለመዱ አዳዲስ በሴቶች እና ህፃናት ላይ እየደረሱ ላሉ ጥቃቶች፤ ጥፋተኞችን ተጠያቂ የሚያደርግ በቂ የህግ ማዕቀፍ የለም ተባለ፡፡

የሴቶችን እና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የህግ ክፍተት እንዳለ አምኖ ያሉትም ህጎች በአግባቡ ተፈፃሚ እየሆኑ አይደለም ይላል፡፡

እድሜያቸው ከ15 እስከ 49 ካሉ ሴቶች 24 በመቶው የአካላዊ ጥቃት ሰለባ ናቸው፡፡

ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ... https://url-shortener.me/31GS

ፋሲካ ሙሉወርቅ

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://youtube.com/?si=MIGhci0wINMYwCmw
Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1
Facebook፡ https://web.facebook.com/Sheger102.1
WhatsApp : https://whatsapp.com/channel/0029VaAOnG9J3juypE0M4G1O
X : https://x.com/shegerfm?s=2

12/12/2025

ታህሳስ 3/2018

የሀገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ሃይል ፍጆታ ካለፈው ሃምሌ ወር ወዲህ እያደገ መጥቷል ተባለ።

ኢትዮጵያ ከተለያዩ ምንጮች ከምታመርተው የኤሌክትሪክ ሃይል 90 በመቶው ለሀገር ውስጥ ፍጆታ የሚውል እንደሆነ ተጠቅሷል።

በዘንድሮው በጀት ዓመት የመጀመሪያዎቹ አራት ወራት ኢትዮጵያ ከውሃ እና ከነፋስ ከ15,300 ጊጋዋት ሰዓት በላይ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጨቷ ተነግሯል።

በየወሩ በአማካይ 3,800 ጊጋዋት ሰአት የኤሌክትሪክ ሃይል አመንጭታለች እንደማለት ነው።

ከመነጨው የኤሌክትሪክ ሃይል ከ90 በመቶ ያላነሰው ለሀገር ውስጥ ፍጆታ እንደዋለ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ነግረውናል።

የሀገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ሃይል ፍጆታ ከጊዜ ወደ እያደገ መጥቷል ያሉት ዳይሬክተሩ ከሃምሌ ህዳር የነበረው መረጃ ይህንኑ እንደሚያሳይ ጠቁመዋል።

በሀገር ውስጥ ያሉ የኤሌክትሪክ ሃይል ተጠቃሚዎች በቤት ውስጥ ካሉ ደንበኞች እስከ ትላልቅ ኢንዱስትሪዎች ያሉትን የሚያካትት እንደሆነ አቶ ሞገስ ተናግረዋል።

በአራት ወራቱ ለሀገር ተጠቃሚዎች በሽያጭ ከቀረበ የኤሌክትሪክ ሃይል ከ14 ቢሊየን ብር በላይ ገቢ መገኘቱንም አቶ ሞገስ ነግረውናል።

ወደ ኬንያ ፤ ታንዛንያ እና ጁቡቲ ከተላከ የኤሌክትሪክ ሃይል ደግሞ ከ 46 ሚሊየን የአሜሪካ ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷን ብለዋል።

ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ሃይል ከሚገዙ ሀገራት አንዷ ሡዳን መሆኗ ይታወቃል።

ባለፉት አራት ወራት ግን ለሀገሪቱ የኤሌክትሪክ ሃይል እንዳልቀረበ ነው የሰማነው።

የዚህ ምክንያቱ ደግሞ በሀገሪቱ ያለው ግጭት እንደሆነ ተነግሯል።

ግጭቱ በሀገሪቱ መሰረተ ልማቶች ላይ ጉዳት በማስከተሉ የኤሌከትሪክ ሃይል ማቅረብ አልተቻለም ተብሏል።

ንጋቱ ረጋሣ

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://youtube.com/?si=MIGhci0wINMYwCmw
Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1
Facebook፡ https://web.facebook.com/Sheger102.1
WhatsApp : https://whatsapp.com/channel/0029VaAOnG9J3juypE0M4G1O
X : https://x.com/shegerfm?s=2

   ደራሲ እና ገጣሚ ፀጋዬ ገብረ መድህን ከጻፈዉ “አፄ ሚኒሊክ” ከሚል ድራማ የተወሰደ አንድ ትዕይንት https://www.youtube.com/watch?v=qxQAjwKI5WU
12/12/2025

ደራሲ እና ገጣሚ ፀጋዬ ገብረ መድህን ከጻፈዉ “አፄ ሚኒሊክ” ከሚል ድራማ የተወሰደ አንድ ትዕይንት

https://www.youtube.com/watch?v=qxQAjwKI5WU

ደራሲ እና ገጣሚ ፀጋዬ ገብረ መድህን ከጻፈዉ “አፄ ሚኒሊክ” ከሚል ድራማ የተወሰደ አንድ ትዕይንት SHEGER 102.1FM 'Yenanetew Radio' is the first private radio statio...

ታህሳስ 3/2018 ባለፉት 4 ወራት በህገ-ወጥ መንገድ ወደ ኢትዮጵያ የሚገባ የኮንትሮባንድ እቃዎች ቁጥር መጨመሩን የገቢዎች ሚኒስቴር ተናገረ፡፡ የገቢዎች ሚኒስቴር ይሄን ያለው ዛሬ በሕዝብ ...
12/12/2025

ታህሳስ 3/2018

ባለፉት 4 ወራት በህገ-ወጥ መንገድ ወደ ኢትዮጵያ የሚገባ የኮንትሮባንድ እቃዎች ቁጥር መጨመሩን የገቢዎች ሚኒስቴር ተናገረ፡፡

የገቢዎች ሚኒስቴር ይሄን ያለው ዛሬ በሕዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ለፕላን በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የ4 ወር የስራ ክንው ሪፖርት ባቀረበበት ወቅት ነው፡፡

ሪፖርቱን ያቀረቡት የገቢዎች ሚኒስትር ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሴ ከገቢ ኮንትሮባንድ ከ8 ቢሊዮን ብር በላይ ፣ ከወጪ ኮንትሮባንድ ደግሞ 0.6 ቢሊየን ብር ማዳን መቻሉን ተናግረዋል፡፡

በድምሩ 8.7 ቢሊየን ብር የሚያወጣ የኮንሮባንድ እቃ መያዙን ተናግረዋል፡፡

የገቢ ኮንትሮባንድ በእጥፍ መጨመሩን የተናገሩት ሚኒስትሯ መድሃኒት፣ አልባሳት ጨርቃ ጨርቅ ፣ ኤሌክትሮኒክስ እና የማዕድን ውጤቶች ከፍተኛውን ድርሻ እንደሚይዝ አስረድተዋል፡፡

ባለፉት 4 ወራት 27 ኪሎ ግራም የሚመዝን ጥፍጥፍ ወርቅ መያዙንም ሚኒስትሯ አክለዋል፡፡

የወጪ ኮንትሮባንድ አብዛኛውን ድርሻ የሚይዘው የግብርና ምርት ነው የተባለ ሲሆን ባለፉት 4 ወራት ቅናሽ ማሳየቱ ተጠቁሟል፡፡

ሚኒስትር ዓይናለም በኮንትሮባንድ ሂደት ሲሳተፉ የተያዙ 353 ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው እየተጣራ እንደሚገኝ ለቋሚ ኮሚቴው አስረድተዋል፡፡

በሌላ በኩል ባለፉት 4 ወራት ሚኒስቴር መ/ቤቱ 482.5 ቢሊየን ብር ገቢ መሰብሰቡ ተናግሯል፡፡
ይህም የእቅዱ 106 በመቶ ነው ተብሏል፡፡

ባለፉት 4 ወራት 444.3 ቢሊየን ብር ለመሰብሰብ ታቅዶ እንደነበር ያስታወሱት ሚኒስትሯ 482.5 ቢሊየን ብር ገቢ ሰብስበናል ብለዋል፡፡

ያሬድ እንዳሻው

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://youtube.com/?si=MIGhci0wINMYwCmw
Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1
Facebook፡ https://web.facebook.com/Sheger102.1
WhatsApp : https://whatsapp.com/channel/0029VaAOnG9J3juypE0M4G1O
X : https://x.com/shegerfm?s=2

ታሀሳስ 3/ 2018 የቀትር ወሬዎች በቀጥታ ይከታተሉ
12/12/2025

ታሀሳስ 3/ 2018 የቀትር ወሬዎች በቀጥታ ይከታተሉ

ሸገር የቀትር ወሬዎች - ታህሳስ 3 2018

ታህሳስ 3/2018   በቀጥታ ይከታተሉ…..
12/12/2025

ታህሳስ 3/2018

በቀጥታ ይከታተሉ…..

ተጠባቂ የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎች እና ሌሎች መረጃዎች

11/12/2025

ኤልያስ መልካ

ሙሉውን ፕሮግራም ዩቱዩብ ላይ ያገኙታል👇👇👇

https://youtu.be/hsJqd3Chs0Y



  ኤልያስ መልካ
11/12/2025



ኤልያስ መልካ

ታህሳስ 1/2018 ኤሌያስ መልካአዘጋጅ ወንድሙ ሀይሉSHEGER 102.1FM 'Yenanetew Radio' is the first private radio station in Ethiopia. We are proud to be Ethiopian and...

ታህሳስ 2/2018 በአዲስ አበባ የኮተቤ አካባቢ የተገነባውን መንገድ ጨምሮ አንዳንድ ቦታዎች በመንገዱ ንድፍ ወይም ዲዛይን ምክንያት አደጋ ሲደጋገምባቸው ይታያል፡፡የመንገዱ ዲዛይን ለ  #አደ...
11/12/2025

ታህሳስ 2/2018

በአዲስ አበባ የኮተቤ አካባቢ የተገነባውን መንገድ ጨምሮ አንዳንድ ቦታዎች በመንገዱ ንድፍ ወይም ዲዛይን ምክንያት አደጋ ሲደጋገምባቸው ይታያል፡፡

የመንገዱ ዲዛይን ለ #አደጋ መደጋገም ምክንያት መሆኑ ከታወቀ ለምን ማስተካከያ አይደረገረበትም የሚል ጥያቄም ይነሳል፡፡

እኛም ጥያቄውን ጉዳዩ ለሚያገባቸው መ/ቤቶች አቅርበናል፡፡

ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…. https://youtu.be/7IPXhgSq8Js

ምህረት ስዩም

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…

Website፡ https://www.shegerfm.com/
YouTube : https://youtube.com/?si=MIGhci0wINMYwCmw
Telegram : https://t.me/ShegerFMRadio102_1
Facebook፡ https://web.facebook.com/Sheger102.1
WhatsApp : https://whatsapp.com/channel/0029VaAOnG9J3juypE0M4G1O
X : https://x.com/shegerfm?s=2

Address

Addis Ababa Bahirdar Road
Addis Ababa

Opening Hours

Monday 08:00 - 00:00
Tuesday 08:00 - 00:00
Wednesday 08:00 - 00:00
Thursday 08:00 - 00:00
Friday 08:00 - 00:00
Saturday 08:00 - 01:00
Sunday 08:00 - 00:00

Telephone

+251111272754

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when SHEGER FM 102.1 RADIO posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to SHEGER FM 102.1 RADIO:

Share

Category