SHEGER FM 102.1 RADIO

SHEGER FM 102.1 RADIO SHEGER 102.1FM 'Yenanetew Radio' is the first private radio station in Ethiopia. We are proud to be Ethiopian and we love our country more than anything!
(4)

Hear us live on www.ShegerFM.com, dedicated phone numbers, and mobile Apps. ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬዲዮ መስከረም 23፣2000 ዓ.ም ሥራ የጀመረ የመጀመሪያው የኢትዮጵያ የግል ኤፍ ኤም ሬዲዮ ጣቢያ ነው፡፡

ይህ ከአዲስ አበባ በ250 ኪሎ ሜትር ክበብ ውስጥ ፕሮግራም እንዲያሰራጭ ፈቃድ አግኝቶ የረጅም ጊዜ የሬዲዮ ሥራ ልምድ ባላቸው ባለሙያዎች የተቋቋመው ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬዲዮ በአጭር ጊዜ ውስጥ በአድማጮች ዘንድ ተወዳጅነትን ሊያተርፍ ችሏል፡፡

ሸገር 102.1 አዲስ የሬዲዮ አቀራረብ መላና አዲስ ቃና ይዞ የቀረበ በሀገሪቱ የሚዲያ ገበያ ላይ መሪ ሚና የሚጫወት ጣቢያ ነው፡

፡ የሸገር ዓላማ ከወገናዊነት የነፃ ትክክለኛ የሕዝብ ድምፅ መሆን፣ ሥነ ምግባርን የጠበቀ የጋዜጠኝነት መርህን መከተልና የተሣካለት የኢንፎቴይመንት (Information & Entertainment) ሬዲዮ ጣቢያ መሆን ነው፡፡

ጣቢያችን ለማንም ባለመወገን ለሁሉም በታማኝነትና በመልካም ሥነ ምግባር መልካም አገልግሎት በመስጠት የሚያምንና ለእነዚህም እሴቶች ትልቅ ክብር የሚሰጥ ሬዲዮ ጣቢያ ነው፡፡

ሁሌም ከሸገር ጋር ሁኑ
ሸገር የእናንተ ነው!
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!

 #የጨዋታእንግዳ መዓዛ ብሩ ከልጅ ጃልዬ መንገሻ የልዑል ራስ መንገሻ ልጅ ጋር ያደረገችው ጨዋታ! ክፍል 2 - ጥቅምት 1 2018
11/10/2025

#የጨዋታእንግዳ

መዓዛ ብሩ ከልጅ ጃልዬ መንገሻ የልዑል ራስ መንገሻ ልጅ ጋር ያደረገችው ጨዋታ! ክፍል 2 - ጥቅምት 1 2018

shegerfm,sheger fm news,sheger maleda,sheger,sheger sport,shegernews,shegercaf...

 #የጨዋታእንግዳ መዓዛ ብሩ ከልጅ ጃልዬ መንገሻ የልዑል ራስ መንገሻ ልጅ ጋር ያደረገችው ጨዋታ! ክፍል 1 - ጥቅምት 1 2018
11/10/2025

#የጨዋታእንግዳ

መዓዛ ብሩ ከልጅ ጃልዬ መንገሻ የልዑል ራስ መንገሻ ልጅ ጋር ያደረገችው ጨዋታ! ክፍል 1 - ጥቅምት 1 2018

shegerfm,sheger fm news,sheger maleda,sheger,sheger sport,shegernews,shegercaf...

 #መቆያ   የሩሲያ ባለውለታ ስለሆኑት ሌተናል ጀነራል ሚኬል ክላሽንኮቭ - በእሸቴ አሰፋ ጥቅምት 1 2018
11/10/2025

#መቆያ

የሩሲያ ባለውለታ ስለሆኑት ሌተናል ጀነራል ሚኬል ክላሽንኮቭ - በእሸቴ አሰፋ ጥቅምት 1 2018

SHEGER 102.1FM 'Yenanetew Radio' is the first private radio station in Ethiopia. We are proud to be Ethiopian and we love our country more than anything!Sheg...

ጥቅምት 1 2018ለሁለት ወር በከፊል ዝግ ሆነዉ የቆዩት ፍርድ ቤቶች  ከሰኞ ጀምሮ ወደ መደበኛ የችሎት አገልግሎት  ይመለሳሉ ተባለ። መደበኛ የችሎት አገልግሎቱም በቴክኖሎጂ የታገዘ፣ ፈጣንና...
11/10/2025

ጥቅምት 1 2018

ለሁለት ወር በከፊል ዝግ ሆነዉ የቆዩት ፍርድ ቤቶች ከሰኞ ጀምሮ ወደ መደበኛ የችሎት አገልግሎት ይመለሳሉ ተባለ።

መደበኛ የችሎት አገልግሎቱም በቴክኖሎጂ የታገዘ፣ ፈጣንና ጥራት ያለዉ የዳኝነት ስራ የሚሰራበት እንዲሆን ዝግጅት ተደርጓል ተብሏል።

ይህ የተነገረው የ2018 ዓ/ም የመደበኛ የችሎት አገልግሎት ማስጀመሪያ ሥነ-ስርዓት ላይ ነዉ።

ነፃና ገለልተኛ የዳኝነት ስርዓትን ለማሳደግ፣ ተዓማኒነት ያለዉ የፍትህ ስርዓት ለመዘርጋት፣ በቴክኖሎጅ የተደገፈ አገልግሎት ከተጠያቂነት ጋር እውን ማድረግ አንደሚገባ ተጠቁሟል።

ፍርድ ቤቶች በየዓመቱ ከነሀሴ 1 እስከ መስከረም 30 ድረስ በከፊል ዝግ ሆነው ቆይተዉ ጥቅምት 1 መደበኛ ስራቸውን እንደሚጀምሩ ይታወቃል።

ዘንድሮም ለሁለት ወር በከፊል ዝግ ሆነዉ የቆዩት ፍርድ ቤቶች ሰኞ ጥቅምት 03/2018 ዓ.ም መደበኛ የችሎት አገልግሎት ይጀምራሉ ተብሏል።

በማስጀመሪያ ስነ-ስርዓቱ ላይ የተገኙት የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ ነፃና ገለልተኛ የዳኝነት ስርዓትን ለማሳደግ፣ ተዓማኒነት ያለው የፍትህ ስርዓት ለመዘርጋት፣ በቴክኖሎጂ የተደገፈ አግልግሎት ከተጠያቂነት ጋር እውን ማድረግ ይገባል ብለዋል።

ከፈጣሪ በታች ለዜጎች ፍትህን የማስፈን ስልጣንና ሀላፊነት የተሰጣቸው ለፍርድ ቤቶች ስለሆነ ዳኞች ለፈጣሪያቸውና ለህሊናቸው ታምነዉ የፍትህ ስራዓቱን በማሻሻል ተዓማኒነት ያለው የዳኝነት ስራ አንዲጎለብት መስራት እንዳለባቸው ተናግረዋል።

በተለይም ከሙስና የተላቀቁ፣ በግልጽነት፣ በታማኝነት፣ በፍጥነትና በጥራት ስራቸዉን ብቻ የሚከውኑ ተቋማትን ለመፍጠር መሰራት አለበት ብለዋል።

አፈ-ጉባኤው ታገሰ ጫፎ የዳኝነት አሰጣጥ ፍጥነትን መጨመር፣ የጥናትና ምርምር አቅምን ማሳደግ፣ የዳኝነት ብቃትን ከፍ ማድረግ፣ የዳኝነትን ነጻና ገለልተኛ መርህን ማረጋገጥ አንዲሁም ሙሉ በሙሉ በቴክኖሎጂ የታገዘ አሰራርን መዘርጋት እንደሚገባም አንስተዋል።

እነዚህ ተግባራት በ2018 ዓ/ም ትኩረት ተደርጎ ይሰራባቸዋል ብለዋል።

የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ-ቤት ፕሬዘዳንት ቴዎድሮስ ምህረት በበኩላቸዉ በ2017 የዳኝነትን ግልፅነትና ተጠያቂነት ለማረጋገጥ፣ የተገልጋዩን ፍላጎት ለማሟላትና ፍትህን ለማስፈን ብዙ ስራዎች አንደተሰሩ አብራርተዋል።

ዳኞች ነፃና ገለልተኛ ሆነው እንዲያገለግሉ የሚያግዙ የህግ ማዕቀፎችን በማፅደቅ ወደ ስራ እንዲገቡ አድርገናል ብለዋል።

ሰኞ በሚጀመረዉ የ2018 ዓ.ም መደበኛ የችሎት አገልግሎትም በቴክኖሎጂ በመታገዝ ፈጣንና ጥራት ያለው የዳኝነት ስራን ለመከወን በትኩረት አንደሚሰራ አቶ ቴዎድሮስ ተናግረዋል።

ገዛ ጌታሁን

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
👇👇👇

🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/
🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478
🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm
💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm3s
🐦X : https://x.com/shegerfm?s=21
👔LinkedIn ፡ https://tinyurl.com/tyfaekvx

ጥቅምት  1 2018  በፌዴራል መንግስትና በሕወሃት መካከል ያለው ልዩነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ ነው፡፡ይህ መካረር ወደ ዳግም ጦርነት እንዳይሸጋገር የሚለው ስጋትም የብዙዎች ነው፡፡መንግስት...
11/10/2025

ጥቅምት 1 2018

በፌዴራል መንግስትና በሕወሃት መካከል ያለው ልዩነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ ነው፡፡

ይህ መካረር ወደ ዳግም ጦርነት እንዳይሸጋገር የሚለው ስጋትም የብዙዎች ነው፡፡

መንግስት ይህ እንዳይሆን ብዙ እየጣረ መሆኑን በተደጋጋሚ ተናግሯል፡፡

በሽምግልናም በሌላም መንገድ ችግሩን ለማርገብ ብዙ ቢሞከርም ስጋቱ ግን እንዳለ ነው፡፡

ከዚህ በኋላስ ምን ቢደረግ ይበጃል?

https://youtu.be/n13hvkAAxzc

ያሬድ እንዳሻው

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
👇👇👇

🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/
🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478
🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm
💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm3s
🐦X : https://x.com/shegerfm?s=21
👔LinkedIn ፡ https://tinyurl.com/tyfaekvx

ጥቅምት  1 2018  ኢትዮጵያ በምትከተለው ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲ ምክንያት ባንኮች በሚሰጡት ብድር ላይ ገደብ ተጥሏል፡፡በቅርቡም ይኸው ከተቀማጭ ገንዘብ፣ 18 በመቶ ሆኖ የቆየው የብድር ጣሪ...
11/10/2025

ጥቅምት 1 2018

ኢትዮጵያ በምትከተለው ጥብቅ የገንዘብ ፖሊሲ ምክንያት ባንኮች በሚሰጡት ብድር ላይ ገደብ ተጥሏል፡፡

በቅርቡም ይኸው ከተቀማጭ ገንዘብ፣ 18 በመቶ ሆኖ የቆየው የብድር ጣሪያ፣ ወደ 24 በመቶ ከፍ ብሏል፡፡

በገበያው ግን የብድር ገደቡ ሙሉ ለሙሉ ይነሳል የሚል ግምት ነበር፡፡

በመንግስት በኩል ገደቡን ሙሉ ለሙሉ ከመልቀቅ ኢኮኖሚው ሳይረበሽ በሂደት እያላሉ መሄድ ምርጫ ተደርጓል፡፡

ይህ አካሄድ በገበያው ውስጥ ምን ተስፋና ስጋትን ይዞ ይመጣ ይሆን?

https://youtu.be/_UWEc9WhF_M

ተህቦ ንጉሴ

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
👇👇👇

🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/
🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478
🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm
💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm3s
🐦X : https://x.com/shegerfm?s=21
👔LinkedIn ፡ https://tinyurl.com/tyfaekvx

ጥቅምት  1 2018  የአዕምሮ ህመም መምጫ መንገድ ብዙ ነው፡፡የኑሮ ጫና፣ ድንገተኛ ሀዘን፣ ሱስ እና ሌላውም ለአዕምሮ ጤና እክል ምክንያት ተደርጎ ይጠቀሳል፡፡በኢትዮጵያ ከ5 ሰው አንዱ በሕ...
11/10/2025

ጥቅምት 1 2018

የአዕምሮ ህመም መምጫ መንገድ ብዙ ነው፡፡

የኑሮ ጫና፣ ድንገተኛ ሀዘን፣ ሱስ እና ሌላውም ለአዕምሮ ጤና እክል ምክንያት ተደርጎ ይጠቀሳል፡፡

በኢትዮጵያ ከ5 ሰው አንዱ በሕይወት ዘመኑ በዚህ የጤና ችግር ውስጥ እንደሚያልፉም ይነገራል፡፡

ግን ለችግሩ የሚሰጠው ትኩረት ዛሬም ያነሰ ነው፡፡

ለመሆኑ የአዕምሮ ጤናን ለመጠበቅ መደረግ ያለበት ጥንቃቄ ምንድን ነው?

ሌሎችንስ ለማገዝ ምን ማድረግ አለብን?

https://youtu.be/6hEG69ahZqg

ምህረት ስዩም

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
👇👇👇

🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/
🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478
🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm
💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm3s
🐦X : https://x.com/shegerfm?s=21
👔LinkedIn ፡ https://tinyurl.com/tyfaekvx

ጥቅምት  1 2018  ዘመን ባንክ በተጠናቀቀው 2017 በጀት ዓመት ያገኘው ትርፍ ከቀዳሚው ዓመት ጋር ሲነፃፀር ከእጥፍ በላይ መሆኑን ተናገረ። የአንድ አክሲዮን ትርፍ ወደ 68.3 በመቶ ማደ...
11/10/2025

ጥቅምት 1 2018

ዘመን ባንክ በተጠናቀቀው 2017 በጀት ዓመት ያገኘው ትርፍ ከቀዳሚው ዓመት ጋር ሲነፃፀር ከእጥፍ በላይ መሆኑን ተናገረ።

የአንድ አክሲዮን ትርፍ ወደ 68.3 በመቶ ማደጉንም አስረድቷል።

ዘመን ባንክ በ2017 በጀት ዓመት 14.4 ቢሊዮን ብር ገቢ ማግኘቱን በዛሬው እለት ዓመታዊ የባለአክሲዮኖች ጉባኤ ላይ ባወጣው ሪፖርት ተናግሯል።

የባንኩ የተጣራ ትርፉም 5.87 ቢሊዮን ብር ሲሆን ይህም ከ2016 በጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር በ145 በመቶ ጨምሯል ተብሏል፡፡

የባንኩ አጠቃላይ ሀብት በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት 88.6 ቢሊዮን ብር ደርሷል ይህም ካለፈው ዓመት በ49.7 በመቶ ጭማሪን ያሳየ መሆኑ በሪፖቱ ተጠቅሷል።

የባንኩ ጠቅላላ ካፒታል 13.2 ቢሊዮን ብር ፣ የተከፈለ ካፒታሉ ደግሞ 9.4 ቢሊዮን ብር መድረሱ ተሰምቷል።

የባንኩ የተበላሸ የብድር መጠን 2.81 በመቶ ብቻ ሲሆን ይህም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ካስቀመጠው የ5 በመቶ አኳያ ሲታይ ጤናማ መሆኑን ያሳያል ተብሏል።

በዘመን ባንክ በሂሳብ አመቱ የተንቀሳቀሰው የውጭ ምንዛሪ ፍስት 588 ሚሊዮን ዶላር ነው፣ ይህም ባንኩ የንግድ ልውውጥ እና ዓለም አቀፍ ንግድን በማመቻቸት ረገድ ቀዳሚ አጋር መሆኑን ያረጋገጠ መሆኑን ያሳል ተብሏል።

ከመተሰረተ 17 ዓመት የሆነው ዘመን ባንክ በአሁኑ ወቅት በመላ ሀገሪቱ 132 ቅርንጫፎች አሉኝ ብሏል፡፡

ዘመን ባንክ ማህበራዊ ሃላፊነቱን ለመወጣት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 61.86 ሚሊዮን ብር መስጠቱን በሪፖርቱ ጠቅሷል።

የዘመን ባንክ የዲሬክተሮች ቦርድ ሰብሳቢ ወ/ሮ እንዬ ቢምር ባንኩ ዛሬ ባደረገው ዓመታዊ ጉባኤ ላይ ባደረጉት ንግግር "ወደ ካፒታል ገበያ፤ ኢንቨስትመንት ባንኪንግ እና ሌሎች ስትራቴጂያዊ ተግባራት ለመግባት ወሳኝ መሠረት እየጣልን ነው"ብለዋል፡፡

የዘመን ባንክ ዋና ሥራ አስፈፃሚአቶ ደረጀ ዘበነ በበኩላቸው “ባንኩ ያመጣቸው ስኬቶች ጠንካራ የአስተዳደር፣ በደንበኞች ላይ ያተኮረ የንግድ ፍልስፍናና የሠራተኞቻችን ቁርጠኛነት ምስክሮች ናቸው" ሲሉ ስረድተዋል፡፡

ንጋቱ ሙሉ

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
👇👇👇

🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/
🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478
🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm
💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm3s
🐦X : https://x.com/shegerfm?s=21
👔LinkedIn ፡ https://tinyurl.com/tyfaekvx

ጥቅምት  1 2018  ዩኒቨርስቲዎች በጥራት ማስተማር ካልቻሉ ዩኒቨርሲቲ ሆነው መቀጠላቸው አጠያያቂ ሊሆን እንደሚችል ተነገረ፡፡ ከዚህ በኋላ የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች በሀገር ውስጥና በአለም ...
11/10/2025

ጥቅምት 1 2018

ዩኒቨርስቲዎች በጥራት ማስተማር ካልቻሉ ዩኒቨርሲቲ ሆነው መቀጠላቸው አጠያያቂ ሊሆን እንደሚችል ተነገረ፡፡

ከዚህ በኋላ የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች በሀገር ውስጥና በአለም አቀፍ መለኪያ እንዲመዘኑ ይደረጋል፡፡

ብሔርን መሸሸጊያ የማድረግ ዝንባሌአቸውም አይቀጥልም ተብሏል፡፡

ሙሉ ዘገባውን ያድምጡ…… https://www.mixcloud.com/ShegerFM/eges/

በረከት አካሉ

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
👇👇👇

🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/
🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478
🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm
💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm3s
🐦X : https://x.com/shegerfm?s=21
👔LinkedIn ፡ https://tinyurl.com/tyfaekvx

 #መቆያ  እሸቴ አሰፋ በመቆያ መሰናዶው፤ የሩሲያ ባለውለታ ስለሆኑት ሌተናል ጀነራል    ይነግረናል፡፡ 7፡30 በሸገር ይጠብቁን... ማፈንጠሪያውን በመጫን የተለያዩ የመቆያ መሰናዶችን ይመል...
11/10/2025

#መቆያ

እሸቴ አሰፋ በመቆያ መሰናዶው፤ የሩሲያ ባለውለታ ስለሆኑት ሌተናል ጀነራል ይነግረናል፡፡

7፡30 በሸገር ይጠብቁን...

ማፈንጠሪያውን በመጫን የተለያዩ የመቆያ መሰናዶችን ይመልከቱ 👇👇👇👇

https://n9.cl/mnt53

  የዛሬ ጥቅምት  1 ቀን 2018  የቅዳሜ ጨዋታ መሰናዶዎቻችንን ከወዲሁ እናስተዋውቃችሁ፡፡ ከቀኑ 7:00 ሲሆን የቅዳሜ ጨዋታችን፤ በሟሟሻ ይጀመራል፡፡ ሟሟሻን ተከትሎ እሸቴ አሰፋ በመቆያ ...
11/10/2025



የዛሬ ጥቅምት 1 ቀን 2018 የቅዳሜ ጨዋታ መሰናዶዎቻችንን ከወዲሁ እናስተዋውቃችሁ፡፡

ከቀኑ 7:00 ሲሆን የቅዳሜ ጨዋታችን፤ በሟሟሻ ይጀመራል፡፡

ሟሟሻን ተከትሎ እሸቴ አሰፋ በመቆያ መሰናዶው፤ የሩሲያ ባለውለታ ስለሆኑት ሌተናል ጀነራል እየነገረ ያቆየናል፡፡

በትዘታ ዘ አራዳ ዝግጅት፤ የ (ፕ/ር) ሃሳብን መነሻ በማድረግ ስለ ሰላምና እርቅ ተፈሪ አለሙ ያሰናዳውን ያቀርብልናል፡፡

በቅዳሜ ጨዋታ የእንግዳ ሰዓታችን፤ የባንክና ፋይናንስ ባለሞያው ከመዓዛ ብሩ ጋር የሚያደርጉት ቆይታ ከቀኑ 9:00 ሰዓት ሲል ይጀምራል፡፡

ድራማ እና ታይምለስ ክላሲክስ(Timeless Classics) በሰዓታቸው ይቀርባሉ፡፡

ሸገር 102.1 የእናንተው ሬድዮ!

የሸገርን ወሬዎች፣ መረጃ እና ፕሮግራሞች ይከታተሉ…
👇👇👇

🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/
🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478
🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm
💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm3s
🐦X : https://x.com/shegerfm?s=21
👔LinkedIn ፡ https://tinyurl.com/tyfaekvx

ከምርጫችሁ ጋር ስትገናኙ እዛው ቆዩ!⚡️ልዩ የሆኑ የሸገር 102.1 ኤፍ ኤም መሰናዶዎች እና ወሬዎች ያድምጡ🎧📲የማህበራዊ ሚዲያዎቻችንን በመቀላቀል ከሸገር ጋር ሁኑ!አሁኑኑ  ከዚህ በታች👇👇👇...
10/10/2025

ከምርጫችሁ ጋር ስትገናኙ እዛው ቆዩ!

⚡️ልዩ የሆኑ የሸገር 102.1 ኤፍ ኤም መሰናዶዎች እና ወሬዎች ያድምጡ🎧

📲የማህበራዊ ሚዲያዎቻችንን በመቀላቀል ከሸገር ጋር ሁኑ!
አሁኑኑ ከዚህ በታች👇👇👇👇 ያሉትን ማስፈንጠሪያ (ሊንክ) በመጠቀም ምርጫዎን ያግኙ!

🌐Website፡ https://www.shegerfm.com/
🎥YouTube https://tinyurl.com/37tux478
🟦Telegram https://t.me/ShegerFMRadio102_1
📘Facebook፡ https://tinyurl.com/4tx8t8wm
💬WhatsApp ፡ https://tinyurl.com/ycxjmm3s
🐦X : https://x.com/shegerfm?s=21
👔LinkedIn ፡ https://tinyurl.com/tyfaekvx

Address

Addis Ababa Bahirdar Road
Addis Ababa

Opening Hours

Monday 08:00 - 00:00
Tuesday 08:00 - 00:00
Wednesday 08:00 - 00:00
Thursday 08:00 - 00:00
Friday 08:00 - 00:00
Saturday 08:00 - 01:00
Sunday 08:00 - 00:00

Telephone

+251111272754

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when SHEGER FM 102.1 RADIO posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to SHEGER FM 102.1 RADIO:

Share

Category