ETHIO FM 107.8

ETHIO FM 107.8 በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ ሊተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብ የሚያስቀድም ኤፍኤም ሬዲዮ ጣቢያ
(157)

የባይደን የመሪነት ዘመን ሊጠቃለል በቀሩት 50 ቀናት ውስጥ የዩክሬንን የጦር መሳሪያ ክምችት ለማሳደግ ይሰራል ተባለ፡፡የዩናይትድ ስቴትስ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ ጄክ ሱሊቫን፤ የባይደን የ...
02/12/2024

የባይደን የመሪነት ዘመን ሊጠቃለል በቀሩት 50 ቀናት ውስጥ የዩክሬንን የጦር መሳሪያ ክምችት ለማሳደግ ይሰራል ተባለ፡፡

የዩናይትድ ስቴትስ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ ጄክ ሱሊቫን፤ የባይደን የመሪነት ዘመን ሊጠቃለል በቀረው የ50 ቀን እድሜ አሜሪካ የዩክሬንን የጦር መሳሪያ ክምችትን ለማሳደግ ትሰራለች ብለዋል።

በእነዚህ 50 ቀናት ውስጥ ዩክሬን በጦር ሜዳ አቋሟን ለማጠናከር የሚረዱ ሁሉንም መሳሪያዎች ለማቅረብ የምንችለውን ሁሉ እናደርጋለን ሲሉ ተናግረዋል፡፡

የሚደረገዉ የመሳሪያ ድጋፍ ዩክሬን በጦር ሜዳ ብቻ ሳይሆን በድርድር ጠረጴዛው ላይም የበለጠ ጠንካራ እንድትሆን ይረዳታል ብለዋል፡፡

አማካሪዉ አክለውም፤በፕሬዝዳንት ባይደን ከፍተኛ ወታደራዊ አቅርቦትን እንዲቆጣጠሩ ኃላፊነት እንደተሰጣቸዉም ተናግረዋል፡፡

ባይደን ስልጣናቸዉን እስኪያስረክቡ ድረስም ወደ ዩክሬን የሚደረጉ እያንዳንዱ የጦር መሳሪያና የገንዘብ ድጋፎች በኮንግረንሱ ፈቃድ ማግኘታቸዉንም አማካሪዉ ገልጸዋል፡፡

ልኡል ወልዴ

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ኀዳር 23 ቀን 2017 ዓ.ም

የነገ የህዳር 24 ቀን 2017 ዓ.ም የኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8  ፕሮግራሞቻችን
02/12/2024

የነገ የህዳር 24 ቀን 2017 ዓ.ም የኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ፕሮግራሞቻችን

አቶ ብናልፍ አንዱዓለም ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው ተሾሙ የቀድሞው የሰላም ሚኒስትር አቶ ብናልፍ አንዱዓለም ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው መሾማቸው ታውቋል።የፕሬዚዳንት ጽህፈት ቤት ...
02/12/2024

አቶ ብናልፍ አንዱዓለም ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው ተሾሙ

የቀድሞው የሰላም ሚኒስትር አቶ ብናልፍ አንዱዓለም ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ሆነው መሾማቸው ታውቋል።

የፕሬዚዳንት ጽህፈት ቤት አቶ ብናልፍ አንዱዓለም ከሕዳር 23 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳዳር ሆነው መሾማቸው ገልጿል ።

ይሁን እንጅ የት እንደመደቡ አልተገለፀም።

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ኀዳር 23 ቀን 2017 ዓ.ም

በአዲስ አበባ ከተማ ደንበኞች የባንክ አካውንት ለመክፈት “ፋይዳ” የዲጂታል መታወቂያ   በግዴታነት እንዲያቀርቡ ታዟል፡፡የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከቀጣዩ ወር ታህሳስ 23/2017 ዓ.ም. ጀም...
02/12/2024

በአዲስ አበባ ከተማ ደንበኞች የባንክ አካውንት ለመክፈት “ፋይዳ” የዲጂታል መታወቂያ በግዴታነት እንዲያቀርቡ ታዟል፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ከቀጣዩ ወር ታህሳስ 23/2017 ዓ.ም. ጀምሮ በአዲስ አበባ ከተማ ደንበኞች የባንክ አካውንት ለመክፈት “ፋይዳ” የተሰኘውን የዲጂታል መታወቂያ በግዴታነት እንዲያቀርቡ አዘዘ።

ከሁለት ዓመት በኋላ ደግሞ በመላ አገሪቱ የሚገኙ ደንበኞች የትኛውንም የባንክ አገልግሎት ለማግኘት የፋይዳ መታወቂያ እንዲይዙ መገደድ እንደሚጀምሩ ባንኩ አስታውቋል።

ብሔራዊ ባንክ፤ የ“ፋይዳ” ዲጂታል መታወቂያ ከሚቀጥለው ወር ጀምሮ በአስገዳጅነት ጥቅም ላይ እንዲውል ያዘዘው ባለፈው ሳምንት ማክሰኞ ሕዳር 17/2017 ዓ.ም. ለሁሉም ባንኮች በጻፈው ደብዳቤ ነው።

እያንዳንዱ ሰው የሚለይበት ባለ 12-አሃዝ ልዩ መለያ ቁጥር እንዲያገኝ የሚያስችለው የ“ፋይዳ” መታወቂያ፤ የነዋሪዎች የባዮሜትሪክ መረጃዎችን በመውሰድ ምዝገባ የሚደረግበት ስርዓት ነው።

የጣት አሻራ፣ አይን አይሪስ ስካን እና የፊት ምስል ነዋሪዎች መታወቂያውን ለማግኘት የሚያቀርቧቸው የባዮማትሪክ መረጃዎች ናቸው።

እስካሁን ድረስም ከ10 ሚሊዮን በላይ ደንበኞች ይህንን የዲጂታል መታወቂያ ለማግኘት እንደተመዘገቡ የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም መረጃ ያመለክታል።

ይህ አስገዳጅ አሰራር በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች ተግባራዊ መሆን የሚጀምረው በተለያየ ጊዜ እንደሆነም ባንኩ ገልጿል።

የብሔራዊ ባንክ ደብዳቤ እንደሚያስረዳው አዲሱ አሰራር ተግባራዊ መሆን የሚጀምረው በአዲስ አበባ ከተማ ነው።

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ኀዳር 23 ቀን 2017 ዓ.ም

ግብጽ ስለ ጋዛ የሰብዓዊ ድጋፍ ለመነጋገር የሚኒስትሮች ጉባዔ አዘጋጀች፡፡አንድ መቶ ሶስት አገራትን እና ተቋማትን የወከሉ ልዑካን በጉባዔዉን ተገኝተዋል፡፡በግብጽ ዋና ከተማ ካይሮ የተጀመረዉ ...
02/12/2024

ግብጽ ስለ ጋዛ የሰብዓዊ ድጋፍ ለመነጋገር የሚኒስትሮች ጉባዔ አዘጋጀች፡፡

አንድ መቶ ሶስት አገራትን እና ተቋማትን የወከሉ ልዑካን በጉባዔዉን ተገኝተዋል፡፡

በግብጽ ዋና ከተማ ካይሮ የተጀመረዉ ስብሰባ በጦርነት ለወደመችዉ ጋዛ የሰብዓዊ ድጋፍ ለማድረግ የተዘጋጀ መሆኑ ተገልጿል፡፡

ስብሰባዉ የተዘጋጀዉ በግብጹ ፕሬዝዳንት አብዱልፈታህ አልሲሲ ተወካዮች እና በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታዉ ምክር ቤት ምክትል ሃላፊ አሚና መሐመድ ነዉ፡፡

የዓለም ምግብ ፕሮግራም በጋዛ ያለዉ የረሐብ ቀዉስ እጅጉን እየከፋ መጥቷል ያለ ሲሆን፤ ከጦርነቱ በፊት የነበረዉ የመሰረታዊ ሸቀጦች ዋጋ አሁን ላይ ከ1ሺህ በመቶ በላይ መጨመሩን ነዉ የገለጸዉ፡፡

በጥቅምት 7 ጦርነቱ ከተጀመረ ጀምሮ ሴቶች እና ህጻናትን ጨምሮ በጋዛ 44ሺህ ንጹሃን ህይወታቸዉ አልፏል፡፡ ከ1መቶ ሺህ በላይ የሚሆኑት ደግሞ ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡

እስራኤል እርዳታዎች እንዳይደርሱ በማድረግ የጋዛን ነዋሪዎች ለማጥፋት ሆን ብላ እየሰራች ነዉ በማለት የዓለም ዓቀፉ ማህበረሰብ እያወገዛት ይገኛል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታኒያሁ እና የቀድሞዉ የመከላከያ ሚኒስትር ዩአቭ ጋላንት በጦር ወንጀሎች ተጠያቂ ተብለዉ በዓለም ዓቀፉ የወንጀለኞች ፍርድ ቤት የእስር ማዘዣ እንደወጣባቸዉ ይታወቃል ሲል አናዶሉ ዘግቧል፡፡

እስከዳር ግርማ

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ኀዳር 23 ቀን 2017 ዓ.ም

በጊኒ ወደ 60 የሚጠጉ የእግር ኳስ ተመልካቾች ህይወታቸውን አጡ በጊኒ ሁለተኛዋ ትልቋ ከተማ ዤረኮር በእግር ኳስ ሜዳ በተከሰተ ግጭት 56 ሰዎች ህይወታቸው ማለፉን የሃገሪቱ መንግስት ተናግሯ...
02/12/2024

በጊኒ ወደ 60 የሚጠጉ የእግር ኳስ ተመልካቾች ህይወታቸውን አጡ

በጊኒ ሁለተኛዋ ትልቋ ከተማ ዤረኮር በእግር ኳስ ሜዳ በተከሰተ ግጭት 56 ሰዎች ህይወታቸው ማለፉን የሃገሪቱ መንግስት ተናግሯል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትር ማማዱ ኡሪ ባህ በእሁዱ ጨዋታ በደረሰ ‹‹መረጋገጥ›› ብዙዎች ህይወታቸውን ማጣታቸውን ገልጸው በዚህ ወቅት የሚያስፈልገው መረጋጋት መሆኑን ተናግረዋል፡፡

አንድ ስሙ እንዳይገለጽ የፈለገ ሃኪም ለኤ.ኤፍ.ፒ ለዓይን የሚያታክት በርካታ አስከሬን በሆስፒታል መመልከቱን ተናግሯል፡፡

የአካባቢው ሚዲያ የእንግዳው ቡድን ደጋፊዎች በአርቢትሩ ውሳኔ ተበሳጭተው ወደ ሜዳ ድንጋይ መወርወራቸውን ተከትሎ ፖሊስ አስለቃሽ ጭስ መጠቀሙን ዘግቧል፡፡

‹‹አጨቃጫቂውን ውሳኔ ተከትሎ ደጋፊዎች ወደ ሜዳ መግባታቸውን›› አንድ የዓይን እማኝ ለኤ.ኤፍ.ፒ ተናግሯል፡፡

ፖል ሳኩቮጊ የተባለ መቀመጫውን ዤሬኮር ያደረገ ጋዜጠኛ ለቢቢሲ እንደተናገረው በአካባቢው የኢንተርኔት አገልግሎት እንዲገደብ መደረጉን እና የሆስፒታል በሮች በሮች በፖሊሶች እየተጠበቁ መሆኑን ገልጿል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስት ባህ ለድርጊቱ ተጠያቂ የሆኑትን ወገኖች ለማግኘት ምርመራ ተጀምሯል ብለዋል፡፡ አጋጣሚውን ‹‹አሰቃቂ›› ብለው ገልጸው ላዘኑት መጽናናትን ተመኝተዋል፡፡

አቤል ጀቤሳ

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ኀዳር 23 ቀን 2017 ዓ.ም

የዛሬ የህዳር 23 ቀን 2017 ዓ.ም የከሰዓት እና የምሽት ፕሮግራሞቻችን
02/12/2024

የዛሬ የህዳር 23 ቀን 2017 ዓ.ም የከሰዓት እና የምሽት ፕሮግራሞቻችን

ሩሲያ  የመከላከያ በጀቷን  ክብረወሰን  በሰበረ መልኩ አሳደገችየሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላዲሚር ፑቲን የሀገሪቱ የመከላከያ በጀት እንዲያድግ ተወስነዋል ።ይህ አዲሱ በጀት ሞስኮ በዩክሬን ላይ እ...
02/12/2024

ሩሲያ የመከላከያ በጀቷን ክብረወሰን በሰበረ መልኩ አሳደገች

የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላዲሚር ፑቲን የሀገሪቱ የመከላከያ በጀት እንዲያድግ ተወስነዋል ።

ይህ አዲሱ በጀት ሞስኮ በዩክሬን ላይ እያደረሰችው ያለውን ጥቃት ተከትሎ ወታደራዊ ፍላጎቶችና ተጨማሪ ግብአቶችን ለማቅርብ እንደሚረዳ ተዘግቧል ።

ለ2025 በጀት ዓመት 13.5 ትሪሊዮን ሩብል ለሀገር መከላከያ ተመድቧል ።

ፑቲን የተጨማሪ በጀቱን ያፀደቁት የአውሮፓ ህብረት ባለስልጣናት ለዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዶሚር ዘለንስኪ ጋር አጋርነታቸውን ለማሳየት ወደ ዩክሬን መጓዛቸውን ተከትሎ ነው ሲል AP ዘገቧል።

ልኡል ወልዴ

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ኀዳር 23 ቀን 2017 ዓ.ም

በህውሃት እና በጊዜያዊው አስተዳደሩ መካከል  የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት በሁለቱም በኩል የሚታይ ቁርጠኝነት የለም ሲሉ የህውሃት መስራች  አቶ ገበሩ አስራት ተናገሩበትግራይ ክልል ያለው  ፖ...
02/12/2024

በህውሃት እና በጊዜያዊው አስተዳደሩ መካከል የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት በሁለቱም በኩል የሚታይ ቁርጠኝነት የለም ሲሉ የህውሃት መስራች አቶ ገበሩ አስራት ተናገሩ

በትግራይ ክልል ያለው ፖለቲካዊ መካረርን ለመፍታት በሁለቱም ወገኖች መካከል ቁርጠኝነት የለም ሲሉ የህወሃት መስራችና የቀድሞ ስራ አስፈጻሚ አባል አቶ ገብሩ አስራት ሊትዮ ኤፍ ኤም ተናግረዋል፡፡

የህውሃት መስራች እና አንጋፋው ፖለቲከኛ አቶ ገብሩ አስራት ከጣቢያችን ጋር በነበራቸው ቆይታ ለችግሩ መነሻው ክልሉን እያስተዳደረ በሚገኘው ጊዜያዊ አስተዳደር እና በህወሓት መከከል የተፈጠረው የፖለቲካ ሽኩቻ የስልጣን ፍላጎት የፈጠረው ነው ብለዋል።

በተለይም ህውሃት ሰላምን ለማምጣት ፍላጎቱ እንደሌለው አንስተው እንደ አጠቃላይ ግን የቁርጠኝነቱ ጉዳይ በሁለቱም አካላት በኩል እንደማይታይ ተናግረዋል ፡፡

የትግራይ ሕዝብ ችግር የመላው ኢትዮጵያዊ ሕዝብ ችግር መሆኑን የሚናገሩት አቶ ገብሩ፤ ተፈናቃዮችን ወደነበሩበት የመመለስ እንዲሁም የወደሙ የመሰረተ ልማትቶችን መልሶ የማቋቋም ጉዳይ ለትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ብቻ የሚተዉ አይደለም ብለዋል።

የፌድራል መንግስት መፍትሄ ለማበጀት መጣር እንዳለበት የሚያነሱት አቶ ገብሩ ነገር መካረሩ የአንድ ፓርቲ የመሰንጠቅ ችግር በመሆኑ የፌድራል መንግስቱ አሁን ላይ እርምጃ ለመውሰድ ይቸገራል ሲሉም ተናግረዋል።

ለአለም አሰፋ

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ኀዳር 23 ቀን 2017 ዓ.ም

ሊቨርፑል ማንችስትር ሲቴን አሽነፍ! በአስራ ሶስተኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሊቨርፑል ከማንችስተር ሲቲ ጋር ያደርጉትን ጨዋታ 2ለ0 በሆነ ውጤት አሽንፈዋል። የሊቨርፑልን...
02/12/2024

ሊቨርፑል ማንችስትር ሲቴን አሽነፍ!

በአስራ ሶስተኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕርሚየር ሊግ መርሐ ግብር ሊቨርፑል ከማንችስተር ሲቲ ጋር ያደርጉትን ጨዋታ 2ለ0 በሆነ ውጤት አሽንፈዋል።

የሊቨርፑልን የማሸነፊያ ግቦች መሐመድ ሳላህ እና ኮዲ ጋክፖ ከመረብ አሳርፈዋል።

ማንችስተር ሲቲ አራተኛ ተከታታይ የፕርሚየር ሊግ ሽንፈታቸውን አስተናግደዋል።

መሐመድ ሳላህ በውድድር አመቱ አስራ አንደኛ የፕርሚየር ሊግ ግቡን ከመረብ አሳርፏል።

ግብፃዊው የፊት መስመር ተጨዋች መሐመድ ሳላህ በውድድር አመቱ በሊጉ 17 የግብ ተሳትፎዎችን በማድረግ ቀዳሚው ተጨዋች ሆኗል።

ሊቨርፑሎች በፕርሚየር ሊጉ ያለመሸነፍ ግስጋሴያቸውን ወደ ዘጠኝ ጨዋታ ከፍ ማድረግ ችለዋል።

የሊግ ደረጃቸው

1 ሊቨርፑል - 34 ነጥብ
2 አርስናል 25 ነጥብ
3- ቼልሲ 25 ነጥብ
4 ብራይትን 23 ነጥብ
5 ማንችስተር ሲቲ - 23 ነጥብ

ጋዲሳ መገርሳ
ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ኀዳር 23 ቀን 2017 ዓ.ም

አዲስ ኢንተርናሽናል ባንክ የዲጂታል የትምህርት ቤት ክፍያ ይፋ አደረገ።ባንኩ ኢ-ስኩል ክፍያ የተሰኘ የዲጂታል የትምህርት ቤት ክፍያ አገልግሎት በዛሬው ዕለት ይፋ አድርጓል።የዲጂታል የክፍያ ...
30/11/2024

አዲስ ኢንተርናሽናል ባንክ የዲጂታል የትምህርት ቤት ክፍያ ይፋ አደረገ።

ባንኩ ኢ-ስኩል ክፍያ የተሰኘ የዲጂታል የትምህርት ቤት ክፍያ አገልግሎት በዛሬው ዕለት ይፋ አድርጓል።

የዲጂታል የክፍያ አገልግሎቱ ስህተቶችና ድጋሚ ክፍያዎች እንዳይፈፀሙ የሚያደርግ መሆኑ ተገልጿል።

የዲጂታል የክፍያ አገልግሎቱን በመጠቀም የግል እና የመንግስት ት/ቤቶች ክፍያዎችን መፈፀም ይችላሉ ነው የተባለው።

ከትምህርት ቤት ክፍያዎች በተጨማሪ ተማሪዎችን ለመመዝገብ እንዲሁም መረጃዎችን ለማደራጀት ያስችላል ተብሏል።

መተግበሪያውን በመጠቀም ትምህርትቤቶች የራሳቸውን ማስተካከያዎች ማድረግ እንደሚችሉም ነው የተገለጸው።

መተግበሪያው የትምህርት ቤት ክፍያዎች ጊዜያቸው እንዳያልፍም ለወላጆች የፅሁፍ መልዕክት በመላክ የማስታወስ ስራ ይሰራል ተብሏል።

ከዚህ በተጨማሪ መተግበሪያውን በመጠቀም በየትኛውም ጊዜ የተፈፀሙ የክፍያ ሪፖርቶችን ማየት እንደሚቻል ተገልጿል።

ባንኩ የዲጂታል ባንኪንግ አገልግሎቶቹን ለማስተዋወቅም አውደርእይ አዘጋጅቷል።

አዲስ ኢንተርናሽናል ባንክ በግንቦት ወር የካርድ ባንኪንግ አገልግሎት የጀመረ ሲሆን ፤ አሁን ላይ ከ88ሺህ በላይ ተጠቃሚዎች እንዳሉት ተገልጿል።

እሰከዳር ግርማ

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ኀዳር 21 ቀን 2017 ዓ.ም

ሩድ ቫኔስትሮይ  በሌሲስተር ሲቲን ዋና አሰልጣኝነት ተሾመ።በቅርቡ አሰልጣኝ ሴቲቭ ኩፐርን ያሰናበተው ሌስተር ሲቲ አዲስ አሰልጣኝ በሃላፊነት መሾማቸውን አስታውቀዋል። ሌስተር ሲቲ ኔዘርላንዳዊ...
30/11/2024

ሩድ ቫኔስትሮይ በሌሲስተር ሲቲን ዋና አሰልጣኝነት ተሾመ።

በቅርቡ አሰልጣኝ ሴቲቭ ኩፐርን ያሰናበተው ሌስተር ሲቲ አዲስ አሰልጣኝ በሃላፊነት መሾማቸውን አስታውቀዋል።

ሌስተር ሲቲ ኔዘርላንዳዊውን አሰልጣኝ ሩድ ቫን ኔስትሮይ የቡድኑ ዋና አሰልጣኝ አድርገው መሾማቸውን ይፋ አድርገዋል።

አሰልጣኝ ሩድ ቫን ኔስትሮይ ሌስተር ሲቲ ማክሰኞ ከዌስትሀም ዩናይትድ ጋር በሚያደርጉት ጨዋታ ቡድኑን በመምራት ስራውን የሚጀምር ይሆናል።

ጋዲሳ መገርሳ

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ኀዳር 21 ቀን 2017 ዓ.ም

የነገ የህዳር 21 ቀን 2017 ዓ.ም የኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8  ፕሮግራሞቻችን
29/11/2024

የነገ የህዳር 21 ቀን 2017 ዓ.ም የኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 ፕሮግራሞቻችን

5ኛው የኢትዮጵያ አትሌቶች ማህበር ጠቅላላ ጉባኤ በአዲስ አበባ ተካሄዷል ።በጠዋቱ መርሃግብር ላይ አጠቃላይ የ2014-2016 ዓ.ም የተከናወኑ አበይት ተግባራት ዝርዝር አፈፃፀም ሪፖርት በማህ...
29/11/2024

5ኛው የኢትዮጵያ አትሌቶች ማህበር ጠቅላላ ጉባኤ በአዲስ አበባ ተካሄዷል ።

በጠዋቱ መርሃግብር ላይ አጠቃላይ የ2014-2016 ዓ.ም የተከናወኑ አበይት ተግባራት ዝርዝር አፈፃፀም ሪፖርት በማህበሩ ጵ/ቤት ኃላፊ አትሌት ሙሉጌታ ደምሴ የቀረበ ሲሆን በጉባኤተኞቹ ለቀረቡት ጥያቄዎች በረዳት ኮሚሽነር አትሌት ማርቆስ ገነቲ ፣ በአትሌት መሰለች መልካሙ እና በጵ/ቤት አመራሮች ማብራሪያ እና መልስ ተሰጥቶባቸዋል ።

በመቀጠልም ለቀጣይ አራት ዓመታት በስራ አስፈፃሚነት የሚመሩት አባላት በጉባኤው ላይ ተመርጠዋል ።በዚህ መሰረት :-

አትሌት የማነ ፀጋይ- ፕሬዝዳንት
አትሌት ተመስገን ወርቁ
አትሌት መርሲት ገብረእግዚአብሔር
አትሌት በላይነሽ ኦልጂራ
አትሌት ግርማ ጥላሁን
አትሌት ባንቺአየሁ ተሰማ
አትሌት በሽንቄ እመሼ

ረዳት ኮሚሽነር አትሌት ማርቆስ ገነቲ አዲስ ለተመረጡት የማህበሩ ስራ አስፈፃሚ አባላት መልካም ምኞታቸውን በመግለፅ ማህበሩን የጀመረውን በጎ ተግባራት እንዲያስቀጥሉ አደራ ሰጥቷል ።

በመጨረሻም አዲሱ ስራ አስፈፃሚ ቃለ መሃላ በመፈፀም ከበፊቱ አመራር አደራውን ተቀብሎ ስራውን ለመስራት ቃል በመግባት ጉባኤውን አጠናቋል ።

ጋዲሳ መገርሳ

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ኀዳር 20 ቀን 2017 ዓ.ም

በአዲስ አበባ የባቡር ትራንስፖርት ታሪፍ ላይ ማሻሻያ ተደረገየአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ትራንስፖርት አገልግሎት ታሪፍ ማሻሻያ መደረጉን የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ አስታወቀ፡፡በዚሁ መሠረት...
29/11/2024

በአዲስ አበባ የባቡር ትራንስፖርት ታሪፍ ላይ ማሻሻያ ተደረገ

የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ትራንስፖርት አገልግሎት ታሪፍ ማሻሻያ መደረጉን የአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ አስታወቀ፡፡

በዚሁ መሠረት ከታኅሣስ 1 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በመዲናዋ ተግባራዊ የሚደረግ የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር አገልግሎት ታሪፍ አሁን እየተሰጠበት ካለው 10 ብር ወደ 20 ብር ማሻሻያ መደረጉን ቢሮው አስታውቋል፡፡

የታሪፍ ማሻሻያው ከታኅሣስ 1 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ እንደሚደረግ ታውቆ ተፈፃሚ እንዲደረግም ቢሮው አሳስቧል፡፡

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ኀዳር 20 ቀን 2017 ዓ.ም

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8

Twitter https://twitter.com/EthioFM

YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos

Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcasWebsite https://ethiofm107.com/

ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።

ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።

ሩሲያ  የመከላከያ ሚኒስትሯን ወደ ሰሜን ኮሪያ ላከችየሩሲያዉ የመከላከያ ሚኒስትር አንድሪ ብሉሶቭ  በሰሜን ኮሪያ ጉብኝት እያደረጉ ነዉ ተብሏል፡፡ብሉሶቭ በሁለቱ አገራት  የወታደራዊ ስምምነት...
29/11/2024

ሩሲያ የመከላከያ ሚኒስትሯን ወደ ሰሜን ኮሪያ ላከች

የሩሲያዉ የመከላከያ ሚኒስትር አንድሪ ብሉሶቭ በሰሜን ኮሪያ ጉብኝት እያደረጉ ነዉ ተብሏል፡፡

ብሉሶቭ በሁለቱ አገራት የወታደራዊ ስምምነት ዙሪያ ከሰሜን ኮሪያ አቻቸዉ ኖ ክዋንክ ኮል ጋር መወያያታቸዉ ተነግሯል፡፡

ሁሉቱ ባላስልጣናት ፑቲንና ኪም ጆንግ ኡን በቅርቡ የፈረሙትን ስምምነተ ተግባራዊ በሚሆንበት ዙሪያ መነጋገራቸዉን አርቲ ኒዉስ ዘግቧል፡፡

የወታደራዊ አጋርነት ስምምነቱ ዋነኛ አላማ በሰሜን እስያ ያለዉን ዉጥረት ለማርገብ ነዉ ተብሏል፡፡

የሩሲያዉ የመከላከያ ሚኒስትር ወደ ፕዮንግያንግ ያመሩት የሰሜን ኮሪያ ወታደሮች ዩክሬን ድንበር ላይ መስፈራቸዉን እነ አሜሪካ እየገለፁ ባሉበት ወቅት ነዉ፡፡

አባቱ መረቀ

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ኀዳር 20 ቀን 2017 ዓ.ም

ውድ አድማጮቻችን እና ተከታዮቻችን የኢትዮ ኤፍ ኤም ወቅታዊ አዳዲስ መረጃዎችና ፕሮግራሞችን ለማግኘት ከታች ያሉትን ገፆቻንን ይጎብኙ ቤተሰብ ይሁኑ ።

Telegram https://t.me/ethiofm107dot8

Twitter https://twitter.com/EthioFM

YouTube https://www.youtube.com/channel/UCn4D20GPsAtNqN5bIC1BhFA/videos

Facebook https://www.facebook.com/onelovebroadcasWebsite https://ethiofm107.com/

ያሎትን አስተያየት እና ጥያቄ በአጭር መልዕክት 6321 ላይ ይላኩልን።

ከኛ ጋር ስለሆናችሁ ከልብ እናመሰግናለን።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ኒውዮርክ ከተማ በየዕለቱ ሊበር ነውየኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአዲስ አበባ ወደ ኒውዮርክ ከተማ ሲያደርገው የነበረውን አራት ሳምንታዊ በረራ በማሳደግ በእየዕለቱ ...
29/11/2024

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ኒውዮርክ ከተማ በየዕለቱ ሊበር ነው

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከአዲስ አበባ ወደ ኒውዮርክ ከተማ ሲያደርገው የነበረውን አራት ሳምንታዊ በረራ በማሳደግ በእየዕለቱ ሊበር መሆኑን አስታውቋል።

አየር መንገዱ ከህዳር 22 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ከተማዋ የሚያደርገውን እለታዊ በረራ እንደሚጀምር ገልጿል ።

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ኀዳር 20 ቀን 2017 ዓ.ም

በሀዋሳ  በህገ ወጥ የቤንዚን ንግድ የተሠማሩ ታሠሩየሲዳማ ክልል የነዳጅ ግብይትና ቁጥጥር ግብረሃይል ሁለት የንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ባለሙያዎችን ጨምሮ “ ህገ ወጥ የቤንዚን ንግድ ሲያከ...
29/11/2024

በሀዋሳ በህገ ወጥ የቤንዚን ንግድ የተሠማሩ ታሠሩ

የሲዳማ ክልል የነዳጅ ግብይትና ቁጥጥር ግብረሃይል ሁለት የንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ባለሙያዎችን ጨምሮ “ ህገ ወጥ የቤንዚን ንግድ ሲያከናውኑ ደረስኩባቸው “ ያላቸውን 34 ሰዎች ማሠሩን አስታወቀ ፡፡

ግብሃይሉ እርምጃውን የወሰደዉ የከተማዋ ነዋሪዎች በነዳጅ ዘይት እጦት መቸገራቸዉን በሚያስታዉቁበት ወቅት ነው ፡፡

የክልሉ ፖሊስ ምክትል ኮሚሽነርና የግብረ ሃይሉ አባል ካሳ ጩቦ እንዳስታወቁት ተጠርጣሪ ባለሙያዎችና አዘዋዋሪዎቹ የተያዙት ፖሊስ ካለፈው ሰኞ ጀምሮ ባደረገው ክትትል ነው ፡፡

ምክትል ኮሚሽነሩ እንዳሉት በሕገ ወጥ የቤንዚን ንግድ ተሰማርተዋል በሚል ጥርጣሬ ከታሠሩት 34ት ሰዎች መካከል ሁለቱ የሀዋሳ ከተማ አስተዳደር ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ ባለሙያዎች ናቸው “ ብለዋል ፡፡

በተጨማሪም ቤንዚን ተመላልሰው በመቅዳት ለጥቁር ገበያ ሻጮች ሲገለብጡ የነበሩ 22 ሞተር ሳይክሎች አጅ ከፍንጅ መያዛቸውን የጠቀሱት ምክትል ኮሚሽነር ካሳ “ ከፋብሪካ ሥሪት ውጭ ተጨማሪ የነዳጅ ማጠራቀሚያ ጋን አስበይደው ለመቅዳት የሞከሩ ሁለት አሽከርካሪዎችም በቁጥጥር ሥር ውለዋል ፡፡

ተጠርጣሪዎቹ ለሕግ እንደሚቀርቡ ምክትል ኮሚሽነሩ አስታዉቀዋል።
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በጥቁር ገበያ ጫና ሥር የወደቀው የሀዋሳ ከተማ የነዳጅ አቅርቦት በአሽከርካሪዎችና በቀን ገቢ የሚተዳደሩ ዜጎችን እንቅስቃሴ እያስተጓጎለ ነዉ፡፡

ችግሩ ያሳሰበው የክልሉ መንግሥት በርዕሰ መስተዳድሩ የሚመራ ግብረሃይል አቋቁሞ የተጠናከረ ቁጥጥር እያደረገ እንደሚገኝ ከቀናት በፊት አስታዉቋል ፡፡

ኢትዮ ኤፍ ኤም 107.8 የኢትዮጵያዊያን

ኀዳር 20 ቀን 2017 ዓ.ም

Address

Bole Medehanialem, Selam City Mall 5th Floor
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when ETHIO FM 107.8 posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Share

Category

ETHIO FM 107.8 Ethiopians

በፍቅር ላይ የተመሰረተ ኢትዮጵያዊነት እንዳይላላ ከልቡ የሚተጋ፣ መከባበርና መተሳሰብን የሚያስቀድም ኤፍኤም ሬዲዮ !!!