The Christian News - የክርስቲያን ዜና

The Christian News - የክርስቲያን ዜና በዚህ ቻናል ተዓማኒነት ያላቸው የክርስቲያን ዜናዎች እና መልዕክቶች ከመላው አለም ይደርሶታል።

The Christian News በተጨማሪም 60ሺህ ቤተሰቦች በyoutube እና ከ5ሺህ በላይ ቤተሰቦች በቴሌግራም ስላሉን አዳዲስ የሆናቹ ቤተሰብ እንድትሆኑ እንጋብዛችኋለን።

ዘማሪ ዓለማየሁ ገ/መስቀል  #ወደ  #ጌታ ተሰበሰቡ፡፡ ከደቡብ ኢትዮጵያ ተነስተው መጽሐፍ ቅዱስን በዝማሬ እየገለጡ በጽናት ሲያገለልሉ የቆዩት ዘማሪ አለማየሁ በስደት ዘመናት ሳይቀር በጌታ ጸ...
23/10/2025

ዘማሪ ዓለማየሁ ገ/መስቀል #ወደ #ጌታ ተሰበሰቡ፡፡

ከደቡብ ኢትዮጵያ ተነስተው መጽሐፍ ቅዱስን በዝማሬ እየገለጡ በጽናት ሲያገለልሉ የቆዩት ዘማሪ አለማየሁ በስደት ዘመናት ሳይቀር በጌታ ጸንተው የቆሙ ወንድም እንደነበሩ ብዙዎች ይመሰክሩላቸዋል፡፡

ዘማሪ ዓለማየሁ ግጥም እና ዜማ ራሳቸው እያዘጋጁ በኦሮምኛ፣ በአማርኛና በጌዴዎፋ ባቀረቧቸው ዝማሬዎች ብዙዎችን ያጽናኑና ያስተማሩ አገልጋይ ነበሩ፡፡

አገልጋዩ በትጋት፣ በጽናትና በመሰጠት ባገለገሉት ሕዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተወዳጅነትና ተቀባይነት እንደነበራቸው የደቡብ ቀጣና አመራሮች ተናግረዋል።

ዘማሪ ዓለማየሁ ገ/መስቀል ባደረባቸው ሕመም ለሕክምና ወደ ሐዋሳ ያኔት ሆስፒታል ከገቡ በኋላ ጥቅምት 12 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም ድካም ማረፋቸው ተገልጿል።

የዘማሪው የቀብር ሥነ ሥርዓት ነገ አርብ ጥቅምት 14 ቀን 2018 ዓ.ም ወዳጅ ዘመዶቻቸውና የቤተ ክርስቲያን አባላት በተገኙበት በቡሌ ሆራ ከተማ እንደሚፈጸም በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤ/ክ የደቡብ ቀጣና ጸሐፊ የሆኑት አቶ ጥላሁን መኮንን አስታውቀዋል፡፡

The Christian News - የክርስቲያን ዜና ለወዳጅ ዘመዶቹ መፅናናትን ይመኛል።

አናሲሞስ አሳታሚ በአንድ ዓመት 10 መፅሐፍት አስመረቀ     አናሲሞስ አሳታሚ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን አገልጋዮች በእግዚአብሔር ቃል ጥናት እንዲበረቱና በአገር በቀል ቋንቋ የሚሰጡ የሥነ መ...
21/10/2025

አናሲሞስ አሳታሚ በአንድ ዓመት 10 መፅሐፍት አስመረቀ

አናሲሞስ አሳታሚ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን አገልጋዮች በእግዚአብሔር ቃል ጥናት እንዲበረቱና በአገር በቀል ቋንቋ የሚሰጡ የሥነ መለኮት ትምህርቶች እንዲጎለብቱ ለማድረግ ባለፉት 12 ወራት 10 መፅሐፍትን አሳትሞ አስመርቋል።

እሁድ ጥቅምት 9 2018 ዓ.ም ሣር ቤት በሚገኘው፣ የኢትዮጵያ ድኀረ ምረቃ የሥነ መለኮት ትምህርት ቤት ኢገስት መሰብሰቢያ አዳራሽ 6ቱ መፅሐፍት የተመረቁ ሲሆን የሥነ መለኮት ተማሪዎች ፣መምህራን እና ሰባኪዎችም ታድመዋል።

የአናሲሞስ አሳታሚ መሥራች እና ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶክተር ተካልኝ ዱጉማ እንዳሉት ለህትመት ከበቁት መፅሐፍት መካከል አንዱ በአማርኛ ቋንቋ የተዘጋጀ የዕብራይስጥ ቋንቋ ማስተማሪያ መጽሐፍ ይገኝበታል።

ይህ መጽሐፍ በአይነቱ በኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የመጀመሪያው መጽሐፍ ሊሆን እንደሚችልም የአሳታሚ ድርጅቱ መሥራች ተናግረዋል። ባለፈው እሁድ ለምረቃ የቀረቡት ስድስት መጽሐፍት ሲኾኑ እነዚህን መጽሐፍት በአስተንትኖት የመጽሐፍ ቅዱስ ማብራሪያዎች ቅጽ ውስጥ የገላቲያ ማብራሪያ መጽሐፍ ጸሐፊ ሔኖክ ኢሳያስ

1. የሐይማኖቶች እና ገመናቸው
2. የእግዚአብሔር እስራኤል ጸሐፊ
3. በእግዚአብሔር መንግስት ውስጥ መኖር
4. የግብዣ ወደ ዮሐንስ ገጾች
5. የመጽሐፍ ቅዱሳዊ ዕብራይጥ መሠረታዊያን በዐማርኛ የሚሉት ናቸው።

ከላይ የተጠቀሱት በዓመቱ ውስጥ ለሕተመት የበቁ መጽሐፍት ናቸው። አናሲሞስ አሳታሚ ልክ የዛሬ ዓመት በኦክቶብር 17 ሦስት መጽሐፍትን ያስመረቀ ሲሆን

1. በአክሊሉ ኩማ የተጻፈው በአስተንትኖት የመጽሐፍ ቅዱስ ማብራሪያዎች ጥራዝ ውስጥ የዮሐንስ ወንጌል ማብራሪያ ቅጽ አንድ
2. በዶክተር ተካልኝ ተጽፎ በ አብዲሳ ወዬሳ የተተረጎመው የማቴዎስ ወንጌል ማብራሪያ እና
3. በሔኖክ ኢሳያስ የተጻፈው ጳውሎስ እና መስሓዊው ምስጢር የተሰኙ መጽሐፍት ናቸው።

በመፅሐፍ ምረቃው ላይ የቤተክርስቲያን መሪዎች ተገኝተው የነበረ ሲሆን በዕውቀት ላይ የተመሠረተ ሥራ ለማከናወን መፅሀፍት ትልቅ አስተዋፅዖ እንዳላቸው ተናግረዋል።
የመፅሀፎቹ የአርትዖት ሥራ በናይእግዚ ኀሩይ የተሠራ ሲሆን በዕለቱም ዶክተር ማሙሻ ፋንታ የእግዚአብሔርን ቃል አካፍሏል።

ምንጭ: ዕዝራ እጅጉ-(ተወዳጅ ሚድያ)

21/10/2025

ትላንት ያለፍኩት ሕይወት 😥😥

ትላንትን ታስታዉሳለህ አዎ ለምን ? በርትቼ አመስግኜ ክብር ልሰጥበት። አሜን

በጌታ ቤት ቆይቶ የተንሸራተተ ሰዉ ትላንትን ለምን ማስታወስ አለበት ? ለመነሳት እና በንሰሃ ለመመለስ። አሜን አሜን

ፖስተር ፍፁም

ሙሉውን የክርስቲያን ዜና የዪቲዩብ ቻናል ላይ ይመልከቱ!!! https://www.youtube.com/channel/UCeHRJCDJ0wUDaBfAFmuMa7A...
゚viralシfypシ゚viralシ #እግዚአብሔር #ወጣት
#ወንጌል #ቤተክርስቲያን #የኢትዮጵያ #ሙሉ #ድንቅ
シ゚ ゚viralシ2024fyp ゚viralシfypシ゚viralシalシ viralシfypシ゚viralシalシ ゚viralシ

#ወንጌል #ቤተክርስቲያን #የኢትዮጵያ #ሙሉ #ድንቅ ゚viralシ2024fyp ゚viralシfypシ゚viralシalシ ゚viralシfypシ゚

 የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል የኢትዮጵያ የሙስሊም ሕብረተሰብ መሪ ዶ/ር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ማረፋቸውን ተከትሎ የተሰማውን ሀዘን ገለፀ።በመላው ኢት...
20/10/2025



የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል የኢትዮጵያ የሙስሊም ሕብረተሰብ መሪ ዶ/ር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ማረፋቸውን ተከትሎ የተሰማውን ሀዘን ገለፀ።

በመላው ኢትዮጵያውያን ተወዳጅ የነበሩት እና ፍቅር እና መቻቻልን በማስተማር የሚታወቁትን፣ የሙስሊሙ ህብረተሰብ መሪና አባት የነበሩትን የክቡር ዶ/ር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ኡመር ኢድሪስ ማረፋቸውን የሰማነው በታላቅ ሀዘን ነው።

በመሆኑም የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያ ክርስቲያናት ካውንስል የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን በመግለጽ፣ ለመላው ሙስሊም ህብረተሰብ እና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናት ይሆን ዘንድ ጸሎታችን ነው ብሏል ካውንስሉ የማህበራዊ ሚድያ ገጹ።

በ  ፈርሰው የነበሩ አብያተ ክርስቲያናት ድጋሚ ተከፈቱበኢራቅ ሞሱል ከተማ ከፈረሱ 10 አመት የሆናቸው ታሪካዊ አብያተ ክርስቲያናት ድጋሜ ለዝማሬ እና ምስጋና ተከፍተዋል።በ7ኛው ክ/ዘመን የተ...
20/10/2025

በ ፈርሰው የነበሩ አብያተ ክርስቲያናት ድጋሚ ተከፈቱ

በኢራቅ ሞሱል ከተማ ከፈረሱ 10 አመት የሆናቸው ታሪካዊ አብያተ ክርስቲያናት ድጋሜ ለዝማሬ እና ምስጋና ተከፍተዋል።

በ7ኛው ክ/ዘመን የተተከለችው የሶሪያ ኮፕቲክ ኦሮቶድክስ የሆነችው ቅዱስ ቶማስ ቤተ ክርስቲያን እና የከልዳዊያን ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የሆነችው አል ጣሂር አብያተ ክርስቲያናት ናቸው የተከፈቱት።

አብያተ ክርስቲያናቱ በተከፈቱበት ወቅት የአካባቢው ነዋሪዎች፣ ቀሳውስት፣ ሶሪያ ኮፕቲክ ቤተ ክርስቲያን መሪ፣ የኢራቅ ካልዳዊ ቤተ ክርስቲያን ፓትሪያርክ፣ የኢራቅ ባህል ሚኒስቴር፣ የነነዌ ግዛት መሪ፣ የፍረንሳይ አምባሳደር እና የዩኔስኮ ተወካዮች ተገኝተዋል ሲል ያስነበበው የቫቲካን ዜና ነው።

አብያተ ክርስቲያኖቹ በአካባቢዎቹ መከፈታቸው ለተፈናቀሉ ክርስቲያኖች ትልቅ የተስፋ ምልክት ነው ብለውታል። ሸሽተው የነበሩ ሰዎች አሁን መመለስ ይችላሉ ተብሏል። ISIS ከ2014-2017 መቀመጫውን በሰሜኗ ኢራቅ ሞሱል ባደረገበት ወቅት የቅዱስ ቶማስን ቤተ ክርስቲያን እስር ቤት፣ የአል ጣሂርን ቤተ ክርስቲያን ደግሞ በቦምብ ደብድቦ ከአገልግሎት ውጪ አድርጎታል።

ከሞሱል ነዋሪዎች መካከል 14 በመቶ የሚሆኑት ክርስቲያን የነበሩ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ከ60 የማይበልጡ ቤተሰቦች ብቻ ናቸው የቀሩት። ከታደሱት መካከል “እውነት ነጻ ያወጣችኋል” እና ሰላምን እተውላችኋለው፣ ሰላሜን እሰጣችኋለው” የሚሉ ጽሁፎች ያለበት የ13ኛው ክ/ዘመን የድንጋይ ላይ ቅርጽ ጽሁፎች አሉ።

በአካባቢው የሚንቀሳቀሰው የባቢሎን እንቅስቃሴ የተሰኘ የፖለቲካ ፓርቲ ክርስቲያኖች በኢራቅ በእኩልነት እና በነጻነት መኖር የሚችሉበት ህጋዊ፣ ፖለቲካዊ እና የደህንነት ስትራቴጂ ያስፈልጋል ሲል ገልጿል። ሁለቱ አብያተ ክርስቲያናት በአካባቢው የክርስቲያን እና ሙስሊም ማህበርሰብ አንድነት ዘንድ ትልቅ ቦታ አላቸው።

ቅዱስ ቶማስ ቤተ ክርስቲያን ሐዋርያው ቶማስ ወደ ህንድ ጉዞ በሚያደርግበት ወቅት ያረፈባት ስፍራ ስትሆን አል ጣሂር ቤተ ክርስቲያን ደግሞ የአካባቢው ነዋሪ በ1743 ዓ.ም ከፐርሺያ ወራሪዎች ከለላን ያገኙበት ስፍራው መሆኑን ታሪካቸው ይናገራል።
በኦቦሌሳ አዶላ

19/10/2025

የዳንኤል አምደሚካኤል #ድንቅ ምስክርነት 🙏🙏

ሙሉውን የክርስቲያን ዜና የዪቲዩብ ቻናል ላይ ይመልከቱ!!! https://www.youtube.com/channel/UCeHRJCDJ0wUDaBfAFmuMa7A...
゚viralシfypシ゚viralシ #እግዚአብሔር #ወጣት
#ወንጌል #ቤተክርስቲያን #የኢትዮጵያ #ሙሉ #ድንቅ
シ゚ ゚viralシ2024fyp ゚viralシfypシ゚viralシalシ viralシfypシ゚viralシalシ ゚viralシ

#ወንጌል #ቤተክርስቲያን #የኢትዮጵያ #ሙሉ #ድንቅ ゚viralシ2024fyp ゚viralシfypシ゚viralシalシ ゚viralシfypシ゚

በሰሜኑ ጦርነት የተጎዱ ሰዎችን መልሶ የመቋቋሚያ ስራ አላማጣን ጨምሮ በ5 ወረዳዎች ተከናወነ።የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን የሰብዓዊ ድጋፍ እና ልማት ኮሚሽን 700 ሺህ ዶላር ወጨ በ...
18/10/2025

በሰሜኑ ጦርነት የተጎዱ ሰዎችን መልሶ የመቋቋሚያ ስራ አላማጣን ጨምሮ በ5 ወረዳዎች ተከናወነ።

የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን የሰብዓዊ ድጋፍ እና ልማት ኮሚሽን 700 ሺህ ዶላር ወጨ በማድረግ በጦርነት የተጎዱ ሰዎችን መልሶ የመቋቋሚያ ስራ አላማጣን ጨምሮ በ5 ወረዳዎች በ21 ቀበሌዎች 4500 ቤተሰብ በቀጥታ ተጠቃሚ የሚያደረግ ቅደም ማገገም የግብርና ፕሮጀክት እየሰራ መሆኑን ገለጸ።

ይህ ፕሮጀክት በአላማጣ ከተማ፣ራያ አላማጣ፣ ኮርም፣ ኦፉላ፣ ጨርጭር እና ዛታ ወረዳዎች በ21 ቀበሌዎች 4500 ቤተሰብ በቀጥታ ተጠቃሚ ያደረገ ሲሆን በጦርነት የተጉዳውን የማህበረሰቡን የግብርና እና የማህበረሰብ ኑሮን በማሻሻል እና በመደገፍ ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጨወተ እንደሚገኝ ተገልጿል።

ፕሮጀክቱም የግብርና መሳሪያዎች እና ሌሎች መሰል ድጋፎችን ለደሃ ደሃ ለሆኑ፣ በጦረነት ለተጎዱ እና ለአካል ጉዳተኞች ድጋፍ ማድረጉን በኮሚሽኑ የአስቸኳይ ጊዜ እርዳታ እና መልሶ ማቋቋም ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ኤፍሬም ከበደ ገልጸዋል።

አቶ ኤፍሬም ከበደ ይህ ፕሮጀክት ተጠቃሚዎችን ከመደገፍ ባሻገር በዘላቂነት የምግብ ዋስትና እንዲያረጋግጡ እና የዕለት ገቢያቸውን እንዲያሳድጉ ያግዛቸዋል ያሉ ሲሆን አከባቢው በጦርነት የተጎዳ በመሆኑ ሁሉንም ለመድርስ ይህ ድጋፍ በቂ ነው ባይባልም ነገረ ግን ድጋፍ የተደረገላቸው ቤተሰቦች ኑሮ መልሶ ከመገንባት አንጻር ሚናው ከፍተኛ እንደሆነ ተናግረዋል።

የ4 ልጆች እናት እና በራያ አላማጣ ወረዳ የሁል ጊዜ ለምለም ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ ፀጋ አብረሀ እንደገለጹልን ከሆነ የጤፍ ዘርን እና መዳበሪያን ከገበያ ገዝተን ለመዝራት አቅማችን አቅም እንደሌላቸው ጠቅሰው የተደረገላቸው ድጋፍ እርሻቸውን በዘር እንዲሸፍኑ እንዳገዛቸው በመግለጽ ይህ ድጋፍ የወደፊት የምግብ ዋስትናችንን እውን ለማድረግ ቁልፍ ተስፋ መሆኑን አመላክተዋል።

ወ/ሮ ፀጋ አብረሀ አክለው ኮሚሽኑ ለሴቶች፣ ህፃናት፣ አካል ጉዳተኞች እና ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው አቅመ ደካሞች እያደረገ ያለውን የድጋፍ ስራም አድንቀዋል።

ሌላኛው የ7 ልጆች አባት እና የአላማጣ ወረዳ ገርጃሌ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት አማረ ሳሌ የፕሮጀክቱ ተጠቃሚ ሲሆኑ በአካባቢው የተካሄደው ጦርነት የእያንዳንዱን ግለሰብ ህይወት እንደጎዳቸው ገልጸው የዚህ ፕሮጀክት ድጋፍ ለተጎዳው ሕዝብ ታላቅ ተስፋ ነው ያሉ ሲሆን በተለይ ለገበሬዎች የዚህ ፕሮጀክት ትርጉም በቃል ከመግለጽ የላቀ መሆኑን ተናግረው ኮሚሽኑ ላደረገላቸው ድጋፍ በራሳቸውን እና በቤተሰባቸው ስም ከልብ አመስግነዋል።

ሌሎችም የፕሮጀክቱ ተጠቃሚዎች የተደረገላቸው ድጋፍ በጦረነት የተጎዳውን ኑሮ በማሻሻል ረገድፍ ላቅ ያለ ሚና እንዳለው ገልጸው የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን የሰብዓዊ ድጋፍ እና ልማት ኮሚሽን ላደረገላቸው ድጋፍ ምስጋናቸውን አቅረበዋል፡፡

በአጠቃላይ ይህ ፕሮጀክት ለአባወራዎቹ ግማሽ ሄክታር መሬት ለመሸፈን የሚያስችል የተሻሻለ ዘር (ጤፍ 12.5 ኪሎ ግራም እና ማሽላ 10 ኪሎ ግራም) ፣ የግብርና መረጃ መሳሪያዎች 4,500 አባ ወራ እና እማ ወራ፣ የማዳበሪያ ድጋፍ 1,357 አባ ወራ እና እማ ወራ፣ የጓሮ አትክልት ዘር ለ25 ታጠቃሚዎች ድጋፍ የተደረገ ስሆን ይህ በአከባቢው በነበር ግጭት ጦርነት የተጎዳውን የማህበረሰቡን የምግብ ዋስትና፣ ኑሮ እና የቤተሰብ ገቢ በማሻሻል ርገድ ቁልፍ ሚና እንዳለው ተጠቅሷል።

በሮማን ከሊል

ጥቅምት 08/2018 ዓ.ም

ዝርዝር መረጃዎችን ለመመልከት የቴሌግራም ገፃችንን ይቀላቀሉ።

https://t.me/TCNEW

18/10/2025

መንፈሳዊ #ሰዉ ከሆንክ የሚታይህ ተልዕኮ ብቻ ነዉ።

አገልጋዮችን ለመጣል የምትታገሉ ሴቶች አትድከሙ። መጋቢ በጋሻዉ ደሳለኝ

ሙሉውን የክርስቲያን ዜና የዪቲዩብ ቻናል ላይ ይመልከቱ!!! https://www.youtube.com/channel/UCeHRJCDJ0wUDaBfAFmuMa7A...
゚viralシfypシ゚viralシ #እግዚአብሔር #ወጣት
#ወንጌል #ቤተክርስቲያን #የኢትዮጵያ #ሙሉ #ድንቅ
シ゚ ゚viralシ2024fyp ゚viralシfypシ゚viralシalシ viralシfypシ゚viralシalシ ゚viralシ

#ወንጌል #ቤተክርስቲያን #የኢትዮጵያ #ሙሉ #ድንቅ ゚viralシ2024fyp ゚viralシfypシ゚viralシalシ ゚viralシfypシ゚

“AI”ን ለወንጌልክርስቲያናዊ ጥያቄዎችን ማስተናገድ የሚችል የ“AI Chat bot” ወይም ሰው ሰራሽ አስተውሎት ቻት ቦት ይፋ ሆነ።“My Faith Assistant” የተሰኘው ቻት ቦት ግልጽ ...
17/10/2025

“AI”ን ለወንጌል

ክርስቲያናዊ ጥያቄዎችን ማስተናገድ የሚችል የ“AI Chat bot” ወይም ሰው ሰራሽ አስተውሎት ቻት ቦት ይፋ ሆነ።

“My Faith Assistant” የተሰኘው ቻት ቦት ግልጽ እና መጽሃፍ ቅዱሳዊ መልሶችን ለመመለስ በሁሉም ጊዜ፣ በሁሉም ስፍራ ተዘጋጅቷል ተብሏል። ልክ እንደ ChatGPT የሚሰራ ሲሆን ምንጩ መጽሃፍ ቅዱስ እና እምነት ላይ ትኩረት ያደረገ ነው።

በሞባይሎች ላይ መተግበሪያ ሆኖ የተለቀቀ ሲሆን በዲጂታል የወንጌል አገልግሎት ትልቅ አስተዋጾ ይኖረዋል ተብሏል።

“My Faith Assistant “ በአሁኑ ወቅት ከ191 በሚበልጡ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ከ2400 በላይ የሙከራ ደረጃ ንግግሮችን ማካተት ችሏል። ይሄ መተግበርያ ጥያቄ ከመመለስ አልፎ ሰዎች በመንፈሳዊ ህይወታቸው ወደ እግዚአብሔር እንዲቀርቡ እና ምርጥ የደቀ መዝሙር ማድረጊያ መስሪያ እንዲሆን ተስፋ ተጥሎበታል።

አሜሪካዊው ፓስተር ሚካኤል ዩሱፍ በሚመሩት “Leading the Way” የተሰኘ ሚኒስትሪ ነው ቻት ቦቱን ይፋ ያደረገው። ፓስተር ሚካኤል ብዙ ክርስቲያኖች የሚፈሩትን ሰው ሰራሽ አስተውሎትን አሁን ልንዋጀው ይገባል ብለዋል።

ሰዎች AIን መፍራታቸውን እረዳለሁ፣ በአደጋው ልክ ትልቅ እድልም አለው። ታድያ AIን ለመዋጀት ጊዜው አሁን ነው ብለውታል።

ፓስተር ሚካኤል ከ58 በላይ መጽሃፍትን ጽፈዋል። እኔ ቴክኖሎጂን አላውቅም፣ ነገር ግን ብሩህ አዕምሮ ያላቸው ክርስቲያኖች ተሰብስበው ይሄንን እውን አድርገውታል።

መሰለ ቴክኖሎጂዎች ወጣቶችን ይበልጥ ወደ እግዚአብሔር እንዲቀርቡ እንደሚረዳቸውም ተነግሯል። አንድ ቀን በአዳኜ ኢየሱስ ክርስቶስ ፊት ቆሜ “ድግ አደረግኽ፣ አንተ መልካም አገልጋይ” መባልን እፈልጋለው ብሏል ፓስተር ሚካኤል ሊዲንግ ዘ ዌይ ላይ ባሰፈረው ጽሁፍ።

በኦቦሌሳ አዶላ

 #አሁን በተሰጠን ዕድል  #ምን እየሰራንበት ነው?   #ቤተክርስቲያን ሚዲያን በአግባቡ እየተጠቀመች ነውን ?  #ክርስቲያን የሚዲያ ባለሞያዎችስ የሚገጥማቸው ተግዳሮት ምንድነው? ይህንን ተግ...
17/10/2025

#አሁን በተሰጠን ዕድል #ምን እየሰራንበት ነው?

#ቤተክርስቲያን ሚዲያን በአግባቡ እየተጠቀመች ነውን ? #ክርስቲያን የሚዲያ ባለሞያዎችስ የሚገጥማቸው ተግዳሮት ምንድነው? ይህንን ተግዳሮት እንዴት በጋራ እንቅረፍ ?

ቴሌቪዥኖቻችን በሙሉ #ሚዲያ ናቸው ብለን አናምንም። ሚዲያ ዕድል ነው። በተሰጠን ዕድልስ ምን እየሰራንበት ነው?

The Christian News - የክርስቲያን ዜና GMM TV በሰጠን ዕድል እነዚህን ሁሉ ሃሳቦች እንሞግታለን። ክርስቲያናዊ በሃሪ ያላቸው ጋዜጠኞችን ለማፍራትም እንሰራለን።

ሊንኩን በመጠቀም በጥንቃቄ ከተመለከታችሁት በኋላ ሃሳባችሁን አካፍሉን!!!

GMM TV International : ጂ.ኤም.ኤም ( ዓለም አቀፍ የተአምራት አገልግሎት ) ቴሌቪዥንThe GMM TV International offers programs that are entertaining and educational, promoting a hea...

ቻይና 30 የፕሮቴስታንት ቤተ እምነት አባላትን አሰረች።ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ ብቻ በፓስተር ጂን ሚንግሪ ከሚመራው ከጽዮን ቤተክርስትያን ጋር ግንኙነት አላቸው የተባሉ 30 ክርስትያኖች ...
17/10/2025

ቻይና 30 የፕሮቴስታንት ቤተ እምነት አባላትን አሰረች።

ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ላይ ብቻ በፓስተር ጂን ሚንግሪ ከሚመራው ከጽዮን ቤተክርስትያን ጋር ግንኙነት አላቸው የተባሉ 30 ክርስትያኖች በቁጥጥር ሥር ውለዋል።

የቻይና መንግሥት በቤት ለቤት አምልኮ የሚታወቁት የክርስትያን ኅብረት አባላትን እያደኑ በቁጥጥር ሥር ማዋል መጀመራቸው እየተገለፀ ሲሆን በሀገሪቱ በኅቡዕ የሚንቀሰቀሱ ቤተ እምነቶችን የሚመለከት አዲስ ሕግ ማውጣቷን አክቲቪስቶች ይገልጻሉ።

ይህንንም ተከትሎ ከቅርብ ወራት ወዲህ በእነዚህ ቤተ ክርስትያን አባላት ላይ ከፍተኛ ጫና እየደረሰ መሆኑን አስታውቀዋል።

ቻይና ምንም እንኳን እምነት የለሽ በሆነ የኮሚኒስት ፓርቲ የምትመራ ቢሆንም ከፍተኛ ቁጥር ያለው የክርስትና እምነት ተከታይ ሕዝብ እንዳላት በቅርቡ የወጣ መረጃ ያሳያል።

በቅርቡ መንግሥት ይፋ ያደረገው አሃዝ እንደሚያሳየው በአገሪቱ ውስጥ 38 ሚሊዮን ፕሮቴስታንቶች እና 6 ሚሊዮን የሚጠጉ ካቶሊኮች እንደሚኖሩ ያሳያል።

ይህ ቁጥር ግን የሚያሳየው በይፋ ለቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ ታማኝነታቸውን ገልጸውና ተመዝግበው የሚንቀሳቀሱት ካቶሊክ ፓትሪዮት አሶሲየሺን እና ዘ ፕሮቴስታንት ስሪ ሰልፍ ፓትሪዮቲክ ሙቭመንት አባላት ብቻ ነው።

የመብት ተሟጋቾች እና ምሑራን አገሪቱ የምትመራባቸውን ርዕዮተ ዓለሞች የማይቀበሉ በአስር ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ያልተመዘገቡ ቤተ እምነቶች እና የቤት ለቤት ኅብረት በሚል የሚታወቁ ይኖራሉ ሲሉ ግምታቸውን ያስቀምጣሉ።

በርካታ እነዚህ ቤተ እምነቶች የቻይና መንግሥት በሃይማኖታዊ ቡድኖች ላይ የሚያደርገውን ቁጥጥር ለማጠናከር ለዓመታት በሚወስዳቸው እርምጃዎች የተለያየ ጉዳት ደርሶባቸዋል።
ከእነዚህም መካከል የቤተ ክርሰትያኖች ሕንጻዎች ፈራርሰዋል፤ መስቀሎች ከሕዝብ ዕይታ እንዲነሱ ተደርገዋል።

ሃይማኖታዊ መጻሕፍት እንዲሁም ሌሎች ቁሳቁሶች ከፍተኛ ቁጥጥር የሚደረግባቸው ሲሆን የተወሰኑ ክርስትያናዊ መተግበሪያዎች በቻይና እገዳ ተጥሎባቸዋል።

እንደ አውሮፓውያኑ በ2005 እና እንደገና በ2018 መንግሥት በሃይማኖት ቡድኖች ላይ ያሉትን መመሪያዎችን በማሻሻል ጥብቅ አድርጎታል።

እአአ በ 2016 ፣ የቻይና መሪ ዢ ጂንፒንግ የክርስትያን ሃይማኖት ተከታዮች "ወደ ቻይና ባሕል እንዲዋሃዱ" መጠየቃቸው የሚታወስ ነው።

ባለፈው አርብ እና ቅዳሜ በአገሪቱ 10 ከተሞች፣ ቤይጂንግ እና ሻንጋይን ጨምሮ በሃይማኖት ተቋማት ላይ ዘመቻዎች ማካሄዳቸውን ጀምረዋል።

በጓንግዚ ግዛት ውስጥ በሚገኘው ቤይሃይ ከተማ ከሚገኘው ዋና የአምልኮ ሥፍራቸው ከተወሰዱት ጂን በተጨማሪ ሌሎች ፓስተሮችን፣ አገልጋዮች እና ምዕመናን መታሰራቸውን ቤተክርስቲያኒቱ ገልጻለች።

ቢቢሲ በቤይሃይ የሕዝብ ደኅንነት ቢሮ ለጂን ይፋዊ የእስር ማዘዣ ያወጣውን ግልባጭ አግኝቻለሁ ያለ ሲሆን የተወሰኑ የታሰሩ የቤተ ክርስትያኑ አባላት የተለቀቁ ቢሆንም በርካቶቹ አሁንም በማረሚያ ቤት ይገኛሉ ሲል አስነብቧል።

ዝርዝር መረጃዎችን ለመመልከት የቴሌግራም ገፃችንን ይቀላቀሉ።

https://t.me/TCNEW

17/10/2025

#ዛሬ #በጣም የምወደው #እና እጅግ የማከብረውን እንዲሁም በጣም የማከብረውን የሕይወቴን ታላቅ ሞዴል አባቴን ዛሬ በክብር ከእናንተ ጋር እሸኘዋለሁ።

አባቴ 60 ዓመት አከባቢ ሰብኳል እኔ ወደ 30 ዓመት እያገለገልኩኝ ነው በቤታችን ወደ 100 አመት ገደማ ደርሷል።

አባቴ #አሁንእሩጫውን ጨርሷል።

ሙሉውን የክርስቲያን ዜና የዪቲዩብ ቻናል ላይ ይመልከቱ!!! https://www.youtube.com/channel/UCeHRJCDJ0wUDaBfAFmuMa7A...
゚viralシfypシ゚viralシ #እግዚአብሔር #ወጣት
#ወንጌል #ቤተክርስቲያን #የኢትዮጵያ #ሙሉ #ድንቅ
シ゚ ゚viralシ2024fyp ゚viralシfypシ゚viralシalシ viralシfypシ゚viralシalシ ゚viralシ

#ወንጌል #ቤተክርስቲያን #የኢትዮጵያ #ሙሉ #ድንቅ ゚viralシ2024fyp ゚viralシfypシ゚viralシalシ ゚viralシfypシ゚

Address

Addis Ababa
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when The Christian News - የክርስቲያን ዜና posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to The Christian News - የክርስቲያን ዜና:

Share