
08/07/2025
እህታችን ዘማሪት ፀዳለ አየለ ከዚህ አለም በሞት ተለይታ ወዳገለገለችው ጌታ ሄዳለች።
#ዜና እረፍቷን ተከትሎ የሀልዎት አማኑኤል ቤተክርስቲያን ሀዘኗን ገልጻለች።
ቤተክርስቲያኒቱ በመግለጫዋ እህታችን ዘማሪት ፀዳለ አየለ በሀልዎት አማኑኤል ኀብረት ቤተክርስቲያን አባል ሆና በሀርመኒ የመዘምራን ኀብረት ውስጥ እንዲሁም በሶሎ ዝማሬ ስታገለግል የቆየች የተወደደች እህት መሆኗን በመጥቀስ ወዳገለገለችው አምላኳ ሔዳለች፤ ወደ ዘላለማዊው እረፍቷ፤ ወደ ሰማዩ ቤቷ ገብታለች ሲሉ ተናግረዋል።
ቤተክርስቲያኒቱ በመግለጫው በእህታችን በስጋ ከእኛ መለየት ብናዝንም ሀዘናችን ግን ተስፋ እንደሌላቸው አይደለም። ከሞት ወዲያ ባለው ሕይወት ዳግመኛ እንደምንገናኝ ስለምናውቅ በሱ እንጽናናለን በማለት ለቡታጅራ ከተማ ምዕመናን መጋቢዎቿና አብራችኋት ስታገለግሉ ለነበራችሁ፣ ለሀልዎት አማኑኤል ኅብረት መዘምራን እንዲሁም ለቤተሰቦቿና ለጓደኞቿ መፅናናትን ተመኝታለች።
ነገር ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ተስፋ እንደሌላቸው እንደ ሌሎች ደግሞ እንዳታዝኑ፥ አንቀላፍተው ስላሉቱ ታውቁ ዘንድ እንወዳለን። …….. ከዚያም በኋላ እኛ ሕያዋን ሆነን የምንቀረው፥ ጌታን በአየር ለመቀበል ከእነርሱ ጋር በደመና እንነጠቃለን፤ እንዲሁም ሁልጊዜ ከጌታ ጋር እንሆናለን።
ስለዚህ እርስ በርሳችሁ በዚህ ቃል ተጽናኑ። (1 ተሰሎንቄ 4:13-18)
The Christian News - የክርስቲያን ዜና በእህታችን ህልፈት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለፅን ለወዳጅ ዘመዶቿ ለጓደኞቿ መፅናናትን እንመኛለን።
Halwot Emmanuel Church
ዝርዝር መረጃዎችን ለመመልከት የቴሌግራም ገፃችንን ይቀላቀሉ።
https://t.me/TCNEW