The Christian News - የክርስቲያን ዜና

The Christian News - የክርስቲያን ዜና በዚህ ቻናል ተዓማኒነት ያላቸው የክርስቲያን ዜናዎች እና መልዕክቶች ከመላው አለም ይደርሶታል።

The Christian News በተጨማሪም 60ሺህ ቤተሰቦች በyoutube እና ከ5ሺህ በላይ ቤተሰቦች በቴሌግራም ስላሉን አዳዲስ የሆናቹ ቤተሰብ እንድትሆኑ እንጋብዛችኋለን።

እህታችን ዘማሪት ፀዳለ አየለ ከዚህ አለም በሞት ተለይታ ወዳገለገለችው ጌታ ሄዳለች።   #ዜና እረፍቷን ተከትሎ የሀልዎት አማኑኤል ቤተክርስቲያን ሀዘኗን ገልጻለች። ቤተክርስቲያኒቱ በመግለጫዋ...
08/07/2025

እህታችን ዘማሪት ፀዳለ አየለ ከዚህ አለም በሞት ተለይታ ወዳገለገለችው ጌታ ሄዳለች።

#ዜና እረፍቷን ተከትሎ የሀልዎት አማኑኤል ቤተክርስቲያን ሀዘኗን ገልጻለች።

ቤተክርስቲያኒቱ በመግለጫዋ እህታችን ዘማሪት ፀዳለ አየለ በሀልዎት አማኑኤል ኀብረት ቤተክርስቲያን አባል ሆና በሀርመኒ የመዘምራን ኀብረት ውስጥ እንዲሁም በሶሎ ዝማሬ ስታገለግል የቆየች የተወደደች እህት መሆኗን በመጥቀስ ወዳገለገለችው አምላኳ ሔዳለች፤ ወደ ዘላለማዊው እረፍቷ፤ ወደ ሰማዩ ቤቷ ገብታለች ሲሉ ተናግረዋል።

ቤተክርስቲያኒቱ በመግለጫው በእህታችን በስጋ ከእኛ መለየት ብናዝንም ሀዘናችን ግን ተስፋ እንደሌላቸው አይደለም። ከሞት ወዲያ ባለው ሕይወት ዳግመኛ እንደምንገናኝ ስለምናውቅ በሱ እንጽናናለን በማለት ለቡታጅራ ከተማ ምዕመናን መጋቢዎቿና አብራችኋት ስታገለግሉ ለነበራችሁ፣ ለሀልዎት አማኑኤል ኅብረት መዘምራን እንዲሁም ለቤተሰቦቿና ለጓደኞቿ መፅናናትን ተመኝታለች።

ነገር ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ተስፋ እንደሌላቸው እንደ ሌሎች ደግሞ እንዳታዝኑ፥ አንቀላፍተው ስላሉቱ ታውቁ ዘንድ እንወዳለን። …….. ከዚያም በኋላ እኛ ሕያዋን ሆነን የምንቀረው፥ ጌታን በአየር ለመቀበል ከእነርሱ ጋር በደመና እንነጠቃለን፤ እንዲሁም ሁልጊዜ ከጌታ ጋር እንሆናለን።

ስለዚህ እርስ በርሳችሁ በዚህ ቃል ተጽናኑ። (1 ተሰሎንቄ 4:13-18)

The Christian News - የክርስቲያን ዜና በእህታችን ህልፈት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለፅን ለወዳጅ ዘመዶቿ ለጓደኞቿ መፅናናትን እንመኛለን።

Halwot Emmanuel Church

ዝርዝር መረጃዎችን ለመመልከት የቴሌግራም ገፃችንን ይቀላቀሉ።

https://t.me/TCNEW

 #የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን የሰብዓዊ ድጋፍና ልማት ኮሚሽን  #አዲስ የተሾሙት የቦርድ አባላትን የእንኳን ደህና መጣችሁ እና የእውቅና መረሃ ግብር አካሄደ። ኮሚሽኑ በመረሃ ግብ...
08/07/2025

#የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን የሰብዓዊ ድጋፍና ልማት ኮሚሽን #አዲስ የተሾሙት የቦርድ አባላትን የእንኳን ደህና መጣችሁ እና የእውቅና መረሃ ግብር አካሄደ።

ኮሚሽኑ በመረሃ ግብሩ በቦርድ አመራርነት እንዲሁም አባል ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩትን በማመስገን እውቅና የመስጠት መረሃ ግብር በቤተክርስቲያኒቱ ዋና ጽፈት ቤት አካሂዷል።

በመድረኩ የኮሚሽኑ የግማሽ ዓመት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት የቀርበ ሲሆን የቀጣይ አምስት ዓመት ስልታዊ እቅድ አሰራር በሚመለከት ከአዲሱ የቦርድ አባላት እና አመራር ጋር ሰፊ ውይይት ተደርጎል ።

እ.ኤ.አ በ2025 በግማሽ በጀት ዓመት ስራ ላይ የዋለው የገንዘብ መጠን 703.6 ሚሊየን ብር ሲሆን ከበጀት ዓመት እቅድ ጋር ሲነጻጸር 96.2% አሳይቷል፡፡ ይህ የበጀት አፈጻጸም ከ2024 በጀት ዓመት ተመሳሳይ ጊዜ ጋር ሲነጻጸር 250.8 ሚሊየን ብር(55.3 %) ብልጫ ማሳየቱን በቀረበው ሪፓርት ተጠቅሶል፡፡ በተሰሩ የሰብዓዊ ድጋፍ እና ልማት ስራዎችም 276 ሺ ሰዎችን በቀጥታ ተጠቃሚ መደረግ መቻሉ እንዲሁም ከዚህም ውስጥ የሴቶች ተሳትፎ 49 በመቶ መሆኑ ተጠቅሷል።

የውስጥ አሰራር ሂደቶችን አጠናክሮ ከማስቀጠል አዃያ ኮሚሽኑ በትጋት መስራቱን በመርሃ ግብሩ መድረክ ላይ ያነሱት የቀድሞ የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን የሰብዓዊ ድጋፍና ልማት ኮሚሽን የቦርድ ሰብሳቢ የአሁን የቤ/ክቱ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ስምዖን ሄሊሶ በአንድነት እና በጋራ በመሆን ብዙ ስራዎችን መስራት እንደሚቻል የተናገሩ ሲሆን #አዲስ ተሿሚ የቦርድ አመራሮች የስራ ቆይታቸው #መልካም እንዲሆን ምኞታቸውን ገልጸዋል።

ዶ/ር ስምዖን ሄሊሶ ጨምሮ ልማት ኮሚሽኑን ላገለገሉ አካላት የእውቅና ስጦታ የተበረከተላቸው ሲሆን የኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ዋና ጸሃፊ ዶ/ር ስምዖን ሙላት ጸሎት በማድረግ ዶ/ር ተስፋዬ ያዕቆብ የእግዚአብሔርን ቃል በማካፈል አገልግለዋል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የቤተክርስቲያኒቱ ዋና ጸሃፊ ዶ/ር ስምዖን ሙላት ፤ የኮሚሽኑ የቦርድ ሰብሳቢ ዶ/ር ዳንኤል ጫዕሜቦ ፤ የኮሚሽኑ ኮሚሽነር ዶ/ር ተፈራ ተሎሬን ጨምሮ የቦርድ አባላት፤ ፕሮግራም ዳይሬክተሮች እና የፕሮጀክት ስራ አስተባበሪዎች ተገኝተዋል።

ዘገባው የቤተክርስቲያኒቱ ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ነው።

መንፈሳዊ ተከታታይ ትምህርቶችን እና መልዕክቶችን ለመከታተል የቴሌግራም ገፃችንን ይቀላቀሉ።

https://t.me/TCNEW

የልቀት ምስጢር ተመርቋል። በፖስተር  #እና ዘማሪ ካሳሁን ለማ የተፃፈዉ እና "የልቀት ምስጢር" የተሰኘዉ መፅሐፍ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ሕብረት ፕሬዝዳንት መጋቢ ፃዲቁ አ...
07/07/2025

የልቀት ምስጢር ተመርቋል።

በፖስተር #እና ዘማሪ ካሳሁን ለማ የተፃፈዉ እና "የልቀት ምስጢር" የተሰኘዉ መፅሐፍ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ሕብረት ፕሬዝዳንት መጋቢ ፃዲቁ አብዶን ጨምሮ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና የፀሐፊዉ ወዳጆች በተገኙበት ተመርቋል።

የመፅሀፉ አዘጋጅ ፖስተር ካሳሁን በዚህ ልዩ የምስጋናና የራዕይ መካፈል ቀን ላይ ያለ ልዩ ጥሪ ወዳጅነትና የክርስቶስን ፍቅር ልታሳዩን የተገኛችሁና ከደስታችንና ከራዕያችን ጋር የቆሙትን ሁሉ አመስግኗል።

The Christian News - የክርስቲያን ዜና ለመፅሀፉ አዘጋጅ ለፖስተር ካሳሁን እና ቤተሰቡ #እንኳን ደስ አለህ እያልን የተሰማንን ደስታ እንገልፃለን።

ዝርዝር መረጃዎችን ለመመልከት የቴሌግራም ገፃችንን ይቀላቀሉ።

https://t.me/TCNEW

21ኛው የክርስቲያን ሴቶች ኮንፈረንስ በቤዛ ኢንተርናሽናል ቤተክርስቲያን ተካሄደ።"አንቺን ለፅድቅ" በሚል በተዘጋጀው በዚህ መርሀ ግብር የፀሎት የትምህርትና የአንድነት ጊዜም ተደርጓል። ከሰኔ...
07/07/2025

21ኛው የክርስቲያን ሴቶች ኮንፈረንስ በቤዛ ኢንተርናሽናል ቤተክርስቲያን ተካሄደ።

"አንቺን ለፅድቅ" በሚል በተዘጋጀው በዚህ መርሀ ግብር የፀሎት የትምህርትና የአንድነት ጊዜም ተደርጓል። ከሰኔ 24 እስከ 27 2017 ዓ.ም በተካሄደው በዚህ ጉባኤም ከተለያዩ ከባህር ማዶ እና ከሀገር ውስጥ የመጡ አገልጋይ እና ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።

#ይህ የሴቶች ጉባኤ ከተጀመረ ሁለት አስርት ዓመታት በላይ ያስቆጠረ ሲሆን ቀደም ሲል በሰሜን #አሜሪካ ፣ በካናዳና በአውሮፓ ሲካሄድም ቆይቷል።

አገልጋይ ሶፊያ አሰፋ እንደገለፁትም ከተለያዩ የአሜሪካ እስቴት እህቶች ተሳታፊ መሆናቸውን በመግለፅ ሁሉም በቅድስና መመላለስ እንደሚገባም መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

በሌላ በኩል ፓስተር ህሊና ግርማ የነበረው የአንድነት ጊዜ #መልካም መሆኑን በመግለፅ ኮንፈረንሱ እህቶች የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡም ማድረጉን ገልፀዋል።

በእለቱም በኪንግደም ሳውንድ የዝማሬና የጋራ የአንድነት ጊዜ የተካሄደም ሲሆን የኢትዮጵያ ኢቫንጄሊካል ቤተክርስቲያን አገልጋይ የሆኑት ዶክተር ትሁት አስፋው በእግዚአብሔር ቃል አገልግለዋል። በመልዕክታቸውም ሁሉም በተሰጠው ፀጋ አገልግሎቱ እንደሚቀጥልም በመግለፅ ይህም አገልግሎት ከትውልድ ትውልድ እንደሚሻገርም ገልፀዋል።

ከዚሁ ጋር ተያይዞም ሁሉም አማኝ በተሰማራበት ሁሉ በትክክልኛ ክርስቲያናዊ አሰራር መስራት እና ማገልገል እንዳለባቸውም ገልፀዋል። ማንኛውም ክርስቲያን አዎንታዊ ተፅዕኖዎችን ማስተጋባት እና ማሻገር እንደሚችል እና ይህንንም ለማድረግ በቅድስና መመላለስ እንደሚገባም በትምህርቱ ወቅት ተወስቷል።

መረጃው የGMM TV Ethiopia ነው።
ሰኔ 30/2017ዓ.ም
#አዲስ አበባ

ዝርዝር መረጃዎችን ለመመልከት የቴሌግራም ገፃችንን ይቀላቀሉ።
https://t.me/TCNEW

"አውነት እና ፍቅር" የተሰኘው ትያትር ተመረቀ።በትላንትናው እለት ሰኔ 29/2017 ዓ.ም በፕሮቪዥን ፈልሞች የተዘጋጀው እና "አውነት እና ፍቅር" የተሰኘው በኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች ዘንድ...
07/07/2025

"አውነት እና ፍቅር" የተሰኘው ትያትር ተመረቀ።

በትላንትናው እለት ሰኔ 29/2017 ዓ.ም በፕሮቪዥን ፈልሞች የተዘጋጀው እና "አውነት እና ፍቅር" የተሰኘው በኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች ዘንድ የመጀመሪያው የሆነው ትያትር በቫምዱስ ሲኒማ የአብያተ ክርስቲያናት መሪዎች ፤ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት በድምቀት ተመርቆ ለእይታ ቀርቧል።

የትያትሩ ደራሲና ደይሬክተር ሄኖክ በቀለ “በኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች ዘንድ እንደዚህ አይነት ስራ አልተለመደም” ያሉ ሲሆን #ይህ የመጀመሪያ ቢሆንም ከዚህ በኋላ ብዙ ስራዎችን በትያትር መልኩ ለመስራት እንዳቀዱ ተናግረዋል።

#እውነት እና #ፍቅር የሚያጠነጥነው አውነትን በቀጥታ መናገርና ፍቅርን መስጠት ላይ የሚያተኩር ሆኖ በሁለት መሃል ያለውን ውዝግብ የሚያሳይ እንደሆነ ደራሲው ገልጿል።

ፕሮቪዥን ፈልሞች ላለፉት ሁለት ዓመታት በጂዶ-ክርስቲያናዊ የሥነ-ምግባር ዕሴት ላይ ታንጾ በጥበብ ዘርፍ እየሠራ የሚገኝ ድርጅት ሲሆን ፕሮቪዥን ፊልሞች የተቋቋመው በኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተክርስቲያናት ህብረት አባል ከሆኑ ቤተ ዕምነት የተወጣጡ የትያትር ፣ የሚድያ #እና የፊልም ባለሙያዎች መሆኑ ተገልጿል።

ትያትሩ 55 ደቃቅ ርዝመት የለው ሲሆን በዚህ ትያትር ላይ 4 ዋና ዋና ተዋናዮችና በረካታ ሰዎች በስራው ላይ ተሳትፈዋል። በትያትሩ ላይ ለተሳተፉት በሙሉ የእውቅና ሰርተፍኬት የተሰጣቸው ሲሆ በቀጣይም በየሳምንቱ በሻምዱስ ሲኒማ የምታይ መሆኑ ተገልጿል።

ሰኔ 30/2017ዓ.ም
#አዲስ አበባ

ዝርዝር መረጃዎችን ለመመልከት የቴሌግራም ገፃችንን ይቀላቀሉ።

https://t.me/TCNEW

የምስራቅ ጉጂ መሠረተ  #ክርስቶስ ኮሌጅ በታሪኩ የመጀመሪያ ተማሪዎቹን አስመረቀ።በመሠረተ ክርስቶስ ሴሚነሪ የምስራቅ ጉጂ ስነ-መለኮት ኮሌጅ ዛሬ ሰኔ 29/2017 ዓ.ም በሻኪሶ ከተማ ተማሪዎ...
06/07/2025

የምስራቅ ጉጂ መሠረተ #ክርስቶስ ኮሌጅ በታሪኩ የመጀመሪያ ተማሪዎቹን አስመረቀ።

በመሠረተ ክርስቶስ ሴሚነሪ የምስራቅ ጉጂ ስነ-መለኮት ኮሌጅ ዛሬ ሰኔ 29/2017 ዓ.ም በሻኪሶ ከተማ ተማሪዎቹን አስመርቋል።

በመሠረተ ክርስቶስ ቤ/ክ የምስራቅ ጉጂ ጊዜያዊ ክልል ስር የሚገኘው ኮሌጁ በዲግሪ መርሐግብር ያስተማራቸውን 14 ተማሪዎች ነው ለመጀመሪያ ጊዜ ያስመረቀው።

በምረቃ ፕሮራሙ ላይ የተገኙት በመሠረተ ክርስቶስ ሴሚናሪ የክልል ካምፓሶች ተጠሪ መምህር ታደሰ በዬቻ የእግዚአብሔር ቃል ከማቅረብ ባለፈ ባደረጉት ንግግር "በድግሪ መመረቅ ማለት ከሳሎን ወደ ግቢ መውጣት ነው ሩቅ የሄዳችሁ እንዳይመስላችሁ ስለዚህ መማራችሁን ቀጥሉ" ብለዋል።

የምስራቅ ጉጂ ጊዜያዊ ክልል ዋና ጸሐፊ መጋቢ ትዕግስቱም "ተመራቂዎች የክልሉ እድገት ማሳያና የመጀመሪያዎቹ ታሪካዊ ምሩቃን በመሆናችሁ #እንኳን ደስ አላችሁ" ሲሉ ተናግረዋል።

ተመራቂዎችም የመጀመሪያ ተመራቂዎች በመሆናቸው መደሰታቸውን ገልጸዋል። በፕሮግራሙ በትምህርታቸው ከፍተኛ ውጤት ላመጡ ተማሪዎች ሽልማት ተበርክቷል።

የመሠረተ ክርስቶስ ሴሚናሪ በአሁን ሰዓት 815 ተማሪዎችን በመያዝ በሀገሪቱ በሚገኙ 23 ካምፓሶች ትምህርት በመስጠት ላይ ይገኛል።

ምንጭ:- Meserete Kristos Church - Head Office
ሰኔ 29/2017ዓ.ም
ሻኪሶ

የኑዌር ክርስትያን ወጣቶች ለሰላምና ልማት መንፈሳዊ የሰላም ኮንፈረንስ በኑዌር ዞን ላሬ ወረዳ አካሄዱ።ከሁሉም የኑዌር ዞን ወረዳዎችና ከጋምቤላ ከተማ የተውጣጡ ወጣቶች የተለያዩ ዝማሬዎችን የ...
06/07/2025

የኑዌር ክርስትያን ወጣቶች ለሰላምና ልማት መንፈሳዊ የሰላም ኮንፈረንስ በኑዌር ዞን ላሬ ወረዳ አካሄዱ።

ከሁሉም የኑዌር ዞን ወረዳዎችና ከጋምቤላ ከተማ የተውጣጡ ወጣቶች የተለያዩ ዝማሬዎችን የፀሎት ፕሮግራም በማድረግ መንፈሳዊ የሰላም ኮንፈረንስ በላሬ ወረዳ አካሂደዋል።

ኮንፈረንሱ በክርስቲያኑ ማኅበረሰብ ውስጥ ጠቃሚ የሆኑ የልማት ውጥኖችን በማስፋፋት መግባባትንና የእርስበርስ ግንኙነትን ለማዳበር ያለመ እንደሆነም ተጠቁመዋል።

ለዘላቂ ዕድገት የትብብር መንፈስን በማጎልበት የሰላም ግንባታ ስትራቴጂ ላይ ግንዛቤዎችን ለመለዋወጥ የወጣቶች እና የማህበረሰብ ሚና ከፍተኛ ነው ተብሏል።

የኑዌር ክርስቲያን ሚሲዮን ኔትወርክ ዳይሬክተር አቶ ቡአይ ቾል ያት በጋምቤላ ክልል ብቻ ሳይሆን በአለም አቀፍ ደረጃም ፕሮግራሙን በማካሄድ አንድነትንና ወንድማማችነትን እያጠናከረ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

ክርስቲያን ወጣቶች ሰላምን፣ ስምምነትን እና ልማትን በማስቀደም የድርሻቸውን ሊወጡ እንደሚገባም አቶ ቡአይ ቾል አሳስበዋል።

እነዚህ እሴቶችን በማሳደግ ማህበረሰቡ ለሰላምና ለልማት ይበልጥ እንዲነሳሳ ወጣቶች በመንፈሳዊ ፕሮግራሞች ላይ በመገኘት መግባባትን ፣ አንድነትና ፍቅርን ለማጠናከር እያከናወኑት ላለው ተግባራትም አመስግነዋል።

የኑዌር ክርስቲያን ሚሲዮን ኔትወርክ ሊቀ መንበር ቄስ ፖል ሮት እንደገለፁት ወጣቶች አንድነትና ዘላቂ ሰላም ለማረጋገጥ እየተደረገ ባለው ጥረት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከቱ እንደሚገኙ ገልፀዋል።

በክርስቲያን ቤተሰብ ውስጥ መረጋጋትና የአንድነት አስፈላጊነት በማጉላት አብረው ዘላቂ ሰላም ማምጣትና በተለያዩ የልማት ስራዎች ላይም ንቁ ተሳታፊ መሆን እንደሚያስፈልግም ቄስ ፖል መልዕክት አስተላልፈዋል።

በደም እጦት ምክንያት የሚያልፈውን የሰው ህይወት ለመታደግ የደም ልገሳ መርሃ ግብር መከናወኑን ለThe Christian News - የክርስቲያን ዜና በተላከልን መረጃ ተጠቂሟል።

መንፈሳዊ ተከታታይ ትምህርቶችን እና መልዕክቶችን ለመከታተል የቴሌግራም ገፃችንን ይቀላቀሉ።

https://t.me/TCNEW

 #በቁጥር 31 ሰዎች ለወንጌል አገልግሎት የደቀመዛሙርት ትምህርት ተከታትሎ ወደ አገልግሎት ደረሱ። #ክብር ምስጋና ለሥራው ባለቤት ለኢየሱስ ክርስቶስ ይሁን ከእኔ ጋር ጌታን አመስግኑት   #...
06/07/2025

#በቁጥር 31 ሰዎች ለወንጌል አገልግሎት የደቀመዛሙርት ትምህርት ተከታትሎ ወደ አገልግሎት ደረሱ።

#ክብር ምስጋና ለሥራው ባለቤት ለኢየሱስ ክርስቶስ ይሁን ከእኔ ጋር ጌታን አመስግኑት

#በኢትዮጵያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ምዕራብ ደቡብ ቀጣና ቦንጋ ዙሪያ ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ሕብረት የቦባ ገጫ ቃ/ሕ/ቤተክርስቲያን በተከታታይ በቤተክርስቲያን የሚሰጠውን የአገልግሎት እና የደቀመዛሙርት ትምህርት የተማሩትን በማስመረቅ እንዲያገለግሉ በቃለ #እግዚአብሔር አስታጠቀች።

በቦባ ገጫ እናት አጥቢያ ሥር የሚገኙት ሁለቱ ተከላዎች ማለትም "የገባ ተከላ ቃ/ሕ/ቤተክርስቲያን የድክ ተከላ ቃ/ሕ/ቤተክርስቲያን የሚገኙት የደቀመዛሙርት ትምህርት የተከታተሉት የተዘጋጀውን ሰርቲፕኬት በመውሰድ በጉባኤ ፊት ማለትም በሦስቱ ቤተክርስቲያን ስብስብ አንድነት ለማገልገል ቃል ኪዳን በመግባት ተመረቁ።

ሰዎችን ሁሉ የእውነተኛ የክርስቶስ ደቀመዛሙርት የማድረግ አገልግሎት ይልቁንም የሚያስፈልግበት ዘመን ይህ ነው ምክንያቱም ብዙ ነገሮች በዘመናችን ቤተክርስቲያን እየተከሰቱ ነው ኢ-መጽሐፍ ቅዱሳዊ ሰነ-ስርዓት ወደ ገሃድ የወጣበት ዘመን ላይ ነን ስለዚህ ትውልድን በቃለ እግዚአብሔር እናስታጥቅ።

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰጠውን ታላቁን ተልዕኮ ማስቀጠል አለብን ተልዕኮም የምፈጸመው፦ በመሄድ ወንጌልን በመስበክ ያመኑትን የክርስቶስ ደቀመዛሙርት ማድረግ ነውና እናስቀጥል።

“እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ።”
— ማቴዎስ 28፥19-20

የክርስቶስ ወንጌል ከትውልድ ወደ ትውልድ ይቀጥላል ኢየሱስ ክርስቶስ ያድናል ።

✍️ሚሽነሪ አክሊሉ ነኝ ከካፋ ዞን ዴቻ ወረዳ

 #ደረሰ  #ደረሰ በክረምት መረሃ ግብር ለጋዜጠኝነት ስልጠና ፈላጊዎች (ክርስቲያኖች)መሰረታዊ የጋዜጠኝነት ስልጠና ተዘጋጅቶላችኋል።ስልጠናውን የሚያተኩርባቸው 1. ተግባቦት (Communicat...
06/07/2025

#ደረሰ #ደረሰ

በክረምት መረሃ ግብር ለጋዜጠኝነት ስልጠና ፈላጊዎች (ክርስቲያኖች)

መሰረታዊ የጋዜጠኝነት ስልጠና ተዘጋጅቶላችኋል።

ስልጠናውን የሚያተኩርባቸው

1. ተግባቦት (Communication)
2. ጋዜጠኝነት ( Journalism )
3. ዜና (NEWS)
4. መጣጥፍ እና ስነ ጽሁፍ (Feature Article & Literature)
5. የሚድያ ስነ ምግባር (Media Ethics)
6. ዲጂታል ሚድያ (Digital Media)
7. ፕሮዳክሽን (Production)
8. ዘጋቢ ፊልምና ቃለ መጠይቅ (Documentary and Interview)

ከሃምሌ 5 - ነሃሴ 25/2017 ዓ.ም

ቦታ፡ #አዲስ አበባ #እና ሀዋሳ

(5ኪሎ መ/ኢየሱስ) (ሞቢል ሕይወት ብርሃን ቤ/ክ)

አዘጋጆች;- የደስ ደስ መልቲ ሚዲያ ፤ ቲኪቆስ ሚዲያ እና የክርስቲያን ዜና በጋራ በመሆን

ለተጨማሪ መረጃ፦
0911454205
0911891822

ለመመዝገብ Scan ያድርጉ አልያም ሊንኩን ተጠቅመው መመዝገብ ይችላሉ።

https://docs.google.com/forms/d/1NvZVALpBBjeOQgkv4gzSRzrVS6Ra_h47F24K1E250Z0/edit

የባለትዳሮች  #ቀን በትላንትናው እለት ተግባቦት ለላቀ ጥምረት በሚል ለ5ኛ ጊዜ  በሀልዎት አማኑኤል ህብረት ቤተክርስቲያን የባለትዳሮች አመታዊ የአንድነት በዓል ተከብሮ ውሏል ከ200 በላይ ...
06/07/2025

የባለትዳሮች #ቀን
በትላንትናው እለት ተግባቦት ለላቀ ጥምረት በሚል ለ5ኛ ጊዜ በሀልዎት አማኑኤል ህብረት ቤተክርስቲያን የባለትዳሮች አመታዊ የአንድነት በዓል ተከብሮ ውሏል ከ200 በላይ ባለርዳሮች የተገኙ ሲሆን #መልካም የህብረት ጊዜ ተከናውኗል።

የኬንያ ፕሬዚዳንት በቤተ መንግሥታቸው ትልቅ ቤተ ክርስቲያን ሊገነቡ ነው።የኬንያ ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶ ናይሮቢ በሚገኘው ቤተ መንግሥታቸው ትልቅ ቤተ ክርስቲያን ሊገነቡ እንደሆነ አሳወቁ።ሩቶ...
05/07/2025

የኬንያ ፕሬዚዳንት በቤተ መንግሥታቸው ትልቅ ቤተ ክርስቲያን ሊገነቡ ነው።

የኬንያ ፕሬዚዳንት ዊልያም ሩቶ ናይሮቢ በሚገኘው ቤተ መንግሥታቸው ትልቅ ቤተ ክርስቲያን ሊገነቡ እንደሆነ አሳወቁ።

ሩቶ ለቤተ ክርስቲያኑ ግንባታ ራሳቸው ወጪያቸውን እንደሚሸፍኑ ገልጸው የማንም ፈቃድ እንደማያስፈልጋቸው አጽንኦት ሰጥተዋል።
"ቤተክርስቲያን ለመገንባት የማንም ይሁንታ አያስፈልገኝም።

ሰይጣንን ሊያበሳጨው ይችላል እናም የፈለገውን ማድረግ ይችላል" ሲሉ ሩቶ አርብ ዕለት ተናግረዋል።

የፕሬዚዳንቱ ንግግር በሳቸው አመራር የቤተ ክርስቲያንን እና የመንግሥት በጽኑ መጣመር ቀድሞውኑ የሚተቹት ኬንያውያንን አበሳጭቷል።

ቢቢሲ የኬንያ መንግሥትን አስተያየት እንዲሰጠው ጠይቋል።
ሩቶ ስቴት ሃውስ በተሰኘው ቤተ መንግሥታቸው በሰጡት አስተያየት "ሰይጣን" ብለው የጠሩት አካል ማን እንደሆነ ግልጽ ባይሆንም የቤተ ክርስቲያኑን ፕሮጀክት ከመቀጠል የሚያግዳቸው ምንም ነገር እንደሌለ ገልጸዋል።

"ይህንን ቤተ ክርስቲያን መገንባት የጀመርኩት ወደ ቤተ መንግሥት ስገባ አይደለም። እዚሁ በቆርቆሮ የተሰራ ቤተ ክርስቲያን አገኘሁ። ይህ ለቤተ መንግሥቱ የሚመጥን ይመስላችኋል?" ሲሉ አርብ ዕለት ከፖለቲከኞች ጋር በነበራቸው ስብሰባ ላይ ተናግረዋል።

አርብ ዕለት ከኬንያ ታዋቂ ከሆኑት ጋዜጦች አንዱ የሆነው ዴይሊ ኔሽን 8 ሺህ ሰዎችን የሚይዝ ትልቅ ህንጻ የሚያሳይ ዲዛይን አትሟል።

ጋዜጣው፤ ይህ ፕሮጀክት መንግሥትና ሃይማኖት የተነጣጠለ ነው የሚለውን የኬንያ ሕገ መንግሥት የሚያከብር ነው ወይ? የሚል ጥያቄን አቅርቧል።

በርካታ ኬንያውያን በዋጋ ግሽበት እና በኑሮ ውድነት እየተፈተኑ ባለበት በዚህ ወቅት 9 ሚሊዮን ዶላር እንደሚያስወጣ የተገመተው ይህ ቤተ ክርስቲያን ትችቶችን እያስተናገደ ነው።

ሩቶ የቤተክርስቲያኑን ወጪ ከኪሳቸው እከፍላለሁ ቢሉም በሕዝብ ንብረት ላይ ይህን ያህል ትልቅ መዋቅር የመገንባት አቅም አላቸው ወይ የሚል ጥያቄ አጭሯል።

የኬንያ ኢ-አማኒያን ማህበር የቤተ ክርስቲያኑን ግንባታ አስደንጋጭ እና ተቀባይነት የሌለው እንደሆነ ገልጾ ሕጋዊ እርምጃ እንደሚወስድ አስጠንቅቋል።

"ይህ ድርጊት ጸረ ዲሞክራሲያዊ፤ እንዲሁም ፕሬዚዳንት ሩቶ ክርስቲያናዊ አርበኝነትን የማነሳሳት ተግባር አድርገን ነው የምንመለከተው። ኬንያ የክርስቲያኖች አገር ብቻ እንዳልሆነች ልናሳስባቸው እንፈልጋለን" ሲሉ የማህበሩ ኃላፊ ሐሪሰን ሙሚያ አጽንኦት ሰጥተዋል፥

ዊልያም ሩቶ የመጀመሪያው የኢቫንጀሊካል ክርስትና ተከታይ ፕሬዚዳንት ሲሆኑ በአንዳንዶችም ዘንድ "የእየሱስ ምክትል" የሚል ቅጽል ስም አትርፈዋል።

ሩቶ በሥልጣን ላይ በቆዩባቸው ዓመታት ከመጽሃፍ ቅዱስ ጥቅሶች በመምዘዝ በአደባባይ ሲያለቅሱ ታይተዋል። ይህም ባህርያቸው የሳቸውን እምነት የማይከተሉ ኬንያውያንን ያገለለ ሆኖ ታይቷል።

ሩቶ ምክትል ፕሬዚዳንት በነበሩበት ወቅት ከረን በሚገኘው መኖሪያቸው ውስጥ ቤተ ክርስቲያን አቁመው የተለያዩ ዕምነት ያላቸውን የሃይማኖት መሪዎችን ለማስተናገድ ይጠቀሙበት ነበር።

በኬንያ 85 በመቶ የሚሆነው ሕዝብ የክርስትና እምነት ተከታይ ሲሆን፣ 11 በመቶ ገደማ ሙስሊሞች እንዲሁም ሂንዱይዝም እና ባህላዊ እምነት ተከታዮች አሉ።

💍 ለተጋቡ ጥንዶች ብቻ!ተመዝግበዋልን?ትዳራችንን ቆም ብለን ለማጤን ጊዜው አሁን ነው። እኛ ባለትዳሮች ስለትዳራችን እና ልጆቻችን ቁጭ ብለን የምንመክርበት ልዩ ቀናት፣🛖 የልብ ልባችንን የምን...
04/07/2025

💍 ለተጋቡ ጥንዶች ብቻ!

ተመዝግበዋልን?

ትዳራችንን ቆም ብለን ለማጤን ጊዜው አሁን ነው። እኛ ባለትዳሮች ስለትዳራችን እና ልጆቻችን ቁጭ ብለን የምንመክርበት ልዩ ቀናት፣

🛖 የልብ ልባችንን የምንጨዋወትበት ፣ አንድነታችን የሚጠናከርበት እና ቃልኪዳናችንን የምናድስበት እድል፣

💬 ተግባቦታችንን የምንቃኝበት፣ የተሰበረ ልባችን የሚፈወስበት፣ መሰረታችን የሚጠናከርበት፣

👨‍👩‍👧 ልጆችን ለማሳደግ በዓላማ የምንታጠቅበት ፣ በአንድ ልብ ለማሳደግ የሚያስችል እሳቤ የምንሸምትበት
የቀረን ቦታ ለ4 ጥንዶች ብቻ ነው።

ዛሬውኑ ይመዝገቡ! ከጥቂቶቹ መካከል ለመሆን ይወስኑ!
ቀን፦ ከሐምሌ 5-26 ቅዳሜ ፣ ቅዳሜ ከ8:00-12:00
ቦታ:- የቀድሞው ኢምፔሪያል ውሃ ልማት አካባቢ በጨጨሆ ገባ ብሎ

ለመመዝገብ በ0911136520/0946693468 ይደውሉ!
📣 ቦታ አነስተኛ ነው—ለ4 ጥንዶች ብቻ!
ለትዳሬ ስምረት ምንስ ብከፍልለት!

ስለትምህርቶቻችን ለማወቅ፦
https://t.me/+LZGZsvB8OWA0OTFk

Address

Addis Ababa
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when The Christian News - የክርስቲያን ዜና posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to The Christian News - የክርስቲያን ዜና:

Share