The Christian News - የክርስቲያን ዜና

The Christian News - የክርስቲያን ዜና በዚህ ቻናል ተዓማኒነት ያላቸው የክርስቲያን ዜናዎች እና መልዕክቶች ከመላው አለም ይደርሶታል።

The Christian News በተጨማሪም 60ሺህ ቤተሰቦች በyoutube እና ከ5ሺህ በላይ ቤተሰቦች በቴሌግራም ስላሉን አዳዲስ የሆናቹ ቤተሰብ እንድትሆኑ እንጋብዛችኋለን።

 #እንኳን  #ደስ አልዎት ቄስ ደረጀ ጀምበሩ የክብር ዶክትሬት ተበረከተላቸው። የሊድስታር ክርስቲያን ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያስተማራቸውን ከ1500 በላይ ተማሪዎች በዛሬዉ እ...
30/08/2025

#እንኳን #ደስ አልዎት

ቄስ ደረጀ ጀምበሩ የክብር ዶክትሬት ተበረከተላቸው።

የሊድስታር ክርስቲያን ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የትምህርት ዘርፎች ያስተማራቸውን ከ1500 በላይ ተማሪዎች በዛሬዉ እለት አስመርቋል።

በእለቱ ዩኒቨርሲቲው ለኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካዉንስል ጠቅላይ ፀሐፊ ቄስ ደረጀ ጀምበሩ የክብር ዶክትሬት አበርክቷል።

The Christian News - የክርስቲያን ዜና የተሰማንን ደስታ እንገልፃለን።

በመጨረሻም በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው ዝማሬ ተለቀቀ !!! ላይክ ሼር ሰብስክራይብ ኮሜንት በማድረግ ብዙዎች እንዲባረኩበት እናድርግ!!!
29/08/2025

በመጨረሻም በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው ዝማሬ ተለቀቀ !!! ላይክ ሼር ሰብስክራይብ ኮሜንት በማድረግ ብዙዎች እንዲባረኩበት እናድርግ!!!

Alfa Neh Omega From The Album Alpha Neh Omega - New Gospel SongORIGINAL SONG

29/08/2025

ግብረሰዶማዊነትን #እና ጾታ መቀየር የመሳሰሉ የሀጢያት ዋና መገለጫዎችን በጽኑ እንቃወማለን!

#ከኢትዮጵያ #ሙሉ #ወንጌል አማኞች #ቤተክርስቲያን #በወቅታዊ ጉዳይ ላይ የተሰጠ መግለጫ።

#እግዚአብሔር #ወጣት
#ወንጌል #ቤተክርስቲያን #የኢትዮጵያ #ሙሉ #ድንቅ


シ゚ ゚viralシ2024fyp ゚viralシfypシ゚viralシalシ viralシfypシ゚viralシalシ ゚viralシ

#ወንጌል #ቤተክርስቲያን #የኢትዮጵያ #ሙሉ #ድንቅ ゚viralシ2024fyp ゚viralシfypシ゚viralシalシ ゚viralシfypシ゚

በሃይማኖት ጉዳይ የሚደረጉ መበሻሸቆች ለሃገር ሰላም አስጊ በመሆናቸው ሊቆሙ ይገባል ሲሉ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ሕብረት ፕሬዚዳንት ፓስተር ጻድቁ አብዶ ገለጹ፡፡ፓስተር ጻ...
28/08/2025

በሃይማኖት ጉዳይ የሚደረጉ መበሻሸቆች ለሃገር ሰላም አስጊ በመሆናቸው ሊቆሙ ይገባል ሲሉ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት ሕብረት ፕሬዚዳንት ፓስተር ጻድቁ አብዶ ገለጹ፡፡

ፓስተር ጻድቁ አብዶ ለጋዜጣ ፕላስ እንደገለፁት፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የአንድ ሃይማኖት ተከታዮች የሌላውን ሃይማኖት ተገቢ ባልሆነ መንገድ የማጥላላት ስራዎች በስፋት እየተስተዋለ ይገኛል።

#ይህ የሚደረገው #ግን በአንድ አንድ ግለሰቦች እንጂ ሃይማኖታቸውን ጠንቅቀው በሚያውቁ አባቶች አይደለም ብለዋል።

በሃይማኖት ጉዳይ የሚደረጉ መበሻሸቆች በተለይም በማህበራዊ ሚዲያው እየተስፋፋ መጥቷል ያሉት ፓስተር ጻድቁ፤ ይህን ለማስቀረትም በሃይማኖት ጉባኤ ውይይት መደረጉን ገልጸዋል።

#ማህበራዊ ሚዲያዎችንም ከመጥፎ ነገር ይልቅ ለመልካም ተግባር መጠቀም አስፈላጊ መሆኑን ገልፀዋል።

በዚህ መጥፎ ተግባር የሚሳተፉ አካላትን የሁሉም ሃይማኖት አባቶች ማስተማር ይገባል ብለው፤ በህግም የሚጠየቁበት ሂደት ስላለ እሱን ተግባራዊ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል።

በዳግማዊት አበበ

ምንጭ
#ኢትዮጵያ

ዝርዝር መረጃዎችን ለመመልከት የቴሌግራም ገፃችንን ይቀላቀሉ።

https://t.me/TCNEW

 በተመድ ድጋፍ የሚደረግለት እና እስከ 10 አመት ድረስ የሚደርሱ ልጆችን ስለ ወሲብ አደራረግ የሚያስተምር ፕሮግራም እንዳለ ያውቃሉ።የቤተሰብ እና ሰብዓዊ መብት ማዕከል የተሰኘ አለም አቀፍ ...
28/08/2025



በተመድ ድጋፍ የሚደረግለት እና እስከ 10 አመት ድረስ የሚደርሱ ልጆችን ስለ ወሲብ አደራረግ የሚያስተምር ፕሮግራም እንዳለ ያውቃሉ።

የቤተሰብ እና ሰብዓዊ መብት ማዕከል የተሰኘ አለም አቀፍ የሃሳብ ቋት (Think Tank) “UNICEF: Attack on the world’s children” ወይም “በዩኒሴፍ በአለም ህጻናት ላይ የተከፈተ ጥቃት” ሲል ባወጣው ባለ 21 ገጽ ጽሁፍ ሁኔታውን አትቷል።

ዩኒሴፍ በህጻናት ላይ የስነ ወሲብ ርዕዮተ አለም እየጫነ ነው ይላል ሪፖርቱ። ግልጽ በሆነ መንገድ የግብረሰዶም እና ለልጆች ልቅ የሆኑ የግብረስጋ ግንኙነት ጉዳዮችን በፕሮግራሞቹ ይዟል።

ለአብነት በዩክሬን ለሚገኙ የአፍላ እድሜ እና ቅድመ አፍላ እድሜ የሚገኙ ህጻናት “አጠቃላይ የስነ ወሲብ ትምህርት” ወይም comprehensive sexuality education የተሰኘ ትምህርትን እየሰጠ ይገኛል። በትምህርቱ አፍላ እድሜ ላይ ያሉ ህጻናት በፊንጢጣ የሚደረግ ግንኙነት፣ ራስን በራስ ማርካት፣ የፈለጉትን ጾታ መውደድ ተፈጥሮዋዊ መሆኑን እና ከትዳር በፊት ከአጋራቸው ጋር ወሲባዊ ጉዳዮችን መወያየትን እስከ 10 አመት ለሚደርሱ ልጆች እያስተማረ ይገኛል።

በተጨማሪ ዩኒሴፍ “ላሃ” የተሰኘ ዲጂታል ፕላትፎርም በማዘጋጀት ሴት ልጆች ያለ ቤተሰብ እውቅና፣ ማግኘት የሚችሉት እራሳቸውን እንዴት ለወሲብ ማዘጋጀት እንዳለባቸው ያስተምራል። ሌላው CSE ከግምት ያላስገባው እና የሚተችበት ደግሞ የፖርኖግራፊን ጉዳት አይዳስስም።

ከ500 በላይ ባለሙያዎች ከ26 በላይ ሃገራት በጋራ በመሆን ለዩኒሴፍ ደብዳቤ ጽፈዋል። አሁን ጉዳዩ በተለይ እንደ አፍሪካ ባሉ ደካማ ኢኮኖሚ ያላቸው ሃገራት ላይ ጫና በማሳደር ተግባራዊ ለማድረግ እየተሞከረ ይገኛል።

እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ CSE በኢትዮጵያ ለመስጠት የሙከራ ተጀመሮ የነበረ ሲሆን፣ በወቅቱ የኢትዮጵያ ልጆችን እንታደግ በሚል በነ ዶ/ር ስዩም አንቶኒዮስ እንቅስቃሴዎች ሲደረጉ ቆይተዋል።

ከ5 አመታት በፊት ጋዜጠኛ ኦቦሌሳ አዶላ በጉዳዩ ዙሪያ የሰራውን ፕሮግራም ድጋሚ እንድትመለከቱት እንጋብዛችኋለን።
ክፍል 1
https://youtu.be/3OIiVek8Ma4?list=PLGlrR-9THPeXNTGB9YMM525Fsp4ZsHMb4
ክፍል 2
https://youtu.be/FQDpmMty8HE?list=PLGlrR-9THPeXNTGB9YMM525Fsp4ZsHMb4
ይገኛል።

 #በአቡ ዳቢ አቅራቢያ ጥንታዊ የክርስቲያን ቅሪቶች ተገኙሲር ባኒ ያስ በተባለ አቡ ዳቢ አቅራቢያ በምትገኝ ደሴት ላይ የተገኘው ይህ ቅሪት፣ በጭቃ ቡኪት የተሰራ የመስቀል ቅርጽ ነው። ቅርሱ ...
25/08/2025

#በአቡ ዳቢ አቅራቢያ ጥንታዊ የክርስቲያን ቅሪቶች ተገኙ

ሲር ባኒ ያስ በተባለ አቡ ዳቢ አቅራቢያ በምትገኝ ደሴት ላይ የተገኘው ይህ ቅሪት፣ በጭቃ ቡኪት የተሰራ የመስቀል ቅርጽ ነው። ቅርሱ የ1400 ዓመታት ታሪክ እንዳለው ተነግሯል። ግኝቱ ወንጌል ወደ ምስራቅ የአለም ክፍል እንዴት እንደተስፋፋ ፍንጭ ይሰጣል ተብሏል።

ቅሪቱ የተገኘበት አካባቢ ጥንታዊ የአብያተ ክርስቲያን እና ገዳማት ፍርስራሽ ይገኛል። ግኝቱ በአካባቢ እስልምና ከመስፋፋቱ በፊት በአካባቢው ተስፋፍቶ የነበረውን ክርስትና ያሳያል ተብሏል።

ቅሪቱን ያገኙ አርኪዮሎጂስቶች ክርስትና በአካባቢውመኖሩን ብቻ ሳይሆን በስፋት እንደነበረ ያሳያል ብለዋል። ቅርሱ 27 ሳንቲም በ17 ሳንቲም የሆነ እና 2 ሳንቲም ስፋት ያለው እና ይንጠለጠል የነበረ መሆኑን ያሳያል።

በአቡ ዳቢ አካባቢ የነበሩ ክርስቲያኖች ከእየሩሳሌም እስከ ህንድ እና ቻይና የተዘረጋው ክርስትና መሸጋገሪያ ነጥብ መሆናቸውን ያሳያል ተብሏል። የገዳማቱ ሁኔታ በአካባቢው ክርስቲያኖች እና የእስልምና እምነት ተከታዮች በሰላም ይኖሩ እንደነበረም ያሳያል ተብሏል። ስፍራው ወንጌል ከአረብ ባህረ ሰላጤ በኩል አድርጎ ወደ እስያ ለመስፋፋቱ መነሻ ስፍራ ነበረ ተብሏል።

በአካባቢው በ1990ዎቹ የክርስትና እምነት ቅሪቶች መገኘት የጀመሩ ሲሆን፣ በ2022 በዚያው አቡ ዳቢ አካባቢ፣ ኡም አል ቁዋይን በተባለ አካባቢ ጥንታዊ ገዳማት መገኘታቸው ይታወሳል። ተመሳሳይ ይዘት ያላቸው ገዳማት በኩዌት፣ ኢራን እና ሳውዲ አረቢያ ተገኝተዋል። Christianity today እና The National እንዳስነበቡት

በኦቦሌሳ አዶላ

ዝርዝር መረጃዎችን ለመመልከት የቴሌግራም ገፃችንን ይቀላቀሉ።

https://t.me/TCNEW

በመጋቢ አመሉ ጌታ የተፃፈው "መንፈሳዊ ተዋጊ" የተሰኘው መፅሐፍ ተመረቀ።መፅሐፉ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አባቶች፣ የአብያተክርስቲያናት መሪዎች፣ አገልጋዮች እንዲሁም የፅሐፊዉ ወዳጆች በተገኙበ...
25/08/2025

በመጋቢ አመሉ ጌታ የተፃፈው "መንፈሳዊ ተዋጊ" የተሰኘው መፅሐፍ ተመረቀ።

መፅሐፉ የኢትዮጵያ ወንጌላውያን አባቶች፣ የአብያተክርስቲያናት መሪዎች፣ አገልጋዮች እንዲሁም የፅሐፊዉ ወዳጆች በተገኙበት በኢቫንጀሊካል ቲዌሎጂካል ኮሌጅ ተመርቋል።

በመረሃግብሩ አርቲስት ቴዎድሮስ በዛብህ እና የቀድሞ የደራሲያን ማሕበር ፕሬዚዳንት ጋሽ ጌታቸው በለጠ የፅሐፊዉን የህይወት ታሪክ በአጭሩ ያቀረቡ ሲሆን ቄስ ሳሙኤል ሀይሉም የመፅሃፉን ዳሰሳ ለታዳሚያን አቅርበዋል።

የመጽሐፋ አርታኢ ወንድም ግርማቸው ሀብቴም የመፅሐፉ አበርክቶት የተደረገላቸውን ባለታሪክ ግለታሪካቸውን ለታዳሚያን አውስቷል።

ይህን ራዕይ ለመደገፍ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ያበረከቱትን ሁሉ በማመስገን በቀጣይም በህትመት ዙርያ ላይ ያላቸውን ራዕይ ለታዳሚያን ያካፈሉት ደግሞ የመፅሀፊ ፀሀፊ መጋቢ አመሉ ጌታ ናቸዉ።

ለፅሐፊዉ ይህ መፅሀፍ 12ኛ መፅሐፋቸው ሲሆን ከዚህ በፊት እናትና አባታችሁን አክብሩ ፣ አስራት ፣ ቅድመ ጋብቻና ድህረ ጋብቻ ጥበብ ፣ ማስተዋል ፣ ሌጋሲ ፣ መንፈሳዊ ባለስልጣን ፣ ታዳጊ ወጣቶች ጋብቻ ፣ ከብዙ ሞት አዳነኝና ቡራኬ የተሰኙ መፅሀፎችን በተለያዩ ቋንቋዎች ለአንባቢያን ማቅረባቸው ይታወሳል።

መንፈሳዊ ተከታታይ ትምህርቶችን እና መልዕክቶችን ለመከታተል የቴሌግራም ገፃችንን ይቀላቀሉ።

https://t.me/TCNEW

ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች በኤርትራ የታሰሩት 7 የሀይማኖት አባቶች እንዲፈቱ ጥሪ አቀረቡ፡፡ ክርስቲያን ዴይሊ እንደዘገበው እነዚህ የሀይማኖት አባቶች ከእስር እንዲለቀቁ የሚጠይቅ ...
23/08/2025

ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች በኤርትራ የታሰሩት 7 የሀይማኖት አባቶች እንዲፈቱ ጥሪ አቀረቡ፡፡

ክርስቲያን ዴይሊ እንደዘገበው እነዚህ የሀይማኖት አባቶች ከእስር እንዲለቀቁ የሚጠይቅ አለም አቀፍ ዘመቻ ተጀምሯል፡፡

እንደዘገባው ከታሰሩት ውስጥ ሶስቱ የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ቀሳውስት ሲሆኑ ከታሰሩ 21 አመት ሆኗቸዋል፡፡

የኤርትራ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አባቶች የሆኑት ቄስ ገብረመድህን ገብረጊዮርጊስ፣ ዶክተር ፍፁም ገብረንጉስና ቄስ ተክለአብ መንግስትአብ ከተያዙበት ኖቬምበር 19 ቀን 2004 አንስቶ ምንም ክስ እንዳልቀረበባቸው የጠቀሰው ዘገባው እንዲሁም ቄስ ሀይሌ ናይግዚ፣ ፓስተር ሚሊዮን ገብረስላሴ፣ ፓስተር መንግስትአብና ፓስተር ኪዳኔ ከ20 አመታት በላይ በወንጀል ምርመራ ቢሮ ያለምንም ክስ በእስር እየማቀቁ መሆኑን አስታውቋል፡፡

እነዚህ የሀይማኖት አባቶች እንዲፈቱ በሚጠይቀው አዲስ ዘመቻ መሰረት በዋሽንግተን ዲሲ በሚገኘው የኤርትራ ኤምባሲ ደጃፍ የተቃውሞ ሰልፍ እንደሚደረግ ተገልጿል፡፡

እንዲሁም በለንደን በሚገኘው የኤርትራ ኤምባሲም ተመሳሳይ ተቃውሞ እንደሚደረግ ያስታወቁት አስተባባሪዎቹ እንዲሁም በፈረንሳይ፣ ጣሊያን፣ ዴንማርክ፣ ካናዳና ስዊድን የተለያዩ የተቃውሞና የፀሎት እንቅስቃሴዎች እንደሚከናወኑ ገልፀዋል፡፡

እንደ ኦፕን ዶርስ ጥናት መሰረት 1.6 ሚሊዮን አከባቢ ክርስቲያኖች እንዳሏት የሚገመተው ኤርትራ ለክርስታን አስቸጋሪ ከሆኑ 50 ሀገራት መካከል ባለፉት 5 አመታት ከ4-6ኛ በመሆን እጅግ አስቸጋሪ ከሚባሉት መካከል ተቀምጣለች።

ዝርዝር መረጃዎችን ለመመልከት የቴሌግራም ገፃችንን ይቀላቀሉ።

https://t.me/TCNEW

ኪንግደም ፓሽን ሴሚናሪ 10ኛውን አመታዊ ስብሰባና የወዳጅነት ቀን አካሄደ፡፡ነሐሴ 15 ቀን 2017 ዓ.ም በናዛሪን ኢንተርናሽናል ቤ/ክ በተካሄደው በዚህ አመታዊ የሴሚናሪው ስብሰባ ላይም ከሀ...
22/08/2025

ኪንግደም ፓሽን ሴሚናሪ 10ኛውን አመታዊ ስብሰባና የወዳጅነት ቀን አካሄደ፡፡

ነሐሴ 15 ቀን 2017 ዓ.ም በናዛሪን ኢንተርናሽናል ቤ/ክ በተካሄደው በዚህ አመታዊ የሴሚናሪው ስብሰባ ላይም ከሀገር ውስጥ #እና ከውጭ የመጡ ተሳታፊዎችም ተገኝተዋል።

በመድረኩም የኪንግደም ፓሽን ፕሬዳንት ዶክተር ዘካሪያስ እና የሴሚናሪው የቦርድ ሰብሳቢ የሆኑት ፓስተር ሰለሞን በንቲ ለታዳሚያ የእንኳን ደህና መጣችው ንግግርም አድርገዋል።

ሚሽን ተኮር የሆነውና በስነ መለኮት ትምህር በርካታ ቦታዎችን ተደራሽ ማድረግ ራዕዩ ያደረገው የኪንግደም ፓሽን ሴሚናሪ በአሁኑ ሰዓትም በአማርኛ ፣ እንግሊዝኛ ና አፋን ኦሮሞ ቋንቋዎችን ጨምሮ በሌሎችም ቋንቋዎች ወንጌልን ተደራሽ በማድረግ ረገድ ዘርፈ ብዙ ስራዎችን እየሰራ እንደሚገኝም በዕለቱ ተወስቷል።

በዝግጅቱም በሉቃስ 14:14-17 ያለውን ክፍል መሰረት በማድረግ ቄስ ትዕግስቱ ሞገስ የእግዚአብሔርን ቃልም አካፍለዋል። በትምህርታቸውም አማኞች ትኩረታቸውን በወንጌል ስራ ላይ ማድረግ እንደሚገባም አሳስበዋል።

የሴሚናሪው ፕሬዘዳንት የሆኑት ዶክተር ዘካሪያስ አዱኛ በመልዕክታቸውም ጉባኤው ለ10ኛ ጊዜ መካሄዱን በመግለፅ ከአጋር አካላት ጋር በትብብር እየሰሩ እንደሚገኙም ተናግረዋል።

በውይይት መድረኩ ላይም በኪንግደም ፓሽን ሴሚናሪ በተካሄደው አመታዊ ጉባኤ በተቋሙ እየተሰሩ ያሉ የስራ እንቅስቃሴዎች እና በቀጣይ ሊሰሩ የታሰቡ እቅዶች ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑንም የገለፁት የሴሚናሪው የቦርድ ሰብሳቢ የሆኑት ፓስተር ሰለሞን በንቲ ናቸው።

በተጨማሪም የናዛሪን ቤተክርስቲያን አገልጋይ የሆኑት መልካሙ እንደተናገሩትም ሴሚናሪው እየሰራ ያለውን በጎ ተግባር በማንሳት ከኪንግደም ፓሽን ሴሚናሪ ጎን እንደሚቆሙም አስታውቀዋል።

የኪንግደም ፓሽን ሴሚናሪ በአሁኑ ሰዓት ወንጌል ባልደረሰባቸው አካባቢዎች ወንጌልን በማድረስ እና የቤተክርስቲያንን ተልዕኮ ለማድረስ ሰፊ ስራ እየሰራ እንደሚገኝም ተነግሯል።

በመጨረሻም በቦርድ አባልነት ሲያገለግሉ ለነበሩ የስልጣን ሽግግርና በተለያዩ ዘርፎች አስተዋጽኦ ላደረጉ ተቋማትም የእውቅና መርሀ ግብርም ተካሄዷል።

በኦቦሌሳ አዶላ
16/1/2017ዓ.ም
አዲስ አበባ

ዝርዝር መረጃዎችን ለመመልከት የቴሌግራም ገፃችንን ይቀላቀሉ።

https://t.me/TCNEW

ጥንታዊቷ ቤተክርስቲያን ከ2 ቀን የመኪና ጉዞ በኋላ ወደ ማረፊያዋ ደረሰች  | ጥንታዊቷ የስዊድን ቤተ ክርስትያን ኪሩና ኪርካ ከሁለት ቀን የመኪና ጉዞ በኋላ ወደ ማረፊያዋ በሰላም ደርሳለች።...
22/08/2025

ጥንታዊቷ ቤተክርስቲያን ከ2 ቀን የመኪና ጉዞ በኋላ ወደ ማረፊያዋ ደረሰች

| ጥንታዊቷ የስዊድን ቤተ ክርስትያን ኪሩና ኪርካ ከሁለት ቀን የመኪና ጉዞ በኋላ ወደ ማረፊያዋ በሰላም ደርሳለች።

የ113 ዓመት ዕድሜ እንዳላት የሚነገረው ይህች ቤተክርስቲያን ቀድሞ ከነበረችበት ስፍራ በማዕድን ቁፋሮ ምክንያት ወደ ሌላ ቦታ መዘዋወሯ ተነግሯል።

በዚህም በግዙፍ ተሽከርካሪ ቤተክርስቲያኗን ወደ ሌላ ስፍራ የማዘዋወር ስራ ከሁለት ቀን በፊት መጀመሩ ነው የተገለጸው።

ቢቢሲ ዛሬ እንዳስነበበው ቤተክርስቲያኗ ከሁለት ቀናት የመኪና ጉዞ በኋላ ወደ አዲስ አገልግሎት ወደምትሰጥበት ቦታ ደርሳለች።

ባላት ልዩ የምህንድስና ጥበብ በስዊድን እና አውሮፓ ልዩ ትኩረት የሚሰጣት ይህች ቤተ ክርስቲያን፤ ያደረገችው ጉዞ በበርካቶች ዘንድ የሚጠበቅ ነበር።

ቤተክርስቲያኗን ለማጓጓዝ 240 ጎማ የተገጠመለት ልዩ ተሽከርካሪ ያስፈለገ ሲሆን፤ አሁን ላይ ቤተክርስቲያኗ ቀድሞ ከነበረችበት 5ኪ.ሜ እርቃ በአዲሱ ይዞታዋ ላይ ማረፏ ተጠቅሷል ሲል ኢቢሲ ዘግቧል፡፡

ዝርዝር መረጃዎችን ለመመልከት የቴሌግራም ገፃችንን ይቀላቀሉ።

https://t.me/TCNEW

በቤይሩት ሊባኖስ  #የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች ጉባኤ ተደረገ።በጉባዔው ከኢትዮጵያ የሄዱ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ፀሐፊ ቄስ ደረጀ ጀምበሩ እና የካ...
22/08/2025

በቤይሩት ሊባኖስ #የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች ጉባኤ ተደረገ።

በጉባዔው ከኢትዮጵያ የሄዱ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ፀሐፊ ቄስ ደረጀ ጀምበሩ እና የካውንስሉ ጽ/ቤት ኃላፊ ፓስተር ጌትነት ለማ፣ በሊባኖስ የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጽ/ቤት አመራሮች፣ በሊባኖስ የሚኖሩ የዕምነቱ ተከታይ ኢትዮጵያውያን፣ ትውልድ ኢትዮጵያውያንና ሊባኖሳውያን እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተሳትፈዋል፡፡

በጉባዔዉ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ቆንስላ በቤሩት-ሊባኖስ ሚሲዮን ጉዳይ ፈጻሚና የዳያስፖራ ዘርፍ ኃላፊ አቶ ጌታቸው ኡታ ጉባዔው እንዲሳካ ላደረጉት ለኃይማኖቱ አባቶችና ምዕመናን ምስጋናቸውን አቅርበው ቆንስላ ጄኔራል ጽ/ቤቱ ለዜጎቻችን አስፈላጊውን አገልግሎትና ድጋፍ እየሰጠ እንደሆነ ተናግረዋል።

በቀጣይም አገልግሎቱን፣ የዜጎቻችንን መብትና ጥቅም በማስከበርና በአገራዊ ጉዳዮች ተሳትፎ ዙሪያ ከካውንስሉ ጽ/ቤት እና ከመላው የዕምነቱ ተከታዮች ጋር የሚያደርገውን ትብብርና ቅንጅታዊ ሥራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል::

የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ፀሐፊ ቄስ ደረጀ ጀምበሩ እና ፓስተር ጌትነት ለማ በበኩሎቸው የኢትዮጵያ የወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል በአዋጅ መቋቋሙንና በዚሁ መሠረት በተዋረድ አደረጃጀት የመዘርጋት ሥራ መሠራቱን በመግለጽ በሊባኖስ በካውንስል ጽ/ቤት እና በቆንስላ ጽ/ቤት መካከል የዕምነቱ ተከታይ የሆኑ ዜጎቻችንን በማገልገል ረገድ የነበራቸው ግንኙነትና ትብብር ተጠናክሮ መቀጠል የሚገባው እንደሆነ ገልፀዋል።

በዚህ የጋራ ትብብር ዙሪያ የካውንስሉ ጠቅላይ ፀሐፊ ቄስ ደረጀ ጀምበሩ እና ፓስተር ጌትነት ለማ እንዲሁም በሊባኖስ የካውንስሉ ጽ/ቤት አመራሮች ጋር በቆንስላ ጄኔራል ጽ/ቤቱ የጋራ ውይይት ተደርጓል፡፡

ጉባኤው የሐይማኖቱ አባቶችና ተጋባዥ እንግዶች ባቀረቡት ንግግሮች፣ የወንልል ትምህርቶች እንዲሁም የዕምነቱ ተከታዮች ዘማሪያን ባቀረቧቸው መዝሙሮች በደመቀ ሁኔታ ተካሂዶ ተጠናቋል፡፡

ዝርዝር መረጃዎችን ለመመልከት የቴሌግራም ገፃችንን ይቀላቀሉ።

https://t.me/TCNEW

 #በኢትዮጵያ የመንፈሳዊ ቴሌቪዥን ሲነሳ የኤልሻዳይ ቴሌቪዥን ኔትወርክ ተቀዳሚ እና ለብዙዎች ምሳሌ ነዉ።በኤልሻዳይ ቴሌቪዥን አንጋፋ እና ወጣት የወንጌል አገልጋዮች እንዲሁም አብያተክርስቲያና...
21/08/2025

#በኢትዮጵያ የመንፈሳዊ ቴሌቪዥን ሲነሳ የኤልሻዳይ ቴሌቪዥን ኔትወርክ ተቀዳሚ እና ለብዙዎች ምሳሌ ነዉ።

በኤልሻዳይ ቴሌቪዥን አንጋፋ እና ወጣት የወንጌል አገልጋዮች እንዲሁም አብያተክርስቲያናት ወንጌልን በዚህ የቴሌቪዥን መስኮት መልክታቸውን ለብዙ ሚሊዮኖች አድርሰዋል።

አብያተክርስቲያናት ወንጌል በብዙ መንገድ በአራቱም አቅጣጫ ሲሰሩ ቆይተዋል በብዙ ሺህ የሚደርሱ ነፍሳት ወደ #እግዚአብሔር መንግስት ሲጨመሩ በመንፈሳዊ ቴሌቪዥን ወንጌል በማድረግ ግንባር ቀደም ሚና ተጫዉቷል ኤልሻዳይ ቴሌቪዥን።

የቴሌቪዥኑ መስራች እና መሪዎች ፖ/ር አበራ ሀብቴ እና ፖ/ር በለጡ ሀብቴ ለወንጌል አማኙ ፣ ለታዳጊ ወጣቶች ፣ ለመሪዎች እና ለአብያክርስቲያናት ባለውለታዎች ናቸው።

እነዚህ አገልጋዬች ዛሬ የተጋቡበት 32ኛ አመት እያሰቡ ነዉ።

ወደ ጌታ መንግስት ከተጨመሩ 36 አመት ያስቆጠሩ ሲሆን፣ 3 አመት ተኩል በእጮኛምነት፣ 19 አመት በመሉ ጊዜ አብሮ በማገልገል ቆይተዋል።

The Christian News - የክርስቲያን ዜና #እንኳን አደረሳችሁ እያልን ቀሪ የአገልግሎት ዘመናችሁ #መልካም እንዲሆን እንመኛለን።

መንፈሳዊ ተከታታይ ትምህርቶችን እና መልዕክቶችን ለመከታተል የቴሌግራም ገፃችንን ይቀላቀሉ።

https://t.me/TCNEW

Address

Addis Ababa
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when The Christian News - የክርስቲያን ዜና posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to The Christian News - የክርስቲያን ዜና:

Share