
28/07/2025
የሁሉንም ክልሎች የሀገር ሽማግሌዎች፣ አባ ገዳ እና ነጋዴዎችን አሳትፏል የተባለ ልዑክ መቐሌ ገባ።
በኢትዮጵያ ከ12 ክልሎችና ከሁለት ከተሞች የተውጣጡ የሀገር ሽማግሌዎች፣ አባ ገዳ እና ነጋዴዎች ጨምሮ ከ50 በላይ ሰዎችን ያቀፈ ልዑክ መቐሌ መግባታቸው ተነግሯል።
እንደ ክልሉ መገናኛ ብዙሃን መረጃ ልዑኩ ከጊዚያዊ አስተዳደር፣ ከፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች፣ ከሃይማኖት አባቶች እና ከሲቪክ ማህበራት ጋር ይወያያሉ ተብሏል።
በትግራይ ኃይሎች እና የፌደራል መንግስት መካከል እየተካረረ የመጣ አለመግባባት ለመፍታት አስታራቂ አካላት ወደ ትግራይ ሲያቀኑ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ይሄ ለሁለተኛ ጊዜ ነው።
@ማለዳ ሚዲያ