Arts Tv World

Arts Tv World Arts Tv World - Digital Media and Satellite Television Service
(3)

በጌዴኦ ዞን ባለፈው ሳምንት በተከታታይ ቀናት በደረሱ ሁለት የመሬት መንሸራተት አደጋዎች የ26 ሰዎች ሕይወት አለፈ።በአደጋው የሞቱ 15 ሰዎች አስከሬን እስካሁን ድረስ ባይገኝም በአከባቢው በ...
01/09/2025

በጌዴኦ ዞን ባለፈው ሳምንት በተከታታይ ቀናት በደረሱ ሁለት የመሬት መንሸራተት አደጋዎች የ26 ሰዎች ሕይወት አለፈ።

በአደጋው የሞቱ 15 ሰዎች አስከሬን እስካሁን ድረስ ባይገኝም በአከባቢው በድጋሚ የመሬት መንሸራተት አደጋ ሊፈጠር ይችላል በሚል ስጋት ምክንያት ፍለጋው እንዲቆም መደረጉን ቢቢሲ ዘግቧል።

በጌዴኦ ዞን በሚገኙት ራጴ እና ቡሌ ወረዳዎች የመሬት መንሸራተት አደጋዎች የደረሱት ባለፈው ሳምንት ማክሰኞ ነሐሴ 20 እና በማግሥቱ ረቡዕ ነሐሴ 21/2017 ዓ.ም. ነው።

የማክሰኞ ዕለቱ የራጴ ወረዳ አደጋ የተከሰተው ከሌሊቱ ሰባት ሰዓት ገደማ እንደነበር ዋና አስተዳዳሪው ተናግረዋል።

ጫራቃ እና ሀሮ በተባሉ ቀበሌዎች በደረሰው በዚህ አደጋ የአንድ ቤተሰብ አባላት የሆኑ ሰባት ሰዎችን ጨምሮ ዘጠኝ ሰዎች ህይወታቸው ማለፉን ተገልጿል።

ምንጭ ቢቢሲ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 50 ቢሊዮን ብር ለዳያስፖራው ማሕበረሰብ ለማበደር መዘጋጀቱን አስታወቀ።በ2018 ዓ.ም ፤ ለዳያስፖራ ማህበረሰብ ለኢንቨስትመንት እንዲሁም ለቤትና መኪና ግዥ የሚውል 5...
01/09/2025

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 50 ቢሊዮን ብር ለዳያስፖራው ማሕበረሰብ ለማበደር መዘጋጀቱን አስታወቀ።

በ2018 ዓ.ም ፤ ለዳያስፖራ ማህበረሰብ ለኢንቨስትመንት እንዲሁም ለቤትና መኪና ግዥ የሚውል 50 ቢሊዮን ብር ለማበደር የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዝግጅት ማድረጉን የባንኩ ፕሬዚደንት አቶ አቤ ሳኖ ገልጸዋል።

ፕሬዚደንቱ ይህን ያሉት በዱባይና ሰሜን ኤምሬቶች ከሚገኙ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ጋር እየመከሩ ባለቡት መሆኑን ባንኩ በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገጹ አስታውቋል።

ፕሬዚደንቱ ባንኩ ከጀመራቸው ሰፊ የለውጥ ስራዎች መካከል የዳያስፖራውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ የሚያደርጉ ስራዎች መሰራታቸውን በማንሳት ከእነዚህም መካከል ይህ የ50 ቢሊዮን ብር አቅርቦት እንደሚገኝበት ጠቅሰዋል።

በሽልማት የደመቀው ምሽት
31/08/2025

በሽልማት የደመቀው ምሽት

ዛሬ በቅዳሜ ገበያ ፕሮግራማችን፣ ቤላ ስፖርት ዌር በቤልቪው ሆቴል ባዘጋጀው የቤላ ስፖርት አዋርድ ላይ ተገኝተን ነበር። በዚህ ቪዲዮ፣ ከዝግጅቱ የተገኙትን ውብ ጊዜያት እና ደማቅ ትዕይ...

የዋንጫውን  መዳረሻ ፍንጭ ይሰጣል የተባለው የሳምንቱ ተጠባቂው ጨዋታበ3ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ዛሬ ምሽት በአንፊልድ ሮድ ስታዲየም ሊቨርፑል ከአርሰናል የሚያደርጉት ጨዋታ ...
31/08/2025

የዋንጫውን መዳረሻ ፍንጭ ይሰጣል የተባለው የሳምንቱ ተጠባቂው ጨዋታ

በ3ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታ ዛሬ ምሽት በአንፊልድ ሮድ ስታዲየም ሊቨርፑል ከአርሰናል የሚያደርጉት ጨዋታ በጉጉት ይጠበቃል፡፡

ሁለቱ ተጋጣሚዎች በተያዘው የውድድር ዓመት ዋንጫውን ያሳካሉ ተብለው ቅድመ ግምት ከተሰጣቸው ቡድኖች መካከል ቀዳሚዎቹ ሲሆኑ የወቅቱ የሊጉ አሸናፊ ሊቨርፑል በአርኔ ስሎት እየተመራ በተከታታይ ለሁለተኛ ጊዜ የሊጉን ዋንጫ ለማሳካት የሚያደርገው ብርቱ ፉክክር ይጠበቃል፡፡

የመርሲሳይዱ ክለብ ሊቨርፑል በመጀመሪያ ሳምንት የሊጉ ጨዋታ ቦርንማውዝን በ2ኛ ሳምንት ደግሞ ኒውካስል ዩናይትድን ማሸነፉ ይታወሳል፡፡

ተጋጣሚው የሰሜን ለንደኑ ክለብ አርሰናል ልክ እንደ ሊቨርፑል ሁሉ በውድድር ዓመቱ ያደረጋቸውን ያለፉትን ሁለት ጨዋታዎች ድል አድርጓል፡፡

አርሰናል በመጀመሪያ ሳምንት የሊጉ ጨዋታ በተቀናቃኙ ማንቼስተር ዩናይትድ በብርቱ ተፈትኖ ድል ያደረገ ሲሆን በ2ኛ ሳምንት ደግሞ ሊድስ ዩናይትድ ላይ 5 ግብ በማስቆጠር አሸንፏል፡፡

ባለፉት ሶስት ዓመታት ሁለተኛ ደረጃን ይዞ በማጠናቀቅ የሊጉን ዋንጫ ያጣው አርሰናል በዚህ የውድድር ዓመት ዋንጫውን ለማሳካት እና የበላይ ሆኖ ለማጠናቀቅ በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት ራሱን በሚገባ አጠናክሯል፡፡

አርሰናል ከዚህ ቀደም ይነሳበት የነበረውን የፊት መስመር ችግር ለመፍታት በክረምቱ የተጫዋቾች የዝውውር መስኮት በስፖርቲንግ ሊዝበን የደመቀውን ኮከብ ቪክቶር ዮኮሬስን ማስፈረሙ ይታወቃል፡፡

ዛሬ 12 ሰዓት 30 ላይ በሚደረገው ጨዋታም በመከላከሉ ጥያቄ እየተነሳበት የሚገኘው የሊቨርፑልን የተከላካይ በብዙ አማራጮች በተሞላው እና ጥልቀት ባለው የአርሰናል የፊት መስመር ይፈትናል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

ዓይኖች ሁሉ ምሽት 12:30 የሳምንቱን ታላቅ ጨዋታ ለመታደም ወደ አንፊልድ ያማትራሉ ።

የጨዋታ ግምቶን ያስቀምጡ !

በዮናስ ግርማ

መኪና መግዛት ይፈልጋሉ? አሁኑኑ እቁብ በመጣል የህልምዎን መኪና ባለቤት ይሁኑ! መኪና ለመግዛት እቁብ ስለመጣል ማወቅ ያለብዎትን ጠቃሚ መረጃዎች በዚህ ቪዲዮ ያገኛሉ
30/08/2025

መኪና መግዛት ይፈልጋሉ? አሁኑኑ እቁብ በመጣል የህልምዎን መኪና ባለቤት ይሁኑ! መኪና ለመግዛት እቁብ ስለመጣል ማወቅ ያለብዎትን ጠቃሚ መረጃዎች በዚህ ቪዲዮ ያገኛሉ

መኪና መግዛት ይፈልጋሉ? አሁኑኑ እቁብ በመጣል የህልምዎን መኪና ባለቤት ይሁኑ! መኪና ለመግዛት እቁብ ስለመጣል ማወቅ ያለብዎትን ጠቃሚ መረጃዎች በዚህ ቪዲዮ ያገኛሉ። ...

Unlock the Future of Business & Leadership!Watch our exclusive chat with the Dubai Business School Dean and Management P...
30/08/2025

Unlock the Future of Business & Leadership!

Watch our exclusive chat with the Dubai Business School Dean and Management Professor !!!

Insights you don’t want to miss!

On this week’s My Africa – Coffee Time, we sit down with Professor Washika, Dean of Dubai Business School and Professor in Management. Our conversation touch...

30/08/2025

“Grand African Run” የተወሰነ ሳምንታት ብቻ ቀሩት።

በሰሜን አሜሪካ በየዓመቱ ወገኖቻችን በአብሮነት በሩጫ፣ በርምጃ፣ እና በሶምሶማ የሚያሳልፉበት ይህ ዝግጅት በኦክቶበር 11 ጠዋት በዋሽንግተን ዲሲ እና አሌክሳንደሪያ ድንበር ላይ (1100 Main Line Blvd, Alexandria, VA 22301) ይካሄዳል።

በቦታው ላይ ተገኝተው መጨረሻም ሆነ መጀመሪያ ርቀቱን ሲያጠናቅቁ የ2026 ቶዮታ ኮሮላ ለማግኘት ዕጣ ውስጥ ይካተታሉ። በዝግጅቱ ዕለት በሚወጣዉ ዕጣ የማሽነፍ ዕድል ይኖሩዎታል።

ሲመዘገቡም የዝግጅቱን ቲሽርት፣ የውሃ ኮዳ፣ እና የስፖንሰሮች ስጦታ የያዘ ፓኬጅ ያገኛሉ፤ ርቀቱን ሲያጠናቅቁም ሜዳሊያ፣ ውሃና አነስተኛ ስናክ ይቀርብልዎታል። በዝግጅቱ ላይ የኦሎምፒክ ጀግኖቻችን በእንግድነት ይገኛሉ፣ አብረዋቸው ያሳልፉ። ለመመዝገብ www.africanrun.com ይጠቀሙ። ከአስሩ የበጎ አድራጎት አጋር ድርጅቶቻችን መካከል ለአንዱ ሲሮጡ ደግሞ በመመዝገቢያ ክፍያዎ ላይ ቅናሽ ያገኛሉ።

ለዚህም www.africanrun.com/charity-partners ይጎብኙ።

"ጥቁር ገበያው ባይኖር እንደአገር አሁን ካለንበት በእጥፍ እናድግ ነበር"የጥቁር ገበያ ተጽእኖ ላይ ያተኮረውን የArts business cafe ውይይት በArts Tv World ይመልከቱ። ሙሉ ...
29/08/2025

"ጥቁር ገበያው ባይኖር እንደአገር አሁን ካለንበት በእጥፍ እናድግ ነበር"

የጥቁር ገበያ ተጽእኖ ላይ ያተኮረውን የArts business cafe ውይይት በArts Tv World ይመልከቱ። ሙሉ ፕሮግራሙን ለመከታተል ሊንኩን ይጫኑ ፦

. ...

የተወደዳችሁ እንዴት ናችሁ?ይህ አርትስ ስፔሻል ነው! በዚህ ሳምንት በአርትስ ስፔሻል:-1.የዘጠናዎቹ ተወዳጅ ድምጻዊት ትዕግሥት በቀለ ከ20 ዓመታት በኃላ የሙዚቃ ኮንሰርቷን በኢትዮጵያ ልታቀ...
29/08/2025

የተወደዳችሁ እንዴት ናችሁ?

ይህ አርትስ ስፔሻል ነው!

በዚህ ሳምንት በአርትስ ስፔሻል:-

1.የዘጠናዎቹ ተወዳጅ ድምጻዊት ትዕግሥት በቀለ ከ20 ዓመታት በኃላ የሙዚቃ ኮንሰርቷን በኢትዮጵያ ልታቀርብ ነው። ኮንሰርቱ የሚካሄድበት ቀን ታውቋል።ድምጻዊቷም ወደ ኢትዮጵያ መጥታለች።በዝርዝር እንነግራችኋለን።

3.በተጠባቂው የመላው አፍሪካ የሙዚቃ ሽልማት (አፍሪማ) ላይ አራት ሴት ድምጻዊያን ከኢትዮጵያ እጩ ሆነዋል። እጩ የሆኑት ድምጻዊያን እነማን ናቸው?።

3.በአዲስ አበባ ከተማ በስፋቱ እና በያዛቸው የመጻሕፍት ዓይነት ግዙፍ ነው የተባለለት ዘመናዊ የመፅሐፍ መደብር ነገ ይከፈታል።

እነዚህና ሌሎችንም የኪነት እና ኩነት መረጃዎች እናቀርብላችኋለን።

"አርትስ ስፔሻል"ዝግጅታችንን ይመለከቱ:

...

አዲስ አበባ ስታዲየም ዳግም የሊጉን ጨዋታዎች ሊያስተናግድ  ይችላል ተባለ ።አንጋፋው የአዲስ አበባ ስታዲየም ዳግም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎችንና የብሔራዊ ቡድን   ጨዋታዎችን ስለሚያ...
29/08/2025

አዲስ አበባ ስታዲየም ዳግም የሊጉን ጨዋታዎች ሊያስተናግድ ይችላል ተባለ ።

አንጋፋው የአዲስ አበባ ስታዲየም ዳግም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎችንና የብሔራዊ ቡድን ጨዋታዎችን ስለሚያስተናግድበት ሁኔታ ውይይት ተካሂዶ ተስፋ ሰጪ ውጤት መገኘቱን ሶከር ኢትዮጵያን ጨምሮ ታማኝነት ያላቸው ምንጮች ገልጸዋል ።

ዛሬ የኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ፕሬዝደንት አቶ ኢሳያስ ጅራ፣ የሊግ ካምፓኒው ፕሬዝደንት መቶ አለቃ ፍቃደ ማሞ እንዲሁም ዋና ስራ አስፈፃሚው አቶ ባህሩ ጥላሁን እና የሊጉ አክስዮን ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ክፍሌ ሰይፉ በጋራ በመሆን የአዲስ አበባ ከተንቲባ ክብርት አዳነች አበቤ ጋር በፅህፈት ቤታቸው በመገኘት ውይይት አድርገው እንደነበረ ተገልጿል ።

በውይይቱም መልካም ነገር እንደተገኘ እና አዲስ አበባ ስታዲየም ዳግም ውድድር እንደሚጀመርበት መልካም ተስፋ ተጥሎበት ስብሰባው እንደተቋጨ የተገኙ መረጃዎች ይጠቁማሉ ።

በቀጣይ የውድድር ዘመን ተወዳዳሪ ቡድኖች ውድድር የሚያደርጉባቸውን የመጀመሪያ እና ሁለተኛ ሜዳዎች ምርጫ እንዲያቀርቡ ሊግ ካምፓኒው መጠየቁ የሚታወስ ሲሆን በተለይም መሰረታቸውን አዲስ አበባ ያደረጉ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ቡድኖች ውድድራቸውን በአዲስ አበባ ስታዲየም የማድረግ እድል ያገኛሉም ተብሏል ።

በተያያዘ መረጃ በ2018 ዓ.ም ግንባታው እንዲጠናቀቅ እየተሰራበት የሚገኘው የአደይ አበባ ስታዲየም የካፍና የፊፋን ስታንዳርድ የሚያሟላ በመሆኑ በተመሳሳይ ሁኔታ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጨዋታዎች በአዲስ አበባ ሊደረጉ እንደሚችሉ ተገልጿል ።

በዮናስ ግርማ

ArifPay Signs as Title Sponsor of the 11th Gumma Awards, Driving a Digital Shift in Ethiopia’s Creative IndustryAddis Ab...
28/08/2025

ArifPay Signs as Title Sponsor of the 11th Gumma Awards, Driving a Digital Shift in Ethiopia’s Creative Industry

Addis Ababa — In a landmark move for Ethiopia’s cultural and creative landscape, ArifPay has officially signed on as the title sponsor of the prestigious Gumma Awards. The signing ceremony, held today at Union Restaurant, marked the beginning of a partnership aimed at merging tradition with digital innovation.

Speaking at the event, ArifPay CEO ; Mr Rediate Tsigeberhan; highlighted the company’s vision of transforming the creative industry into a creative economy through digital solutions. “This partnership with Gumma is a significant milestone in our journey to digitize and empower the creative sector,” he said.

This year’s 11th Gumma Awards will also serve as the launchpad for two of ArifPay’s latest innovations: Jami, Ethiopia’s first digital tipping app, and Arts Plus, a bold Afrocentric movie streaming platform designed to showcase cinematic African stories to the world.

Yonas Berhane Mewa, Founder and Director of the Gumma Awards, shared that the upcoming edition will feature “new and exciting elements,” promising an even more memorable celebration of Ethiopia’s creative excellence.

The partnership signals a transformative era where technology and creativity converge, empowering artists and audiences alike.

Address

Bole Medhanialem, Awlo Business Center, 8th & 9th Floors, Cameroon Street
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Arts Tv World posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Arts Tv World:

Share

Category