Arts Tv World

Arts Tv World Arts Tv World - Digital Media and Satellite Television Service
(6)

ኢትዮጵያ የክፍያ ሥርዓቷን ከጥሬ ገንዘብ ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ እያሸጋገረች ነው ተባለ። የብሔራዊ ባንክ የባንኮችና የክፍያ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ሰለሞን ዳምጠው፣ ኢትዮጵያ ከጥሬ ...
12/08/2026

ኢትዮጵያ የክፍያ ሥርዓቷን ከጥሬ ገንዘብ ወደ ዲጂታል ኢኮኖሚ እያሸጋገረች ነው ተባለ።

የብሔራዊ ባንክ የባንኮችና የክፍያ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ሰለሞን ዳምጠው፣ ኢትዮጵያ ከጥሬ ገንዘብ ተኮር አሠራር ወደ ተገናኝቶ ወደሚሰራ ዲጂታል የፋይናንስ ሥርዓት እየተሸጋገረች መሆኑን ገለፀዋል።

አቶ ሰለሞን በ29ኛው የConnected Banking Summit ላይ ባደረጉት ንግግር፣ በሀገሪቱ የሞባይል ገንዘብ አካውንቶች ቁጥር በአጭር ጊዜ ከፍተኛ እድገት አምጥቷል ያሉ ሲሆን የተጠቃሚው ቁጥር ከ157 ሚሊዮን በላይ መድረሱን ጠቁመዋል።

ነገር ግን ከተመዘገቡት አካውንቶች ውስጥ በንቃት የሚጠቀሙ ሰዎች መጠን ከ15 በመቶ በታች መሆኑን ጠቁመው፣ የዲጂታል ክፍያ አጠቃቀምን ማሳደግ ቀጣዩ ትኩረት መሆኑን አስረድተዋል።

የክፍያ ሥርዓት ጉዳይ ከቴክኖሎጂ ባሻገር ከኢኮኖሚ ዕድገት፣ ከሥራ ዕድል ፈጠራና ከፋይናንስ አካታችነት ጋር ተያይዞ መታየት እንዳለበትም ሰለሞን ዳምጠው ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ የዲጂታል ክፍያ ሥርዓት ቀጣዩ ትኩረት የፋይናንስ አካታችነትን ማሳደግ፣ የግል ዘርፉን ተሳትፎ ማጠናከር፣ የክፍያ ሥርዓቶችን ማገናኘትና ዲጂታል ክፍያን ለኢኮኖሚ ዕድገት የበለጠ አስተዋፅኦ እንዲያደርግ ማድረግ እንደሆነ ተጠቁሟል።

አርትስ ቴሌቪዥን ብቸኛ የሚዲያ አጋር የሆነበት 29ኛው የተገናኘ የባንክ አገልግሎት ጉባኤ (Connected Banking Summit) በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው ። 29ኛው የ Connecte...
12/08/2026

አርትስ ቴሌቪዥን ብቸኛ የሚዲያ አጋር የሆነበት 29ኛው የተገናኘ የባንክ አገልግሎት ጉባኤ (Connected Banking Summit) በአዲስ አበባ እየተካሄደ ነው ።

29ኛው የ Connected Banking Summit እና Innovation & Excellence Awards 2026 ዛሬ በኢትዮጵያ አዲስ አበባ ስካይላይት ሆቴል በመካሄድ ላይ ይገኛል። መድረኩ በባንክ፣ በፊንቴክ፣ በቴክኖሎጂ እና በፋይናንስ ዘርፍ የሚሰሩ አመራሮችን፣ ባለሙያዎችን እና ተቆጣጣሪዎችን ያሰባሰበ ነው ።

“ዲጂታል የፋይናንስ ሥርዓቶችን መገንባትና የባንክ ዘመናዊነትን ማፋጠን” በሚል ጭብጥ የሚካሄደው ጉባኤው በዲጂታል ክፍያ፣ በሞባይል ባንኪንግ፣ በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ፣ በሳይበር ደህንነት እና በፊንቴክ ፈጠራዎች ላይ ያተኮሩ ውይይቶችም ይደረጋሉ።

ጉባኤው በተጨማሪም የአፍሪካን የዲጂታል ፋይናንስ ሽግግር ለማፋጠን በባንኮች፣ በፊንቴክ ተቋማት እና በቴክኖሎጂ ኩባንያዎች መካከል ትብብርን ለማጠናከር ትኩረት ሰጥቷል።

አርትስ ቴሌቪዥን የዚህ ትለቅ ጉባኤ ብቸኛ የሚዲያ አጋር ነው ።

11/08/2026

''ቅዱስ ጊዮርጊስን መምራት አገር እንደመምራት ከባድ ነው''

አማራ ባንክ አዲስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ሾመአማራ ባንክ አቶ ይህንዓለም አቅናውን አዲስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አድርጎ መሾሙን ይፋ አደረገ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክም የአዲሱን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ...
11/08/2026

አማራ ባንክ አዲስ ዋና ስራ አስፈፃሚ ሾመ

አማራ ባንክ አቶ ይህንዓለም አቅናውን አዲስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አድርጎ መሾሙን ይፋ አደረገ። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክም የአዲሱን ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሹመት በዛሬው ዕለት ማጽደቁ ታውቋል።

የባንኩ የዳይሬክተሮች ቦርድ እንደገለጸው፤ እጩዎችን በጥንቃቄና በኃላፊነት ሲገመግም የቆየ ሲሆን፣ የአቶ ይህንዓለምን ከፍተኛ የትምህርት ዝግጅት፣ በባንክ ኢንዱስትሪው ያካበቱትን የረጅም ዓመታት የሥራ ልምድ እና ስትራቴጂያዊ የአመራር ብቃት ከግምት ውስጥ በማስገባት ለቦታው መርጧቸዋል።

ይህ ሹመት ባንኩ በቅርቡ ያጸደቀውን አዲስ ስትራቴጂያዊ ዕቅድና መዋቅር ተከትሎ ከተደረጉ የዋና መኮንኖች ሹመት ጋር ተደምሮ፣ አማራ ባንክን ወደ ተሻለ የዕድገት ደረጃ ለማሻገር ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው ታምኖበታል።

አቶ ይህንዓለም አቅናው በኢትዮጵያ የባንክ ኢንዱስትሪ ውስጥ ከ25 ዓመታት በላይ የሥራ ዘመን ያሳለፉ ሲሆን፣ አብዛኛውን ጊዜያቸውን በዳሸን ባንክ ከጀማሪ ባለሙያነት እስከ ከፍተኛ የአመራር እርከን (የቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ፣ የብድርና ስትራቴጂ መምሪያ ዳይሬክተር፣ የስትራቴጂ እና ከስተመር ኤክስፔሪያንስ ዋና መኮንን፣ የሪቴይል እና ኤስኤምኢ ዋና መኮንን እንዲሁም የኢንቨስትመንት ባንክ አማካሪ) በመሆን አገልግለዋል።

11/08/2026

«ከማጋራትዎ በፊት!»

በየቀኑ በማኅበራዊ ሚዲያ የምናያቸውና የምንሰማቸው መረጃዎች ስንቶቹ እውነት ናቸው? ያልተረጋገጡ የሐሰት መረጃዎች ወይም (Fake information) ማለት ምን ማለት ነው? የመረጃ ማጣራት ባለሙያዋ ርሆቦት አያሌው በዛሬው ምጥን ዝግጅታችን ያብራሩልናል።

ተመካካሪዎች በሃይማኖት ጉዳዮች እና የሰላም ግንባታ አጀንዳዎች ባቀረቧቸው ምክረ ሃሳቦች ከመግባባት ላይ መድረሳቸው ተነገረበሃይማኖት ጉዳዮች እና በሰላም ግንባታ አጀንዳዎች ላይ ሲመካካሩ የቆ...
11/08/2026

ተመካካሪዎች በሃይማኖት ጉዳዮች እና የሰላም ግንባታ አጀንዳዎች ባቀረቧቸው ምክረ ሃሳቦች ከመግባባት ላይ መድረሳቸው ተነገረ

በሃይማኖት ጉዳዮች እና በሰላም ግንባታ አጀንዳዎች ላይ ሲመካካሩ የቆዩ ሁለት ቡድኖች ዛሬ ነሐሴ 5/2018 ዓ.ም በተጠናቀሩ ምክረ ሃሳቦቻቸው ላይ ተስማማተው በተዘጋጀው ቃለ ጉባኤ ላይ መፈራረማቸውን የኢትዮጵያ አገራዊ ምክክር ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

የሌሎች አጀንዳዎች ተመካካሪዎችም በቀጣይ ቀናት በተመሳሳይ መልኩ የአጀንዳ ሃሳቦቻቸውን የጋራ አድርገው በቃለ ጉባኤዎቻቸው ላይ በመፈራረም እንደሚስማሙ ይጠበቃል ተብሏል፡፡

የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከሐምሌ 8/2018 ዓ.ም ጀምሮ እያካሄደ ባለው የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ በኮሚሽኑ ምክር ቤት በተለዩ ስምንት አጀንዳዎች ላይ ምክክር እየተደረገ መሆኑ ይታወቃል፡፡

አጀንዳዎቹ 500 አባላት ባሏቸው ስምንት የስራ ቡድኖች ምክክር እየተደረገባቸው ሲሆን በኮሚሽኑ የአሰራር ሥነ-ዘዴ መሰረት 500 አባላት ያሉት አንድ ቡድን በአንድ አጀንዳ ላይ እየተመካካረ ይገኛል፡፡

10/08/2026

ማንቸስተር ዩናይትድን ለመረከብ ከጫፍ ደርሼ ነበር - ጆዜ

10/08/2026

አርሰናል የባርኮላን ዝውውር ሊጠልፍ?

10/08/2026

ለዓለም ዋንጫ ያለፉ የአፍሪካ አገራት ታውቀዋል

ኢትዮጵያ በኦሪገን ተጨማሪ የወርቅ ሜዳልያ አሸነፈች -sport -በአሜሪካው  የኦሬገን የዓለም አትሌቲክስ ከ 20ዓመት በታች ሻምፒዮና ኢትዮጵያ ሁለተኛዋን የወርቅ ሜዳልያ ማግኘት ችላለች።ለኢ...
09/08/2026

ኢትዮጵያ በኦሪገን ተጨማሪ የወርቅ ሜዳልያ አሸነፈች

-sport -በአሜሪካው የኦሬገን የዓለም አትሌቲክስ ከ 20ዓመት በታች ሻምፒዮና ኢትዮጵያ ሁለተኛዋን የወርቅ ሜዳልያ ማግኘት ችላለች።

ለኢትዮጵያ የተገኙትን ተጨማሪ ሜዳሊያዎች
በሴቶች 3000ሜትር ፍፃሜ አትሌት ዮርዳኖስ ፀጋአብ 8:43.65 በሆነ ሰዓት በመግባት ለሀገሯ ሁለተኛውን የወርቅ ሜዳልያ ስታስገኝ ከቀናት በፊት ለአገሯ የመጀመሪያውን የብር ሜዳልያ ያመጣችው ሽቶ ጉሚ ሁለተኛ በመውጣት ተጨማሪ የብር ሜዳልያ አስገኝታለች።

እስከአሁን ባለው አጠቃላይ ውጤትም ሁለት የወርቅ ሜዳሊያዎችን ጨምሮ ስድስት ሜዳሊያዎችን የሰበሰበችው አገራችን ኢትዮጵያ በኦሪገን እየደመቀች ትገኛለች።

ዛሬ ፍጻሜውን በሚያገኘው ውድድሩ ኢትዮጵያ ለተጨማሪ የወርቅ ሜዳሊያ የምትጠበቅባቸው ውድድሮች ይደረጋሉ።

Address

Bole Medhanialem, Awlo Business Center, 8th & 9th Floors, Cameroon Street
Addis Ababa

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Arts Tv World posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Arts Tv World:

Shortcuts

Share

Category