Gebeya Media

Gebeya Media Welcome to Gebeya Media! Gebeya Media is an online media startup that offers you market research, job opportunities, and a variety of business ideas.
(1)

የሪሚዲያል ፕሮግራም ምደባ ይፋ ተደረገገበያ ሚዲያ ጥቅምት 19/2018 ዓ.ምትምህርት ሚኒስቴር በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ብሔራዊ ፈተና ወስደው ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ ...
29/10/2025

የሪሚዲያል ፕሮግራም ምደባ ይፋ ተደረገ

ገበያ ሚዲያ ጥቅምት 19/2018 ዓ.ም

ትምህርት ሚኒስቴር በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ ብሔራዊ ፈተና ወስደው ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች የሪሚዲያል (Remedial) ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች የትምህርት ተቋም ምደባ ይፋ አድርጓል፡፡

ተማሪዎች ተቋማት በሚያስተላልፉት ጥሪ መሠረት፤ የ Remedial ፕሮግራሙን እንዲከታተሉም ሚኒስቴሩ ያሳሰበ ሲሆን በዚህም መሠረት ተማሪዎች የተቋም ምደባቸውን ከታች በተዘረዘሩት አማራጮች ማየት የሚችሉ መሆኑን አስታውቋል፡፡

የተማሪዎች የተመደባችሁበትን ተቋም ለማየት 👇
በድረ-ገፅ፦ https://student.ethernet.edu.et
በቴሌግራም ቦት፦

ከ2.72 ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ በበርካታ አካባቢዎች የንፁህ መጠጥ ውሃ የማውጣት ቁፋሮ ሊከናወን ነው ገበያ ሚዲያ ጥቅምት 19/2018 ዓ.ም የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከ2.72 ቢሊየን...
29/10/2025

ከ2.72 ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ በበርካታ አካባቢዎች የንፁህ መጠጥ ውሃ የማውጣት ቁፋሮ ሊከናወን ነው

ገበያ ሚዲያ ጥቅምት 19/2018 ዓ.ም

የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከ2.72 ቢሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ በሱማሌ፣ ብላቴ፣ በአሳሳ፣ በቦቆጂ፣ በላይኛው ወይጦ እና በላይኛው ኦሞ አካባቢ የከርሰ ምድር ውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ ለማከናወን ውል ስምምነት መደረጉን አስታውቋል።

ስምምነቱ በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር እየተተገበረ የሚገኘው የአፍሪካ ቀንድ ዘላቂ የከርሰ ምድር ውሃ ፕሮጀክት አካል መሆኑም ተመላክቷል፡፡

ፕሮጀክቱ ከዓለም ባንክ በተገኘ 2 ቢሊየን 723 ሚሊየን ብር የገንዘብ ድጋፍ የሚከናወን ሲሆን፣ በውሉ መሰረት በ240 ቀናት እንደሚጠናቀቅ ሚኒስቴሩ አስታውቋል፡፡

የአካባቢውን ህብረተሰብ ከውሃ ጋር ተያይዞ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን በሚመልስ መልኩ ለመፍታት እና ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ ጥራቱን ጠብቆ እንዲሰራና የማማከር ስራውን በሚገባ በማከናወን ኃላፊነትን መወጣት እንደሚገባ የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር (ዶ/ር ኢ/ር) ሀብታሙ ኢተፋ አሳስበዋል።

በተጨማሪም በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የሚኒስትሩ አማካሪ አቶ ሞቱማ መቃሳ በበኩላቸው፣ በፕሮጀክቱ 49 የከርሰ ምድር ውሃ ጉድጓድ ቁፋሮ የሚከናወን ሲሆን፣ ከ500 ሜትር በላይ ጥልቀት እንደሚሸፍን ገልጸዋል፡፡

በዚህም ከ8 ኮንትራክተሮች ጋር የተወሰደው የጉድጓድ ቁፋሮ ውል ለመጠጥ ውሃ አገልግሎት ብቻ ሳይሆን፣ ኢትዮጵያ ያላትን የከርሰ ምድር ውሃ መጠን በማጥናትና በማወቅ ጉድጓዶችን መፈተሽ መሆኑንም አብራርተዋል።

Via AMN

የገበያ ሚዲያ ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን

Telegram:https://t.me/gebeyanews
Youtube: https://youtube.com/
Facebook: https://web.facebook.com/gebeyapromotion
TikTok: https://www.tiktok.com/



በአንድ ቦታ ብቻ 21 ትሪሊዮን ኪዩቢክ ጫማ የጋዝ ክምችት ተገኝቷል_ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ ገበያ ሚዲያ ጥቅምት 18/2018 ዓ.ም በዛሬው ዕለት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ ...
28/10/2025

በአንድ ቦታ ብቻ 21 ትሪሊዮን ኪዩቢክ ጫማ የጋዝ ክምችት ተገኝቷል_ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐብይ አህመድ

ገበያ ሚዲያ ጥቅምት 18/2018 ዓ.ም

በዛሬው ዕለት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ ማዕድንና ጋዝን በተመለከተ ለምክር ቤቱ በሰጡት ማብራሪያ፤ የማዕድን ሥራ በሀገር ኢኮኖሚ ዕድገት ውስጥ አንድ ከመቶ ድርሻ እየተጫወተ እንደሚገኝ ገልፀዋል።

በተለይም የጋዝ ፕሮጀክት በተጀመረበት ሶማሌ ክልል አካባቢ ትልቅ ክምችት መኖሩን አስታውቀው፤ በአንድ ቦታ ብቻ 21 ትሪሊዮን ኪዩቢክ ጫማ የጋዝ ክምችት ኢትዮጵያ እንዳላት በሶስተኛ ወገን መረጋገጡን ጠቅሰዋል።

ይህንንም ሃብት ላለፉት ዓመታት ለምን መጠቀም አልቻልንም ብሎ ከመቆጨት ይልቅ አሁን ያለውን አውቆ በፍጥነት መጠቀም ከሁላችንም የሚጠበቅ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሳስበዋል።

በተጨማሪም ከሁለት ዓመታት በፊት የጋዝ ፕሮጀክት የወሰደው አካል በበቂ መስራት ስላልቻለ ከቻይና መንግስት ጋር ስምምነት በመፈጸም GCG ግሩፕ ከሚባል ኩባንያ ጋር ውል ገብተን በ14 ወራት ውስጥ የመጀመሪያውን ዙር አጠናቀናል ብለዋል።

እንዲሁም ጋዝ በኢትዮጵያ ውስጥ መምረት ይችላል የሚለው እሳቤ በመፈጠሩ ሁለተኛውን ዙር ጋዝ ለማምረት ሂደቱ ተጀምሯል ብለው፣ በ24 ወራት ተጠናቆ ሪፖርት ለምክር ቤት እንደሚያቀርቡ ተናግረዋል።

የገበያ ሚዲያ ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን

Telegram:https://t.me/gebeyanews
Youtube: https://youtube.com/
Facebook: https://web.facebook.com/gebeyapromotion
TikTok: https://www.tiktok.com/



በተሽከርካሪ ላይ በደረሰ አደጋ የሰው ህይወት ማለፉንና በንብረት ላይ ጉዳት መድረሱ ተሰማገበያ ሚዲያ ጥቅምት 17/2018 ዓ.ምበምስራቅ ጎጃም ዞን በአነደድ ወረዳ አምበር ዙሪያ ቀበሌ የዳ ከ...
27/10/2025

በተሽከርካሪ ላይ በደረሰ አደጋ የሰው ህይወት ማለፉንና በንብረት ላይ ጉዳት መድረሱ ተሰማ

ገበያ ሚዲያ ጥቅምት 17/2018 ዓ.ም

በምስራቅ ጎጃም ዞን በአነደድ ወረዳ አምበር ዙሪያ ቀበሌ የዳ ከተባለው ስፍራ ጥቅምት በትናንትናው ዕለት ከቀኑ በግምት 11:00 ሰዓት አካባቢ በደረሠ የመኪና አደጋ የኤፌሳሩ እረዳት ህይወት ሲያልፍ በሁለት ሰዎች ላይ ከባድ የአካል ጉዳት ደርሷል ተብሏል።

አደጋው የደረሠው የሠሌዳ ቁጥር ኮ -3-A30015ኢ ት ካሶኒ ከአዲስ አበባ ወደ ደብረ ማርቆስ እና የሠሌዳ ቁጥር ኮድ 3-43763A.Aኤፌሳር ከደብረ ማርቆስ ወደ አዲስ አበባ በሬ ጭኖ ይጓዝ ከነበረው ጋር ተጋጭተው ነው የተባለ ሲሆን የአደጋው መንስኤ እየተጣራ ነው ተብሏል።

በደረሰው አደጋ በእንስሳቶችም ላይ ጉዳት ደርሷል የተባለ ሲሆን አሽከርካሪዎች አንደኛው በደብረ ማርቆስ ሪፈራል ሆስፒታል የህክምና እርዳታ የተደረገለት ሲሆን አንደኛው አሽከርካሪ ከስፍራው መሠወሩን የተናገሩት የወረዳው ወንጀል ምርመራ ክፍል ሀላፊ ኢ/ር ላመስግን ሞሴ በጥንቃቄ በማሽከርከር በሰውና በንብረትን ላይ የሚደርሰውን ጉዳትን በጋራ እንከላከል ሲሉ ጥሬቸውን አስተላልፈዋል፡፡

የገበያ ሚዲያ ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን

Telegram:https://t.me/gebeyanews
Youtube: https://youtube.com/
Facebook: https://web.facebook.com/gebeyapromotion
TikTok: https://www.tiktok.com/



Gebeya Media

የመንግስት ሠራተኞች የሥራ መደባቸው ሲሰረዝ እና መሥሪያ ቤታቸው ሲዘጋ ይቀነሳሉ ተባለገበያ ሚዲያ ጥቅምት 17/2018 ዓ.ም ማንኛውም የመንግስት ሠራተኛ የሥራ መደቡ ሲሰረዝ እና መሥሪያ ቤቱ...
27/10/2025

የመንግስት ሠራተኞች የሥራ መደባቸው ሲሰረዝ እና መሥሪያ ቤታቸው ሲዘጋ ይቀነሳሉ ተባለ

ገበያ ሚዲያ ጥቅምት 17/2018 ዓ.ም

ማንኛውም የመንግስት ሠራተኛ የሥራ መደቡ ሲሰረዝ እና መሥሪያ ቤቱ ሲዘጋ ከስራ ገበታ እንደሚቀነስ የፌደራል ሲቪል ስርቪስ ኮሚሽን አስታወቀ።

ኮሚሽኑ ይሄንን ያስታወቀው የመንግስት ሰራተኞች የተሻሻለው አዋጅ 1353/2017 ስለ መንግስት ሰራተኞች ቅነሳ ምን ይላል በሚል በማህበራዊ ድረገጹ ባሰፈረው ጽሁፍ ነው።

በዚህም በአዋጁ ክፍል አስራ አራት አንቀፅ 139 ላይ ማንኛውም የመንግስት ሠራተኛ የሥራ መደቡ ሲሰረዝ፣ መሥሪያ ቤቱ ሲዘጋ፣ ትርፍ የሰው ኃይል ሲኖር፤ እና ያለ በቂ ምክንያት ዝውውርን ካልተቀበለ እንደሚቀነስ ተመላክቷል።

በተጨማሪም በዚህ አዋጅ አንቀፅ 55/1 መሠረት ለመደልደል ካልተቻለ ወይም የመንግስት ሠራተኛው ዝቅ ባለ የሥራ ደረጃ ላይ ለመሥራት ፍቃደኛ ካልሆነ ይቀነሳል፡፡

በሌላ በኩል በዚህ አንቀፅ ንዑሰ አንቀፅ 1 (ሐ)መሠረት ቅነሳ የሚደረገው የመንግስት ሠራተኛው በመሥሪያ ቤቱ ውስጥ በተመሳሳይ የሥራ መደብ ላይ ካሉ ሌሎች የመንግሰት ሠራተኞች ጋር ሲወዳደር በሥራ ውጤቱና ባለው ችሎታ ዝቅተኛ መሆኑ ሲረጋገጥ እንደሆነ ያሳያል።

የገበያ ሚዲያ ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን

Telegram:https://t.me/gebeyanews
Youtube: https://youtube.com/
Facebook: https://web.facebook.com/gebeyapromotion
TikTok: https://www.tiktok.com/



Gebeya Media

የፈረሱ ነዳጅ ማደያዎች በድጋሚ ተገንብተው ወደ ሥራ ሊገቡ መሆኑ ተሰማገበያ ሚዲያ ጥቅምት 17/2018 ዓ.ምበአዲስ አበባ ከተማ በተካሄደው የኮሪደር ልማት ምክንያት ሙሉ ለሙሉ የፈረሱ እና በ...
27/10/2025

የፈረሱ ነዳጅ ማደያዎች በድጋሚ ተገንብተው ወደ ሥራ ሊገቡ መሆኑ ተሰማ

ገበያ ሚዲያ ጥቅምት 17/2018 ዓ.ም

በአዲስ አበባ ከተማ በተካሄደው የኮሪደር ልማት ምክንያት ሙሉ ለሙሉ የፈረሱ እና በከፊል የተጎዱ 13 የነዳጅ ማደያዎች በአዲስ ቦታ ተገንብተው በቅርብ ጊዜ ሥራ እንደሚጀምሩ ነዳጅ እና ኢነርጂ ባለሥልጣን አስታውቋል።

የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ዶ/ር ደስታው መኮንን፤ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስር ሲሰሩ የነበሩ እና በኮሪደር ልማት ምክንያት የፈረሱት ማደያዎች ተገቢ ቦታ ተመቻችቶላቸው በድጋሚ እንዲገነቡ መደረጋቸውን ገልጸዋል።

የማደያዎቹ በድጋሚ መገንባት በልማቱ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸውን ተቋማት ወደ ቀድሞ ሁኔታቸው የመመለስ ጥረት አካል መሆኑን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ፤ በክልል ከተሞችም ከኮሪደር ልማት ጋር በተያያዘ በከፊልና ሙሉ ለሙሉ የፈረሱ የነዳጅ ማደያዎችን በማደስ ወደ ሥራ እንዲገቡ ፈቃድ መሰጠቱን ተናግረዋል።

በከተሞች መካከል ያሉ የነዳጅ ማደያዎች ቁጥር አነስተኛ መሆኑን እንደ ችግር ያነሱ ሲሆን፤ ችግሩን የፈጠረው በሀገሪቱ ያሉ ነዳጅ ማደያዎች በጥናት ላይ ተመስርተው አለመገንባታቸው ነው ብለዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት ማደያዎች የሚገነቡት ከከተማ አስተዳደሩ በሚሰጥ ፈቃድ መሆኑን አስታውሰው፤ ባለሥልጣኑ ይሄንን ችግር ለመፍታት በየትኛው አካባቢ ምን ያህል የነዳጅ ማደያ ያስፈልጋል የሚለውን በማጥናት የጥናቱ ውጤት እና ምክረ-ሐሳቦቹን ለጠቅላይ ሚንስትር ጽሕፈት ቤት ልኳል ብለዋል።

በጥናት የተደገፈው አሰራር ተግባራዊ ሲደረግ ከፍተኛ ወረፋ እና መጨናነቅ ያለባቸውን እና የነዳጅ ማደያ እጥረት ያለባቸውን አካባቢዎች ችግር ያቃልላል የሚል እምነት እንዳላቸውም የባለስልጣኑ ዋና ዳይሬክተር መናገራቸውን አሃዱ ሬድዮ ዘግቧል።

የገበያ ሚዲያ ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን

Telegram:https://t.me/gebeyanews
Youtube: https://youtube.com/
Facebook: https://web.facebook.com/gebeyapromotion
TikTok: https://www.tiktok.com/



Gebeya Media

ለሳምንታት ተቋርጦ የነበረው የውሃ አገልግሎት ተመልሷል  _የአዲስ አበባ ከተማ ውሃ እና ፍሳሽ ባለሥልጣንገበያ ሚዲያ ጥቅምት 17/2018 ዓ.ም  የአዲስ አበባ ከተማ ውሃ እና ፍሳሽ ባለሥልጣ...
27/10/2025

ለሳምንታት ተቋርጦ የነበረው የውሃ አገልግሎት ተመልሷል _የአዲስ አበባ ከተማ ውሃ እና ፍሳሽ ባለሥልጣን

ገበያ ሚዲያ ጥቅምት 17/2018 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ከተማ ውሃ እና ፍሳሽ ባለሥልጣን የለገዳዲ ግድብ የውሃ ማስተላለፊያ ማማ የቫልቭ ቅየራ ስራ ከጥቅምት 2 ቀን 2018 ዓ/ም እስከ ጥቅምት 16 ቀን 2018 ዓም ድረስ እንደሚከናወን አስታውቆ ነበር።

በዚህም የቫልቭ ቅየራ ስራው እስከሚጠናቀቅም በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ፣ በቦሌ ክፍለ ከተማ እና በቂርቆስ ክፍለ ከተማ አንዳንድ ወረዳዎች የውሃ አቅርቦት ተቋርጦ ቆይቷል።

በመሆኑም ባለሥልጣኑ የቫልቭ ቅየራ ስራው መጠናቀቁን እና የለገዳዲ ግድብ በሙሉ አቅሙ ምርት መጀመሩን አስታውቋል።

ስራውን ሲያከናወ የቆየው ዊ ቢውልድ /ሳሊኒ/ ሲሆን የኢትዮጵያ ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን በማማከር አገልግሎት ተሳትፏል ተብሏል።

በዚህም " ያረጀ ቫልቩ ጥገና ባይከናወን የግድቡን ህልውና አደጋ ውስጥ ይከተው ነበር " ሲሉ የባለስልጣኑ ዋና ስራ አስኪያጅ ኢ/ር ዘሪሁን አባተ ተናግረዋል።

የገበያ ሚዲያ ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን

Telegram:https://t.me/gebeyanews
Youtube: https://youtube.com/
Facebook: https://web.facebook.com/gebeyapromotion
TikTok: https://www.tiktok.com/



Gebeya Media

የዉጪ ምንዛሬን ለመግዛት ሆነ ለመሸጥ ምርጥ እና አመቺ መንገድ መጣልዎጉዞ ካለብዎት ቪዛ እና ትኬትዎን ብቻ ይዘዉ ቢመጡ 10ሺ ዶላር ይገዛሉወደ አገር ቤት እየተመለሱ ከሆነ የከተማዉን ምርጥ ...
27/10/2025

የዉጪ ምንዛሬን ለመግዛት ሆነ ለመሸጥ
ምርጥ እና አመቺ መንገድ መጣልዎ
ጉዞ ካለብዎት ቪዛ እና ትኬትዎን ብቻ ይዘዉ ቢመጡ 10ሺ ዶላር ይገዛሉ
ወደ አገር ቤት እየተመለሱ ከሆነ የከተማዉን ምርጥ ዋጋ እኛ ጋር ያገኛሉ
ሮሃ የምንዛሬ ቢሮዎች ነን!
በሳር ቤት አዳምስ ፓቪሊዮን እንዲሁም በካዛንቺስ ማህቡባ አፓርትመንት ግራንድ ፓላስ ሆቴል ፊትለፊት
እና ድሬደዋ ብሎሰም ሆቴል ከመጡ ሁሉን ያገኛሉ
አቅጣጫን ለመጠየቅ የሚከተሉትን ስልኮች ይጠቀሙ
- በ251-956-555-333፣
- በ251-991-332-000፣
- በ251-960-444-333፣
በተሻለ ዋጋ መመንዘር ኢንቨስትመንት ነው!
የየለቱን የምንዛሬ ዋጋ ለመከታተል የሮሃን የምህበራዊ ሚዲያ ገጾች ይከታተሉ
ቴሌግራም፡ https://t.me/roohaforex
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/share/19hCtXhSH3/?mibextid=wwXIfr
ሊንክዲን፡ https://www.linkedin.com/company/rooha-forex-bureau/

አከራካሪው  የቅድመ ግብር ክፍያ ተነሳ።ገበያ ሚዲያ ጥቅምት 16/2018 ዓ.ም የገቢዎች ሚኒስቴር፣ የስንዴ ምርት አቀነባባሪ አምራቾች ለሚያደርጉት የስንዴ ግዥ የሚፈጸም ክፍያ ላይ የነበረው ...
26/10/2025

አከራካሪው የቅድመ ግብር ክፍያ ተነሳ።

ገበያ ሚዲያ ጥቅምት 16/2018 ዓ.ም

የገቢዎች ሚኒስቴር፣ የስንዴ ምርት አቀነባባሪ አምራቾች ለሚያደርጉት የስንዴ ግዥ የሚፈጸም ክፍያ ላይ የነበረው የ2% ቅድመ ግብር ክፍያ ሥርዓት ተፈጻሚ እንዳይሆን መወሰኑን አስታውቋል።

ሚኒስቴሩ ጥቅምት 4 ቀን 2018 ባሰራጨው ሰርኩላር የስንዴ ምርት አቀነባባሪ አምራቾች ለስንዴ ግዢ የሚፈጸም ክፍያ ላይ የነበራቸው ተደጋጋሚ ቅሬታ ላይ የገንዘብ ሚኒስቴር ውሳኔ መሰጠቱን ገልጿል።

በመሆኑም ይህ ውሳኔ የተላለፈው የስንዴ አቀነባባሪ አምራቾች በግዥ ወቅት ለሚከፍሉት ቅድመ ክፍያ፣ በታክስ ባለስልጣኑ ሻጮቹ ደረሰኝ መስጠት ስለማይገደዱ ግብይቱን ውድቅ በማድረግ ከፍተኛ ግብር እየጠየቀ ነው በሚል ለብሔራዊ ኢንዱስትሪው ካውንስል ባቀረቡት ጥያቄ መሠረት መሆኑ ተጠቁሟል።

ችግሩን ለመፍታት የተቋቋመው የጥናት ኮሚቴ ያቀረበው የውሳኔ ሀሳብ ተቀባይነት በማግኘቱ፣ የገንዘብ ሚኒስቴር ከወር በፊት በተጻፈ ደብዳቤ ውሳኔ አስተላልፏል።

ይህን ተከትሎ ለስንዴ ግዥ የሚፈጸም ክፍያ የቅድመ ግብር ክፍያ ሥርዓት ተፈጻሚ እንዳይሆን የተወሰነ ሲሆን ውሳኔውም በታክስ ውሳኔ ቅሬታ አጣሪ ጽ/ቤት በሂደት ላይ ባሉና በቀጣይ ኦዲት ሥራዎች ተፈጻሚ እንዲደረግ ታዟል።

የገቢዎች ሚኒስቴር ከሰሞኑ በላከዉ ሰርኩላር ላይ እንደተመላከተዉ ፤ የገንዘብ ሚኒስትር ዉሳኔ መሰረት በግዥ ማረጋገጫ የተፈጸመ ግብይት በሌሎች መረጃዎች እየተረጋገጠ ወጪውን የሚያዝበት ሥርዓት በታክስ ባለስልጣኑ በኩል እንዲዘረጋ አሳስቧል።

Via Capital

የገበያ ሚዲያ ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን

Telegram:https://t.me/gebeyanews
Youtube: https://youtube.com/
Facebook: https://web.facebook.com/gebeyapromotion
TikTok: https://www.tiktok.com/



Gebeya Media

25/10/2025

ገንብቶ በማስረከብ የሚታወቀው ዳኮርድ ሪል እስቴት በመሀል አዲስ አበባ ጀሞ_1 ግንባታቸው 90% እንዲሁም 40% የደረሡ ቤቶችን በ10% ቅድመ ክፍያ ብቻ ለሽያጭ አቀረበ፡፡
_በ1ወለል ላይ 3አባውራ ብቻ _በቂ የሆነ የመኪና ማቆሚያ ፣ ከሠፊ የአረንጓዴ ስፍራ ጋር አቀረበላችሁ፡፡
_ባለ1 መኝታ 80 ካሬ
_ባለ2 መኝታ 110 እና 118ካሬ
_ባለ3 መኝታ 135 ካሬ 70/30 የባንክ ብድር አመቻችቶ ከ623.000ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ የመኖሪያ ቤቶችን ለሽያጭ አቀረበ፡፡
ለበለጠ መረጃ በ 0911057674/0933219065ይደውሉ
ዳኮር እሪል እስቴት (በልዩነት የተገነባ)

ሙሉ ቪዲዮውን ለመመልከት ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ
⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️
https://youtu.be/nJ8qyOBD6qM

25/10/2025

በ90ሺ ብር ካፒታል በወር ከ40ሺ ብር በላይ የተጣራ ትርፍ ያለዉ አዋጭ ስራ

ሙሉ ቪዲዮውን ለማየት ከታች ያለውን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ።
⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️⬇️
https://youtu.be/-K9bccuIsrk

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሰበር መግለጫ ሰጠገበያ ሚዲያ ጥቅምት 14/2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የግል እና የሦስተኛ ወገን የባንክ ሒሳብ አጠቃቀም ዙሪያ በዛሬው ዕለት መግለጫ ሰጥ...
24/10/2025

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሰበር መግለጫ ሰጠ

ገበያ ሚዲያ ጥቅምት 14/2018 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የግል እና የሦስተኛ ወገን የባንክ ሒሳብ አጠቃቀም ዙሪያ በዛሬው ዕለት መግለጫ ሰጥቷል።

በዚህም በአዋጅ ቁጥር 1359/2017 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባደረገው ምርመራ ቁጥራቸው ቀላል የማይባሉ የባንክ ደንበኞች በዋናነት የንግድ ድርጅቶችና ግለሰብ ነጋዴዎች ለንግድ ሥራቸው ተብሎ ከተከፈተው እና በሚመለከተው የግብር ሰብሳቢ ተቋም ካስመዘገቡት የባንክ ሒሳቦች ውጭ የግል የባንክ ሂሳባቸው ወይም የሶስተኛ ወገን የባንክ ሒሳብ ተጠቅመው የተለያዩ የንግድ ግብይቶች እና የገንዘብ እንቅስቃሴዎች እየፈጸሙ መሆናቸውን አረጋግጫለሁ ብሏል።

ይህ አሰራር ከግብር ሰብሳቢ ባለስልጣናት ቁጥጥርና ክትትል ለመሸሽ የሚደረግ ተግባር ከመሆኑ በተጨማሪ በዚህ አግባብ የሚፈጸሙ የፋይናንስ ግብይቶች እና የገንዘብ እንቅስቃሴዎች የወንጀል ፍሬ ወይም ሽብርተኝነትን በገንዘብ ከመርዳት ጋር የተያያዙና የተገናኙ ሊሆኑ ይችላሉ ሲል በመግለጫው አስታውቋል።

ብሔራዊ ባንክ በመግለጫው አክሎም ፣ እነዚህን መሰል ተግባራት ለመግታት አስፈላጊው የተቀናጀ እርምጃ እንዲወሰድ ሲል ወስኗል።

በመሆኑም የፋይናንስ ሥርዓቱን ጤናማነትና ታማኝነት እንዲሁም በአጠቃላይ የኢኮኖሚ ደህንነት ለመጠበቅ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለሁሉም ባንኮች የግል ባንክ ሂሳቦችን ለንግድ እና ለሕገ-ወጥ ድርጊት የሚጠቀሙ ደንበኞችን አስመልክቶ አስፈላጊ መረጃዎችን በማደራጀት እንዲልኩ መመሪያ አስተላልፏል፡፡

የገበያ ሚዲያ ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን

Telegram:https://t.me/gebeyanews
Youtube: https://youtube.com/
Facebook: https://web.facebook.com/gebeyapromotion
TikTok: https://www.tiktok.com/



Gebeya Media

Address

Addis Ababa
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gebeya Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Gebeya Media:

Share