Gebeya Media

Gebeya Media Welcome to Gebeya Media! Gebeya Media is an online media startup that offers you market research, job opportunities, and a variety of business ideas.
(1)

ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን የምታደርገው ጥረት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ መድረሱ ተገለጸ ገበያ ሚዲያ ታህሳስ 02/2018 ዓ/ምኢትዮጵያ የአለም አቀፍ የንግድ ድርጅት አባል የመሆን...
11/12/2025

ኢትዮጵያ የዓለም ንግድ ድርጅት አባል ለመሆን የምታደርገው ጥረት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ መድረሱ ተገለጸ

ገበያ ሚዲያ ታህሳስ 02/2018 ዓ/ም

ኢትዮጵያ የአለም አቀፍ የንግድ ድርጅት አባል የመሆን ህልሟን እውን ለማድረግ ባደረገችው ፅናት የተሞላበት ጉዞና የድርድር ሂደት ወሳኝ ምዕራፍ ላይ ሲሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ተናገሩ፡፡
ይህ የተገለጸው ንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር " ኢትዮጵያን በንግድ በማስተሳሰር ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገር" በሚል መሪ ቃል የአለም የንግድ ድርጅት አባልነት የድርድር ሂደት እና እስካሁን በተከናወኑ ስራዎች ላይ ለባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ባተካሄደበት ወቅት ነው፡፡

በዚህም በ6ኛው የስራ ቡድን ስብሰባ ላይ የኢትዮጵያ የእስካሁኑ የስራ ቡድን ስብሰባ ሪፖርት ወደ ረቂቅ የስራ ቡድን ሪፖርትነት እንዲያድግ በመደረጉ የድርድር ሂደቱን አንድ እርምጃ ከፍ አድርጎታል ያሉት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይህም የባለ ብዙ ወገን የድርድር ሂደት መቋጫ ላይ እየደረስን መሆኑን ያሳያል ብለዋል።

ኢትዮጵያን የአለም የንግድ ድርጅት አባል ለማድረግ የተጀመረው የድርድር ሂደት ከሁለት አስርተ ዓመታት በላይ የፈጀ ቢሆንም ባሰለፍናቸው 7 ወራት ውስጥ በተካሄዱ 5ኛ እና 6ኛ የስራ በድን ስብሰባዎችም የድርድር ሂደቱ ወሳኝ ምዕራፍ ላይ መድረሱን እንደሚያመላክት ከንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር የተገኘው መረጃ ያሳያል፡፡

በተሰነጠቁ መሬቶች አማካኝነት የወጣው ድፍድፍ ነዳጅ ላይ ውሳኔ ሊሰጥ ነው ተባለገበያ ሚዲያ ታህሳስ 02/2018 ዓ/ምሰሞኑን በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ለገሂዳ ወረዳ ለዘመናት ከምድር ስር...
11/12/2025

በተሰነጠቁ መሬቶች አማካኝነት የወጣው ድፍድፍ ነዳጅ ላይ ውሳኔ ሊሰጥ ነው ተባለ

ገበያ ሚዲያ ታህሳስ 02/2018 ዓ/ም

ሰሞኑን በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ለገሂዳ ወረዳ ለዘመናት ከምድር ስር ሲብላላ የቆየ የነዳጅ ክምችት በተፈጥሮ አስገዳጅነት ከከርሰ ምድር በላይ መውጣቱ መዘገቡ አይዘነጋም።

ይህን ተከትሎም ለገሂዳና ወረኢሉ ወረዳዎችን በሚያዋስነው መቸላ ወንዝ በአለት ስንጥቅ ወጥቶ የሚታየው ነዳጅ ለሀገር ልማት እንዲውል ለማድረግ የሚቻልበት ሁኔታ ለመገምገም እና ውሳኔ ለመስጠት ከፌዴራል፣ ከክልል፣ ከዞን ዘርፉ የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት እንዲሁም ከወሎ እና ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተወጣጡ ባለድርሻ አካላት ትላንት ታህሳስ 1 ቀን 2018 ዓ.ም በቦታውተገኝተው ምልከታ ማድረጋቸው ተገልጿል።

በቦታው የተገኙት ባለድርሻ አካላት በአለት ላይ ከሚታየው ፈሳሽ ናሙና መውሰዳቸው የተሰማ ሲሆን ከዚህም በተጨማሪ በ2005 ዓ.ም ነዳጅ ሲያፈላልግ የነበረው ድርጅት ከፍተኛ ክምችት እንደሚገኝበት ጠቁሞት የነበረውን ጎራና ት/ቤት አካባቢ ከነዋሪዎች በተሰጣቸው ጥቆማ በመነሳት በጂፒኤስ መረጃ መውሰዳቸው ተነግሯል።

በተፈጥሮ አስገዳጅነት ከከርሰ ምድር በላይ ወጣ የተባለው ነዳጅ ለመመልከት በቦታው የተገኙት ባለድርሻ አካላት መንግስት ለማዕድን ዘርፍ ልዩ ትኩረት እንደሚሰጥ የተናገሩ ሲሆን ባለሙያዎቹ በደቡብ ወሎ ዞን ለገሂዳ ወረዳ ያዩትን ሀብትም ክትትል እንደሚደረግበት ማረጋገጣቸውን ገበያ ሚዲያ ከለገሂዳ ወረዳ ኮሚኒኬሽን ያገኘው መረጃ ያሳያል።

የገበያ ሚዲያ ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን

Telegram:https://t.me/gebeyanews
Youtube: https://youtube.com/
Facebook: https://web.facebook.com/gebeyapromotion



በሀገር አቀፍ ደረጃ የማርበርግ ቫይረስ ልየታ ሊደረግ ነው ተባለገበያ ሚዲያ ታህሳስ 1/2018 ዓ/ምይህ የተባለው የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት እና ጤና ሚኒስቴር የፖሊዮ ቀንን አስመልክቶ ከ...
10/12/2025

በሀገር አቀፍ ደረጃ የማርበርግ ቫይረስ ልየታ ሊደረግ ነው ተባለ

ገበያ ሚዲያ ታህሳስ 1/2018 ዓ/ም

ይህ የተባለው የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት እና ጤና ሚኒስቴር የፖሊዮ ቀንን አስመልክቶ ከተለያዩ አካላት ጋር ውይይት ባደረጉበት መድረክ ላይ ነው።

እንደ ሀገር እየተከሰቱ ያሉ በሽታዎች እና ወረርሽኞችን መነሻ በማድረግ በህብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት እና በጤና ሚኒስቴር በኩል የተለያዩ ስራዎች እየተሰሩ ነው ያሉት የኢትዮጵያ ህብረተሰብ ጤና አንስቲዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር መልካሙ አብቴ ከቀናት በኃላ በሚጀምረው የሀገር አቀፍ የፖሊዮ ክትባት ላይም ሁሉም ህፃናት መከተብ እንደሚኖርባቸው አስገንዝበዋል።

ዶክተር መልካሙ አክለውም ክትባቱን በሃገር አቀፍ ደረጃ ለመከወን በሚያስችል ሁኔታ ተቋማቸው ዝግጅቱን መጨረሱ ገልፀዋል። እድሜያቸውም ከ5 አመት በታች ለሆኑ ህጻናት ክትባቱ እንደሚሰጥ የገለጹት ምክትል ዳይሬክተሩ ከ25 ሚሊየን በላይ ህንጻናትን ለመከተብ መታቀዱን ተናግረዋል፡፡

ከታህሳስ 3 ቀን 2018 ዓ/ም ጀምሮ በሚካሄደው የፖሊዮ ክትባት ዘመቻ ከዚህ ቀደም የፖሊዮን ክትባት የወሰዱ እንዲሁም ወስደው ያቆሙ ህፃናት እንደሚከተቡ የገለፁት ዶ/ር መልካሙ የአሁኑ የፖሊዮ ክትባት ለየት ከሚያደርጉት ጉዳዮች ውስጥም በሀገሪቱ የተከሰተውን የማርበርግ ቫይረስን በሀገር አቀፍ ደረጃ ልየታ የሚደረግበት በመሆኑ ነው ብለዋል።

Via - መናኸሪያ ሬዲዮ

የገበያ ሚዲያ ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን

Telegram:https://t.me/gebeyanews
Youtube: https://youtube.com/
Facebook: https://web.facebook.com/gebeyapromotion



በነዳጅ ምርቶች ላይ የሚጣል የ30 በመቶ ግብር እንደማይኖር ተነገረገበያ ሚዲያ ታህሳስ 1/2018 ዓ/ምየነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ከታኅሳስ ወር 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በነዳጅ ምርቶች ላይ የ...
10/12/2025

በነዳጅ ምርቶች ላይ የሚጣል የ30 በመቶ ግብር እንደማይኖር ተነገረ

ገበያ ሚዲያ ታህሳስ 1/2018 ዓ/ም

የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ከታኅሳስ ወር 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በነዳጅ ምርቶች ላይ የሚተገበር የ30 በመቶ ግብር እንደማይኖር አስታውቋል።

ከታኅሳስ ወር 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በነዳጅ ምርቶች ላይ የ30 በመቶ ግብር ይጣላል የሚል መረጃ በማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ ሲዘዋወር መቆየቱን የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ደስታው መኳንንት ተናግረዋል።

በመሆኑም ይህ ሲዘዋዋር የነበረው መረጃ ሐሰተኛ መሆኑን ገልፀው ፣ከታኅሳስ ወር 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በነዳጅ ምርቶች ላይ የሚተገበር የ30 በመቶ ግብር አይኖርም ብለዋል።

የገንዘብ ሚኒስቴርን ጨምሮ በጉዳዩ ላይ በየትኛውም የመንግሥት አካል የተሰጠ መግለጫ እንደሌለ ማረጋገጣቸውን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ፣ ይጣላል የተባለው ግብር በማኅበራዊ ሚዲያው ላይ የተፈጠረ እንጂ፣ የነዳጅና ኢነርጂ ባለሥልጣንም የሚያውቀው ከዚህ ወር ጀምሮ የሚጣል ምንም ዓይነት የግብር ጭማሪ እንደማይደረግና መንግሥትም ይህን የማድረግ ዕሳቤ እንደሌለው ተናግረዋል ሲል ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል።

በዚህም ‹‹በሐሰተኛ መረጃ የተነሳ ኅብረተሰቡ ላልተገባ ሠልፍና እንግልት እየተዳረገ ይገኛል፤›› ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ፣ ያለ ምንም ይፋዊ የመንግሥት ውሳኔ ከወጣው የነዳጅ ዋጋ ውጪ ያለ አግባብ ጭማሪ የሚያደርጉ የነዳጅ አከፋፍይ ኩባንያዎችና ማደያዎች ተጠያቂ እንደሚደረጉም አሳስበዋል።

በአዲስ አበባ ከተማ በመደበኛ ሁኔታ ነዳጅ እየቀረበ መሆኑን ተናገረው፣ ነገር ግን በዚህ ሐሰተኛ መረጃ ምክንያት ፍጆታ ላይ ጭማሪ መፍጠሩን ገልጸዋል።

በዚህም የተናፈሰው መረጃ ስህተት መሆኑን ለነዳጅ ኩባንያዎችና ማደያዎች በተደጋጋሚ እያሳወቁ መሆናቸውን የገለጹት ዶ/ር ደስታው፣ ኩባንያዎች ባልተፈለገ መንገድ ተታለው ከጂቡቲ የተረከቡትን ነዳጅ ላልተገባ ጥቅም የማዋል ዕሳቤ እንዳይፈጠርባቸው ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

በሌላ በኩል ሰሞኑን በነዳጅ ምርቶች ላይ 15 በመቶ ተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) እና 15 በመቶ ደግሞ ኤክሳይዝ ቀረጥን ያካተተ አጠቃላይ 30 በመቶ ታክስ ይተገበራል መባሉ ይታወሳል።
Via ሪፖርተር

የገበያ ሚዲያ ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን

Telegram:https://t.me/gebeyanews
Youtube: https://youtube.com/
Facebook: https://web.facebook.com/gebeyapromotion



በጎረቤቷ ላይ አሲድ የደፋችው ግለሰብ 9 ዓመት ከ8 ወር ጽኑ እስራት ተፈረደባት  ገበያ ሚዲያ ህዳር 30/ 2018 ዓ.ም የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ተከሳሽ አበበች ቡናሻ የተባለች ...
09/12/2025

በጎረቤቷ ላይ አሲድ የደፋችው ግለሰብ 9 ዓመት ከ8 ወር ጽኑ እስራት ተፈረደባት

ገበያ ሚዲያ ህዳር 30/ 2018 ዓ.ም

የአዲስ አበባ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ተከሳሽ አበበች ቡናሻ የተባለች ግለሰብ ወንጀሉን የፈጸመችው መስከረም 7 ቀን 2018 ዓ/ም ከቀኑ 7 ሰዓት በየካ ክ/ከተማ ወረዳ 10 ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን አካባቢ መሆኑን አስታውቋል።

ተከሳሿ የግል ተበዳይ በር ላይ ቆሻሻ ደፍታ ስትመለስ የግል ተበዳይም ለምን እንደዚህ ታደርጊያለሽ ብላ በምትጠይቅበት ሰዓት በተፈጠረ አለመግባባት ተከሳሽ ፊት ላይ አሲድ በመድፋት በግራ አካሏ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ማድረሷን በየካ ክ/ከተማ ፖሊስ መምሪያ የኮተቤ አካባቢ ፖሊስ ጣቢያ ገልጿል።

ይህን ተከትሎ ፖሊስ የግል ተበዳይ መጎዳት ሪፖርት ከደረሰው ጀምሮ ወዲያው በቦታው ደርሶ ተጎጂን ወደ ህክምና በመውሰድ እንድትረዳ ማድረጉ ተጠቁሟል።

በዚህም ከህክምው ጎን ለጎን ተከሳሿን በቁጥጥር ስር በማዋል ተገቢውን መረጃና ማስረጃ የማሰባሰብ ሂደት እና የምርመራ ስራ በማጠናቀቅ በተጠርጣሪዋ ላይ በህክምና እና በሰው ማስረጃ የተጠናከረውን የምርመራ ውጤት ለአቃቤ ህግ ልኳል።

ጉዳዩ በአቃቤ ህግ ክስ ከተመሰረተ በኋላ ሂደቱን ሲከታተል የቆየው የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት የካ ምድብ 1ኛ ወንጀል ችሎት ህዳር 16 ቀን 2018 ዓ/ም በዋለው ችሎት በ9 ዓመት ከ8 ወር ጽኑ እስራት እንድትቀጣ ወስኖባታል።

የገበያ ሚዲያ ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን

Telegram:https://t.me/gebeyanews
Youtube: https://youtube.com/
Facebook: https://web.facebook.com/gebeyapromotion



ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ የሚደረግበት ቀን ይፋ ተደረገገበያ ሚዲያ ህዳር 30/2018 ዓ/ምየኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ የድምጽ መስጫ ቀን ሰኞ ግንቦት 24/2018 ዓ...
09/12/2025

ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ የሚደረግበት ቀን ይፋ ተደረገ

ገበያ ሚዲያ ህዳር 30/2018 ዓ/ም

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ የድምጽ መስጫ ቀን ሰኞ ግንቦት 24/2018 ዓ/ም ሆኖ መጽደቁን አስታውቋል።

ቦርዱ ከየካቲት 16 ቀን 2017 ዓ/ም ጀምሮ የምርጫ ፅህፈት ቤቶችን ማደራጀት የጀመረ ሲሆን፣ እስክ ታህሳስ 15 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስም እንደሚቀጥል ገልጿል።

እስከ ድምፅ መስጫ ቀን ድረስ ባሉ ቀናት፣ የመራጮች ትምህርት ለሚሰጡ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እውቅና መስጠት፣ የምርጫ አስፈፃሚዎች ምልመላ፣ የምርጫ አስፈፃሚዎችን ዝርዝር ለፖለቲካ ፓርቲዎች እና ለግም ዕጩዎች ቅድመ ምዝገባ ሰነዶች ማቅረብ፣ የመሳሰሉ እና ሌሎች በርካታ ድርጊቶችን እንደሚከውን ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ አስታውቋል።

ቦርዱ ባወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት ከጥር 01 እስከ የካቲት 01 ቀን የዕጩዎች ምዝገባ እንደሚካሄድ ያስታወቀ ሲሆን፣ ከጥር 01 እስከ ግንቦት 19 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ ደግሞ የምረጡኝ ቅስቀሳ የሚደረግበት ጊዜ መሆኑ ተጠቅሷል።

ከዚህ በተጨማሪ የምርጫ ውጤት በቦርዱ ደረጃ ይፋ የሚደረገው ሰኔ 4 ቀን እንደሆነ ገልጿል።

የገበያ ሚዲያ ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን

Telegram:https://t.me/gebeyanews
Youtube: https://youtube.com/
Facebook: https://web.facebook.com/gebeyapromotion



ቲክቶከሮቹ በቁጥጥር ስር ዋሉገበያ ሚዲያ ህዳር 30/2018 ዓ/ምየኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከባህልና ሥነ-ምግባር ያፈነገጠ አስነዋሪ አለባበስ ለብሰው በአደባባይ እና በቴሌቪዥን በቀጥታ ስርጭት...
09/12/2025

ቲክቶከሮቹ በቁጥጥር ስር ዋሉ

ገበያ ሚዲያ ህዳር 30/2018 ዓ/ም

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከባህልና ሥነ-ምግባር ያፈነገጠ አስነዋሪ አለባበስ ለብሰው በአደባባይ እና በቴሌቪዥን በቀጥታ ስርጭት ለሕዝብ የታዩ ተጠርጣሪዎች ላይ ምርመራ መጀመሩን አስታውቋል።

ፌደራል ፖሊስ በ3ኛው የG-Power TikTok Creative Award ላይ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ባህልና ሥነ-ምግባር ባፈነገጠ አኳሃን ሰውነታቸውን የገላለጠ አለባበስ ለብሰው በአደባባይና በቴሌቪዥን ቀጥታ ስርጭት ለሕዝብ የታዩ ተጠርጣሪዎችን ከነግብረ-አበሮቻቸው በቁጥጥር ሥር ማዋሉን ገልጿል።

‎በዚህም መሰረት ወንጌላዊት ገብረ እንድርያስ በርሄ፣ በርከት ፀጋዬ ጅፋር፣ መቅድም ደረጄ መንግስቱ፣ ግሩም ገዛሀኝ ቀጭኔ እና ዮሃንስ መኮንን ሀ/ማርየም ‎የተባሉ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ መጀመሩን ገልጿል።

የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከህብረተሰቡ ባህልና እሴት ያፈነገጡ አለባበሶችና መጤ ባህሎች ተስፋፍተው በትዉልዱ ላይ አሉታዊ ተጽእኖ እንዳያስከትሉ ተጠርጣሪዎቹ ላይ የሕግ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ የጀመረውን ምርመራ አጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጧል።

የገበያ ሚዲያ ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን

Telegram:https://t.me/gebeyanews
Youtube: https://youtube.com/
Facebook: https://web.facebook.com/gebeyapromotion



የሰኞ የውጭ ምንዛሬ ተመን! ዶላር፣ ዩሮ ፣  ድርሃም ወይም ፓውንድ ይፈልጋሉ? ሮሃ ፎሬክስ (Rooha Forex) አዲሱን ሳምንት በምርጥ ዋጋ ጀምሯል!የዛሬ ዋጋዎችን በሰንጠረዡ ይመልከቱ ፈጣ...
08/12/2025

የሰኞ የውጭ ምንዛሬ ተመን!

ዶላር፣ ዩሮ ፣ ድርሃም ወይም ፓውንድ ይፈልጋሉ?

ሮሃ ፎሬክስ (Rooha Forex) አዲሱን ሳምንት በምርጥ ዋጋ ጀምሯል!

የዛሬ ዋጋዎችን በሰንጠረዡ ይመልከቱ

ፈጣን አገልግሎት፣ አስተማማኝ ቦታ እና ተወዳዳሪ የሌለው ዋጋ።

የየቀኑን ትኩስ የምንዛሬ መረጃ ለማግኘት ገጻችንን ይቀላቀሉ:

ቴሌግራም፡ https://t.me/roohaforex
ፌስቡክ፡ https://www.facebook.com/share/19hCtXhSH3/?mibextid=wwXIfr
ሊንክዲን፡ https://www.linkedin.com/company/rooha-forex-bureau/

ይደዉሉ፡
- በ251-956-555-333፣
- በ251-991-332-000፣
- በ251-960-444-333፣

የኢሳያስ ውድቀት ተቃረበ!
07/12/2025

የኢሳያስ ውድቀት ተቃረበ!

ገበያ ሚዲያን ይወዳጁ !Telegram👉 https://t.me/gebeyanewshttps://youtube.com/ to Gebeya Media! Gebeya Media is an online media startup that offers...

ማንኛዉም የኦንላይን ነጋዴ የንግድ ፈቃድ ማውጣትና ደረሰኝ የመቁረጥ ግዴታ አለበት ተባለገበያ ሚዲያ ህዳር 27/2018 ዓ.ምበኦንላይን ግብይቶችን የሚያከናዉን ማንኛዉም ዜጋ የንግድ ፈቃድ ማው...
06/12/2025

ማንኛዉም የኦንላይን ነጋዴ የንግድ ፈቃድ ማውጣትና ደረሰኝ የመቁረጥ ግዴታ አለበት ተባለ

ገበያ ሚዲያ ህዳር 27/2018 ዓ.ም

በኦንላይን ግብይቶችን የሚያከናዉን ማንኛዉም ዜጋ የንግድ ፈቃድ ማውጣትና ደረሰኝ የመቁረጥ ግዴታ አለበት ተብሏል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ በኦንላይን የሚደረጉ ማንኛዉም አይነት ግብይቶችን በደረሰኝ ለማከናወን አዲስ ዲፓርትመንት መቋቋሙን አስታዉቋል።

አዲስ የተቋቋመዉ ዲፓርትመንት በቅርቡ ተግባራዊ እንደሚሆን በመግለጽ፤ በከተማ አስተዳደሩ ገቢዎች ቢሮ ስር በመሆን የቁጥጥር ስራዎችን ያከናዉናል ሲሉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ገቢዎች ቢሮ የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተር አቶ ሰዉነት አየለ ለገበያ ሚዲያ ተናግረዋል።

በዚህም በኦንላይን ምርቶችን የሚሸጥ ማንኛዉም አካል ንግድ ፈቃድ ማዉጣት እንዳለበት እና ደረሰኝ የመቁረጥ ግዴታ እንዳለበት በማወቅ ካሁኑ ዝግጅት ማድረግ ያስፈልጋል ያሉት አቶ ሰዉነት ፤ ይህን አሰራር ተግባራዊ ለማድረግ ደግሞ የቁጥጥር ስራው በቅርቡ ይጀመራል ብለዋል።

የህዝብ ግንኙነት ዳይሬክተሩ አክለዉም፤ በቅርቡ የወጣው የገቢ ግብር አዋጅ ቁጥር 1195/2017ም በኦንላይን የሚደረጉ ግብይቶችን የሚያከናውን ማንኛዉም ዜጋ (የኦንላይን ነጋዴ) ንግድ ፈቃድ ማዉጣት እንዳለበት ይደነግጋል ሲሉ ከገበያ ሚዲያ ጋር በነበራቸው ቆይታ አብራርተዋል።

በተጨማሪም አሰራሩ ወደ ተግባር ሲገባ ከቦታ ቦታ እቃ ዴሊቨር በሚደረግበት ጊዜም ከደረሰኙ ጋር አብሮ ለሸማቹ እንዲደርስ ማድረግ እንዳለበትም የተጠቆመ ሲሆን፤ ከእዚህ ውጪ በኦንላይን በማስተዋወቅ ያለ ደረሰኝ የሚደረጉ ግብይቶች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር እየተደረገ በመሆኑ፣ ሁሉም ሰው ተገንዝቦ ወደ ህጋዊ ስርአት መምጣት እንደሚኖርበትም ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

በሌላ በኩል በኦንላይን የሚደረጉ ግብይቶችና ማንኛውም ምርቶችን የሚሸጥ ነጋዴ ንግድ ፈቃድ ሊኖረው ይገባል ብለዉ፣ ኦንላይን መሸጡን እናበረታታለን ነገር ግን ማንኛዉም ዜጋ በኦንላይን ምርቶችን በሚሸጥበት ጊዜ ደረሰኝ የመቁረጥ ግዴታ አለበት ሲሉ የገቢዎች ቢሮ ሃላፊ አቶ ቢኒያም ምክሩ ከቀናት በፊት ገልጸው እንደነበር መዘገባችን አይዘነጋም።

በመላኩ ደምሰው

የገበያ ሚዲያ ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን

Telegram:https://t.me/gebeyanews
Youtube: https://youtube.com/
Facebook: https://web.facebook.com/gebeyapromotion



ከሃያት ወደ ጦር ኃይሎች  መስመር የባቡር ትራንስፖርት ሙሉ በሙሉ መቋረጡ ተገለፀ ገበያ ሚዲያ ህዳር 27/2018 ዓ.ም በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ትራንስፖርት መስመር ላይ የሚገኘው ከሃያት ...
06/12/2025

ከሃያት ወደ ጦር ኃይሎች መስመር የባቡር ትራንስፖርት ሙሉ በሙሉ መቋረጡ ተገለፀ

ገበያ ሚዲያ ህዳር 27/2018 ዓ.ም

በአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ትራንስፖርት መስመር ላይ የሚገኘው ከሃያት ወደ ጦር ኃይሎች የሚወስደው መስመር መገናኛ አካባቢ ለም ሆቴል መሻገሪያ ላይ በተፈጠረ ብልሽት ምክንያት አገልግሎቱ መቋረጡ ተገልጿል።

ብልሽቱ የተከሰተው ለም ሆቴል አቅራቢያ በቅርቡ ለመተላለፊያነት በተሰራ መንገድ ላይ ሲሆን፣ ተደራራቢ የአንበሳ አውቶቡስ መንገዱን ሲያቋርጥ የቀላል ባቡሩን ማስተላለፊያ የኤሌክትሪክ ገመድ በመበጠሱ አደጋው እንደደረሰ ተነግሯል።

በዚህ አደጋ ምክንያት የባቡር አገልግሎቱ ሙሉ በሙሉ በመቋረጡ፣ በወቅቱ በመስመሩ ላይ የነበረው ባቡርም ተሳፋሪዎችን ለማውረድ መገደዱም ተገልጿል።

ይህን መሰል የባቡር መሠረተ ልማት ብልሽት (የኤሌክትሪክ ገመድ መበጠስ) ከዚህ በፊት አጋጥሞ እንደማያውቅና የባቡር ትራንስፖርት አገልግሎት ድርጅት የኤሌክትሪክ ገመዱን በአስቸኳይ ለመጠገን ጥረት እያደረገ ነው ተብሏል።

በዚህም የሃያት-ጦር ኃይሎች መስመር ተጠቃሚዎችም አገልግሎቱ ወደ መደበኛ ሥራው እስኪመለስ ድረስ የትራንስፖርት አማራጮችን እንዲጠቀሙ ተጠይቀዋል።

Via Capital

የገበያ ሚዲያ ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን

Telegram:https://t.me/gebeyanews
Youtube: https://youtube.com/
Facebook: https://web.facebook.com/gebeyapromotion



የትራንስፖርት ክልከላዉ መነሳቱ ተገለፀ ‎ገበያ ሚድያ ህዳር 27/2018 ዓ/ም‎በጂንካ በተከሰተዉ የማርበርግ ቫይረስ ስርጭት ምክንያት ተጥሎ የነበረዉ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች እንቅስቃ...
06/12/2025

የትራንስፖርት ክልከላዉ መነሳቱ ተገለፀ

ገበያ ሚድያ ህዳር 27/2018 ዓ/ም

‎በጂንካ በተከሰተዉ የማርበርግ ቫይረስ ስርጭት ምክንያት ተጥሎ የነበረዉ የህዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪዎች እንቅስቃሴ ገደብ መነሳቱን የአሪ ዞን መንግስት ኮሚኒኬሽን ኃላፊ አቶ ደምበላሽ አቦነሀሰ አስታውቀዋል።

‎ለክልከላዉ መነሳት እንደ ምክንያት የተጠቀሰው አሁናዊዉ የማርበርግ ቫይረስ ስርጭት መቀነስ ሲሆን፤ በትራንስፖርት መቋረጥ ምክንያት ማህበረሰቡ የእለት ተዕለት እንቅስቃሴ ላይ ከፍተኛ ጫና እያሳደረ መምጣቱን የዞኑ ግብረሃይል ከገመገመ በኋላ ገደቡን ለማንሳት መወሰኑን ገልፀዋል።

‎በዚህም መሰረት ከዛሬ ህዳር 27 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ክልከላው እንደሚነሳ የገለፁት ኃላፊዉ ጉዞዎች ግን ከወትሮዉ በተለየ በጥንቃቄ መሆን እንዳለባቸውና በየመናኻሪያ የሚደረጉ የግንዛቤ ማስጨበጫና የጥንቃቄ ሂደቶች ተጠናክረዉ እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።

‎ሕብረተሰቡና የተሽከርካሪ ባለንብረቶችም ይህንኑ በመረዳት አስፈላጊውን ጥንቃቄ እንዲያደርጉም አቶ ደምበላሽ አሳስበዋል።

Via - ቲክቫህ ኢትዮጵያ

የገበያ ሚዲያ ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን

Telegram:https://t.me/gebeyanews
Youtube: https://youtube.com/
Facebook: https://web.facebook.com/gebeyapromotion



Address

Addis Ababa
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gebeya Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Gebeya Media:

Share