Gebeya Media

Gebeya Media Welcome to Gebeya Media! Gebeya Media is an online media startup that offers you market research, job opportunities, and a variety of business ideas.

የፓስፖርት አገልግሎት የሚሰጥበት ሰዓት ተራዘመ ገበያ ሚዲያ መስከረም 03/2018 ዓ.ም  የኢሚግሬሽንና ዜግነት አግልግሎት መስከረም 02/2018 ዓ.ም ጀምሮ አዲስ አበባን ጨምሮ በሌሎች የክ...
13/09/2025

የፓስፖርት አገልግሎት የሚሰጥበት ሰዓት ተራዘመ

ገበያ ሚዲያ መስከረም 03/2018 ዓ.ም

የኢሚግሬሽንና ዜግነት አግልግሎት መስከረም 02/2018 ዓ.ም ጀምሮ አዲስ አበባን ጨምሮ በሌሎች የክልል ከተሞች በሚገኙ ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች እስከ ምሽት 4 ሰአት አገልግሎት ሊሰጥ መሆኑን አስታውቋል።

በዚህም በአዲስ አበባ ጎተራ እና ጥቁር አንበሳ ቢሮዎች ጨምሮ በሌሎች የክልል ከተሞች በሚገኙ ቅርንጫፍ ፅ/ቤቶች እስከ ምሽት 4 ሰአት የፓስፓርት አግልግሎት መስጠት መጀመሩን አገልግሎቱ ገልጿል።

በዚሁ መሰረት ተቋሙ ከሰኞ እስከ ቅዳሜ እስከ ምሽት 4፡00 ድረስ እሁድ ደግሞ እስከ ማታ 12፡00 ሰአት አግልግሎት እንደሚሰጥ አክሏል።

በሌላ በኩል የፓስፓርት ፈላጊዎች በተቋሙ ትክክለኛ ድረ ገፆች ላይ የአስቸኳይ ፥ የእድሳት እና ሌሎች የፓስፓርት አገልግሎቶችን ማግኘት እንደሚችሉ አመልክቷል።
የገበያ ሚዲያ ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን

Telegram:https://t.me/gebeyanews
Youtube: https://youtube.com/
Facebook: https://web.facebook.com/gebeyapromotion
TikTok: https://www.tiktok.com/



Gebeya Media

11ኛው የብሔራዊ ባንክ አዲሱ ዋና ገዢ ታወቀገበያ ሚዲያ መስከረም 3/2017 ዓ.ም የፕላንና ልማት ሚኒሰትር የነበሩት  ዶ/ር ፍፁም አሰፋ የብሔራዊ ባንክ ገዢ ሆነው መሾማቸው ታውቋል።ዶ/ር ...
13/09/2025

11ኛው የብሔራዊ ባንክ አዲሱ ዋና ገዢ ታወቀ

ገበያ ሚዲያ መስከረም 3/2017 ዓ.ም

የፕላንና ልማት ሚኒሰትር የነበሩት ዶ/ር ፍፁም አሰፋ የብሔራዊ ባንክ ገዢ ሆነው መሾማቸው ታውቋል።

ዶ/ር ፍፁም አሰፋ በመንግሥት በተለያዩ የስልጣን ዘርፍ ያገለገሉ ሲሆን የብሔራዊ ባንክ ገዢ ከመሆናቸው በፊት የፕላንና ልማት ሚኒስትር ሆነው እየሰሩ ነበር።

የቀድሞ የብሔራዊ ባንክ ገዢ የነበሩ አቶ ማሞ ምህረቱን በመተካት 11ኛዋ የብሔራዊ ባንክ ገዢ በመሆን መሾማቸው ተሰምቷል።

የገበያ ሚዲያ ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን

Telegram:https://t.me/gebeyanews
Youtube: https://youtube.com/
Facebook: https://web.facebook.com/gebeyapromotion
TikTok: https://www.tiktok.com/



Gebeya Media

ልጆችን ወደ ትምህርት ቤት የማይልክ ወላጅ ከፍተኛ ቅጣት ሊጣልበት ነው።ገበያ ሚዲያ መስከረም 2/2017 ዓ.ምየትምህርት ሚኒስቴር የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ነጻና ግዴታ መሆኑን በመገንዘብ ወላ...
12/09/2025

ልጆችን ወደ ትምህርት ቤት የማይልክ ወላጅ ከፍተኛ ቅጣት ሊጣልበት ነው።

ገበያ ሚዲያ መስከረም 2/2017 ዓ.ም

የትምህርት ሚኒስቴር የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ነጻና ግዴታ መሆኑን በመገንዘብ ወላጅ ወይም አሳዳጊ ዕድሜው ለትምህርት የደረሰ ልጅን ወደ ትምህርት ቤት መላክ እንዳለበት አሳስቧል።

በዚህም ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ልጆችን ወደ ትምህርት ቤት አለመላክ ደግሞ የሚያስቀጣ ህግ መደንገጉን በሚኒስቴሩ የትምህርት ፕሮግራሞችና ሥርዓት ማሻሻል ዴስክ ኃላፊ ዳዊት አዘነ ተናግረዋል።

በተጨማሪም የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ነጻ እና ግዴት እንዲሆን በትምህርት ሕጉ ላይ ተደንግጓል ያሉት ኃላፊው፣ ወላጆች ፣ አሳዳጊዎች፣ ሕብረተሰቡና ባለድርሻ አካላት ዕድሜያቸው ለትምህርት የደረሱ ልጆች ከትምህርት ገበታ ውጭ እንዳይሆኑ ሊረባረቡ ይገባል ሲሉ አሳስበዋል።

በሌላ በኩል በ2018 ከቅድመ መደበኛ እስከ 12ኛ ክፍል 31.9 ሚሊዮን ተማሪዎችን ለማስተማር መታቀዱን እና ከእነዚህ ደግሞ መካከል 15 ሚሊዮኑ ሴቶች መሆናቸውን ተጠቁሟል።

በዚህም ከመጪው መስከረም 5 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በሁሉም ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች የዘንድሮው ዓመት የመማር ማስተማር ሥራ ይጀመራል ሲል ሚኒስቴሩ አስታውቋል።

Via ኢዜአ

የገበያ ሚዲያ ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን

Telegram:https://t.me/gebeyanews
Youtube: https://youtube.com/
Facebook: https://web.facebook.com/gebeyapromotion
TikTok: https://www.tiktok.com/



Gebeya Media

🌼እንኳን ለ2018 አዲስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ🌼ለመላው ኢትዮጵጵያዊያን አዲሱ አመት የሰላም፣ የጤና፣ የስኬት እንዲሆንላችሁ ልባዊ ምኞታችን ነው።ገበያ ሚዲያ መስከረም 1/ 2018 ዓ.ም🌼መ...
11/09/2025

🌼እንኳን ለ2018 አዲስ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ🌼

ለመላው ኢትዮጵጵያዊያን አዲሱ አመት የሰላም፣ የጤና፣ የስኬት እንዲሆንላችሁ ልባዊ ምኞታችን ነው።

ገበያ ሚዲያ መስከረም 1/ 2018 ዓ.ም

🌼መልካም አውደ ዓመት!🌼

የገበያ ሚዲያ ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን

Telegram:https://t.me/gebeyanews
Youtube: https://youtube.com/
Facebook: https://web.facebook.com/gebeyapromotion
TikTok: https://www.tiktok.com/



Gebeya Media

አስገራሚው የበግና ፍየል ዋጋ! የ2018 አዲስ ዓመት ገበያ ቅኝት
10/09/2025

አስገራሚው የበግና ፍየል ዋጋ! የ2018 አዲስ ዓመት ገበያ ቅኝት

አስገራሚው የበግና ፍየል ዋጋ! የ2018 አዲስ ዓመት ገበያ ቅኝት | Ethiopian New Year's Market Review | Gebeya Review

ሌላ ታላቅ ብስራት ‼️
09/09/2025

ሌላ ታላቅ ብስራት ‼️

ገበያ ሚዲያን ይወዳጁ !Telegram👉 https://t.me/gebeyanewshttps://youtube.com/ to Gebeya Media! Gebeya Media is an online media startup that offers...

የቀድሞው ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ፕሮጀክት እፈልግላሁ  በፍጥነት ስራው አለኝ _ፔትሮ ሳሊኒገበያ ሚዲያ ጳጉሜ 4/2017 ዓ.ም  በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ምርቃት ላይ የታደሙት የጣሊያ...
09/09/2025

የቀድሞው ጠ/ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ፕሮጀክት እፈልግላሁ በፍጥነት ስራው አለኝ _ፔትሮ ሳሊኒ

ገበያ ሚዲያ ጳጉሜ 4/2017 ዓ.ም

በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ምርቃት ላይ የታደሙት የጣሊያኑ ሳሊኒ ኩባንያ ስራ አስኪያጅ ፔትሮ ሳሊኒ ስለ ቀድሞው የኢትዮጵያ ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ የተናገሩት ንግግር አነጋጋሪ ሆኗል።

ፔትሮ ሳሊኒ በጉባ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር ቀድሞው የኢትዮጵያ ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ ለዚህ አገር ሕልም አለኝ፤ የተትረፈረፈ የኃይል ሉዓላዊነት፣ እናም ዓባይ ላይ ፕሮጀክት ልትነድፍልኝ ትችላለህ ? ታላቅ ፕሮጀክት፤ ቢያንስ 6 ሺህ ሜጋ ዋት የሚያመነጭ እፈልግላሁ ብሎኝ ነበር ማለታቸው ተሰምቷል።

ስራ አስኪያጁ አክለውም ፣ቀድሞው ጠ/ሚ መለስ በፍጥነት ስራው አለኝ ግን ከአንድ ዓመት በኋላ ሕይወቱ አለፈ ሲሉ ተናግረዋል።

የጣሊያኑ ሳሊኒ (ዊ ቢውልድ) ኩባንያ ስራ አስኪያጅ ፔትሮ ሳሊኒ፤ ኢትዮጵያ የዓባይ ግድብን እንድትሰራ ማንም ፍላጎት እንዳልነበረውና ብዙ ፖለቲካዊ ችግሮች እንደነበሩ አንስተው፤ ኢትዮጵያዊያን ግን ችግር ፈሪ ስላልሆኑ ግድቡን እውን አድርገውታል ሲሉ ተደምጠዋል።

በሌላ በኩል 25 ሺህ ወጣቶች በሥራ ላይ የአቅም ግንባታ ስልጠና እንደተሰጣቸው ጠቅሰው፤ ይህም ለሀገሪቱ የእውቀት፣ የክህሎትና ቴክኖሎጂ ሽግግር መሰረታዊ አበርክቶ እንዳለው አስገንዝበዋል።

የገበያ ሚዲያ ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን

Telegram:https://t.me/gebeyanews
Youtube: https://youtube.com/
Facebook: https://web.facebook.com/gebeyapromotion
TikTok: https://www.tiktok.com/



Gebeya Media

ከህዳሴ ፕሮጀክት በተጨማሪ በቅርቡ የሚገነቡና የሚመረቁ ከ5 በላይ አዳዲስ ሜጋ ፐሮጀክቶች ይፋ ሆኑ።ገበያ ሚዲያ ጳጉሜ 4/2017በዛሬው ዕለት በታላቁ ህዳሴ ግድብ  የምርቃት ሥነሥርዓት ላይ ...
09/09/2025

ከህዳሴ ፕሮጀክት በተጨማሪ በቅርቡ የሚገነቡና የሚመረቁ ከ5 በላይ አዳዲስ ሜጋ ፐሮጀክቶች ይፋ ሆኑ።

ገበያ ሚዲያ ጳጉሜ 4/2017

በዛሬው ዕለት በታላቁ ህዳሴ ግድብ የምርቃት ሥነሥርዓት ላይ ንግግር ያደረጉት ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ፤ በርካታ አዳዲስ ሜጋ ፐሮጀክቶችን ይፋ አድርገዋል፡፡

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ይፋ ካደረጓቸው ሜጋ ፐሮጀክቶች መካከል ፣ ከሕዳሴ ግድብ የሚስተካከል፣ ለሰላማዊ አገልግሎት የሚውል የኒውክሌር ማበልጸጊያ ግንባታና ነዳጅ የማውጣት ፍላጎት እውን የሚያደርገው የንዳጅ ማጣሪያ ፕሮጀክት ይገኝበታል።

በተጨማሪም በአፍሪካ ግዙፍ የሆነው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግንባታ በቅርቡ ይጀመራል ያሉት ጠ/ሚኒስትሩ፤ በጥቂት ሳምንታት ውስጥ ደግሞ የመጀመሪያው የጋዝ ፋብሪካ ይመረቃል፤ በዛው ዕለት ከመጀመሪያው በ10 እጥፍ የሚበልጠው ሁለተኛው የጋዝ ፋብሪካ ግንባታ እንደሚጀመርም ገልጸዋል፡፡

አክለውም፤ የኢትዮጵያን የረጅም ዘመን ነዳጅ የማውጣት ፍላጎት እውን የሚያደርገው የንዳጅ ማጣሪያ እውን እንደሚሆን ተናግው፣ በቅርቡ የተፈረመው የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታም በቀጣይ ጥቂት ጊዜያት እንደሚጀመር ጠቁመዋል፡፡

በሌላ በኩል በሚቀጥሉት 5 እና 6 ዓመታት በትንሹ ከ1.5 ሚሊየን በላይ ቤቶች ይገነባሉ ብለው ፣ በአጠቃላይ ከ30 ቢሊየን ዶላር በላይ ሃብት የሚፈስስባቸው ሜጋ ፕሮጀክቶች እንደሚከናወኑ ገልጸዋል።

የገበያ ሚዲያ ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን

Telegram:https://t.me/gebeyanews
Youtube: https://youtube.com/
Facebook: https://web.facebook.com/gebeyapromotion
TikTok: https://www.tiktok.com/



Gebeya Media

ህዳሴ ተመረቀ!ገበያ ሚዲያ ጳጉሜ 4፣ 2017 ዓ.ም  ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ  የኢትዮጵያውያን ሕብረ ብሔራዊነት መገለጫ የሆነውን ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ በዛሬው ዕለት መ...
09/09/2025

ህዳሴ ተመረቀ!

ገበያ ሚዲያ ጳጉሜ 4፣ 2017 ዓ.ም

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ የኢትዮጵያውያን ሕብረ ብሔራዊነት መገለጫ የሆነውን ታላቁ የኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ በዛሬው ዕለት መርቀዋል።

የኢትዮጵያውያን የዘመናት ቁጭት የነበረው ታላቁ ኢትዮጵያ ኅዳሴ ግድብ ግንባታ ተጠናቅቆ የምረቃ ሥነ ሥርዓት በጉባ እየተካሄደ ይገኛል።

በምረቃ ሥነ ሥርዓቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ፣ የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባዔ አገኘሁ ተሻገር፣ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባዔ ታገሰ ጫፎ እና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ተገኝተዋል፡፡

በተጨማሪም በም/ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የዴሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ማስተባበሪያ ማዕከል ኃላፊ እና የብልጽግና ፓርቲ ም/ፕሬዚዳንት አደም ፋራህ፣ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ሃይለማሪያም ደሳለኝ፣ የቀድሞ ም/ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኮንን፣ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች እና ሚኒስትሮች ታድመዋል፡፡

የገበያ ሚዲያ ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን

Telegram:https://t.me/gebeyanews
Youtube: https://youtube.com/
Facebook: https://web.facebook.com/gebeyapromotion
TikTok: https://www.tiktok.com/



Gebeya Media

በሃገሪቱ የተለያዩ አከባቢዎች የታላቁ ህዳሴ ግድብ ምርቃትን አስመልክቶ ማህበረሰቡ ደስታውን በአደባባይ እየገለጸ ይገኛልገበያ ሚዲያ ጳጉሜ 4/2017 ዓ.ም ከ 14 ዓመታት ግንባታ በኋላ በዛሬ...
09/09/2025

በሃገሪቱ የተለያዩ አከባቢዎች የታላቁ ህዳሴ ግድብ ምርቃትን አስመልክቶ ማህበረሰቡ ደስታውን በአደባባይ እየገለጸ ይገኛል

ገበያ ሚዲያ ጳጉሜ 4/2017 ዓ.ም

ከ 14 ዓመታት ግንባታ በኋላ በዛሬው ዕለት ማለትም ጳጉሜ 4 ቀን 2017 ዓ.ም በታላቅ ድምቀት ይመረቃል።

ይህንን ተከትሎም በኢትዮጵያ የተለያዩ አከባቢዎች ያሉ ህዝቦች የህዳሴ ግድብ ምርቃትን በማስመልከት ደስታቸው እየገለጹ ይገኛሉ።

የ14 ዓመት የልፋት፣ የመስዋዕትነት እና የጽናት ምልክት፤ የማሰብ፣ የመጀመር እና የመጨረስ የተሰናሰለ የጋራ የድል ውጤት፤ ወድቆ መነሳት፣ ጨክኖ መስራት ሞቶ ማስቀጠል፣ ሳይታክቱ መሟገት ያመነጨው ኃይል፤ የእያንዳንዱ ዜጋ የልብ ትርታ፣ ቁጭት፣ እንባና ጸሎት ያልተለየው የኢትዮጵያዊ የጋራ ስኬት የታላቁ ህዳሴ ግድብ!

የገበያ ሚዲያ ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን

Telegram:https://t.me/gebeyanews
Youtube: https://youtube.com/
Facebook: https://web.facebook.com/gebeyapromotion
TikTok: https://www.tiktok.com/



Gebeya Media

እንኳን ደስ አላችሁ! እንኳን ደስ አለን!🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹እንኳን የ14 አመታት ህልማችን እውን ለሆነበት የጽናት፣ ተስፋ ያለመቁረጥ፣ የአንድነት እና የድል ምሳሌ ለሆነው የ...
09/09/2025

እንኳን ደስ አላችሁ! እንኳን ደስ አለን!

🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹🇪🇹

እንኳን የ14 አመታት ህልማችን እውን ለሆነበት የጽናት፣ ተስፋ ያለመቁረጥ፣ የአንድነት እና የድል ምሳሌ ለሆነው የኢትዮጵያ ታላቁ የህድሴ ግድብ የምርቃት እለት በሰላም አደረሳችሁ።

ጨርሰናል! ፈጽመናል! ድል አድርገናል!

ገበያ ሚዲያ ጳጉሜ 4/ 2017 ዓ.ም

የገበያ ሚዲያ ማህበራዊ ሚዲያ አማራጮቻችን

Telegram:https://t.me/gebeyanews
Youtube: https://youtube.com/
Facebook: https://web.facebook.com/gebeyapromotion
TikTok: https://www.tiktok.com/



Gebeya Media

Address

Addis Ababa
1000

Alerts

Be the first to know and let us send you an email when Gebeya Media posts news and promotions. Your email address will not be used for any other purpose, and you can unsubscribe at any time.

Contact The Business

Send a message to Gebeya Media:

Share